uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 348 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 755-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 537-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 348 obunachiga ega bo‘ldi.

18 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 91 ga, so‘nggi 24 soatda esa 11 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 41.16% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.44% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 491 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 060 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 19 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 348
Obunachilar
+1124 soatlar
+477 kunlar
+9130 kunlar
Postlar arxiv
ኢመአ ያለፉት ሶስት ዓመታት ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዘርፍ አፈፃፀም እና የቀጣይ ሶስት ዓመታት ዕቅድን አስመልክቶ ውይይት አካሄደ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከ2013 እስከ 2015 በጀት አመት የነበረውን የአስር አመት ሀገራዊ የመጀመሪያ ዘመን የልማት እቅድ አፈፃፀም እና  ከ2016 እስከ 2018 የሚፈፀመውን የመካከለኛ ዘመን የልማትና የኢንቨስትመንት ዕቅድ ዋና ዋና ግቦች አስመልክቶ ነው ውይይት ያካሄደው። ውይይቱ የተካሄደው በዋናው መስሪያቤት ፣ በቃሊቲ የጥናት ማዕከል እና በአለምገና ኢንጅረንግና ማሰልጠኛ ማዕከል ነው። የተለያዩ ዘርፎች ያለፉት ሶስት ዓመታት የኢኮኖሚ አፈፃፀምና የቀጣይ ሶስት ዓመታት ሀገራዊ የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ የትኩረት መስኮችን ታሳቢ ያደረጉ የትኩረት አቅጣጫዎች በሰነዱ ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከዚህም ባሻገር በቀጣዮ ሶስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ ይፈፀሙ ዘንድ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተሰጡ የትኩረት አቅጣጫዎች ለስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ቀርበዋል። በዕለቱ በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያጋጠሙ ችግሮችን አስመልክቶ በሰነዱ የቀረበውን ሪፖርት አስመልክቶ ወይይት ተደርጓል። በዚህም ረገድ በመንገድ መሰረተ ልማት ዘርፉ እስከ 2012 በጀት ዓመት መጨረሻ በወረዳ ፣ በክልልና በፌዴራል ደረጃ የነበረው አጠቃላይ የሀገራችን የመንገድ ሽፋን ተደራሽነት 144 ሺህ ኪሎ ሜትር የነበረ ስለመሆኑና በሶስት ዓመታት ውስጥ የ23 ሺህ ኪሎ ሜትር ዕድገት በማስመዝገብ 167 ሺህ ኪሎ ሜትር ስመለድረሱ በሪፖርቱ ቀርቧል። በዚህም መሰረት በቀጣዩ ሶስት አመታት አሁን ያለውን የመንገድ ሽፋን 190 ሺህ ኪሎ ሜትር ለማድረስ ስለመታቀዱ ነው በመድረኩ የተገለፀው። ከዚህም ባሻገር በአሁኑ ወቅት ከ20 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ  መንገድ በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን ፣ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በተገቢው መልኩ ተጠናቀው አስፈላጊውን አገልግሎት ለመስጠት ይችሉ ዘንድ ካለፈው ጊዜ በላቀ ሁኔታ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሰፊ እንቅስቃሴ እንደሚጠይቅ ተገልጿል። በመጨረሻም ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን እና ባለፉት ጊዜአት የዘርፉ ተግዳሮት የነበሩ ችግሮችን አስመልክቶ ሰፊ ውይይት ተካሂዶ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የዕለቱ መርሃ-ግብር ተጠናቋል።

የ953 ኪሎሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታና 238 ኪሎሜትር የነባር መንገዶች የማጠናከር እና ደረጃ ማሻሻል ሥራ ተከናውኗል ------------------------------------------------------------------------------------------------------------------ አዲስ አበባ፡- ነሐሴ 22 ቀን 2015 ዓም (ኢመአ)፡ በበጀት ዓመቱ 953 ኪሎሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታና 238 ኪሎሜትር የነባር መንገዶች የማጠናከር እና ደረጃ ማሻሻል ሥራ ተከናውኗል ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መንገዶችን የፌዴራል መንዶችን የመገንባትና የማስተዳደር ተልዕኮን እየተወጣ ይገኛል፡፡ አዳዲስ መንገዶች ከመገንባት በተጨማሪ ነባር መንገዶችን የማጠናከር እና ደረጃቸውን ማሻሻል እንዲሁም የተገነቡ መንገዶች የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት እንዲሰጡ በተለያዩ የጥገና ዘዴዎች ተጠቅሞ መንገዶችን የመጠገን ሥራዎችን ይሠራል፡፡ ተቋሙ የሚያሰተዳድረው አጠቃላይ የፌደራል መንገድ ሽፋን 30,549 ኪሎ ሜትር ሲሆን 18,232 ኪሎሜትር አስፋልት እንዲሁም 12,317 ኪሎሜትር ጠጠር መንገድ ይገኝበታል፡፡ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመትም 953 ኪሎሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታ የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም 238 ኪሎሜትር የነባር መንገዶች የማጠናከር እና የነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል ሥራ ተከናውኗል፡፡ እነዚህ መንገዶች በሚገነቡበት ወቅት የሚከናውኑ የክትትልና ድጋፍ ሥራዎችን ይበልጥ ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ እንዲቻል በበጀት ዓመት 27 የመንገድ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ\ቤቶች ተቋቁመው ሂደቱን በቅርበት በመከታተል አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በተለይ ከወሰን ማስከበር (right-of-way) ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮችን ከመፍታት አንጻር የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማመቻቸት የጋራ መግባባት የመፍጠር ሥራም አየተሰራ ይገኛል፡፡ ይህም ባለጉዳይ እስከ ዋናው መሥሪያ ቤት መምጣት ሳይጠበቅበት በቅርበት ባለው የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ቀርቦ አገልግሎቱን እንዲያገኝ እያስቻለው በመሆኑ ለተገልጋዮች እፎይታ የሰጠ ነው፡፡ ከመንገዶች ጥገና አኳያም ከቅድመ-ጥንቃቄ ሥራዎች አንስቶ የመደበኛ፣ ወቅታዊ፣ የከባድ እና የድንገተኛ ጥገናዎች ተከናውነዋል። ከባድ ጥገና/Overlay Projects/ 254ኪሎሜትር እና (ወቅታዊና መደበኛ) ጥገና 11685 ኪሜ በአጠቃላይ 12892 ኪሎሜትር የመንገደችጥገና ተከናውኗል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቶቹ የተጠገኑት በራስ-ኃይል የመንገድ ጥገና ዲስትሪክቶች ፣ በመንግስትና በግል የሥራ ተቋራጮች አማካኝነት ነው። በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጠሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን ፥በእቅድ በመያዝ ነው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ ያደረገው ። የከባድ እና ኦቨርሌይ ጥገና እየተከናወነላቸው ከሚገኙ ፕሮጀክቶቸ መካከል የሚሌ-ጋላፊ፣ የወልዲያ-ፍላቂት እንዲሁም የአዋሽ-ቁልቢ-ድሬዳዋ/ሐረር አስፋልት ኦቨርሌይ ኮንትራት 1እና 2 ፕሮጀክቶች ይጠቀሳሉ፡፡ ተቋሙ፣ ይህን የጥገና ሥራ አጠናክሮ በመቀጠል በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ከ 13 ሺህ 400 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው መንገዶችን ለመጠገን ነው አቅዶ እየሠራ የሚገኘው። በቀጣይም የመንገድ ጥገና ሥራውን ቀልጣፋ እና ተደራሽ ለማድረግ እንዲቻል ኢ.መ.አ በቅርቡ የተለያዩ የግንባታ ማሽነሪዎችን ግዢ በመፈጸም ለሁሉም የጥገና ዲስትሪክቶች እንዲሰራጩ አድርጓል።

የመንገድ ፈንድ ወደ ኢመአ ከተቀላቀለበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው መንገድ ፈንድ በአዋጅ ቁጥር 66/89 በጽ/ቤት ደረጃ ተቋቁሞ ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ከየካቲት 2014 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሥር በዳይሬክቶሬት ደረጃ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ፣ በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚተዳደሩ የመንገድ ኤጀንሲዎች በጸደቀላቸዉ የበጀት ድልድል መሰረት መንገዶቻቸዉን የመጠገን ፣ መልሶ የመገንባት እና የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬት ኃላፊነት በዋናነት ለመንገድ ጥገና የሚዉል ገንዘብ የማሰባሰብ ፣ የመመደብ እና የመደበዉን በጀት ለታቀደለት አላማ መዋሉን የመከታተል እና የመቆጣጠር ሥራን መስራት ነው፡፡ የጊቢ ምንጮቹ በዋናነት ለመንገድ ጥገና የተጣለ የነዳጅ ታሪፍ ፣ በተሽከርካሪ ቅባትና ዘይት ሽያጭ ላይ የተጣለ ታሪፍ ፣ ክብደትን መሠረት ካደረገ ዓመታዊ የተሽከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ክፍያ ፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ እና ከተፈቀደ ክብደት በላይ በመጫን ከሚጣል ቅጣት የሚሰበሰቡ ገቢዎች ናቸው። በዚህም መሰረት በ2015 ዓ.ም ዳይሬክቶሬቱ 7.4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ችሏል። የተሰበሰበው ገንዘብም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን ጨምሮ ለሁሉም የክልል እና የከተማ መስተዳድር የመንገድ ኤጄንሲዎች ተከፋፍሏል። በበጀት ዓመቱ የተሰበሰበው ብር የተለያዩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን ለመከወን እና የመንገድ ሃብትን ለመንከባከብ እየዋለ ይገኛል። በተያዘው 2016 በጀት ዓመት ተቋሙ ከመንገድ ፈንድ 18.5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን የመንገድ ፈንድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንጅ. ካሳሁን በጅጋ ገልፀዋል። ይህንንም ለማሳካት የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ስልቶች እና ማሻሻያዎች የተዘጋጁ ሲሆን በቅርቡ ተግባራዊ ይደረጋሉ። ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል በሁሉም የገቢ ምንጮች ቀደም ብሎ ተጥሎ በነበረው ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደርጎ በቀጣይ ወደ ተግባር እንደሚገባ ተጠቁሟል። ከዚህ በተጨማሪም ከተሽከርካሪ ሚዛን ጣቢያዎች የሚሰበሰበው ታሪፍ ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ ለክልሎች ይውል የነበረ ሲሆን በቀጣይ በአንድ ቋት በኢመአ በኩል ተሰብስቦ ለሁሉም የሚከፋፈልበት ሥርዓት እየተዘረጋ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። የመንገድ ሃብትን መንከባከብ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሃላፊነት መሆኑን በመገንዘብ ከተፈቀደው ክብደት በላይ ባለመጫን እንዲሁም በቀጣይ በሚደረገው የታሪፍ ማሻሻያ ላይ ሁሉም በቅንነት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።

የወይጦ-ቱርሚ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ በሚጠናቀቅበት ሁኔታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ ጂንካ ነሐሴ 08፣ 2015 (ኢመአ) ፡-በደቡብ ኦሞ ዞን የወይጦ-ቱርሚ 120 ኪሎ ሜትር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት፣ የገጠሙት ችግሮች ተፈትተው በተያዘለት ጊዜ በሚጠናቀቅበት ሁኔታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  የጂንካ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና የደቡብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፥ ፕሮጀክቱ የሚገኘበትን የግንባታ ደረጃ ጎብኝተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ 120 ነጥብ 188 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፥ ከፌደራል መንግስት በተመደበ ከ 2 ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ፣ በራማ ኮንስትራክሽን ነው እየተገነባ የሚገኘው። በውሉ መሠረት ፕሮጀክቱን በአራት ዓመታት ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፥ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ችግር ግንባታው በተደጋጋሚ መቋረጡ፣ የሥራ ተቋራጩ አቅም ማነስ እንዲሁም የግንባታ እቃዎች አቅርቦት እጥረት እና ዋጋ መናር፣ ግንባታው እንዲስተጎጒል ማድረጋቸው በውይይቱ ላይ ተገልጿል።  በአካባቢው ነዋሪ የሚነሱ ተገቢነት የጎደላቸው ጥያቄዎች ከግንዛቤ ማነስ የሚመነጩ እንደሆነ በውይይቱ ላይ የተነሳ ሲሆን፣ ችግሩን ለመቅረፍ ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ይሠራሉ ተብሏል። በሥራ ተቋራጩ እና አማካሪ መሀንዲሱ በኩል የሚስተዋሉ የአፈጻጸም ክፍተቶችን በተመለከተ አስፈላጊው የእርምት ርምጃዎች ይወሰዳሉም ተብሏል። የመንገድ ግንባታው በታለመለት ጊዜ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ፣ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑም በውይይቱ ተመላክቷል። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 21 ነጥብ 35 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ የጠረጋ፣ የዓፈር ቆረጣ እና ሙሌት የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ እንዲሁም የጠጠር ማምረት ሥራዎች እየተሠሩ ናቸው፡፡ መንገዱ በዋናነት የወይጦ ፣ አልቦሬ እና ቱርሚ ከተሞችን የሚያገናኝ ሲሆን ፣ ግንባታው ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የ3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል፡፡ በተጨማሪም አካባቢው የኦሞ ሸለቆ አርኪኦሎጂካል ሳይት እንዲሁም በዞኑ የሚገኙ የተለያዩ ብሔረሰቦች ባህላዊ እና ቁሳዊ የቱሪስት መስህቦች (በተለይም የሐመር ብሔረሰብ) መዳረሻ በመሆኑ ከወይጦ ወደ ቱርሚ የሚደረገውን ሁለገብ እንቅስቃሴ በእጅጉ ከማሳለጡም ባሻገር ለቱሪዝም ዘርፋ መስፋፋትም ከፍተኛ አስተዋጽዎ ይኖረዋል፡፡ ፕሮሜ እና ኦሜጋ ምህንድስና ሥራዎች የተሰኙ ሀገር-በቀል አማካሪ ድርጅቶች፥ ፕሮጀክቱን የማማከርና የመቆጣጠር ሥራ በጥምረት እየሠሩ ይገኛሉ።

የመሰል-ኮሪ-ቴሩ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 04 ፣ 2015 (ኢመአ):- በአፋር ክልል ውስጥ የሚገኘው የመሰል-ኮሪ-ቴሩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመስክ ስራ ተቃኝቷል። 84 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይኸው መንገድ ከመንግሥት በተመደበ 1,511,330,392.07 ብር በአስፋልት ደረጃ ግንባታው እየተካሔደ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጅነሪንግ ኮርፖረሽን ኤል.ቲ. ዲ. የተባለ የውጭ ሀገር ስራ ተቋራጭ ነው። የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠርና በማማከር ረገድ ደግሞ ኢንስራድ ሲቪል ሲስተም ኢንጅነሪንግ ፒ.ኤል.ሲ.በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱ የጎን ስፍት የመንገድ ትከሻን (Shoulder) ጨምሮ 12 ሜትር በገጠራማ አካባቢ እና 19 ሚትር በወረዳ ከተሞች እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም ከፕሮጀክቱ መነሻ እስከ 49 ኪ.ሜ በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ፣ የተቀረው 35.2 ኪ.ሜ አዲስ መንገድ ነው። ነባሩ የጠጠር መንገድ እጅግ የተጎዳ እና የተቀረው የመንገዱ ክፍል ምንም አይነት የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽተነት ያልነበረው በመሆኑ ህብረተሰቡ ለበርካታ እንግልት ሲዳረግ ቆይቷል። ሆኖም ግን አሁን ላይ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከግምት ውስጥ ገብቶ በአስፋልት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣ ፣ የስትራክቸር ፣ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የሰባት ድልድዮች ግንባታ ፣ የሰቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ስራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ግንባታዎችን (የመንገድ ምልክቶችን መትከል ፣ መንገድ ቀለም መቀባት) ባካተተ መልኩ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ በሰሜኑ ሀገራችን የነበረው ጦርነት ፣ በአካባቢው የውሃ እጥረት በከፍተኛ ደረጃ መኖሩ ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ላይ የሚሰተዋለው ስራን የማወክ ተግባራት በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ አስተዋጽኦ እንዳሳደረ በመስክ ቅኝታችን ለመገምገም ተችሏል። ሆኖም ግን የሰመራ እና አካባቢው ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ችግሮችን በቅርብ ርቀት በመከታተል መፍትሄ ለማምጣት እየሰራ እንደሆነ ስራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ሰመራን ከአጎራባች ወረዳዎች ማለትም ከመሰላ ፣ ኮሪ እና ቴሩ ከተሞች ጋር በቅርቀት በማገናኝት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲሳለጥ ያደርጋል። በአካባቢው በርካታ ቁጥር ያላቸው የፍየል እና ግመል እንሰሳት የሚገኙ በመሆኑ አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ መንገዱን ተጠቅሞ በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገቢያ በማድረስ ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችለዋል። ከዚህም ባሻገር የዚህ መንገድ ግንባታ መነሻው ወደ መቀሌ ከሚወስደው ዋና አውራ ጎዳና ጋራ የሚያገናኝ በመሆኑ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ጋር በአቋራጭ ለመገናኘት ይረዳል።

በሳላይሽ-ኦሞ ኮንትራት-3 መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ስራ ተጀመረ ጅንካ፣ ነሐሴ 01፣ 2015 (ኢመአ):- ደቡቡን የሀገራችን ክፍል ከምዕራቡ ጋር በሚያገናኘው የሳላይሽ-ኦሞ ኮንትራት-3 (ከ ኪሎ ሜትር 0+000 እስከ 37+000) መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ስራ ተጀመረ ፡፡ የመንገድ ግንባታው 37 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣ በአሁን ወቅት ከሁለት ኪሎ ሜትር በላይ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተሠርቷል። በተጨማሪም የጠረጋ ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ እንዲሁም የሦስት ድልድዮች ግንባታ ሥራ በመከናወን ላይ ነው። የግንባታውን አጠቃላይ ሥራ በቀጣይ አንድ ዓመት ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ ነው እየተሠራ የሚገኘው። ከዚህ ቀደም ፕሮጀክቱ በሌላ ሀገር በቀል የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ሲከናወን የቆየ ቢሆንም፥ ከአፈጻጸም ውስንነቶች ጋር በተገናኘ ችግር ሲጓተት ቆይቷል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ 508,349,626.36 (አምስት መቶ ስምንት ሚሊዮን ሦስት መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ስድስት መቶ ሃያስድስት ብር ከሰላሳ ሰድስት ሳንቲም) በሆነ ወጪ፣ የግንባታውን ቀሪ ሥራ ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየሠራ ይገኛል። ክላሲክ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ/የተ/የግ/ማኅበር ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ይሠራል። የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የሚሸፈነው። በሥራ ተቋራጩ ከግንባታ ማሽነሪዎች አቅርቦት ጋር በተገናኘ የተስተዋሉ የአቅም እጥረቶች ፣ የስትራክቸር ማለትም የድልድይ እና የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታ ሥራ መዘግየት እንዲሁም በፕሮጀክቱ ክልል ላይ የመሬቱን ተፈጥሯዊ ለምነት ተከትሎ በተደጋጋሚ የሚከሰት የመሬት መንሸራተት ፣ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ችግሮቹ በሚቀረፉበት ሁኔታ ላይ ፣ ከሥራ ተቋራጩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ያካሄደ ሲሆን ፣ ለፕሮጀክቱ አስፈላጊውን የቅርብ ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህን ተከትሎም ችግሮቹ በከፊል መፍትሄ በማግኘታቸው ፥ ፕሮጀክቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው ከፍተኛ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን ፥ በዋናነትም የኦሞ-ወንዝ የሚያቋርጥበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በስፋት የግብርና እንዲሁም የስኳር ፋብሪካ ምርት ውጤቶችን ወደ ተለያዪ የሀገሪቷ ክፍሎች ለማድረስ እንደ አማራጭ ያገለግላል፡፡ በአካባቢው የሚገኘውን የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው።

የሳውላ-ቃቆ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የቃቆ-ወሞሮ ግንባታ ሥራ በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2015 (ኢመአ):- በደቡብ ኦሞ ዞን የሳውላ-ቃቆ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነውን የቃቆ-ወሞሮ ግንባታ ሥራ በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ፕሮጀክቱ 29 ነጥብ 77 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ፣ የጠጠር እና የአስፋልት ኮንክሪት ግንባታ ሥራዎችን ያካትታል። የመንገድ ግንባታው ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሥራ ተቋራጮች ሲከናወን የቆየ ቢኾንም፥ ከአፈጻጸም ውስንነቶች ጋር በተያያዘ ችግር እንዲጓተት ሆኗል። የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ለማጠናቀቅ እንዲቻል፣ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሶዶ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ውል ወስዶ እየሠራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው 16 በመቶው ተጠናቅቋል። እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከልም፣ የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የጠጠር ማምረት፣ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የተጎዱ የመንገዱን ክፍሎች የመጠገን ሥራዎች እየተሠሩ ነው። በሥፍራው በተደረገ የመስክ ምልከታ ለማረጋገጥ እንደተቻለው፥ መንገዱን ለትራፊክ እንቅስቃሴ በከፊል ክፍት ለማድረግ የሚያስችሉ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው። ይህ ፕሮጀክት በተለይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምንያህል በራስ ኃይል ግንባታዎችን መሥራት እንዲሚችል ማሳያ እንደሆነም ተመልክቷል። ለግንባታው የሚውለው 433,614,697.80 (አራት መቶ ሠላሳ ሦስት ሚሊዮን ሥድስት መቶ አሥራ አራት ሺህ) ብር ወጪ በፌደራል መንግስት ነው የሚሸፈነው። የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ትራንስፖርት ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች፣ ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጠር ይሳተፋል። የመንገዱ አስቸጋሪ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና የግንባታ ግብዓት እጥረት እና የዋጋ መናር በግንባታው ላይ ያገጠሙ እክሎች ሲሆኑ፣ ከተለያዩ የባለ ድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ለጉዳዩ መፍትሄ ለመስጠት ጥረት እየተደረገ ይገኛል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ ጂንካ ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የ 784 ኪ.ሜ የጉዞ ርቀት በወላይታ ሶዶ-ቃቆ-ጂንካ በኩል በ 100 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል። በተጨማሪም የወላይታ ሶዶ፣ የጋሞ፣ የጎፍ እና የደቡብ ኦሞ ዞኖች የሚገናኙበት ኮሪደር ነው። በአካባቢው የሚገኙትን የተለያዩ የእህል ምርት ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ ባጠረ ጊዜ ለማቅረብ ያስችላል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et