uz
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 740
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+17 kunlar
-630 kunlar
Postlar arxiv
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2017ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ኦረንቴሽን በመስጠት የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አደረገ:: ሰልጣኝ ተማሪዎቹን ለመቀበል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት መድረኩን ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በቅድሚያ አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን በኮሌጁ ለመሰልጠን እዚህ በመገኘታቸው እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ወቅቱ ሚጠይቀውን ምርጫ መርጣችሁ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለመሰልጠን ዘርፉን በመቀላቀላችሁ እጅግ እድለኞች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን ቀጥለውም እንዳሉት በኮሌጁ በተለያዩ ሙያዎች ለመሰልጠን እዚህ የተገኛችሁ ወጣቶች አሁን የምትገኙበት እድሜ በራሳችሁ ውሳኔ ምትወስኑበት እድሜ ነውና ትክክለኛውን መንገድ በመምረጥ የወጣትነት እድሚያችሁን በአግባቡ በመጠቀም ለቀጣይ ህይወታችሁ ፍሬ የምታፈሩበት ሊሆን እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል:: እሁን ላይ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ራሱን ችሎ እስከ ከፍተኛው የትምህርት እርከን ድርስ ማሰልጠን እንደጀመረ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አንድ ሰልጣኝ ከታች ከ ደረጃ 1(ሰርተፊኬት) ጀምሮ እራሱን እያሻሻለና እያበቃ እስከ ደረጃ 8(ዶክትሬት) ድረስ መድረስ እንደሚችልና መንገዱም የተመቻቸ መሆኑን ለሰልጣኞቹ ገልፀው ሰልጣኞችም ህንን ትልቅ አጋጣሚ በመጠቀም ለራሳቸውም ብሎም ለሀገራቸው የሚጠቅሙ ብቁ ዜጋ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል:: የኮሌጁ ዲን በመጨረሻም በኮሌጁ የትኩረት ዘርፍ ተብለው የተያዙትና በዓለም ባንክ ፕሮጀክት ጭምር የሚደገፉ ሁለት ዘርፎች መኖራቸውን ገልፀው እነርሱም የማኑፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት እና የኤክትሪካል/እሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት ናቸው ያሉ ሲሆን በእነዚህ ሁለት ዘርፎች ውስጥ ያሉ ሙያዎችን ለመሰልጠን የመረጡ ሰልጣኞችም ከምንም በላይ እድለኞች ያረጋቸዋል ብለዋል:: በመጨረሻም ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጁ የሚኖራቸው ቆይታንና የትምህርትና ስልጠናው ሂደት ምን እንደሚመስል በዝርዝር ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን በተጨማሪም ስልጠናቸውን አጠናቀው እስኪወጡ ድረስ በኮሌጁ ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ ወቅት የተቀመጠላቸውን መብትና ግዴታዎች ከወዲሁ እንዲያውቋቸው በትምህርትና ስልጠና አስተባባሪው በኩል ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል:: ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በቀጣዮቹ 3ቀናት በኮሌጁ በሚኖራቸው ቆይታ የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና የሚወስዱ ሲሆን እሱን እንዳጠናቀቁ የትብብር ስልጠና የሚወጡባቸውን የተለያዩ እንዱስትሪዎችና ተቋማትን እንዲጎበኙ መርሃ-ግብር መያዙም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም

በ2017 ዓ.ም በኮሌጁ ሊሰሩ በታቀዱ ቴክኖሎጂዎች ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ:: በመድረኩ አሰልጣኝ መምህራን በበጀት አመቱ ሊሰሯቸው ያቀዷቸውን የቴክኖሎጂ አርዕስቶች ለጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ክፍል በግልና ቡድን ባስገቡት መሰረት ስለሚሰሩት ቴክኖሎጂ ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል:: በተጨማሪም በዕለቱ በቀረቡት የቴክኖሎጂ አርዕስቶች ላይ ከሚመለከታቸው ዲፓርትመንቶች እና ከክፍሉ ባለሙያዎች እንዲሁም አሰልጣኝ መምህራን ጋር በመሆን ከማህበራዊ ጠቀሜታ፣ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ፣ከአካባቢ ደህንነት እና ከቴክኖሎጂ አንጻር ገንቢ አስተያየት ተሰጥቶባቸው ወደ ቀጣይ ስራ እንዲገቡም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 24/2017 ዓ.ም

ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት እቅድ እና የዝግጁነት ምዕራፍ አፈፃፀም ሪፖርት በተመለከተ ኮሌጁ ማህበረሰብ በተገበት የውይይት መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ በቅድሚያ በኮሌጁ የዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን በዋነኛነትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001:2015 የጥራት አስተዳደር ስርዓት እውቅና ያገኘበትን የላቀ ትግበራ ያከናወነበት ምዕራፍም ነበር:: በተጨማሪም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደ ተቋም የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ከዋና ስራ ሂደቶች ጀምሮ እስከ ፈፃሚው ድረስ የጠራ እቅድ ዝግጅት የተከናወነበት ወቅት ሲሆን እንዲሁም የአረንጏዴ አሻራ፣የደም ልገሳን ጨምሮ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስና መሰል ትግበራዎችም በዝግጁነት ምዕራፍ ወቅት እንደተከናወኑ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሪፖርት ቀርቧል:: በመጨረሻም የ2017 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የቀረበ ሲሆን የቀረበውን እቅድ መነሻ በማድረግም ከመድረኩ ተሳታፊዎች ሀሳብ ተሰቶበት ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጎበታል:: በማጠቃለያውም በተጠናቀቀው በጀት አመት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠል እንዲሁም በ2017 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በጋራ መረባረብ እንደሚገባ ተገልፆ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም

የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡ በሥራ
+2
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ደ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጻ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር ተሻለ በመግለጫቸው የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ እንደሚዘጋጅ ገልጸው በዚህ ዓመትም የ12 ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 526,683 የሚሆኑት ከደረጃ 1 እስከ 5 በመደበኛ ስልጠና ለመሰልጠን ተቋማቱን ይቀላቀላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ ገበያ ተኮር በሆኑ በአጫጭር ስልጠናዎች ደግሞ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች በተቋማቱ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ሰልጣኞች በተቋማቱ በቂ ክህሎት ታጥቀው እንዲወጡ በክረምቱ የአሰልጣኞች የአቅም ግንበናታ ስልጠና፣ የማሽነሪዎች ጥገና እና አስፈላጊ የማሰልጠኛ ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ በሀገሪቱ የሚገኙ የመንግስት እና የግል ማሰልጠኛ ተቋማት ይህንን የመቁረጫ ነጥብ መነሻ አድርገው ሰልጣኞችን መቀበል ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለተፈጥሮ ሳይንስ የተቀመጡ የመቁረጫ ነጥቦች ዝርዝር ከታች ይመልከቱ ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥቅምት 11፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols

"የዘንድሮውን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ለየት ከሚያደርጉት አንዱና ዋነኛው ኮሌጃችን በምስራቅ ኢትዮጵያ የመንግስት ተቋም ሆኖ የአለም አቀፍ የጥራት ደረጃ የሆነውን የISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM እውቅና ያገኘ የመጀመርያው የመንግስት ተቋም በሆነ ማግስት መደርጉ ልዩ ያደርገዋል" የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ