cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Ministry of Labor and Skills - Ethiopia

FDRE, Ministry of Labor and Skills

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
25 716
Obunachilar
+524 soatlar
+1097 kunlar
+29030 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

"የጥናትና ምርምር ሥራዎች ፋይዳ የሚኖራቸው ወደ ተግባር መሸጋገር ሲችሉ ነው፡፡" ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩና በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት የተጠኑ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በውይይቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የሚኒስቴሩ ካውንስል አባላት እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡ በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለፁት፤ የተጠኑ ጥኖቶች እቅዶቻችን ላይ እሴት መጨመር በሚያስችል መልኩ መተግበር አለባቸው። ጥናቶች ፋይዳ የሚኖራቸው ወደ ተግባር መሸጋገር ሲችሉ ነው ብለዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በበኩላቸው ጥናቶቹ እንደ ሀገር እጅግ ወሳኝ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰው ወደ ተግባር መሸጋገር እንዲችሉ ወደ ስርዓት ትምህርት እየቀየሩ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የጥናትና ምርም ስራዎቹ በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች (Technology Mapping on Prioritized Government Development Sectors, Study on TVTrelated Indigenous Knowledge and Skills in Ethiopia and Implementation of Zoning and Differentiation Initiatives: Brief Assessment) ያተኮሩ ናቸው፡፡ ሐምሌ 4/2016 ዓ.ም ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
Hammasini ko'rsatish...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

21👍 20🙏 2
#Happeningnow #አሁን ችግር ፈቺ የሆኑ የተለያዩ የጥናትና ምርምር ሥራዎች የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በተገኙበት እየቀረበ ይገኛል። የጥናትና ምርም ስራዎቹ በሦስት ርዕሰ ጉዳዮች (Technology Mapping on Prioritized Government Development Sectors, Study on TVT-related Indigenous Knowledge and Skills in Ethiopia and Implementation of Zoning and Differentiation Initiatives: Brief Assessment) ያተኮሩና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋም በሆነው የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢኒስቲቲውት የተጠኑ ናቸው። በመድረኩ ክብርት ሚኒስትርን ጨምሮ ሚኒስትር ድኤታዎች ፣ የካውንስል አባላት እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች የተገኙ ሲሆን የጥናትና ምርምር ሥራዎቹ ከቀረቡ በኳላ ሰፊ ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ሐምሌ 4/2016 ዓ.ም ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
Hammasini ko'rsatish...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 15 6👌 3👏 1
አሮጌውን እሳቤ ጥሳ የወጣች፣ ለሌሎችም ምሳሌ የሆነች ቴክኖሎጂስት…. አህላም አሊ ትባላለች፡፡ ከዓመታት በፊት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን አጠናቃ ወደ ኮሌጅ ስታመራ የመረጠችው የስልጠና መስክ በዙሪያዋ ያሉትን ሁሉ በእጅጉ ያስገረመ ነበር፡፡ የአህላም ወዳጅ ዘመዶች በምርጨዋ የተደነቁት አውቶሞቲቭ በአብዛኛው ለወንዶች የተሰጠና በሴቶች የማይመረጥ የሙያ መስክ በመሆኑ ነበር፡፡ አህላም ግን አውቶሞቲቭን የመረጠችው እንዲሁ በነሲብ ሳይሆን ለመካኒካል ሥራዎች ያላትን ፍቅር መነሻ አድርጋ ነበር፡፡ ይህን ዝንባሌዋን የተመለከቱ አባቷም በሙያው እንድትገፋ ዘወትር ያበረታቷት ነበር፡፡ ለሙያው ያላት ፍቅር ከአባቷ ማበረታቻ ጋር ተደማምሮ በእጅጉ ስላበረታት ስልጠናዋን በከፍተኛ ውጤት አጠናቃ በተማረችበት የወራቤ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህር ለመሆን በቃች፡፡ አህላም በአሰልጣኝ መምህርነት ቆይታዋ አካላዊ ብቻ ሳይሆን አእምሯዊ እና ስነ ልቦናዊ ጥንካሬንም እንደተጎናፀፈች ትናገራለች፡፡ ለሙያው ያላት ፍቅር ደግሞ በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለመፍጠር እድትነሳሳ አድርጓታል፡፡ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የተዘጋጀው 3ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር አህላም የክህሎት ብቃቷን ያሳየችበት አጋጣሚ ነበር፡፡ ወራቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ወክላ በአሰልጣኝ ዘርፍ የተሳተፈችበተን የክህሎት ዘርፍ ውድድር በ3ኛነት ማጠናቀቅ ችላለች፡፡ ይህም ሴቶችን በተመለከተ በሀገራችን ተንሰራርፍቶ የቆየውን አሮጌ እሳቤ ጥሳ በመውጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ የአይቻልም ባይነትን እሳቤ ሰበባብራ ለሌሎችም ምሳሌ የሆነች ቴክኖሎጂስት ለመሆን በቅታለች፡፡ ይህ ብቃቷ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ዜጎች በአንድነት በማሰባሰብ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ምርት ለማሻገር በተዘጋጀው ልዩ የክረምት ወራት የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች መርሃ ግብር የመታቀፍ ዕድልን ይዞላት መጣ፡፡ አህላምና ልክ እንደሷ ከተለያየ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መርሃ ግበሩ ካሰባሰባቸው ሌሎች አሰልጣኝ መምህራን በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡ ሁሉም የየራሳቸው ቴክኖሎጂና ፈጠራ ሃሳብ ባለቤቶች ናቸው፡፡ ሃሳባቸውን፣ ክህሎትና ብቃታቸውን በአንድ ላይ አቀናጅተውም ችግር ፈቺ ፣ ለሰፊው ህብረተሰብ አገልግሎት የሚሰጥ፣ ከአካባቢና ከተፈጥሮ ጋር ተስማሚ የሆነ ቴክኖሎጂ ለማምረት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት አደረጉ፡፡ በመጨረሻም የተለያዩ ተረፈ ምርቶችን በግብዓትነት በመጠቀም የእንስሳት መኖ እና ከሰል የሚያመርት ቴክኖሎጂ ለመፍጠር ከስምምነት ላይ ደረሱ፡፡ ላለፉት ወራት በፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢኒስቲትዩት ፣ አውቶሞቲቭ ወርክሾፕ ሲገነባ የቆየው የእነአህላም ማሽን የተለያዩ ደረጃዎችን አልፎ ለመጠናቀቅ ጥቂት ነገሮች ብቻ ቀርተውታል፡፡ በሥራቸው ላይ ዕለት በዕለት የሚታየው ለውጥ ተስፋቸውን ይበልጥ እያለመለመው የማሽኑ የተለያዩ ክፍሎች ተጠናቀው ወደ ምርት የሚገቡበትን ቀን በናፍቆት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ የአውቶሞቲቭ ባለሙያዋ አህላም የሁልጊዜ ምኞቷ የሆነው አዲስ ቴክኖሎጂን በስፋት የማምረት ህልሟ ዕውን የሚሆንበት ጫፍ ላይ በመድረሷ በእጅጉ ደስተኛ እንደሆነች ትናገራለች፡፡ በሀገራችን ቆላማ ቦታዎች በሥፋት የሚበቅሉ እንደ ፕሮሶፊስ ጁሊፍሎራ ያሉ ጎጂ የአረም ዘርያዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል፣ የአየር ንብረት ላይ ምንም ጉዳት ሳያደርስ የሕብረተሰቡን የኃይል አቅርቦት ችግር የሚያቃልልና ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ቴክኖሎጂን ገና በወጣትነት ዕድሜዋ ለውድ ሀገሯ ማበርከት ችላለች፡፡ አህላም እና ጓደኞቿ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እየተተገበረ የሚገኘውን ልዩ የክረምት ወራት የቴልኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልፀጊያ መርሃ ግብር እንደ መደላድል ተጠቅመው ብዙ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት ቀጣይ ዕቅድ ነድፈዋል፡፡ ጉዟቸው የህብረተሰባቸውን ችግሮች መፍታትን፣ሀገራቸውን ወደ ታላቅነት ማሻገርን መዳረሻ ግቡ አድርጎ እና በብሩህ ተስፋ ታጅቦ እንደሚቀጥልም በኩራት ትናገራለች፡፡ ሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
Hammasini ko'rsatish...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

👍 20 3
02:33
Video unavailableShow in Telegram
8.59 MB
👍 12 5👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
#እንኳን_ደስ_አላችሁ! የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው እና በኢትዮጵያ የክህሎት ልማት ዘርፍ ላይ ትልቁን ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዛሬ ሰልጣኞቹን በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርም ለመላው ተመራቂዎችና ቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ቀጣዩ የሕይወት ምዕራፍም የስኬት እንዲሆንላችሁ ይመኛል። ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት https://lmis.gov.et
Hammasini ko'rsatish...
👍 47 8🙏 3
06:37
Video unavailableShow in Telegram
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከዘርፍ እና ከተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር  በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያደረጉት ውይይት
Hammasini ko'rsatish...
94.58 MB
👍 12👏 1
03:33
Video unavailableShow in Telegram
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የሥራ ዕድል ፈጠራን በተመለከተ ያስተላለፉት መልዕክት
Hammasini ko'rsatish...
Aby +++.mp4360.44 MB
👍 21 5🤩 5
Photo unavailableShow in Telegram
👍 29
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.