uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 369 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 753-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 530-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 369 obunachiga ega bo‘ldi.

20 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 129 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 38.47% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.24% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 143 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 037 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 21 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 369
Obunachilar
+824 soatlar
+697 kunlar
+12930 kunlar
Postlar arxiv
የዱራሜ - ደምቦያ _ አንጋጫ- አመቾ እና ዋቶ - ሀላባ 65 .1 ኪ.ሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ በይፋ ተጀመረ። በመንገዱ ጅማሮ መርሀ -ግብር ላይ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣ የደቡብ ብ/ብ/ሕ /ክ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ርስቱ ይርዳው ፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል ፡፡ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ በዱራሜ ከተማ በተካሄደው የፕሮጀክቱ ጅማሮ መርሀ_ግብር ላይ እዳሉት መንገዱ በአገልግሎት ብዛት ከነዋሪውም አልፎ መስመሩን በሚጠቀሙ አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ ሲፈጥር የቆየ መሆኑን እውስተው በቀጣይ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ችግር ከመቅረፉም ባለፈ በአካባቢው የሚመረተውን የሰብል እና ፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎች የተፈጥሮ ፀጋዎችን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል ብለዋል። የደቡብ ብ/ብ/ሕ /ክ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው የህዝቦች የአመታት የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ምላሽ እያገኙ ስለመምጣታቸው ዛሬ ግንባታውን ያበሰርነው የዱራሜ - ደምቦያ _ አንጋጫ- አመቾ ዋቶ - ሀላባ መንገድ አንዱ ጉልህ ማሳያ ነው ብለዋል። ለፕሮጀክቱ ስኬትም መላው የአካባቢው ህዝብ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ድጋፍ እና ክትትል እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በበኩላቸው የደምቦያ- ዱራሜ አንገጫ አመቻ አመቾ እና ሀላባ - ዋቶ መንገድ በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1,980,658,256.31 ቢሊዮን ብር በጀት ከጠጠር ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ እንደሆነ ገልጸዋል ። ይህም ከአካባቢው አልፎ ለሀገር የኢኮኖሚ ግንባታ ግዙፍ ፋይዳ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት በመጀመሩ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። ፕሮጀክቱ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የጥራት ደረጃ እንዲሁም ወጪ እንዲጠናቀቅ ህገ ወጥ ግንባታ እና በስራ ላይ የሚያጋጥሙ የወሰን ማስከበር ጥያቄዎች በአፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ውሳኝ እንደሆነም ገልጸዋል። በቀጣይም የሻሸመኔ ሃላባ ፣ አዲስ አበባ ሆሳህና ሶዶ ፣ ዱራሜ ዱርጊ መንገዶች ግንባታ እንደሚጀመሩ እና የዱርጊ ወልደሀኔ ኦሞ ወንዝ ፕሮጀክት ለማስጀመር በዳግም ጨረታ ሂደት ላይ እንደሚገኘ ዋና ዳይሬክተሩ በመርሃግሩ ላይ ባደረጉት ንግግር አብራርተዋል ። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ስራ አስፈጻሚ ኢ/ር ዮናስ አያሌው የፕሮጀክቱን ስራ በውሉ መሰረት በሶስት አመት ውስጥ የጥራት ደረጃውን ጠብቀን የህዝቦቹን የዘመናት ጥያቂ ምላሽ እንሰጣለን ሲሉ ቃል ገብተዋል። የደምቦያ- ዱራሜ አንገጫ አመቻ ዋቶ ሀላባ - ዋቶ መንገድ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በሻሸመኔ ሃዋሳ የሚዘልቀው አውራ መንገድ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በቡታጅራ ወደ ወላይታ ሶዶ የሚያመራውን ሌላኛወ አውራ መንገድ በአቋራጭ የሚያገናኝ ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት ነው ። 65.1 ኪሜ ርዝመት ያለው ሲሆን ፕሮጀክቱ ለመገንባት 1,980,658,256.31 በጀት የተመደበ ሲሆን ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ መንገዱ የሚገነባው በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን በተባለ የመንግስት ልማት ድርጅት ነው፡ አሁናዊ የመንገዱ ይዞታ በጠጠር ደረጃ ያለ እና በግልጋሎት ብዛት ሳቢያ ከፍተኛ ጉዳት ተዳርጎ የቆየው መንገዱ በቀጣይ ከሚኖረው መህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንጻር ደረጃቸውነ በጠበቀ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት የሚገነባ ይሆናል ፡፡ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቀው ፕሮጀክቶቹ ከዚህ ቀደም ለመጓጓዝ ከ3 ሰዓታት በላይ ይፈጅ የነበረውን የተሸከርካሪ የጉዞ ጊዜ በግማሽ በማሳጠር የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ያሳድጋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም በክርምት ወቅት መንገዱን ለመጠቀም በእጅጉ ፈታኝ እና ለተደጋጋሚ ተሸከርካሪዎች ብልሽት እንዲሁም ይወጣ የነበረን አላስፈላጊ የመለዋወጫ ወጪ በማስቀረት ነዋሪውም ሆነ አሽከርካሪዎች ዘመናዊ እና ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል፡፡ ከዛም ባለፈ በአካባቢው ታዋቂ የሆነውን የሃላባ በርበሬ ጨምሮ ሌሎች ቋሚ የሰብል ምርቶችን ፣ የፍራፍሬ ውጤቶች እና የቁም እንስሳትን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ፍጥነት በማድረስ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ፡፡ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ድርጅት የመንገዱን ግንባታ ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር የሚሳተፍ ይሆናል፡፡ የመንገድ ግንባታ ቢጠናቀቅበት ወቅት የጎን ስፋቱ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በዞን 21.5 ሜትር ፣ በወረዳ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር ስፋት ይኖረዋል ፡፡

The 7th Annual National Road Research Conference
The 7th Annual National Road Research Conference

የኩርባ መገንጠያ-ጋሸና 44.6 ኪ.ሜ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለሥልጣናት በተገኙበት በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ። በመርሃ-ግብሩ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ፣በሚኒስትር ማዕረግ የእስትራቴጂ ጥናትና ምርምር ማእከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሀንስ ቦያለው፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘና ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለሥልጣናት ታድመዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ከደሴ ወደ ላሊበላ ከተማ ለመሄድ ምንም ዓይነት ደረጃውን የጠበቀ አማራጭ መንገድ ባለመኖሩ ህብረተሰቡ የደሴ-ወልድያ-ጋሸና መንገድን በዋናነት ሲጠቀም ቆይቷል። ይህም ለእንግለት ና ለከፍተኛ የትራንስፖርት መጉላላት ነዋሪውን ዳርጎት ቆይቷል። ይህ የመንገዱ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የሕብረተሰቡን የቆየ እንግልት የሚያስቀር ከመሆኑም ባሻገር የጥንታዊው እና ታሪካዊው የላሊበላ ታሪካዊ ቅርሶች መዳረሻ በመሆኑ የአካባቢውን የቱሪስት ተደራሽነት ከማሳደግ አንፃር የሚኖረው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው። የመንገዱን ግንባታ የሚያከናውነው ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ነው። የአማራ ክልል የመንገድና ህንፃ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ስራዎች ድርጅት ማማከርና የቁጥጥር ስራውን ያካሂዳል፡፡ ፕሮጀክቱ የሚጠይቀውን አጠቃላይ የግንባታ ወጪ አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ አራት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራ ዘጠኝ ሺህ ብር በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ ከዚህ ቀደም ህብረተሰቡ በመንገድ ዘርፉ ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥያቄዎቹን ሲያቀርብ ቆይቷል። ነገር ግን ከለውጡ በኃላ የክልላችንን ህዝብ በዘርፉ ፍትሃዊ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስት ጠንክሮ እየሰራ ይገኛል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናግረዋ። የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ፍፃሜቸውን እንዲያገኙ በተለይም የወሰን ማስከበር ተግዳሮት እንዲፈታ ክልሉ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጦዋል ። የትራንስፓርት ሚኒስትሯ ክብርት ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ በበኩላቸው ይህ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ ወጪ የሚደረግለት መንገድ በሚጠበቀው የጥራት ደረጃና ፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎ ለመስጠት እንዲችል ሁላችንም የድርሻችን ልንወጣ ይገባል ብለዋል። እንደ ሀገር የተያዙ የመንገድ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን መንግስት በትኩረት መገንባቱን ይቀጥላል ብለዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ህብረተሰብ ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ የሚመለከታችሁ የመስተዳድር አካላትና ነዋሪዎች አስፈላጊውን ትብብር እንድያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል ። ኢመባ ኘሮጀክቱ በስኬት እንዲጠናቀቅም የቅርብ ድጋፍ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል ፡፡ የመንገድ ግንባታውን የሚያከናውነው ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በበኩሉ በተገቢው ጥራት ከተያዘለት የጊዜ ገደብ ቀድመን እንጨርሳለን ሲል ቃል ገብቷል። የኩርባ መገንጠያ-ጋሸና መንገድ አሁናዊው ገጽታ በጠጠር መንገድ ደረጃ ያለ ከመሆኑም በላይ በአገልግሎት ሳቢያ እጅግ የተጎዳ ነው፡፡ በቀጣይ መንገዱ በገጠር የመንገድ ትከሻን ሳይጨምር 7 ሜትር እንዲሁም በከተማ 19 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ይገነባል፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከደሴ-በወልድያ-ጋሸና-ላሊበላ ለመሄድ ይወስድ የነበረውን ረጅምና ዙሪያ ጥምጥም መንገድ በማሳጠር ምቹ የሆነ የትራንስፖርት ፍሰትን ይፈጥራል፡፡ በአጠቃላይ የመንገዱ መገንባት በአካባቢው ላለው የቱሪዝም እንቅስቃሴ መነቃቃት ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ በሥፍራው በስፋት የሚመረቱትን የሰብልና የፍራፍሬ የግብርና ምርቶች በተቀላጠፈ መንገድ ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላል፡፡

በዛሬው ዕለት የመንገድ ልማት ሪፎርም ሰነዶች ማጽደቂያ መርሃ ግብር ተካሄደ። በውይይቱ መድረክ ላይ ክብርት የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ዴኤታዎች ክቡር አቶ ካሳሁን ጎፌ እና ክቡር ኢንጅ. የኋላሸት ጀመረ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅ. ሀብታሙ ተገኘ እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ታድመውበታል። በእለቱም የሚኒስቴር መ/ቤቱ ያፀደቃቸውን ብሔራዊ የትራንስፖርት ፓሊሲ እና 10 ዓመት መሪ ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ከመንገድ ልማት ሪፎርም አንጻር ወሳኝ የፖሊሲ እና ስትራቴጅያዊ ሰነዶችን ወደ ትግበራ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ሰነዶች እንዲቀርቡ ተደርጓል። ጥናት ተደርጎባቸው ከቀረቡት ችግር ፈቺ ከሚባሉት ሰነዶች መካከል :- የመንገዶች የአገልግሎት ደረጃ ምደባ ጥናት:- ዋና አላማው ወቅታዊ መረጃን መነሻ በሚያደርገው የተከለሰ የትራፊክ አመንጪ አካባቢዎች ላይ በመመርኮዝ ነባር መንገዶችን በዚሁ መሰረት መመደብ ፣የዓዲስ መንገዶችን ደረጃ መመደብ ፣እንዲሁም የመንገድ ንምባለብልትነት ስልጣን እና የዓስተዳደር ሀላፊነትን የሚወስን ሲሆን በጥናት ደረጃ ተጠናቆ ቀርቧል። የክልሎች አቅም ግንባታ :- ዓላማው ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ የተዘጋጀውን የመንገዶች አገልግሎት ደረጃ ለመተግበር የክልሎችን አቅም በመገንባትና አደረጃጀታቸውን ወጥ በማድረግ የስራ ክፍፍል ወይም ክልሎች በተሻለ ብቃት የመንገድ መሰረተ ልማቶችን እንዲዘረጉ አቅም መገንባት። የ10 ዓመት የገጠር መንገድ ዕቅድ:- በቀጣይ 10 ዓመታት የገጠር መንገድ ልማትና ሀብት አስተዳደርን በማሻሻል አብዛኛው የገጠር የህብረተሰብ ክፍል ከዋና ዋና መንገዶች ጋር እንዲገናኙ በማድረግ ትስስርን እና ሁሉን አቀፍ ተደራሽነትን ማረጋገጥ ያስችላል። የመንገድ አዋጅ :- የመንገድ አገልግሎት ደረጃ ምደባ ጥናትንና ሌሎች ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ በመንገድ ዘርፍ ውሳኔ እና አቅጣጫ ለሚሹ ጉዳዮች የሕግ ማእቀፍ በመሆን አሁን ላይ ለሚስተዋሉት አደረጃጀት የስልጠና ሃላፊነት የመንገድ ባለቤትነት ወ ዘ ተ ... ክፍተቶች ምላሽ የሚሰጥ ሰነድ እንዲዘጋጅ ተደርጓል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ መንገዶች ኔትዎርክ መረጃ ስርዓት (ERNIS) ይፋ ተደርጓል። ይህ ስርዓት የተለያዩ የዌብ ቴክኖሎጂ ምንጮችን በመጠቀም የተዘጋጀ የትግበራ ሶፍትዌር ሲሆን አገልግሎቱም ለሀገሪቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ስርዓትን በመጠቀም አጠቃላይ የመንገድ መረጃ መረብ ነው። ይህ ሶፍትዌር በአዲስ አበባ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ቡድን አማካሪነት ተጠንቶ በዛሬው ዕለት ጸድቋል። በቀረበው ጥናታዊ ሰነድ ላይ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች እንዲሁም በዘርፉ ወሳኝ አካላቶች ውይይት ተደርጓል።

የኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመስክ ጉብኝት
+7
የኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመስክ ጉብኝት

የኦሮሚያ ክልልን ከሲዳማ ክልል ጋር በማሰተሳሰር ከማዕከላዊ የሀገራችን ክፍል ጋር የሚያገናኘው የኤዶ - ሶሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ አፈፃፀም በመሰክ ምልከታ ተቃኝቷል :: የመንገድ ፕሮጀክቱ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም በተቋማቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ነው የተቃኘው። የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አሁናዊ አፈጻጸም ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና ቀጣይ የሰራ እቅድ ላይም ምክክር ተካሄዷል። 73 ኪሜ የሚረዝመው የኤዶ - ሶሮፍታ - ወርቃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸሙ ጥሩ መሆኑም ተገምግሟል። የአፈር ቆረጣ የመሬት ድልዳሎ የሰብ ቤዝ የድልድዮች ስራን ጨምሮ አስቸጋሪ የሚባሉ የፕሮጀክቱ ክፍሎች ስራ በጥሩ መልኩ መሰራቱ ተመልክቷል ። ፕሮጀክቱ ካለው ሀገራዊ ፋይዳ አኳያ ምርታማነትን በመጨመር በፍጥነት ወደ አስፋልት ማልበስ ስራ እንዲሸጋገር የሰራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል ። መንግስት በመደበው በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወጪ በዓለማየሁ ከተማ ጀነራል ኮንትራክተር እየተገነባ የሚገኘውን ይህን ፕሮጀክት የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ጎንድዋና ኢንጂነሪንግ እያከናወነ ይገኛል። ምንም እንኳን የግንባታው ሂደት ከታቀደው አንፃር መጠነኛ ውስንነት የሚታይበት ቢሆንም ኮንትራክተሩ ስራውን አጥብቆ የያዘበት አግባብ ለሚኖረው ቀጣይ አፈጻጸም መፍትሄ እንደሚሆን እምነት የሚጣልበት መሆኑን የተቋማቱ የሰራ ኃላፊዎች አንሰተዋል። የአፈር ሁኔታ ለመንገድ ግንባታው ምቹ አለመሆን እና የአካባቢው የዓየር ጸባይ ዝናባማ መሆኑ እንዲሁም የወሰን ማሰከበር ተግዳሮቶች ስራውን ቢያከብዱትም፤ ይህ ፕሮጀክት በአግባቡ እየተፈፀሙ ካሉ የመንገድ ግንባታዎች መካከል አንዱ በመሆኑ ተቋራጩ አለማየሁ ከተማ እና አማካሪ ድርጅቱ ይበልጥ እንዲተጉም የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ እና የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ አሳሰበዋል ።

የሮቤ - ጋሴራ - ጊኒር የመንገድ ስራ ፕሮጀክት
+7
የሮቤ - ጋሴራ - ጊኒር የመንገድ ስራ ፕሮጀክት

የሮቤ - ጋሴራ - ጊኒር የመንገድ ስራ ፕሮጀክት በከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በመስክ የስራ ቅኘት ተገመገመ። በዚሁ መርሃ -ግብር የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ።፣የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ፣ የኢመባ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የክልልና የዞኑ አመራሮችም ታድመዋል። የተቋማቱ መሪዎች ከአካባቢውዎቹና ከዞኑ ከተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ጋርም ምክክር አካሂደዋል። የሮቤ - ጋሴራ - ጊኒር የመንገድ ስራ ፕሮጀክት አሁናዊ ሁኔታና በእስካሁኑ አፈጻጸም የተሰሩ ስራዎች ያግጠሙ ችግሮችና ቀጣይ የስራ እቅዶችን በተመለከተ ግምገማም ተካሂዶል። በሁለት ምዕራፎች የሚገነባው የሮቤ - ጋሴራ - ጊኒር የመንገድ ስራ ፕሮጄክት ሲጠናቀቅ የ121 ኪ.ሜ ርዝመት ይኖረዋል፡፡ ይህም ከሮቤ ጋሴራ 60 ኪ.ሜ ሲሆን ከጋሴራ ጊኒር ደግሞ 60 ነጥብ 84 ኪ.ሜ ርዝመትን ይሸፍናል። የመጀመሪውን ፕሮጀክት ግንባታ የሚያከሂዱት አፍሮጽዮን ኮንስትራክሽን ከራማ ኮንስትራክሽን ጋር በጋራ ነው። በተደረገው የፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማም መከናወን ከነበረበት አኳያ የዘገየ ሆኗል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ የአፈጻጸም ድክመቱን በፍጥነት አስተካክሎ የመንገድ ግንባታውን እንዲከናወን የመጨረሻ ማሳሰቢያ ሰተዋል። በስፍራው የተገኙት የራማ ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ ፍሬው ተድላ ድርጅታቸው ፕሮጀክቱን ከአፍሮ ጽዮን ተቋራጭ ጋር በጋራ የወሰደው በመሆኑ ችግሮች እንዳሉበት አምነው፣ የህዝብን ቅሬታ ለመፍታት ተቋራጫቸው ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። የግንባታ ፕሮጀክቱ በአፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ስር ያለው ሁለተኛውን ምዕራፍ ማለትም ከጋሴራ ጊኒር የሚወስደውን መንገድ እጅግ መዘግየቱ ተገምግሟል። በተደጋጋሚ ድጋፍና ክትትል ቢደረግም አፈጻጻሙ ፈቅ ሊል አለመቻሉም የስራ ሀላፊዎቹ በመስክ ምልከታ ጭምር አረጋግጠዋል። በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ጉልህ አፈጻጸም ማሳየት ካልቻለ መንግስት አፍጣኘ የመፍትሄ እርምጃ እንደሚወስድም የስራ ሃላፊዎቹ አቅጣጫን አስቀምጠዋል። የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ የመስክ ቅኝቱ መሰረታዊ አላማ ህዝቡ የሚያነሳውን ቅሬታ አዳምጦ ላልተገባ ቅሬታ ምክንያት የሆኑ የስራ ተቋራጮች ላይ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ነው ብለዋል። መንግስት መዋዕለ ነዋይ መድቦ ድጋፍና ክትትል እያደረገም ለዘመናት የቆየ የህዝቦችን የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥ ፕሮጀክትን በማጓተት ህዝብን ቅሬታ ውስጥ የሚከቱ ድርጅቶችን እንደማይታገስ ገልጸዋል። የስራ ሃላፊዎቹ የጀመሩትን የተጠናከረ የመስክ ቅኘትና ግምገማ አጠናክረው በመቀጠል ችግር ያለባቸውን ፕሮጀክቶች እንዲተረሙ በማድረግ የሀገሪቱ የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ እንዲፋጠን እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ የአካባቢው ህዝብ ላነሳቸው የመሰረተ ልማት ጥያቄ ፡ መንግስት ከፍተኛ የተፈጥሮ ጸጋ እና አምራች አካባቢ መሆኑን በመረዳትና በመንገድ መሰረተ ልማት እጅግ የተጎዳ መሆኑን በማጥናት በጀት መድቦ የተነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ እየሰጠ መሆኑን የስራ ሃላፊዎቹ አረጋግጠዋል። ህዝቡም ሰላሙን በመጠበቅና በማስጠበቅ ለልማት ፕሮጀክቶች ድጋፋን ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል ።

በመስክ ጉብኝት ወቅት
+5
በመስክ ጉብኝት ወቅት

የባሌና የአርሲ ዞንን በማገናኘት ከማዕከላዊ የሀገራችን ክፋል ጋር የሚያስተሳስረው የዋቤ ድልድይ -አጋርፍ -አሊ ከተማ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በመስክ የስራ ቅኘት ተጎበኘ። በአካባቢው በተካሄደው የመስክ የስራ ቅኘት መርሃ-ግብር ላይ የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም የተቋማቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የዞኑና የክልል አመራሮችም ታድመዋል ፡፡ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ ያለበትን ሁኔታን የሚዳስስ ገለጻም ለስራ ሀላፊዎቹ ተደርጎላቸዋል። 56ነጥብ6ኪሎሜትር የሚረዝመው ይህ ፕሮጀክት አሁናዊ አፈጻጻሙ 44ከመቶ ላይ ደርሳል። በዚህም ወሳኝና አስቸጋሪ የሚባሉ የፕሮጀክቱ ስራዎች እየተከናወኑ ነው ። ከፋተኛ የአፍርና የተራራ ቆረጣ የመሬት ድልዳሎ የእስትራክቸርና የአቃፊ ግንብ ስራዎች ተሰርተዋል። በቅርቡም ወደ አስፖልት ንጣፍ ስራ ለመሸጋገር በቂ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተመላክቷል። የፕሮጀክቱ አካል የሆነው እና 180ሜትር የሚረዝመው የዋቤ ወንዝ ዘመናዊ የድልድይ የቅድመ ግንባታ ስራዎችም እየተፋጠኑ ነው። የስራ ሀላፊዎቹ በዛሬው የመስክ ቅኝታቸው ከአካባቢው ነዋሪዎችና የመስተዳድር አካላት ጋርም ውይይት አካሂደዋል። ፕሮጀክቱ ያለውን ከፍተኛ ሚና በመረዳትም የአካባቢው ህዝብ እያደረገ ላለው ቀና ትብብር ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ከህብረተሰቡ የተነሱ ተጨማሪ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን መንግስት ምላሽ ለመስጠት የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል ብለዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ ይህ ፕሮጀክት ከላው ከፍተኛ ሀገራዊ ፋይዳ አኳያ በልዩ ትኩረት ይበልጥ እንዲፋጠን አሳስበዋል ። የዋቤ ድልድይ- አጋርፋ- አሊ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሀገራዊ ከፍተኛ አምራች አካባቢዎችን የባሌና የአርሲ ዞኖችን ከማእከላዊ የኢትዮጵያ ክፍል ጋር የሚያቆራኘ በመሆኑ ለአምራች ሸማቹ ሚናው የላቀ እንደሆነ የተቋማቱ የስራ ሀላፊዎች ገልጸዋል። በቀጣይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሃ -ግብር እንዲጠናቀቅ አቅጣጫንም አስቀምጠዋል። የዚህ ፕሮጀክት ወጪ 2.1 ቢሊየን ብር ሲሆን ሙሉ ለሙሉ የሚሸፈነውም በኢትዮጵያ መንግስት ነው። ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው China Communications Construction Company Limited ( CCCC) ሲሆን Hong - IK Engineering እና ልደት አማካሪ ድርጅት ደግሞ የቁጥጥርና የማማከር ስራን እየሰሩ ነው። በተቀመጠው የጊዜ እና የጥራት ደረጃ ፕሮጀክቱን ግንብቶ ለማጠናቀቅ ይበልጥ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በተለይም በአፋር ክልል እየተገነቡ ያሉ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም እና በቀጣይ የአገሪቱ የመንገድ ልማት ውስጥ የክልል መንገድ ባለስልጣናት የሚኖራቸውን ሚና እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚገባውን አቅም እና አደረጃጀት በተመለከተ የውይይት መድረክ በሰመራ ከተማ ተካሄደ። በውይይት መድረኩ ላይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አወል አርባ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ፣ የኢመባ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የክልል የስራ አመራሮች ታድመዋል። በመድረኩ ላይ አሁን በፌደራል ደረጃ ያለውን የሥራ ጫና እና የቀጣይ የአስር አመታት የሀገራችን የመንገድ መሪ እቅድ ዋና ዋና ይዘትን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀው የክልል መንገድ ባለስልጣናት መነሻ አደረጃጀትና መዋቅር ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ከዚህ አኳያ በመንገድ ግንባታ ሂደት ውስጥ ክልሎችን በአደረጃጀት፣ በመዋቅር፣ በአቅም ግንባታ ማሳደግ የመሰረተ ልማት አውታሩን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳለጥ የጎላ ሚና እንዳለው ሰነዱ በዝርዝር አስቀምጧል። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታና በቀጣይ ከሚኖረው ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ የክልሎችን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የተዘጋጀው ሰነድ ፋይዳው የጎላ መሆኑን እና ክልላቸውም ጥናቱን ወስዶ በተሟላ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊውን እንደሚፈጽም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል። በትግበራ ወቅት ሊታዩ እና ሊካተቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን አንኳር ነጥቦችንም የክልሉ የስራ ሃላፊዎች አንሰተዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ የአደረጃጀት ሰነዱ እና ተያያዥ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ክልሎች በስፋት በመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ እና ጥገና እንዲሳተፉ እድል በመፍጠር አንድ ተቋም ላይ ተንጠልጥሎ የቆየውን ከፍተኛ የስራ ጫናን ለክልሎች የሚያጋራ ከመሆኑም ባሻገር በየጊዜው እየጨመረ ለመጣው የህብረተስቡ የመንገድ ጥያቄ አፋጣኝ መልስ ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል ። ይህም የሀገራችንን የመንገድ አውታር በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ለመከወን እንደሚያስችል አብራርተዋል። የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ በበኩላቸው ሰነዱ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ብልጽግናዎችን ለማጎናጸፍ የመንገድ ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ እንዲሸጋገር የሚያስችለው እንደሆነ ገልጸዋል። መንግስት በመስኩ የክልሎችን አቅም ለመገንባት የሚያስችል መጠነ ሰፊ ስራዎችን እንደሚያከናውንም አረጋግጠዋል ። በተለይም የክልሎችን ሚና እና ሃላፊነት በግልጽ አስቀምጦ ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ፣ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ ለሀገራዊ የመንገድ የመሰረተ ልማት ግንባታ ፋይዳው ዘርፈ ብዙ እንደሆነም ተናግረዋል። ይህን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ዝርዝር የፖሊሲና የህግ ማእቀፍችን መንግስት እያዘጋጀ እንደሆነም የስራ ሀላፊዎቹ ገልጸዋል። በዚሁ በሰመራ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ በተለይሞ በክልሉ በግንባታ ላይ ያሉ እና በቅርቡ ግዥያቸው ተጠናቆ ወደ ግንባታ የሚሸጋገሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች በዝርዝር ቀርበዋል። በተለይም በግንባታ ላይ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻም እና እያጋጠማቸው ያሉ ተግዳሮቶች ላይ ዝርዝር ምክክር ተካሂዷል። በውይይቱ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ችግሮችን ይበልጥ ተናቦ ለመፍታት የጋራ አቅጣጫን አስቀምጠዋል። አቶ አወል አርባ በቀጣይ ለሚተገበሩ እቅዶችና ማሻሻያዎች እንዲሁም አሁን በግንባታ ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ክልሉ እያደረገ የሚገኘውን ክትትልና ድጋፍ የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።