uz
Feedback
Ethiopian Association of Civil Engineers

Ethiopian Association of Civil Engineers

Kanalga Telegram’da o‘tish

Channel for Ethiopian Association of Civil Engineers members to updated current construction issues, information and opportunities

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
3 353
Obunachilar
+524 soatlar
+677 kunlar
+22630 kunlar
Postlar arxiv
Our former executive member, Eng. Tekola G/Medhin passed away. His burial is on 24 Feb. 2021 at 3:00pm , St. Selassie Church.

የሀዘን መግለጫ የኢንጅነር ተኮላ ገ/መድህን የቀብር ስነ ስርዓት ረቡዕ የካቲት 17 ቀን በቅድስት ስላሴ ቤ/ክ ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት ይፈጸማል።

It has been 10 years since the first #UNESCO #Engineering #Report was released… and a lot has changed. The second UNESCO Engi
It has been 10 years since the first #UNESCO #Engineering #Report was released… and a lot has changed. The second UNESCO Engineering Report - scheduled for release on #WorldEngineeringDay - will point to the 2030 Agenda for Sustainable Development as presenting a blueprint for action and explain how #engineers are now at the forefront to deliver on the #SustainableDevelopmentGoals, using their scientific knowledge and experience to turn innovative ideas into #sustainability projects for the benefit of all. bit.ly/WorldEngDay for more info. #WorldEngineeringDay #WED2021 #WFEO #UNESCO #UNSDG #WFEO #EACE1962 @eaceg @ecethiopia2 @eacec

በመስራችነትና በአባልነት አስተዋፅኦ ያደረጉባቸውን የሙያ ማህበራትን በሚመለከት የኢትዮጲያ ሲቪል ኢንጅነሮች ማህበር፣ የአሜሪካ ሲቪል ኢንጅነሮች፣ በአሜሪካ የትልልቅ ሕንፃዎች ካውንስል፣ የኢተርናሽናል የድልድይና ስትራክቸራል ኢንጅነሮች ማህበር፣ የአፍሪካ ኔቶርክ ሳይንቲፊክ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እንዲሁም ዘዴ ጆርናል የኢትዮጵያ ኢንጅነሮችና አርክቴክቶች ማህበር ይገኙበታል፡፡ እኚህ የስትራክቸራል ምህንድስና ምሁር ባከናወኑት የላቀ ተግባር በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ከፍተኛ ሽልማትና እውቅና የተበረከተላቸው ሲሆን ከእነዚህም የሚከተሉት ዋንኛዎቹ ናቸው፡፡  በዩንቨርስቲ መምህርነት፣ በስተራክቸራል ምህንድስና ሙያ ባደረጉት ከፍተኛ የምርመራ ስራና ለሀገሪቱ በአበረከቱት ከፍተኛ የምርመራ ስራና ለሀገሪቱ በአበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጻኦ ምክንያት በ1981 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው የሲቪል ምህንድስና የሙሉ ፕሮፌሰርነት መአረግ ሰጥቷቸዋል እርሳቸው የሙሉ ፕሮፌሰርነት ያገኙበት ወቅት ዩኒቨርስቲው ይህንን መዕረግ መስጠት በጀመረበት በጥቂቱ አመታት ውስጥ በመሆኑ በወቅቱ በአገሪቱ በዚህ ማዕረግ ይጠሩ ከነበሬ ጥቂት ምሁራን መካከል በመጀመሪያዎቹ ረድፍ የሚገኙ ናቸው፡፡  በ1994 ከኢትዮጲያ ሳይንትፊክ ሶሳይት የፋክሊቲ የሳይንስ አሸናፊ ሆነዋል፡፡  በ2005 ከአሜሪካ ኮንክሪት ኢንስትቱይት የኢትዮጵያ ቻፕተር በዲዛይንና በኮንክሪት ኮንስትራክሽን ስራ የህይወት ዘመን የላቀ አስተዋፅኦ የእውቅና ተሸላሚ ሆነዋል፡፡  በ2009 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢዩቤልዩ ሽልማት አግኝተዋል  እንዲሁም በ2009 በኢትዮጵያ በሳይንስ ረገድ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የበጎ ሰው ተሸላሚ ሆነዋል  ኤመሪተስ ፕሮፌሰር ንጉሴ በተለይ በሚከተለው ጉዳዮች ስማቸው ጎልቶ በመውጣት በብዙዎች ዘንድ አድነቆትና ክብርን ያተረፉ ናቸው  በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ የትምህርት መርሀ ግብር ለበርካታ አመታት በማስተማር በጥናትና ምርምር ስራ በመሳተፍና የማመሪያ መጻህፍትን በማሰተም እውቀታቸውን ለሌሎችም በማጋራት በርካታ ምሁራንን ማፍራታቸው ፤  የታላላቅ የድልድይና ግንባታ ስራዎችን በማቀድ በማማከርና ችግሮችን በመፈታት የነበራቸው አስተዋፅዖ ከፍተኛ መሆኑ በዚህም ረገድ በተለይም በተደጋጋሚ ከሚታወሱባቸውና እንደ እንደ አስረጂነት ከሚተቀሰው መካከል በ1998 ዓ.ም የአባይ ድልድይን ለመገንባት የሚያገለግል ከባድ ማሽን ሲያጓጉዙ የነበሩ ሁለት ከፍተኛ የጭነት ተሸከረካሪዎች የአባይ ድልድይ ጋር ሲደርሱ ድልድዩ እነዚህን ማዙፍ ማሽነሪ የጫኑ ተሸከርካሪዎች የማሳለፍ አቅም ስለመኖሩ ለመወሰን ባለመቻሉ ዕውቀት ችግሩን ሊፈታው መቻሉ ነው፡፡ ከሙያቸው ውጪ የነበራቸውን የማህበራዊ ተሳትፎና የግል ህይወት በሚመለከት የቀድመሞ መንግስት ከፖለቲካና ከፓርቲ የአባልነት ተሳትፎ ውጪ ያሉ ጥቂት የሥነ ጥበብና የልዩ ልዩ ሙያ ባለቤት የሆኑ ታዋቂ ሰዎች በኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ብሔራ ሸንጎ እንዲገቡ ባደረገበት ወቅት እርሳቸውም በሞያቸው በነበራቸው ታዋቂነት ተመርጠው የብሄራዊ የመማክርት ጉባኤ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የግል ህይወታቸውንና አኗኗራቸውንና በሚመለከት ኤመሪተስ ፕሮፌሰር ንጉሴ በስነ ጥበብ ረገድ ከዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች መካከል ፒያኖ መጫወት የሚችሉ ሲሆን በተለይ በወጣትነት የሚያውቋቸው ይመሰክሩላቸዋል፡፡ የስዕል ጥበብ አፍቃሪ በመሆናቸውም በሀገራች ከእውቅ ሰዓሊያን ጋር ቅርበት የነበራቸው ሲሆን የእነርሱን የጥበብ ስራዎች በመግዛት የስነ ጥበብ ባለሙያዎችን የሚያበረታቱ ነበሩ፡፡በቋንቋ ረገድም ከአማርኛና ከእንግሊዘኛ በተጨማሪ የፈረንሳይ ቋንቋ የሚያውቁ ነበሩ፡፡ የእረፍት ጊዜያቸውን በሚመለከት ገና ከዩኒቨርስቲ መምህርነት አነስቶ በቋሚነት ቴኒስ ስፖርት መጫወትን ያዘውትሩ የነበረ ሲሆን ከአቅም በላይ ካልሆነ በስተቀር ከጨዋታ ሜዳ የማይታጡ ነበሩ፡፡ከሚቀርቧቸው ወዳጆቻቸው ጋር እየተገናኑ ስለማህበራዊና የተለያዩ ጉዳዮች መጫወት የሚያደስታቸው ሲሆን ይህም ከነበረባቸው የሥራ ውጥረት ፋታ በማግኘት የሚዝናኑበት መንገድ ነው፡፡ ከተወሰኑ የቅርብ ወዳጂቻቸው ጋርም የጓደኛሞች ማህበር በማቋቋም በመደበኛነት የሚገናኙ ሲሆን ይህም ለእርሳቸው አስደሳችና ከፍተኛ ቦታ የሚሰጡት ጉዳይ ነበር፡፡ ምንም እንኳን እሳቸው ከብዙዎች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት ቁም ነገር ላይ እጂ ጨዋታ የሚያውቁ መስለው ባይታዩም ከዚህ በተቀራኒው ከቅርም ወዳጆቻቸው ጋር ሲሆኑ ተጫዋችና ተግባቢ ሰው ነበሩ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በትርፍ ጊዜያቸው የተለያዩ ማህበራዊና ታሪክ ላይ የሚያተኩሩ መጽሐፍትማንበብና በቤታቸው ሆነው የአገር የአለም ዘቀፍ ዜናዎችን አስተማሪና አዝናኝ ታሪካዊና ዶክመንተሪ ልፊሞችን ፣የአውሮፓ የእግር ኳስ የአለም የሜዳ ቴኒስ ውድድሪችን መከታታል ያደስታቸው ነበር፡፡ የቤተሰብ ሕይወታቸውን በሚመለከት ከወይዘሮ አይናበባ አመኑ ጋር ትዳር መስርተው ላለፉት 30 አመታት በትዳር ኖረዋል፡፡በዚህም ወቅት ከአብራካቸው ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች ልጆች አፍርተው የአራት ልጆች አባት በመሆን ለቤተሰባቸው ተገቢውን ፍቅርና ክብካቤ በማሳት ልጆቻቸውን ለቁምነገር አድርሰዋል፡፡ በአጠቃላይ ኤመሪተስ ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ በሰስትራክቸራል ምህንድስና ዘርፍ በሀገራችን የተከበሩ ስመጥር ባለሞያ፣ የሞያ እገዛቸውን ለሚሹ ለማናቸውም አካላት ምክራቸውንና እውቀታቸውን ሳይሰስቱ በፈቃደኝነት የሚያጋሩ ሁሌም የሚያምኑበትን መፈፀማቸውን እንጂ ለታይታ ዝናና ክብር ለማግኘት የማይጣጣሩና ለዚህም ቦታ የማይሰጡ ፣የመርህ ሰው ፣በማናቸውም ረገድ ሰላማዊ ግንኙነት የሚሹና በቀጥታ በሚመለከታቸው ጉዳይ ላይ ማተኮር እንጂ በማይመለከታቸው ጉዳይ ላይ ጣልቃ መግባት የማይፈልጉ፣በቅርብ ወዳጆቻቸው ዘንድ ተግባቢና ተወዳጅ የሆኑመ አብረዋቸው ላደጉት ወንድሞቻቸውና እህቶታቸው ልዩ ፍቅር ያላቸው የራሳቸውን ቤተሰብ በፍቅርና በልዩ ክብካቤ የሚመሩ ተወዳጅና ተከባሪ ናቸው፡፡ ኤመሪተስ ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ ባደረባቸው ህመም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ሕክክና ሲከታተሉ ከዮዩ በኋላ ጥር 12 ቀን 2013 ዓ በአዲስ አበባ ከተማ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ በደረሰብን መሪር ሀዘን በቅርብ በመገኘትና በተለያየ መንገድ ላጽናናችሁን ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ከቤተሰቦቻቸው!

Asemahagn Worku: 💚💛❤ ሀገራችን ትልቅ ሰው አጣች! በኢትዮጰያ የእስትራክቸራል ምህድስና ረገድ ግንባር ቀደም ከሆኑ ምሁሮች አንዱ ነበሩ። መልካም ሰው ነበሩ! ነብሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርልን ለቤተሰቦቻቸውም መፅናናት ይስጥልን። -------------------------------------------- ©ጌጡ ተመስገን የስትራክቸራል ምህንድስና ሊቅ ንጉሴ ተበጀ (ኤመሪተስ ፕሮፌሰር) 1937-2013 ንጉሴ ተበጀ በ1937 ዓ.ም በወርሃ ጥቅምት በስድስተኛው ቀን በዕለተ ሰኞ ተወለደ፡፡ የትውልድስፍራው በቀድሞ መጠሪያው በቤጌምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረ ታቦር አውራጃ ልዩ ስሙ ፈረስ ሜዳ በተባለው ቦታ ነው፡፡ ወላጅ አባቱ ፓስተር ተበጀ ጉዳዬ የተቃወቁ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን አገልጋይ የነበሩ ሲሆን ወላጅ እናቱ ወይዘሮ ደብሬ ቦጋለ ደግሞ ልጆቻቸውን በቤት ተንከባክበው የሚያሳድጉ የቤት እመቤት ነበሩ፡፡ ወላጆቻቸው ካፈሯቸው ከሦስት ወንድሞቹና ከአራት እህቶቹ መካከል እርሱ ለቤተሰቡ የመጀመሪያ ልጅ ሲሆን ያደገው ጥሩ ፍቅር ባለበት ቤተሰብ ውስጥ ነው፡፡ ንጉሴ ተበጀ ትምህርት የጀመረው ገና በልጅነት ዕድሜው ሲሆን እስከ አምስተኛ ክፍል በቀነናና በአቃቂ የአድቬንቲስት ሚሲዮን ትምህርትቤት ተማረ፡፡ አባቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ወደ ጎንደር ሲዛወሩ እርሱም ወደ ደብረታቦር በመሄድ በቀጥታ ሰባተኛ ክፍል ገብቶ የተማረ ሲሆን ስምንተኛ ክፍልን እንደቨረሰ ወደ ኩየራ አድቬንቲስት ሚሰዮን ትምህርት ቤት ተዛውሮ ከዘጠነኛ እስከ አስራ አንደኛ ክፍል ትምህርቱን ተከታተለ፡፤ከዚያም የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቱን በመድሐኒያለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቋል፡፤ገና ከልጅነት እድሜው ትምህርት ለመቀበል ብሩህ አዕምሮ ስለነበረው በትምህርቱ የላቀ ውጤት ያመዘግብ የነበረ ሲሆን በአጠቃላይ ከትምህርት ቤቱ አንደኛ የሚወጣባቸው በርካታ ጊዜያት ነበሩ፡፡ ከዚያም በልጅነት እድሜው የነበረውን የህክምና ሙያ የማጥናት ፍላጎቱን በመተው በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ዩኒቨርስቲ (በአሁኑ መጠሪያ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ )ገብቶ የሲቪል ምህንድስና ሙያ በመከታተልበ1957 ዓ.ም ከዩኒቨርስቲው ብቸኛው ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ በመሆን የባችለር ኦፍ ሳይንስ ዲግሪው አግኝቷል፡፡በዩኒቨርስቲው ጥቂት አመታት ከስራ በኋላ በአገነው የከፍተኛ ትምህርት እድል በመተቀም ወደ አሜሪካን አገር አቅንቶ በፔንስልቬኒያ ግዛት ከሊሀይ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን የተከታተለ ሲሆን በ1961 ዓ.ም በማተር ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ ተመርቋል፡፡ባስመዘገበው የላቀ ውጤት በዩኒቨርስቲው የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመቀጠል በ27 ጫመቱ በ1964 ዓ.ም የዶክሬትሬት ዲግሪውን አግኝቷል፡፡ ከወጣትነት እድሜ አንስቶ በጉልምስናና ከዚያም በኋላ ባለው የህይወት ዘመን ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ብሎም ለትውልድ የሚተርፍ በርካታ ተግባራትን በመፈፀም በምህንድስናው የሙያ ዘርፍ የፕሮፌሰርነትን ማዕድ ለማግኘትና ”አንቱ“ ለመባል በቅቷል፡፡ ኤመሪተስ ፕሪፌሰር ንጉሴ ተበጀ ያገለገሉበት የስራ ልምዳቸውን በተመለከተ፣  ከ1957 እስከ 1959 ለሁለት አመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመምህርነት፣  ከ1959 እስከ 1965 ለስድስት አመታት በአሜሪካ አገር በሊሀይ ዩኒቨርስቲ የምርመራ ስራ በረዳትነት እና የድህረ ዶክትሬት ምርምር ስራ፣  ከ1965 እስከ 1967 በፈረንሳይ አገር በፓሪስ በሲ.ቲ.አይ.ሲ.ኤም(CTICM) ድርጅት በስትራክቸራል መሀንዲስነት ፣  ከ1967 እስከ 1983 ለአስራ ሰባት አመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመምህርነት ያገለገሉ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያትም ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የቴክኒዮሎጂ ፋካልቲ የሲቪል ኢንጅነሪንግ የትምህርት ክፍልን በኃላፊነት የመሩ ሲሆን በሌለ ተጨማሪ አምስት አመታት ቤኒበርስቲው የቴክኒዮሎጂ ፋካልቲ ዲንነት ተመድበው ኃላፊነታቸውን በብቃት ተወጥተዋል፣  ከ1983 እስ 2013 ራሳቸው ባቋቋሙት አክመ(ACME) ዲዛይነርና ኮንሰልታንት በተሰኘ ድርጅት በስራ አስኪያጅነት አገልግለዋል፡፡ ያከናወኑትን የሳይንሳዊ ምርመር ስራቸውን በተመለከተ በአለም አቀፍ ደረጃ በሚታተሙ ጆርናሎች በጠቅላላው ከሃያ ሁለት በላይ ሳይንሳዊ የምርምር ጽሁፎችን ያዘጋጀና ለህትመት ያበቁ ሲሆን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመማሪያነት የሚያገለግሉትን ጨምሮ በሙያቸው ስምንት የተለያዩ መጽኃፍትን በሀገር ውስጥና በውጭ አገር አሳትመዋል፡፤ ከዚህም በተጨማሪ የሀገራችንን የህንፃ ስታንዳርድ የሥራ ህግጋትና ማሻሻያዎችን ስድስት ቅጾች አዘጋጅተዋል፡፡ከዩኒቨርስቲው መምህርነት ፣በድህረ ምርቃ ፕሮግራም በፈታኝነትና ከምርምር ስራች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ከሀገራቸው ተጨማሪ በአሜሪካ በፈረንሳይ፣በኡርንዳ፣በታንዛኒያና በደቡብ ሱዳን ተዘዋውረው ሰርተዋል፡፡ በህንፃ ዲዛይንና የማማከር ስራን በሚመለከት ከአርባ በላይ ለሚሆኑ ከአምስት እስከ ሰላሳ ሶስት የሚደርሱ ወለል ያላቸውን ህንፃዎች የስትራክቸር ዲዛይንና የማማከር ስራዎችን አከናውነዋለው፡፡ ከነዚህ መካከል የአዋሽ ባንክና ኢንሹራንስ፣የንብ ባንክ፣የአማራ የገንዘብና ብድር ተቋም፣ የራምዳ ሆቴል፣ የማርዮት ሆቴል፣ ዬንኮማድ፣ የጌት ኮሜርሻል፣ የመቀሌ ስታዲዮምና የአዳማ ስታድዮም ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የድልድይ ዲዛይኖችንና የማማከር ስራዎችን በተመለከተ ካከናወኗቸው በርካታ ስራዎች መካከል ከሞጆ ሀዋሳ ፈጣን መንገድ፣ ከሳውላ ማጂ፣ ከሞጣ ደብረ ታቦር፣ ከካሳ በር አዋሽ አርባ፣ ከጎንደር ሁመራ፣ ከጌዶ ነቀምትና ከገዋሌ ሚሌ የመንገድ ስራዎች ሲከናወኑ ለሚሰሩ ድልድዮች የሙያ ድርሻቸውን ማበርከታቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በተለይም በአባይና የግልገሌ ጊቤ ሁለት ሳይት 146 ቶን ያህል ተሸከርካሪዎቻችን የመሸከም አቅም የነበረውን ድልድይ ወደ 213 ቶን እንዲሻሻል በማድረግ ረገብ ከፍተኛ አስተዋፆኦ አድርገዋል፡፡ ከውኃየስትራክቸር ስራ ጋር በተያያዘም ከ300 ሜትር ኪዮብ መያዝ የሚችል የኮንክሪት የውኃ ታንከር ስራዎች በአቃቂ፣ በቃሊቲና በጎተራ አካባቢ ዲዛይነሮች ሰርተዋል፡፡የመተላለፊያ መንገዶችን በሚመለከትም በመዲናችን በአዲስ አበባ ሳር ቤት፣ በኦሎምፒያ፣ በወሎ ሰፈር፣ በሩዋንዳና በመሷለኪያ አካባቢ ያሉ የመንገድ መተላለፊያዎች የእርሳቸው የሙያ አስተዋፅኦና አሻራ ያረፋባቸው ስራዎች ናችው፡፡ በዲዛይንና በማማከር ካበረከቱት አስተዋፅኦ በተጨማሪ ለትላልቅ ህንፃዎች የዲዛይን ተጫራቾች መረጣ በሚካሄድበት ወቅት በውድድር ሂደት ላይ በሙያቸው የዳኝነት ስራ ተሳታፊ በመሆን የድርሻቸውን የተወጡ ሲሆን በዚህም ታሳታፊ ከነበሩባቸው ማካከል የህብረት ባንክ፣ የህብረት ኢንሹራንስ፣ የንብ ባንክና ኢንሹራንስ፣ የቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስትያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስትይንና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከግንባታ ስራ ጋር በተያያዘም በተለያዩ ወቅቶች በግንባታ አሰሪዎችና በአገር ውስጥና የውጭ አገር ተቋራጮች መካከል አለምግባባት ሲከሰት በሙያቸው በግልግል ዳኝነት በመሳተፍ ስምንት ለሚደሱ ጉዳዮች አለመግባባቶችና ጋጭቶች ዕልባት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡

የሀዘን መግለጫ የማህበራችን አባል የሆኑት ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ (Fellow Engineer) ከዚህ አለም በሞት መለየት ማህበሩ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸን በማህበራችን ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ማህበሩን በመመስረትና ከመደበኛ አባልነት እስከ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ በመሆኑ ያገለገሉ ሲሆን ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ማህበሩን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በዕውቀትና በገንዘብ ሲደግፉ የቆዩ ሲሆን የኢትዮጵያ ሲቪል መሐንዲሶች ማህበርም የተሰማውን ልባዊ ሐዘን እየገለፀ ነገ በቀን 14/05/2013 ዓ.ም ላይ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስትያን ከቀኑ 6፡00 በሚፈፀመው የቀብር ስነስርዓት ላይ በሚደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የማህበሩ አባላት በመገኘት ሐዘናችሁን እንድትገልፁ እናሳውቃለን፡፡ ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ (Fellow Engineer) በታማኝነት እና በስነምግባር በሞያቸው አገራቸው ሲያገለግሉ የነበሩ መሆናቸውን ማህበሩ ይመሰክራል:: የኢትዮጵያ ሲቪል መሐንዲሶች ማህበር Condolence On behalf of the Ethiopian Association of Civil Engineers we want to express our deepest and most sincere condolences to the family and friends of Prof. Nigussie Tebeje (Fellow engineer) and EACE Community. May his soul Rest in Peace Ethiopian Association of Civil Engineers

የሀዘን መግለጫ የማህበራችን አባል የሆኑት ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ (Fellow Engineer) ከዚህ አለም በሞት መለየት ማህበሩ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸእየገለጸን በማህበራችን ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ማህበሩን በመመስረትና ከመደበኛ አባልነት እስከ የስራ አስፈፃሚ ቦርድ በመሆኑ ያገለገሉ ሲሆን ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ማህበሩን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በዕውቀትና በገንዘብ ሲደግፉ የቆዩ ሲሆን የኢትዮጵያ ሲቪል መሐንዲሶች ማህበርም የተሰማውን ልባዊ ሐዘን እየገለፀ ነገ በቀን 14/05/2013 ዓ.ም ላይ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስትያን ከቀኑ 6፡00 በሚፈፀመው የቀብር ስነስርዓት ላይ በሚደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የማህበሩ አባላት በመገኘት ሐዘናችሁን እንድትገልፁ እናሳውቃለን፡፡ ፕሮፌሰር ንጉሴ ተበጀ (Fellow Engineer) በታማኝነት እና በስነምግባር በሞያቸው አገራቸው ሲያገለግሉ የነበሩ መሆናቸውን ማህበሩ ይመሰክራል:: የኢትዮጵያ ሲቪል መሐንዲሶች ማህበር Condolence On behalf of the Ethiopian Association of Civil Engineers we want to express our deepest and most sincere condolences to the family and friends of Prof. Nigussie Tebeje (Fellow engineer) and EACE Community. May his soul Rest in Peace Ethiopian Association of Civil Engineers

In celebration of World Engineering Day on March 4th #WorldEngDay2021, WFEO invites you to submit a video before Feb. 12th, to showcase contributions that #YoungEngineers are making towards a more #sustainable, #resilient, and #inclusive world More info https://bit.ly/3iyYliL #Agenda2030 #GlobalGoals #SDGs #ClimateAction #Engineering #WomenInSTEM

Call for Decade of Action Short Stories.pdf0.44 KB

Call Women in Engg Awards_ 2020_ .pdf2.33 KB

Call_Women_in_Engg_Awards-2020_NOMINATION_FORM.docx2.98 KB

Call for Papers #EACE Ethiopian Association of Civil Engineers invites interested researchers to submit a full Paper, which is going to be Published in its upcoming Applied Engineering and Construction Journal. Abstract should be 200 to 700 words.     Submit to: eaceresearch@gmail.com only! Subject should be labeled as “Paper”   The paper should be in word file and not more than 16 pages The theme of the paper should in Civil engineering and Construction. Deadline till Dec 10th, 2020. Www.eacecivil.org

Please send your comments ASAP

October 26, 2020 Dear All: On behalf of the “ETHIOPIA2050 – Challenges and Opportunities” Initiative, we are very pleased to invite you to the ETHIOPIA2050 Blue Ribbon Panel Report Press Conference to be held through Zoom Virtual Platform on October 31, 2020 (4:00PM - 5:30PM - Addis Ababa Time). Date: Saturday, October 31, 2020, 4:00PM – 5:30PM (Addis Ababa Time) 9:00AM – 10:30AM (Eastern Standard Time) 6:00AM – 7:30AM ( Pacific Standard Time) Zoom: https://SDSU.zoom.us/j/82537817677 (password: Sheger) The Press Conference will be opened by a Guest of Honor and there will also be distinguished guests from inside and outside Ethiopia. The Press Conference will concentrate on introducing the specific recommendations outlined in the report in the areas of food, water, health, and energy security, rapid urbanization, rural development, digital economy, and the like, as Ethiopia’s population is projected to reach 200 million by 2050. These recommendations were forwarded as a response to what were identified as “Ten Grand Challenges and Opportunities” associated with the generational and historical demographic shift we are experiencing now and that is expected to accelerate in the years ahead. We have attached the final schedule and eagerly look forward to seeing you all in this exciting event. Respectfully, Professor Samuel Kinde ETHIOPIA 2050 Initiative, Co-Chair