uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 361 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 755-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 537-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 361 obunachiga ega bo‘ldi.

19 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 119 ga, so‘nggi 24 soatda esa 19 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 40.59% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.42% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 423 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 060 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 20 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 361
Obunachilar
+1924 soatlar
+677 kunlar
+11930 kunlar
Postlar arxiv
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ባለፉት ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም እና በቀጣይ ስራዎች ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደ። በዕለቱ በነበረው ውይይት ፤ የተቋማዊ እና ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች አፈፃፀም ፣ የመደበኛ ስራዎች ፣ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች አፈፃፀም እና በስድስት ወራት የስራ እንቅስቃሴ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች ተዳሰዋል። የኢትዮጵያ መንዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሃመድ አቡዱራህማንን ጨምሮ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ፣ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች በተገኙበት ነው ውይይቱ የተካሄደው። በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ህብረተሰቡን በቅርበት ለማገልገል እና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በቅርበት ለመቆጣጠር እንዲረዳ ታስቦ በአዲስ መልኩ ከተደራጁት 27 የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ፅ/ቤቶች መካከል 25 ፅ/ቤቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ስራ ገብተዋል። ባለፋት ስድስት ወራት ውስጥ የ14 መንገድ ፕሮጀክቶች ግዢ ተፈፅሟል። በተያያዘም የ19 ግንባታ ቁጥጥር (Consultant) ግዥ መፈፀም ተችሏል። በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ውስጥ 397 ኪሎሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ተካሂዷል። ከዚህም ባሻገር በመደበኛ ፣ ወቅታዊ እና ከባድ ጥገና በአጠቃላይ 5,123 ኪ.ሜ የመንገድ ጥገና ስራ ተከናውኗል። በበጀት አመቱ የመጀመሪያ 6 ወራት ለተከናወኑ ተግባራት 26.27 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጓል። ባለፉት ስድስት ወራት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ የፀጥታ ስጋቶች እና የስራ ተቋራጮች አቅም ማነስ እንዲሁም የግንባታ ግብአት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት በግንባታ ፕሮጀክቶቹ ሂደት ላይ መስተጓጐልን እንደፈጠረ በቀረበው ሪፖርት ላይ ተመላክቷል። ከዚህ በተጨማሪም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጉዳዮች በርካታ የመንገድ ግንባታዎች እንዲስተጓጎሉ ስለማድረጋቸው በመድረኩ ተገልጿል። ይህንንም ችግር ለመቅረፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እና መናበብ እንደሚያስፈልግም አፅንኦት ተሰጥቶበታል። ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ የታዩትን ክፍተቶች በመድፈን በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ በርካታ ስራዎች እንደሚከናወኑ በውይይቱ ላይ ተመላክቷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቀጣይ የመንገድ ዘርፍ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቋማችን የመንገድ ዘርፉን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም በቀጣይ ሊደረስበት የታሰበውን ግብ መነሻ በማድረግ የአስር ዓመት መሪ እቅድ አዘጋጅቶ ወደ ተግ
+6
የቀጣይ የመንገድ ዘርፍ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቋማችን የመንገድ ዘርፉን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም በቀጣይ ሊደረስበት የታሰበውን ግብ መነሻ በማድረግ የአስር ዓመት መሪ እቅድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር መግባቱ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎችን እንደ መነሻ በመውሰድ ዕቅዱን ሊያሳኩ የሚችሉ የትኩረት አቅጣጫዎች የተለዩ ሲሆን ፣ እነዚህ የትኩረት አቅጣጫዎችም የሚከተሉት ናቸው፡- - የተጀመሩ የግንባታ እና ጥገና ፕሮጀክቶችን ቅድሚያ ሰጥቶ በፍጥነት ማጠናቀቅ - በየደረጃው ያለውን የመንገድ ሀብት መንከባከብ - ኢኮኖሚያዊ ፋይዳና እምቅ ሀብት ያላቸውን አካባቢዎች መክፈት - በሁሉም አካባቢዎች መሠረታዊ ተደራሽነትን ማረጋገጥ - ከጎረቤት አገራት እና ከወደቦች ጋር ያለውን ትስስር ማጠናከር - ህዝቦችን ማስተሳሰር - ለሥራ እድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት - የአገር ውስጥ ሀብት እና አቅምን ማጎልበት እና በስፋት መጠቀም - የተሳለጠ፣ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝ እና መረጃ ሰጪ የትራንስፖርት ስርአት /ITS/ - የአስፈጻሚ ተቋማትን እና ፈጻሚ አካላትን አቅም መገንባት ከእነዚህ የትኩረት አቅጣጫዎች በተጨማሪ ዘላቂ የልማት ግቦች እና የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ጨምሮ የተለያዩ አለምአቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች ከግምት ውስጥ ገብተዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክከርና የትውውቅ መድረክ አካሄደ። ቡታጅራ፣ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓም(ኢመአ)፡ የቡታጂራ አካባቢ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክከርና የትውውቅ መድረክ በጽህፈት ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ አካሄደ፡፡ በአዲሱ የኢመአ የአደረጃጀት ለውጥ መሰረት ከተቋቋሙ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የቡታጂራ አካባቢ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ስራውን ከ 6 ወራት በፊት የጀመረ ሲሆን በእነዚህ ወራት ውስጥም በርካታ ተግባራትን እንዳከናወነ ይታወቃል ፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ በአካባቢው ከሚገኙ የከተማ ፣ የዞን ፣ የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ከመንገድ ግንባታ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላትን በአንድነት የሚያገናኝ የጋራ ምክክርና የትውውቅ መድረክ ነው በጽ/ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተዘጋጀው ፡፡ በእለቱ ተገኝተው የነበሩት ተሳታፊዎች የመድረኩ መዘጋጀትን አድንቀው ከዚህ በፊት በስልክ ለመፍታት የሚያዳግቱ ጉዳዮችን በቅርበት ለመፍታት እና በርካታ ወጪዎችን ለመቀነስ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ መቋቋም ወሳኝ ሚና የሚጫወት በመሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል ፡፡ የቡታጂራ አካባቢ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ እንጂነር ብሩክ ተክሌ፣ “ በፅህፈት ቤታችን ሥር የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ብሎም ጥራታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እናደርጋለን “ ብለዋል፡፡ መንግስት ለመንገድ ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱ ይታወቃል፡፡ ከዚህም አኳያ የመንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም በማሻሻል የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታዎችን ለማጎልበት የፕሮጀክት ጽቤቶች በየአካባቢው መቋቋማቸው አስፈላጊነቱ ይታመንበታል፡፡ የቡታጂራ አካባቢ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በአሁኑ ወቅት 6 ፕሮጀክቶችን(በዲዛይንና ጨረታ ሂደት ላይ ያሉትን ሳያካትት) ይቆጣጠራል ፡፡ እነዚህም ወራቤ - ቦዣበር ፣ ቆሾ - ሚጦ - ወራቤ ፣ ቡልቡላ - አራጌ ፣ ኦሞወንዝ - ተርጫ ፣ ቱሉቦሎ - ኬላ እና ጉንቹሬ - ቆሴ - ጌጃ -ሌራ - የመንገድ ፕሮጀክቶች ናቸው ፡፡ ከእነዚህ መሃከልም ኦሞወንዝ - ተርጫ እና ቱሉቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክቶች በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙም በመድረኩ ላይ ተገልጽዋል ፡፡ በሌላ በኩልም በወራቤ - ቦዣበር የመንገድ ፕሮጀክት የሚስተዋለው ከፍተኛ የአፈጻጸም ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ተግባራት በቀጣይ የሚከናወኑ ይሆናል፡፡

ቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት
+6
ቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት

ቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም 79.05 ላይ ደርሷል -------------------------------------------------------------------------------- የካቲት 6፣ 2015(ኢመአ) ፦ የአሰላ እና ሻሸመኔ ከተመኮችን የሚያገናኘውና 92.238 ኪ.ሜ. የሚረዝመው ቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም 79.05 ላይ ደርሷል ፡፡ ፕሮጀክቱ፣ በመጋቢት 19 ቀን 2011 ዓ.ም. የተፈረመ ሲሆን ወደ ሥራ የገባው ነሐሴ 10 ቀን 2011 ዓ.ም. ነበር፡፡ እስከ አሁን የድልድይ ግንባታ እና የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ስራ፣ የሰብ-ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ስራ፣ የአስፋልት ንጣፍ እና የመንገድ ጠርዝ ቀለም የመቀባት ስራ በድምሩ 72.92 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ሥራ የተከናወነ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 71 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ ስራ ነው፡፡ ግንባታውን የቻይና ኮሚዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (CCCC) ተቋራጭ እያከናወነ ነው። የማማከሩን ሥራ ደግሞ ሽላዲያ አሶሴት ከኢንሲራድ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ሲስተም እና ሂትከን ኢንጅነሪንግ ጋር በጣምራ እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡ መንገዱ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ሲሆን አሁን በአስፋልት ደረጃ ተሸሽሎ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ለግንባታው የሚውለው 1,668,745,531.73 ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት የሚሸፈን ነው። መንገዱ በዋናነት ቢላሎ ከተማን፣ ኤጎ ከተማን፣ ቀርሳ ከተማን እና ጎልጆታ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን ይኸውም የአሰላ እና ሻሸመኔ ከተማን ለማገናኘት ቀላል ያደርገዋል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያልፍባቸው ዞን እና ወረዳዎች በስንዴ እና ድንች አምራችነት በሃገራችን ከሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ተጠቃሽ ስለሆኑ እነዚህን የግብርና ምርቶች ወደ መሃል ሃገር ገበያ ለማምጣት የመንገዱ ግንባታ ጉልህ ሚና አለው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመንገዱ መገንባት የአዲስ አበባ-ሻሸመኔ መንገድን እና የአዳማ-አሰላ-ዶዶላ መንገድን ለማገናኘት የሚረዳ ሲሆን ይኸውም ከሻሸመኔ ወደ አሰላ እና አዳማ የሚደረጉ ጉዞዎችን በእጅጉ ቀላል ያደርጋቸዋል፡፡

ከመሬት መንሸራተት ጋራ ተያይዘው የሚከሰቱ ችግሮች ላይ እና በቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ፅሁፍ በማቅረብ ዉይይት ተካሄደ፡፡ የመሬት መንሸራተትን ለመቅረፍ በዲዛይን ወቅት ቅድመ ጂኦ ቴክኒካል ጥናት በጥልቀት መከናወን እንዳለበት በቀረበዉ ጥናት ላይ ተመላክቷል፡፡ ይህ የተገለጸው ከመሬት መንሸራተት ጋራ ተያይዞ የሚከሰቱ የመንገድ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል የባለሙያዎች ጥናትና ምክክር መድረክ (Workshop) ቃሊቲ በሚገኘው የኢመአ መንገድ ምርምር ማዕከል በተካሄደበት ወቅት ነው። በውይይት መድረኩ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቃሊቲ መንገድ ምርምር ስራተኞች እና ሀላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ምሁራን፣ የሲቪል መሐንዲሶች ማህበር ተወካይ፣የኢመአ የመንገድ ዲዛይን ክፍል ሰራተኞች እና አማካሪ መሃንዲሶች ተሳትፈውበታል። ጥናቱ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሲሆን በጥናቱ የተገኙ ግኝቶች ለተሳታፊዎች ቀርበዋል። በመላው አገሪቱ ከተገነቡት እና በግንባታ ሂደት ላይ በሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የመሬት መንሸራተት እንደሚከሰት በጥናቱ ላይ ተመልክቷል። ለጥናቱ መነሻነት ከአዲስ አበባ ባህርዳር በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው የአባይ ሸለቆ፣ ከደብረብርሃን -አጣዬ- ደሴ እና ዋቻ-ማጂ የመንገድ መስመሮች እንደ ማሳያነት ተወስደዋል። በዕለቱ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር የቀረበው ወርክሾፕ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን ከአሁን በኃላ ተከታታይ ወርክሾፖች ከተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋራ በመናበብ እንደሚዘጋጅ ተጠቁሟል። በመሬት መንሸራተት ምክንያት የተበላሹትን መንገዶች ለመጠገን በአመት መንግስት ብዙ ገንዘብ እንደሚያወጣ በጥናቱ ላይ ተመላክቷል። ይህንን እና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ ኢመአ በመንገድ ምርምር ማዕከል ውስጥ በርካታ የጥናት እና ምርምር ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያስገነባቸው ያሉ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀቶችን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችለውን አዲስ አደረጃጀት በመፍጠር ወደ ስራ እንደገባ የሚታወስ ነው፡፡ በአዲሱ የአደረጃጀት የግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶቹ የመንገድ ፕሮጀክቶች በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተቋቋሙ በመሆናቸው፤ ኘሮጀክቶቹን በቅርበት ለመከታተልና ለመደገፍ አስቻይ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ በዚህም ረገድ ከተቋቋሙት የኘሮጀክት ጽ/ቤቶች መካከልም የፍጥነት እና ልዩ ፕሮጀክቶች ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ስር የአዳማ አዋሽ ፣ የሞጆ-ሐዋሳ እና የኮይሻ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች ይገኛሉ፡፡ የሞጆ-ሐዋሳ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ፅ/ቤት በአጠቃላይ 17,850,833,680.64 በሚሆን የገንዘብ መጠን 6 የመንገድ ፕሮጀክቶችን (በዲዛይንና በጨረታ ሂደት ላይ ያሉትን ሳያካትት) እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የአዳማ-አዋሽ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ፅ/ቤት በአጠቃላይ 6,688,456,565.74 በሚሆን የገንዘብ መጠን 1 (በዲዛይንና በጨረታ ሂደት ላይ ያሉትን ሳያካትት) የመንገድ ኘሮጀክት እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት የሞጆ-ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ፅ/ቤት እና የአዳማ-አዋሽ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ፅ/ቤት ያካተቷቸውን ፕሮጀክቶች መረጃ እናስተዋውቃለን፡፡ ከታች የተጠቀሱትን ፕሮጀክቶች አስመልክቶ የአካባቢው ህብረተሰብ እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ጥያቄዎችን ለማቅረብ በአዳማ-አዋሽ እንዲሁም በሞጆ-ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ማምራት እንደምትችሉ እየገለጽን ፣ እነዚህ ጽ/ቤቶች የታለመላቸውን ግብ እንዲመቱ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ የአዳማ ኪ.ሜ60 የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት መገኛ አድራሻ፡- አዳማ ከተማ ሞኤንኮ ፊትለፊት የሞጆ-ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት መገኛ አድራሻ፡- ሻሸመኔ ከተማ ሲሲሲሲ ካምኘ ውስጥ ፖ.ሳ.ቁ. 1770 ድረ ገጽ www.era.gov.et ፌስ ቡክ www.facebook.com/ethiopianroadsauthority ቴሌግራም@ethioroadsለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡

ፖ.ሳ.ቁ. 1770 ድረ ገጽ www.era.gov.et ፌስ ቡክ www.facebook.com/ethiopianroadsauthority ቴሌግራም@ethioroadsለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ
+1
ፖ.ሳ.ቁ. 1770 ድረ ገጽ www.era.gov.et ፌስ ቡክ www.facebook.com/ethiopianroadsauthority ቴሌግራም@ethioroadsለማንኛውም ተጨማሪ መረጃ የዋናው መ/ቤት ነፃ የስልክ መስመር 8561 ይጠቀሙ፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። ኢንጂነር ሀብታሙ ላለፉት አራት አመታት ተኩል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደ
+1
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። ኢንጂነር ሀብታሙ ላለፉት አራት አመታት ተኩል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን በዋና ዳይሬክተርነት የመሩ ሲሆን በቆይታቸውም በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ ችለዋል። በተለይም የመንገድ ዘርፉ መሰረታዊ ችግሮች እንዲፈቱ ወሳኝ የሆኑ የፖሊሲ እና ስትራቴጅያዊ ጉዳዮች ተግባራዊ እንዲደረጉ ከማድረጋቸውም ባሻገር የተለያዩ የተቋም ግንባታ እና የሪፎርም ስራዎችን ተግባራዊ በማድረግ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል። ከዚህም በተጨማሪ ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ አካባቢዎች በኅብረተሰቡ የሚነሱ የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ከግንዛቤ በማስገባት ምላሽ እንዲሰጥባቸው በማድረግ የመንገድ መሰረት ልማት እንዲስፋፋ አድርገዋል። በተያያዘም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽንን በሃላፊነት የመሩት ኢንጅነር መሀመድ አብዱራህማን ከጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሹመዋል። እንጂ. መሀመድ ላለፋት 20 ዓመታት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን ከፕሮጀክት መሀንዲስነት እስከ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተርነት እንዳገለገሉ የሚታወስ ሲሆን ካላቸው የትምህርት ዝግጅት በተጨማሪ የረጅም አመታት የካበተ የስራ ልምዳቸው የተጣለባቸውን ሀላፊነት በብቃት ኢንዲወጡ ያስችላቸዋል።

የመንገድ ወሰን ማስከበር ስራ እና የባለድርሻ አካላት ሚና:- መንገድ ለአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ መሆኑ ይታወቃል። የመንገድ መሰረት ልማትን ማስፋፋት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን ከማጎልበት ባሻገር ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገትን ይበልጥ ያሳልጣል። የመንገድ መሰረተ ልማት መስፋፋት አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ ለማድረስ ያግዘዋል፣ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችን በመጎብኘት ከቱሪዝም እንዱስትሪ የሚገኘውን ገቢ ለሌሎች የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ መጠቀም ይቻላል። በአጠቃላይ የመንገድ መስፋፋት ለሁሉም መሰረት ልማት ዝርጋታዎች ምሶሶ ነው። ስለሆነም የተጀመሩ መንገዶች በተያዘላቸው ጊዜ፣የጥራት ደረጃና በጀት መጠናቀቅ ይችሉ ዘንድ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ትብብር ያስፈልጋል። ሆኖም ግን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እና በጀት እንዳይጠናቀቁ ተጽዕኖ ከሚያሳድሩ በርካታ ምክንያቶች መካከል የመንገድ ወሰን ማሰከበር ከፍተኛ ድርሻ አለው፡፡ ኢመአ ከወረዳ፣ ከዞንና ከክልል የመስተዳደር አካላት ጋራ በመናበብ በሚያስገነባቸው የመንገድ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶችን ካሳ ከፍሎ ንብረት አስነስቶ ለሥራ ተቋራጮች ማስረከብ ይጠበቅበታል፡፡ ከወሰን ማስከበር ጋራ ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮችን በመናበብ መፍታት ከተቻለ መንገዶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ በተመደበላቸው የገንዘብ ልክ እና የጥራት ደረጃ ተገንብተው እንዲጠናቀቁ ጉልህ ሚና አለው። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መንገዱን ከሚገነባው ከሥራ ተቋራጩ እንዲሁም የምህንድስና እና የቁጥጥር ስራውን ከሚያካሂደው አማካሪ ድርጅት ጋር የኮንትራት ውል ከፈፀመ በኋላ የመንገድ ወሰንን መለየት የመጀመሪያ ስራው ይሆናል። ይህንኑ ማስፈጸም ይቻል ዘንድ የህዝብን ጥቅም በማይጎዳ መልኩ የመንገድ መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ንብረት የሚነሳበትንና ለንብረት ካሣ ስለመክፈል የሚደነግግ አዋጅ በቁጥር 1161/2011 ተደንግጓል፡፡ በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እያንዳንዱ ባለድርሻ አካል የወሰን ማስከበር ሥራን በተመለከተ ሊወጣው የሚገባውን ኃላፊነት /ግዴታ ለግንዛቤ ያክል እንደሚከተለው ቀርቧል:: 👉የሥራ ተቋራጭ ኃላፊነት > በመንገድ ክልል ውስጥ የሚገቡ ንብረቶች እንዲነሱለትና በሚያቀርበው መጠየቂያ የተነሺ ንብረት ዝርዝር እና የሚገኝበት ሥፍራ በግልፅ ማስቀመጥ ይጠበቅበታል። > የሚጠየቀው ቦታ ለሥራው ከሚያስፈልገው ጋር ተመጣጣኝ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል (ለካምፕ ለግብዓት ማውጫ የሚጠየቁ ቦታዎች)። > የሚቀርበው መጠየቂያ የአገልግሎት መስመሮችን የማዛወር ሥራ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። > የግብዓት ቦታዎች ለመንገድ ግንባታ በሚፈለገው መጠንና ጥራት ያለው መሆኑን የሚያረጋግጥ Laboratory Test result ከመጠየቂያው ጋር አያይዞ ማቅረብ ይጠበቅበታል። 👉የአማካሪ ድርጅት ኃላፊነት > የሥራ ተቋራጩ ባቀረበው መጠየቂያ ላይ የተዘረዘሩትን ንብረቶች በመንገድ ክልል ውስጥ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል። > ማንኛውም የንብረት ይነሳልኝ ጥያቄ በአካባቢ ላይ /Enviromental IMPACT/የሚያደርሰውን ተፅእኖ ግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል:: > በመንገዱ ግራና ቀኝ የመንገዱን ወሰን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል። > የመንገዱን ወሰን የሚያመላክቱ ችካሎች መኖራቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል። 👉የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ኃላፊነት > ግምት ስራ የሚያስተባብርና ልኬት የሚወስድ የግምት ሰነድ የሚያዘጋጅ የመንገድ መብት ማኔጅመንት ኦፊሰር(Row management officer) ይመድባል። > ለስራው የሚያሰፈልገውን መሬትና መሬቱ የሚገኝበትን ትክክለኛ ስፍራ የሚያሳይ መረጃ ማቅረብ። > የመንገድ መብት ማኔጅመንት ኦፊሰሩ ለወረዳ /ከተማ አስተዳደሩ ለሚሰይማቸው የንብረት ገማች ኮሚቴዎች ለህዝብ ጥቅም ሲባል ንብረት የሚነሳበትና ካሣ የሚከፈልበትን ስርዓት አስመልከቶ የታወጀውን 1161/2011 እና የሚኒስትሮች ምክርቤት የፀደቀውን ደንብ ቁጥር 472/2012 ያስተዋውቃል፣ የግንዛቤ ማስጨበጫም ይሰጣል። > የካሣ ክፍያ ግምት በመንገድ ክልል ውስጥ የገቡ ንብረቶችን ብቻ በተመለከተ መሰራቱን ያረጋግጣል። > የካሣ ግምት ሰነዱ በሚመለክታቸው የኮሚቴ አባላት ሰርቬየሮች የወረዳ/የከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች መፀደቁን ያረጋግጣል ክፍያ ለማስፈፀም ለሚመለከተው የኮንትራት አስተዳደር ዳይሬክቶሬቶች ያስተላልፋል ደንብና መመሪያን ተከትሎ የተዘጋጀ ሰነድ መሆኑን አረጋግጦ ክፍያ ይፈፀማል። > የካሳ ክፍያ የተፈፅመባቸውን አካባቢዎች ከንብረት ነፃ መደረጋቸውን ይከታተላል። የወረዳ (ከተማ) አስተዳደር ኃላፊነት > የንብረት ገማች ኮሚቴ አካላትን መርጦ ይሰይማል የአባላቱን ዝርዝር ለኢመአ ያሳውቃል። > ለሰብሎችና ለሌሎች ተነሽ ንብረቶች የነጠላ ዋጋ ያዘጋጃል የነጠላ ዋጋው ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት የባለስልጣን መሥሪያ ቤቱን ይሁንታ እንዲያገኝ ያሳውቃል። > በመንገድ ግንባታ ምክንያት የሚፈናቀሉ ተነሺዎች ባለንብረቶች መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ያቀርባል። > ለህዝብ ጥቅም ሲባል በመንግስት አካላት፣ በግል ባላሃብቶች፣ በማህበራት ወዘት ለልማት ስራ ሲፈለግ አግባብ ባለው የክልሉ ወይም የፌደራል መንግስት ወይም የበላይ አካል ለዚሁ አላማ እንዲውል የተጠየቀውን የገጠር ወይም የከተማ መሬት በአዋጅ ቁጥር 455/97 መሰረት ካሳ እንዲከፈል በማድረግ ንብረቱን ከመንገድ ክልል ውስጥ ያስነሳል/ያስለቅቃል። > በመንገድ ክልል ውስጥ ህገወጥ ግንባታ እንዳይከናወኑ ይከላከላል ተፈጽሞ ሲገኝ ያስነሳል አስፈላጊውን እርምጃዎችን ይወስዳል ።

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል!!

አዲስ አበባ ጥር 08 ቀን 2015 (ኢመአ) በአማራ ፣ በትግራይ እና በአፋር ክልሎች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ስድስት ድልድዮች ተገቢው ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስ
+1
አዲስ አበባ ጥር 08 ቀን 2015 (ኢመአ) በአማራ ፣ በትግራይ እና በአፋር ክልሎች የሚገኙና በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸው የነበሩ ስድስት ድልድዮች ተገቢው ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ ለእነዚህ ድልድዮች ጥገናም ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል። በአስተዳደር መስሪያ ቤቱ የድልድይ እና ስትራክቸር ሥራዎች ዳይሬክተር አቶ ጌትነት ዘለቀ የአልውሃን ድልድይ ጨምሮ የስድስት ድልድዮች ጥገና ስለመከናወኑ ገልፀዋል፡፡ የአልውሃ ድልድይ ከዚህ ቀደም ጉዳት ደርሶበት የነበረ ሲሆን ፣ በወቅቱ 54 ነጥብ 86 ሜትር ርዝመት ያለው የብረት ድልድይ ተሰርቶለት አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን ድልድዩ ዳግመኛ በመጎዳቱ ምክንያት በጊዜያዊነት በተሠራው የብረት ድልድይ ላይ የመውደቅ ስጋት በማስከተሉ 109.73 ሜትር ርዝመት ያለው አዲስ የብረት ድልድይ ሊገነባ ችሏል። ከወልዲያ ወደ ቆቦ ከሚያሻግረው የአልወሃ ድልድይ ባሻገር ፣ ከሚሌ-ጭፍራ- ወልዲያ የሚያሻግረው 48 ነጥብ 86 ሜትር የሚረዝመው የጨረቲ ድልድይ ፣ ሁመራ እና ሽሬን የሚያገናኘው 27. 43 ሜትር የተከዜ 3 ድልድይ ፣ ከቆቦ የገጠር አካባቢዎች ጋር የሚያገናኘው 48 ነጥብ 86 ሜትር የጎቡ ድልድይ ፣ ከአምደወርቅ ወደ እብናት በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው 48 ነጥብ 86 ሜትር የተከዜ ድልድይ እና ከኮረም ወደ ሰቆጣ የሚወስደው 42 ነጥብ 67 ሜትር የጽላሬ ድልድዮች ተገቢው ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። በቀጣይም በእነዚህ አካባቢዎች ጉዳት በደረሰባቸው ድልድይና መንገዶች ላይ አስፈላጊ የጥገና ብሎም የደረጃ ማሻሻል እና የማሳደግ ተግባራት ይከናወናሉ፡፡

ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የቡሬ-ጎመርና ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። ቡሬ ጥር 03 ቀን 2015 (ኢመአ) ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው የቡሬ-ጎመርና ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 43 ኪሎ ሜትር የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል። በቡሬ እና አካባቢው የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት በዕቅድ የተያዙትን እንዲሁም በጨረታ እና ዲዛይን ሂደት ላይ የሚገኙትን ሳያካትት 726.76 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው 11 ፕሮጀክቶች ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የገንዘብ መጠን ግንባታቸው በመካሄድ ላይ ይገኛል። ከእነዚህ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መካከልም የቡሬ-ጎመርና ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አንዱ ነው። የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ሜድሮክ ኮንስትራክሽን ሲሆን ፣ አይ.ኤም.ኤስ ኢንጅነርስ ከፕሮፌሽናል ኢንጅነርስ ኮንሰልቲንግ ጋር በጋራ በመሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን በማካሄድ ላይ ይገኛል። እየተገነባ ያለው የቡሬ-ጎመርና ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በከተማ 21.5 በቀበሌ 15.5 ሜትር እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። አጠቃላይ ሥራውን በሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ እየተሰራ ይገኛል። የግንባታ ስራው ከተጀመረ አንድ ዓመት ከሁለት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ፣ የስራ ተቋራጩ በአሁኑ ወቅት የዕቅዱን 22.7 በመቶ ስራ ማከናውን ችሏል። መንገዱ በተገቢው ሁኔታ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል የአካባቢው ህብረተሰብ ከፍተኛ ትብብር በማድረግ ላይ እንደሚገኝ የቡሬ እና አካባቢው ኮንሽትራክሽን ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ሁሉ አለምነህ ገልፀዋል። የዚህ አካባቢ ህብረተሰብ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ ተጠቃሚ ያልነበረ በመሆኑ ምክንያት የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎች ይኖሩታል፡፡ በዚህ አካባቢ ከፍተኛ የበርበሬ ምርት ፣ የተለያዩ የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ፣ ማር ፣ የጎጃም ማኛ ጤፍ ፣ ስንዴ ፣ በቆሎ እና ሌሎች የግብርና ምርቶች በከፍተኛ ደረጃ ይመረታሉ፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ፣ እነዚህን የግብርና ምርቶችን ያለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጀ እንዲያድግ ለማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም በክልሉ ለሚገኙ የኢንዱስትሪ ዞኖች የትራንስፖርት ፍሰት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር ባለሃብቶች በአካባቢው የተለያዩ የኢንዱስትሪ ዞኖችን እንዲገነቡ ለማስቻል ከፍተኛ ተነሳሽነትን ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል፡፡

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል!!