cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Ethiopian Premier league Share company

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
23 292
Obunachilar
-2824 soatlar
-757 kunlar
+6 05430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

በክለቦች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ለክልልና ዞን አመራሮች ፣ ከተማ ከንቲባዎች እና ሌሎች የህዝባዊና የኮርፖሬት ክለብ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ። በ2017 ዓ.ም በሚተገበረው የክለቦች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ዙሪያ ለእግር ኳሱ ባለድርሻ አካላት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች ሲሰጥ ቆይቷል። በዚሁ ሰነድ ላይ ለክለብ አመራሮች፣ ለሊጉ ተሳታፊ ክለቦች የፋይናንስ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ ለተጫዋችና አሰልጣኝ ሙያ ማህበራት እንዲሁም ለስፖርቱ ጋዜጠኞች ተከታታይ መድረኮች ተዘጋጅተዋል። በቀደሙት የባለድርሻ አካላት ውይይት መድረኮች በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረውና በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር እቅድ ከተያዙ ጉዳዮች ዋነኛው ለክለቦችን በጀት የሚመድቡ እና በበላይነት የሚያስተዳድሩ አካላት ተመሳሳይ ውይይቶችን ማዘጋጀት ነው። ሰኔ 06/2016 በሂልተን ሆቴል የአስራ ዘጠኙ የሊጉ ተሳታፊ ክለቦች የበላይ አስተዳዳሪዎች(የክልል የስራ ሃላፊዎች፣ የዞን አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ ከንቲባዎች እና ሌሎችም የህዝባዊ ክለብ አመራሮች) በክለቦች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ተዘጋጅቶላቸዋል። በእለቱ መድረክ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ታደለ ቦርቃ ባደረጉት ንግግር እቅድን በመመሪያ መምራት የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ገልፀው በቀጣይም ለስፖርቱ ችግሮች ሌሎች መመሪያ እና ደንቦች መዘጋጀት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት በንግግራቸው ከስፖርቱ ሁሉ ተወዳጅ የሆነውን እግር ኳስ የበለጠ ለማዘመን እንዲህ ያሉ መመሪያዎች ተግባራዊ ማድረግ ለነገ የሚባል እንዳልሆነ አብራርተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ክለቦች ክለብ ላይሰንሲንግን ተግባራዊ በማድረግ ከተጨማሪ ቅጣትና እገዳ እንዲድኑ እንዲሁም በደሞዝ አከፋፈል ላይ ያሉ ክፍተቶች እንዲፈቱ መልእክት አሰተላልፈዋል። መ/አ ፈቃደ ማሞ(የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ) መመሪያው ስለተዘጋጀበት ሂደት እና ቀጣይ ሰለሚተገበርበት መንገድ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በእለቱ መመሪያውን ለተሳታፊዎች ያቀረቡት የአጥኚ ቡድኑ ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ ም/ሰብሳቢ ረ/ፕ ጌቱ ደጉ ሲሆኑ ከአንቀፆቹ በተጨማሪ ያለንበት የእግር ኳስ ደረጃ ከክፍያ አንፃር የሚያሳይ ዝርዝር መረጃዎች አቅርበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየት አንስተው በቀጣይ ለተግባራዊነቱ ሁሉም እንዲረባረብ ቃል ገብተው ውይይቱ ተቋጭቷል።
Hammasini ko'rsatish...
WB 30 Book E.pdf9.32 MB
WB 30 Book A (1).pdf9.45 MB
የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዲጂታል መፅሔት - ቅፅ 3 ቁጥር 65 ቅፅ 3 ቁጥር 65 ሳምንታዊ ዲጂታል መፅሔት የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ስታቲክሳዊ መረጃዎች ይዞ መጥቷል። በመፅሔቱ ውስጥ የጨዋታ ሪፖርት እና ተጨማሪ መረጃዎች ተካተዋል። ከታች ባሉት ሊንኮች በሁለት ቋንቋ(በአማርኛ እና እንግሊዘኛ) ያገኙታል። በቴሌግራም ገፃችን በፒዲኤፍም ቀርቧል። https://online.fliphtml5.com/gmtiv/qmgd/ https://online.fliphtml5.com/gmtiv/eifp/ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ
Hammasini ko'rsatish...
ተጨማሪ ምስሎች📸 ሰኔ 29/2016 በሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊዎች - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር
Hammasini ko'rsatish...
Po'stilar arxiv
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.