Orthodox picture
ሰላም ውድ የተዋህዶ ልጆች ይህ ቻናል የተከፈተው የተለያዩ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ ምስሎችን እንዲተላለፉበት ነው። ✞በዚህ ቻናል ላይ የምንለቃቸው 🔸ቤተክርስቲያናዊ ምስሎች ፤ 🔸የንግስ በአላት ጥሪዎች 🔸መዝሙሮች 🔸ስብከቶች
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
166
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Repost from Zehohitebirhan_official ዘኆኅተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ቻናል
ሠላም አድርጊው ቅድስተ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በተነሳ የእሳት አደጋ የአብነት ትምህርት ቤቱ ሙሉ በሙሉ ወደመ!
+++++++++++++++++++++++++++++++++++
(አደባባይ ሚዲያ ፡አዲስ አበባ፡መጋቢት 28/2014 ዓ.ም፡April 6/2022)
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በባሕር ዳር ሠላም አድርጊው ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በተነሳ የእሳት አደጋ ከ2000 በላይ ደቀመዛሙርት የሚማሩበት ማረፊያና ንብረት የአብነት ትምህርት ቤቱ ሙሉ በሙሉ ወድሟል !!!
በዛሬው ዕለት መጋቢት 28/2014 ዓ.ም ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ጀምሮ በተከሰተው መንስኤው ያልታወቀ አደጋ ሁለት ተማሪዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የመማሪያ አዳራሾችን ጨምሮ ከ200 በላይ የሚሆኑ የደቀ መዛሙርቱ መኖሪያ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል ።
የነገ የሃይማኖት ሊቃውንት ለሚሆኑ የሠላም አድርጊው ቅድስት ማርያም ደቀመዛሙርት፣ መምህራን፣የአብነት ተማሪዎች ግዚአዊ መጠለያ በማዘጋጀት አስቸኳይ የምግብና የአልባሳት ድጋፍ እንዲደረግላቸው ተጠይቋል ።
መጋቢት 27 (በዓለ ስቅለቱ ለኢየሱስ ክርስቶስ)
በዚህ ቀን መጋቢት 27 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከወደቀበት የኃጢያት አዘቅት ሊያወጣው ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ስጋን ነስቶ ሳይገባው በበረት ተወልዶ፤ ስደታችንን ሊያስቀር ሳይገባው ተሰዶ፤ በክፉዎች አይሁድ ምክር ተከሶ በባህርይው መንገላታት የማይገባው አምላክ ለኛ ሲል የተንገላታና የተደበደበ፣ በጥፊ የተመታ፣ የተዘባበቱበት፣ ምራቅ የተተፋበት፣ እርጥብ መስቀል ተሸክሞ ከሄሮድስ ወደ ጲላጦስ እየተመላለሰ ከዚያም በቀራንዮ የራስ ቅል በምትባል ሥፍራ ተሰቅሎ ለኛ ሲል ሞታችንን በሞቱ ሽሮ በዋጋ ገዝቶናል። /ማቴ. 27፥1፣ ማር.15 ፥1፣ ሉቃ. 23፥1፣ ዮሐ.19፥ 1/
Repost from ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
ዜና ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ አቃቂ ጣቢያ ሰፈር በምትገኘው ደብረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስትያን አከባቢ ፓሊስ በከፈተው ተኩስ አንድ ምዕመን ሰማዕትነትን ተቀበለ
~
የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ተከታይ ግለሰቦች በአቃቂ ጣቢያ ሰፈር ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን አከባቢ "የአምልኮ ስፍራ እንከፍታለን" በሚል ግርግር በተነሳው ሁከት የአዲስ አበባ ፓሊስ ወደ ምዕመናንኑ ተኩስ ከፍቷል።
በተኩሱም አንድ ኦርቶዶክሳዊ ሰማዕትነትን ሲቀበል ስፍራው ላይ አሁንም ያለመረጋጋት ይታያል።
👉 @ortodoxmezmur
07/25/14 ዓ.ም
መዝሙር ዘገብር ኄር መኑ ውእቱ ገብርኄር
የዕለቱ ምስባክ :- መዝ ፴፱(፵)፥፰
ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ፡፡
ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ፡፡
ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ፡፡
ትርጒም፦
አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ ፤ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው፡፡
በታላቅ ጉባኤ ጽድቅን አወራሁ፡፡
የዕለቱ ወንጌል፦ ማቴ ፳፭ ፥ ፲፬ -፴፩
ቅዳሴ፦ ዘባስልዮስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️