cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Yalelet Wondye

Ko'proq ko'rsatish
Efiopiya1 731Amxar1 581Toif belgilanmagan
Reklama postlari
6 959
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-307 kunlar
-15330 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

የሲዳማ ወጣቶች (ኤጄቶ) እናመሰግናለን‼️ ድል ለህዝባችን‼️
Hammasini ko'rsatish...
ይህን ሕዝብ በቅጡ ካላስተዳደራችሁት የዋዛ አይምሰላችሁ ፤ ይህ ህዝብ፥ አፄ ቴዎድሮስን ወልዶ የበላ፤ የአፄ ዮሐንስን አንገት ያስቆረጠ፤ በእምዬ ምንሊክ ሐውልት ላይ ቁማር የሚጫወት፤ አባባ ጃንሆይን (ሥዩመ-እግዚአብሔር) አንግሶ ያዋረደ፤ ቆራጡን መሪ ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያምን አንቆራጦ ያባረረ (በቁሙ አስቀምጦ ቲያትር የሚያሳይ)፤. መሪዎቹን የሚፈራ- መሪዎቹን የሚጠላ መሪዎቹ የሚፈሩት-መሪዎቹ የማይወዱት ሠምና ወርቅ የሆነ ሕዝብ ነው፡፡ ይሕ ሕዝብ ፥ ፍቅሩንም ጥላቻውንም በሆዱ የሚፈጅ ምሥጢረ ሥላሴ የሆነ ሕዝብ ነው፡፡ ይሕ ሕዝብ ፥ ንጉሡ ጥለውት ጠፍተው (ተሰደው) ለራሡ የጎበዝ አለቃ በመፍጠር ፋሺሽቶችን ተዋግቶ አገሩን ነፃ ያወጣ፤ መንግሥቱም (ኃይለማሪያም)ወደ ዚምባቡዬ ሪፈር በተባለ ጊዜ ራሱን በራሱ ያስተዳደረ ጨዋና ንጉሡ ከሥደት ሲመለሱ አልጋውን ያስረከበ የዋህ ሕዝብ ነበር (አይገርምም?)፡፡ ይሕ ሕዝብ ፥ በራሡ ቋንቋ ፍቅሩን አስከመቃብር የጻፈ፤ ሼክስፒርን ፈቶ የመግጠም ፀጋ (ዬ) የተሠጠው ሕዝብም ነው፡፡ ይሕ ሕዝብ ፥ በቅዱስ ያሬድ በኩል ከሠማየ ሠማያት የመልአክትን ዝማሬ ሰምቶ ዜማ የሠራ ዜመኛ ሕዝብ ነው፡፡ ይሕ ሕዝብ፡- ጦርነትን በባዶ እጁ እንዳሸነፈ ሁሉ ኦሎምፒክንም በባዶ እግሩ ድል ያደረገ ጉደኛ ሕዝብ ነው፡፡ (ሮም ሁለቴ ጉድ ሆነች እንዳሉት የአውሮፓ ወሬኞች…) ይሕ ሕዝብ፡- የዓባይን ልጅ ውሀ ጠማው ተረቱን እያደሰ ሱዳንን አልፎ ግብፅን እስከ ሲናይ በርሀ ውሃ የሚያጠጣ ሳይተርፈው የሚቸር ውሃ የሚያደርግ ሕዝብ ነው፡፡ ይሕ ሕዝብ፡- ሌላው የአፍሪካ ሕዝብ የቀኝ ግዛት እባጩ ንፍፊት ሳይፈነዳለት አብዮት ያፈነዳና እውነተኛው መንገድ የእኔ ብቻ ነው ብሎ ባላብ አደርና በወዛደር በእናቸንፋለንና በእናሸንፋለን ጎራ ለይቶ አንድ ጥይትና ወጣት እስኪቀር ድረስ የሚጫረስ ግራ የገባው-ግራ -ዘመም ሕዝብ ነበር (ው)። ይሕ ሕዝብ፡- ከእናቱ ልጅ ይልቅ በመጽሐፍ ለሚያውቃቸው አብዮተኞች በማድላት ወንድሙን የሚገድል፤ አገር ለመገንጠልና ለማስገገንጠል እስ-በሱ የተጫረሰ ጉደኛ ሕዝብ ነው፡፡ ሲገርም!!! የሆነው ሆኖ… ይሕ ሕዝብ፡- መሪዎቹን የሚፈራ- መሪዎቹን የሚጠላ መሪዎቹ የሚፈሩት-መሪዎቹ የማይወዱት ፡፡ ሠምና ወርቅ የሆነ ሕዝብ ነው፡፡ ፍቅሩንም ጥላቻውንም በሆዱ የሚፈጅ ምሥጢረ ሥላሴ የሆነ ሕዝብ ስለሆነ በቅጡ አስተዳድሩት። ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን
Hammasini ko'rsatish...
ይድረስ ላልታወቁ ሃይሎች!!! ******************** የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪና የነፍሰ በላው ሽፍታው ቡድን መሪ ለሜሳ ዋወያ ማለት ይሄ ነው። ብዙውን ጊዜ እንጂባራ እና ቻግኒ ይውላል። ወደ አሶሳና አዲስ አበባ ሲመላለስ በባህር ዳር ኤርፖርት አድርጎ ነው። የስልክ አድራሻው 0918742386
Hammasini ko'rsatish...
ጥንቃቄ Alert 🚨 *************** ላለፈው አንድ አመት ከመንፈቅ አንፃራዊ ሰላም ሰፍኖበት የነበረው የመተከል ዞን ድጋሜ ወደ ስጋት ቀጠናነት ተቀይሯል። በመንግስት በጀት ሲቀለብ የሰነበተው የጉሙዝ ሽፍታ ከተጠለለበት ካምፕ ትላንት ሌሊት እስከነ ሙሉ ትጥቁ ወደ ጫካ እንዲገባ ተደርጓል። በዚህም መተከልና ዙሪያ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብቷል። በዛሬው ዕለትም ግልገል በለስ ከተማ ዙሪያ ያሉ ቀበሌዎች ላይ ህዝብ ተፈናቅሎ ወደ ከተማ እየገባ መሆኑን ለማወቅ ችያለሁ። ሽፍቶቹ ከካምፕ ጠፍተው ወደ ጫካ እንዲገቡ የፈቀዱት ለሜሳ የተባለ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ እና ካምፑ ላይ የተመደቡ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች መሆናቸውን መረጃ ደርሶኛል።
Hammasini ko'rsatish...
Hammasini ko'rsatish...

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ በችሎት ከተናገረው ታሪካዊ ንግግር‼ << ጠቅላይ ሚኒስርት ዐቢይ አህመድ 'የፍትህ ተቋማት ዳኞች ሌቦች ናቸው' ብለዉ ተናግረዋል። ነገር ግን ዐቃቢ ህግ  አልከሰሳቸውም። >> << ..እኛ 'የፖለቲካ እስረኞች ነን' ስንል በምክንያት ነው።  51ዱም ተከሳሾች በሙሉ አማራዎች ናቸው። የተከሰስነው ሰርቀን አይደለም ወይም ወለጋ ሰዉ ጨፍጭፈን አይደለም ፤ ሸገር ሲቲ ዜጎችን አፈናቅለን አይደለም። ነገም ደጋግመን እንለዋለን ክሳችን ወንጀላችን አማራ ሆነን ነው። ይሄ አይቀየርም ፤ ከፈለጋችሁ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሄዳችሁ ብታዩ  በሙሉ አማራ ብቻ ናቸው። >> <<...እኔ በአንድ ወቅት የመንግስት መገናኛ ብዙኸን ውስጥ ጋዜጠኛ ነበርኩኝ ። እንዴት እንደሚሰራ አውቃለሁ። የፓርቲ ትእዛዝ እንደወረደ አይቀርብም። በእኔና በረ/ፕሮፌሰር  ሲሳይ አውግቸው 'የፀጥታ ደህንነት ግብረሃይል መግለጫ' በማለት ሽብርተኛ ብሎ በእኛ ላይ ሁለት ጊዜ ዘገባ ሰርቷል። >> << በዚህ ችሎት ባሉ ተከሳሾች ሁሉም ላይ በተደጋጋሚ የሽብርተኝነት ዘገባ ተሰርቷል። ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። እኔ ጋዜጠኛ ነኝ ፤ ወረቀትና እስኪብርቶ እንጅ የጦር መሳሪያ ይዤ ፎቶ አልተነሳሁም። ከየት አምጥቶት ነው ግብረሃይሉ ፎቶሾፕ ያቀናበረው? ስለዚህ ፍ/ቤቱ  ፋና ዋልታ እና OBN የመንግስት መገናኛ ብዙሀን በሰሩት ዘገባ መጥተዉ እንዲያስረዱ ጥብቅ ትህዛዝ ይሰጥልን። በተሰራው ዘገባ የሞራል ድቀት አድርሰውብናል ፤ ቤተሰቦቻችን በእጅጉ ተጎድተዋል። በፍርድ ቤት ሂደት ያለን ሰዎች ነፃ ሆነን የመታየት ህገመንግስታዊ መብታችን ተጥሷል። >> << የአማራ ተወላጅ በመሆናችን የፖለቲካ እስረኛ ነን ፥ የምንለው በተጨባጭ ማሳያ ነው። የሚዲያዉ ኃላፊዎች መጥተው ለምን እንደዘገቡት ያስረዱ። ይህ ካልሆነ ጠንከር ያለ እርምጃ እኛም እንወስዳለን።>> << ጠቅላይ ሚኒስርት ዐቢይ አህመድ የፍትህ ተቋማት ዳኞች ሎቦች ናቸው ብለዉ ተናግረዋል። ነገር ግን ዐቃቢ ህግ አልከሰሳቸውም። >> //ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ ሀምሌ 3/2015 ዓ.ም በችሎት የተናገረውን -ስንታየሁ ቸኮል እንዳጋራው/
Hammasini ko'rsatish...
"እኛ ነን...!" << .. መጀመሪያ እኔን የያዙኝ ሰዎች ፦ 'ፖሊስ እኛ ነን ፤ ፍርድ ቤት እኛ ነን ፤ ዐቃቢ-ህግ እኛ ነን ስለዚህ ምንም አታመጣም' ብለውኝ ነበር። አሁን ያየሁት 'እኛ ነን' የሚለው አቅም እንዳለው ነው። 'ዐቃቢ ህግ እኛ ነን ፍርድ ቤት እኛ ነን' ላሉን ሰዎች ይሄ ችሎት ጥሩ ማሳያ ሆኖኛል። የዋስትና ብይን ለመስጠት ተቸግሯል። "እኛ እና እኛ" ውጤቱ ምን እንደሆነ ይታወቃል። >> // ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ዛሬ ሀምሌ 3/2015 ዓ.ም በችሎት የተናገረውን ስንታየሁ ቸኮል እንዳቀረበው //
Hammasini ko'rsatish...
መምህር መስከረም አበራ በችሎት ዛሬ የተናገረችው ተመዝግቧል። " አማራ ተነስቷል። በእዚህ ችሎት በመቆሜ ለልጆቼ የምናገረው በኩራት ነው ነገ አያፍሩብኝም አሁን የአማራ ህዝብ ተነስቷል ከልጆቼ ተነጥዬ ይኽን መከራ የምከፍለው ከፀረ አማራ ሃይሎች ጋር አብሬ ባለመቆሜ ነው። ዛሬ የዋስትና ብይን ውሳኔ ጠብቄ ነበር ፍትህ ሳይሆን ውሳኔ ይሰጣል የሚል ጠብቄ ነበር ግን አልሆነም ዳኞች ለምን እንደተቀየሩ እንኳ የማወቅ መብት ነበረን እሱም አልሆነም። "..እኔ የታሰርኩት በፖለቲካ አመለካከቴ ነው ከ83 ጀምሮ ስልጣን የያዘ አማራ ጠል እስረኛ መሆኔን ነው የማውቀዉ ከዚህ ችሎት ምንም አይነት ፍትህ ላገኝ እንደማልችል ቀድሜ አቀዋለሁ ዛሬ ይበልጥ አረጋግጫለሁ። ከ83 ጀምሮ በስልጣን የቆየ ፀረ አማራ ህዝባችን ጠበቃ እንዲኖረው አይፈልግም አማራን የሚጨፈጭፉ ሃይሎች ለሚሞተው ህዝብ የሚከራከር ጠበቃ እንዳይኖረው ይፈልጋሉ። የታሰረኩት አደባባይ ላይ እንድንቆም ባለመፈለጉ ነው ስለዚህ የፖለቲካ እስረኛ ነኝ። በእዚህ ችሎት በመቆሜ ለልጆቼ የምናገረው በኩራት ነው ነገ አያፍሩብኝም ። አሁን የአማራ ህዝብ ተነስቷል። ከልጆቼ ተነጥዬ ይኽን መከራ የምከፍለው ከፀረ አማራ ሃይሎች ጋር አብሬ ባለመቆሜ ነው። ከዚህ ክስ ፍትህ አልጠብቅም ለህዝቤ በከፈልኩት ዋጋ ክብር ይሰማኛል በፍጹም አልጸጸትም። ውጤቱ ምንም ይሁን እበረታለሁ አማራ ስለሆንኩ አልሰበርም። ሀምሌ 3/2015 ዓ,ም ታሪካዊ ንግግር ተመዝግቧል
Hammasini ko'rsatish...
Hammasini ko'rsatish...