cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

እመጓ

ለበጎ ነገር እንፍጠን

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
306
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-27 kunlar
-1130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
ለሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት:-ለብፁዕ አቡነ መርሐ ክር ስቶስ፥ለብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ እና ለብፁዕ አቡነ ጴጥ ሮስ ፖለቲካን ሽፋን አድርጎ ስለሚንቀሳቀሰውና የቤተ ክርስትያን መገንጠል ፕሮጀክት ባለቤት ስለ ሆነው ተሃድሶ መናፍቃን በተፈለገው መጠን ባይሆንም በተለያየ መንገድ ተነግሮአችኋል.።በቀጣይነት ስንነ ግራችሁ ግን:-የነበረውን እየዘረዘርን፥መናፍቃንን በስም እየጠቀስን፥ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሆነ ሁሉ እውነቱን እንዲያውቅ እንደርጋለን። አንድ ጥያቄ እንጠይቃችሁ? ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፈቃድ ውጭ እና ቀኖና ቤተ ክርስትያንን በመጣስ ኤጲስ ቆጶሳት ሹሞ መንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን የሚባል ሲኖዶስ እናቋ ቁማለን የምትሉት ለትግራይና ለትግራውያን የሚሰ ጠው ጥቅም ምንድር ነው? ዛሬ እናንተን ማየት የም ንፈልገው ያለ አባት ለቀሩ ልጆች እንደወላጅ አባት ስትሆኑ፥ጧሪ ደጋፊ ልጃቸው አንደ ወጣ ለቀረባቸው አዛውንት ድጋፍ ስትሆኑ፥ልጇ ይኑር ይሙት ለማወቅ ተቸግራ ቀኑ ለጨለመባት እናት መፍተሔ ስትፈልጉ ነው።ከሰላም ስምምነቱ በኋላ እንኳን ስንቱ ትግራ አዊ በረሃብ አልቋል።መቼ ነው? እንደ ሊቃነ ጳጳሳት ከፍ ብላችሁ በዓለም መድረክ ተገኝታችሁ መድኃ ኒትና ምግብ የምትፈልጉልን።እኛ ካህናት በርሃብ እያለቅን ነው፥ልጆቻችን እንደወጡ ቀርተ ዋል፥ብዙ አብያተ ክርስትያናት በቀዳስያን እጥረት ተዘግተዋል። መቼ ነው? ለእኛና ለቤተ ክርስትያን ማሰብ የምትጀም ሩት።መጪው ግዜ በትግራይ ለምትገኘው ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አጅግ አስፈሪ ነው። ለመሾም የተሰለፉትን መነኳሳት እያወቅናቸው ነው።በእርግጠኝነት የምንነግራችሁ አንዳቸውም ቢሆኑ በየትኛውም ትግራይ በምትገኝ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳት ሁነው አይገቡም።ቤተ ክርስ ቲያንን የመናፍቃን መነሃርያ ስታደርጉ፥የሀገረ ስብከታ ችሁን አስተዳደር ለተሃድሶ አስልፋችሁ ስትሰጡ፥ በጦርነት ወስጥ ስለነበርን ብዙ ገፍተን አልነገርናች ሁም።አሁንም በየሀገረ ስብከታችሁ የተሾሙላችሁ ተሃድሶ መናፍቃን አዲስ አበባ ከሚገኙ አለቆቻቸው ጋር ተቀናጅተው በየገዳማቱና አድባራቱ ሰዎችን እየ መለመሉ ሥልጠና እየሰጡ ነው።እናንተም ኤጲስ ቆጶሳት ልተሾሙላቸው ደፋ ቀና እያላችሁ ነው። ጽዋዉ ሞልቷል።ትግራይ ሰላም ይራቅሽ ተብላ የተረ ገመች ይመስል አሁን ደግሞ ሌላ ጦርነት።አሁን ደግሞ በእናንተ በሊቃነ ጳጳሳት የተቀሰቀሰ ጦርነት። አሁን ደግሞ በሃይማኖት ምክንያት የስንቱ ሰው ደም ይፈስ ይሆን? አንቺ መከረኛ እናት አሁንስ የትኛው ልጅሽ ይሆን እንደወጣ የሚቀረው? (ከመምህር ፋንታሁን ዋቄ ገጽ የተገኘ)
Hammasini ko'rsatish...
“ማኅበረ ሰላማ ዘትግራይ ቤተ ክህነት፤” በተቀደሰው አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ስም ያልተቀ ደሰ ሥራ፤(ቀሲስ ሓጎስ ፍሥሐ ጽዮን ተክለ ማርያም በትግርኛ ጽፎት ወደ አማርኛ የተተረጎመ)። አሁንስ ለሕዝቡ እንናገራለን "ገንጥሎ ከትግራይ ኤጲስ ቆጶሳትን የማሾም” ፕሮጀክት **** በሓጎስ ፍስሓ ጽዮን ተ/ማርያም (ቀሲስ) ግንቦት 2015 ትርጉም በዝግጅት ክፍል ለትግራይ ከትግራይ ዐሥር ኤጲስ ቆጶሳትን እንሾማ ለን ከተባለ ትንሽ ቆይቷል።ምን አልባት ብዙ ሰው የሰ ማው ግን ከሰሞኑ ግንቦት 24 2015 ዓ/ም በሚድያ ከተነገረ በኋላ ነው።እዚህ ትግራይ የምንገኝ ካህናት እርስ በርሳችን እንዲሁም ከብዙ ምዕመናን ጋር በዚህ ጉዳይ ተነጋግረናል።ሁላችንም በጋራ የጠየቅነው “ለመሆኑ ይህ ራስን ገንጥሎ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፈቃድ ውጭ የሚደረገው ሹመት ለትግራይ ሕዝብ የሚያመጣው ጥቅም ምንድር ነው?” የሚል ነው።በተሠራብን ግፍ ቤተሰቦቻችንን በክፉ ጦርነት ላጣን፤ተምረን እንዳልተማርንና እያለን እንደሌለን ሁነን እጅግ በሚያሳፍር ሁኔታ ልመና ለወጣን፤ በጦር ነቱ ምክንያት አካለ ስንኩል ሁነን የሰው እጅ አይተን እንድንኖር በግፍ ለተፈረደብን የሚደረገው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ምንድር ነው ፋይዳው? የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተ ክህነት ተመሥርቶ ያመጣ ልን ጥቅም ምንድር ነው? ምን ተቀየረ? ምንስ ተለወጠ? ዓላማውስ ምንድር ነው? ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስን ቢቢሲ ትግርኛ:- “ኤጲስ ቆጶሳትን ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፈቃድ ውጭ መሾሙ ጥቅሙ ምንድር ነው?”ብሎ ሲጠይ ቃቸው እንዲህ ብለው መለሱለት። “ ለሕዝባችን ደስታ ነው፥የሕዝባችንን ልብ የሚያረሰ ርስ ነው ”።አይ ጋዜጠኛ! ምን ቢበድሉህ ነው እንዲህ ያሳጣሃቸው? እያወቅህ።እሳቸው ምንም እንደማያ ውቁ።ከሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት እንዳቸው እንኳን የዚ ህን ጥያቄ መልስ አያውቁትም። የግንቦት 24ቱን ጨምሮ በየሚድያው ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት በንባብ የሚያቀርቡትን አንዱንም መግለጫ አልጻፉትም ወይመ‍እ አላጻፉትም።ረቂቁን እንዲያዩ ትና ለሚድያ ከመቅረቡ በፊት ሀሳብ እንዲሰጡበት እንኳን እድል አልተሰጣቸውም።ታድያ ማን ነው? እየ ጻፈ የሚያድላቸው።ማን ነው? ከኋላ ሁኖ የሚዘውራ ቸው።ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፈቃድ ውጭ እንዲሁም ቀኖና ቤተ ክርስትያን እየጣሰ ኤጲስ ቆጶሳ ትን እንዲሾሙ የሚወተውተው ማን ነው? የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተ ክህነት የሚባል መሥርቶ የሚዘውረው ማን ነው? መሪዎቹና ዘዋሪዎቹ የተለ ያየ ዓላማ ያላቸው ሁለት አካላት ናቸው። 1ኛ/የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው አካላት ናቸው፤ከአንድ ዓመት በፊት ሕወሃት በትግራይ የሚገኝ እያንዳንዱ ቤተ እምነት በሚድያ እየወጣ አዲስ አበባ ከሚገኘው ማዕከሉ መገንጠሉን እንዲያውጁ አደረገች ።”መን በረ ሰላማ የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት” የሚባልም ለኦርቶዶካሳዊት ቤተ ክርስትያን አቋቋ መች።የሌሎች ቤተ እምነቶች እንዲሁ አጃቢዎች ስለነበሩ ጦሩነቱ ቆሞ ጦረኞቹ ተቃቅፈው ሲሳሳሙ ቤተ እምነቶቹም ከማዕከላዊ አሰተዳደራቸው ጋር እንደገና ተስማምተው ቀጠሉ።ኦርቶዶካሳዊት ቤተ ክርስትያንን ግን ሕወሃት በደንብ ጠርንፋ በመያዝ በፖለቲካ ላልተሳካው ዓላማ ቤተ ክርስትያንን መያዣ አድርጋ ለወደቀው ፖለቲካ ማገገሚያ፥ለተበታተነው ደጋፊዎቿ መሰብሰብያ እና ለወደ ፊቱ ፖለቲካዋ መቀ ስቀሻ አድርገዋለች።ለዚህም ይረዳት ዘንድ አባቶችን ዕለት ዕለት የሚከታተል፥የሚያወጡትን መግለጫ ዎች የሚጽፍ ሦስት ብርቱ ካድሬዎች ያሉበት ቡድን አቋቁማለች። ይህ በሓለቃ ጸጋየ የሚመራው የካድሬዎች ቡድን ሃይማኖታዊ ዓላማ ይዘው ሕወሃትን ተጠቅመው ኦርቶዶካሳዊት ቤተ ክርስትያንን የመበታትን አጀንዳ ለሚያራምዱት ተሃድሶ መናፍቃን የሚሠራ ነው። 2ኛ/ሃይማኖታዊ ተልዕኮ ያላቸው አካላት ናቸው፤ ይህ ሃይማኖታዊ የሆነው ገፊ ምክንያት ዋናው በትግ ራይ ለሚገኙ አባቶች ተገንጥለናል፥ተለይተናል፥ኤጲስ ቆጶሳትንም አንሾማለን እንዲሉ የሚያደርገው ነው። ተሃድሶ መናፍቃን በመላው ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ከብዙ ሥል ጠና በኋላ ጠንካራ አደረጃጀት ፈጥረው በ1990ዎቹ እጅግ ተጠናክረው በየሰንበት ትምህርት ቤቱ እና በየ ገዳማቱ ተበተኑ።ነገር ግን እንዳሰቡት ሳይሆን በማኅ በረ ቅዱሳን መሪነት ወጣቱ ከየቦታው እየለቀመ አጋ ለጣቸው።በትግራይ ደብረ ዳሞ ሳይቀር በመግባት መነኮሳትን ለማስኮብለል ሲሞክሩ፥ደብረ አባይ ተማሪ ዎችን ሲያግባቡ እና ከእንዳ ማርያም ጀምረው ሰን በት ተማሪዎችን ለመቀሰጥ ሲጥሩ ምንም ማጭበር በር በማይችሉበት መረጃ እየተያዙ ተለቀሙ።የተወሰ ኑት ሙሉ በሙሉ ተመ ለሱ።ሌሎች ተለይተው ሄዱ። የቀሩት በተለያየ ምክንያት እዚሁ እኛው ቤት ቀር ተው ቀሰ በቀስ መስፋፋት ጀመሩ። እነዚህ በተለያየ ቦታ ተደብቀው የነበሩ መናፍቃን በትግራይ የበለጠ ተጠናክረው እንዲወጡ ማኅበረ ቅዱሳንን ማሰጠላት፥መበተንና ማፈራረስ ትልቁ ታክ ቲካቸው አደረጉ።ይህም በትግራይ ተሳካላ ቸው። በመቀጠል ትግራይ ያለችው ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኃይልም ሆነ ጉልበት እንዳታገኝ ከማዕ ከሉ ከቅዱስ ሲኖዶስ በመለየት አስተዳደሩን መቆጣ ጠር ቻሉ።ጦርነቱ ትግራይን አወደመ።ተሃድሶ መናፍ ቃን ግን ጦርነቱን እንደ ጥሩ አጋጣሚ ተጠቅመው የሀገረ ስብከቶችን አስተዳደር እስከሚችሉት ድረስ ተቆጣጠሩ። በመቀጠልም “ማኅበረ ቅዱሳንን እንደ ድርጅት ከትግራይ አጥፍተነዋል፥አሁን ደግሞ የዘራውን የሸ ዋን እምነትና ተከታዮችን እናጠፋለን፤”ብለው በዚያ አሰቃቂ ጦርነት ወቅት ሳይቀር ብቸኛ መጽናኛ ቤታች ንን አማናዊት ምስካየ ኅዙናንን አመሷት።ልጆቿን አሳደዱ።የተወሰኑትንም ከቤተ ክርስትያን አባረሩ። “ማርያም አማላጃችን ናት፥ቅዱሳን ያማልዳሉ” የሚ ለው የሸዋ ትምህርት ነው አያሉ የሚቃወማቸውን ሁሉ “ሸዋ” “ማኅበረ ቅዱሳን” “ባንዳ” እያሉ ያሳድ ዳሉ።“አማላጃችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” እያሉ በቤተ ክርስትያን ዐውደ ምሕረት በይፋ ያስተምራሉ። መሠረታዊ የቤተ ክርስትያንን መጻሕፍት እየቆነጻጸሉ ወደ ትግርኛ እየተረጎሙ ነው።ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በትግራይ ለመቆጣጠር ከቅዱስ ሲኖዶስ ትግራይን ነጥለን የራሳችንን ኤጲስ ቆጶሳ ትን እንሾማለን ብለው ተነሥተዋል።በመቀጠል በአንድ ዓመት ውስጥ የትግራይ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ይቋቋማል።የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ፓትርያርክ ይሾማል።እዚህ ላይ “ተዋሕዶ” የሚለው ስም እንደሚቀርም ወስነዋል።“በመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ሲኖዶስ አማካኝነት ትግራይ ወደ ጥንቱ እምነቷ ትመለሳለች። የሸዋ እምነት ይወገዳል”ይላሉ። ይህ የጥንት እምነት የሚሉት ቅጥፈት ክርስቶስ አማላጃችን የሚል በወላዲተ አምላክ እና በቅዱሳን አማላጅነት የማያምን ጾም ጸሎትን የሚጸየፍ ስሙን ብቻ የቀየረ የፕሮስቴንታንት እምነት ነው።ምንም እንኳን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በትግ ራይ ለመገንጠልና ዐሥር ኤጲስ ቆጶሳትን ሾመን በመ ንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ሲኖዶስ እናቋቁማለን የሚ ለው የመሰሪዎቹ የተሃድሶ መናፍቃን ልዩ ፕሮጄግት ቢሆንም ሕወሃትን ከወቀሳ ብፁዐን አባቶ ችን ከተ ጠያቁነት አያድንም።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
#የሐዋርያት ቀኖና አልተሻረምን??? የሐዲስ ኪዳን ክህነት ባህርየ ቃል ባህርየ ሥጋን በተዓቅቦ ቢዋሐድ የቃል ገንዘብ ለሥጋ የሥጋ ገንዘብ ለቃል ሆነ ። ንጉሰ ነገሥት ሊቀ ካህናት ተባለ ። የባህርይ መሥዋዕትነቱን ራሱ ሠዋዒ ተሠዋዒ ሁኖ ለራሱ አቀረበ ።ክርስቶስ ነቅዓ ክህነት ወሀቤ ሀብት ነውና በእግርም በግብርም ለተከተሉት አባቶቻችን ሐዋርያት ከምንጩ በጸጋ ሥልጣነ ክህነትን ተቀበሉ።በዕለተ ዕርገት ሐዋርያትን እየባረካቸው አፈፍ አለ፣ በድረግ አለ ፣ የርቀት ያይደለ የርህቀት ተሠወራቸው። ሐዋርያትም የተቀበሉትን ክህነት ለመጻኢው ትውልድ የሚገባውን እየለዩ በአንብሮተ እድ አቀብለዋል።ወደእኛም ከሐዋርያት ወደ ቅዱስ ማርቆስ ከማርቆስ ወደ አቡነ ባስልዮስ ኢትዮጵያዊ ከዚያም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዘመናችን ደርሷል።ያለምንም ተመትሮ በቅብብሎሽ የሚሰጡ ፦ 1.ሐዋርያዊ ክህነት፦ብዙ ጳጳሳት ፣ካህናት ቢኖሩም ብዙ ክህነት የለም። 2.ሐዋርያዊ ትምህርት፦12ሐዋርያት ቢኖሩንም ብዙ የሐዋርያነት ተልእኮ የለም። 3.ሐዋርያዊ አረዳድ፦ብዙ የሚረዱ ቢኖሩም ግላዊ መረዳት የለም 4.ሐዋርያዊ ልጅነት፦ብዙ ልጆች ቢኖሩም ብዙ ልጅነት የለም። 5.ሐዋርያዊ አምልኮ፦ብዙ አምላኪዎች ቢኖሩም ብዙ ተመላኪ የለም ያው አንዱ ነው እንጁ 6.ሐዋርያዊ ዕለተ ዓርብነ፦ብዙ ዓርቦች ቢኖሩም ብዙ ዕለት ስቅለት የለም አንዲቷ ሐዲስ ዕለት ናት 7.ሐዋርያዊ እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ...ናቸው።እነዚህ በቅብብሎሽ የሌሉት ሰው ኦርቶዶክሳዊ ሊባል አይችልም። አባቶቻችን ሐዋርያት የክህነት ቀኖናን በሠሩበት አንቀጽ ሹመትን በውግዘት የሚከለክሉ ዋና ዋናዎች ፦ ሲሞናዊነት(በእጅ መንሻ መሾም)መለካዋነት(በንጉሥ ግዳጅ መሾም)በቃሁ ነቃሁ ብሎ በራስ መሾም፣ ምእመናን ሳይቀበሉት መሾም...ፈጽሞ በውግዘት የተከለከለ ነው። የሐዋርያት ቀኖና በውግዘት እና ያለ ውግዘት የተሠራ ቀኖና ነው።በውግዘት የተሠራውን ቀኖና እስከ ዕለተ ምጻት እንጠብቀዋለን እንጂ አንለውጠውም ።ያለው ውግዘት የሠሩት ግን ብያኔያዊ ነውና ቦታውን ሁኔታውን አይተው ሊያሻሽሉት ይችላሉ ፦ለምሳሌ፦ምእመናን አሥራት በኩራታቸውን ይስጡ ይላል፦ድርቅ ቢሆን፣ስደት ቢሆን በመሳሰለው ዘመን ተቸግረው ሳለ ባይሰጡ ዘእንበለ ግዘት ነው። ውግዘት የለውም ይላል ፍት.ነገ አን.5። ክህነትን በተመለከተ ግን ፦አምላካችን "ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው?"የማቴ6፥27 ያለውን ማለትም ከእናንተ በቃሁ ነቃሁ ብሎ ለራሱ ሥልጣነ ክህነትን ገንዘብ ማድረግ የሚቻለው የለም ።እንዳለ ።የግድ ሹሙኝ ብሎ የሚሾም የለም።በሹመት ምክንያት አስፈራርቶ ቢሾም ከምእመናን አንድነት የተወገዘ ነው። ወይም በንጉሥ አስፈራርቶ ሹመትን የሚሻት እና የሚሾም ፣ወይም የሚሾምባቸው ምእመናን ያልፈቀዱለት ያልተቀበሉት የተወገዘ ነው ይለናል ። ያንድ ሊቀ ጳጳስ ሀገረ ስብከቱ እንደሚስቱ ትቆጠራለች ሳይወዳት ሳትወደው እንደምን ጋብቻው ይፈጸማል።? ከዚት ቀኖና ጋር እንዴት ነው የምንታረቀው?በአራተኛ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ንጉሡ ያለውን የግድ ተቀበሉ ሲባል አባታችን ቅዱስ ዲይስቆሮስ የሰማያዊ ንጉሥ ሕግ እያለ የምድራዊ ንጉሥ ኑፋቄን አልቀበልም ቢል ፦ጽህሙን ነጭተው ጥርሱን አርግፈው አባረውታል በጎሳ ሥሁት ፖለቲካ ሲመት ይፈጸም ይሾሙ የሚባል ከሆነ የዲዮስቆሮስ ሃይማኖት አለችን ማለት ይቻላልን? ይሄ ቀኖና ተጥሶ ሹመቱ ሲፈጸም ከሐዋርያት አንድነት ጉባኤ እየተለየን እንደሆነ መታወቅ አለበት።ቤተ ክርስቲያንም ወደማያባራ የቀኖና ንትርክ መግባቷ አይቀርም።በዚህ መካከል የሚጠፋውን ምእመን መገመት አያዳግትም። ክፍል፩
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የአባታችን የብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ዘመን ተሻጋሪ ንግግር፦ «ታላላቅ አብያተ ክርስቲያናትን ገንብተን በውስጣቸው የሚያገለግሉ ታላላቅ ሊቃውንትን ከምናጣ፥ ታላላቅ ሊቃውንትን አፍርተን እንደ ጥንቱ በድንኳን ብንገለገል ይሻላል።» [ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ]🥰❤️❤️💒✝️ #ኦረቶዶክስ_ተዋህዶ_የነበረች_ያለችና_ለዘላለም_የምትኖር_ነች_ኦርቶዶክስ #ኦርቶዶክስ_ለዘላለም_ትኑር🙏🙏🙏😍💚💛❤🌍💒💒💒💒💒💒💒🙏😭😪😭💚💛❤🌍💒💒💒💒🙅🙏 #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ለዘላለም_ትኑር_አምላከ_ቅዱሳን_ቤተክርስቲያንን_ይጠብቅልን💒❤🙏 #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ለዘለዓለም_ፀንታ_ትኑር
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
“ቤተ ክርስቲያን መነገጃ አይደለችም! ሌቦች ይውጡ! ጉበኞች ይውጡ! ሠርተው ይብሉ! በቤተ ክርስቲያን አውደልዳይ አይብዛ ፤ ቦታ አይሰጠው” “በጎጥ እና በቋንቋ የምንመራው እስከ መቼ ድረስ ነው?”ቢሮው የማን ነው? በጉቦ የገባው ማን ነው? ወንጌሉ የሚሰበከው ለማን ነው???? ሕዝቡ ተሰብኮ፣ ተሰብኮ ዐውቆታል፤ ቢሮ ውስጥ ነው ችግሩ ያለው፤ ጥያቄው ሲጎርፍ አለመመለስ ነው ችግሩ፤ በዚኽ ዓለም ያልታመነ በእግዚአብሔር መንግሥትስ ቦታ አለው እንዴ? ትምህርቱ የጆሮ ቀለብ ኾኗል፤ ውስጥ ገብተው ሲያዩት ያስለቅሳል፡፡” “ምርጫ በሞያ ይኹን፤ በጎጥ አይደለም፤ ሲጠየቅ መልስ የሚሰጥ ቤተክርስቲያንን የሚያውቅ የሕዝብ አባት ይኹን፤ ድኻ ተበደለ፤ ፍርድ ተጓደለ የሚል አባት ከሌለ ትርጉሙ ምንድን ነው መሰብሰባችንም ምንም በቈዔት የለውም፤” “አእምሯችን ሳይገራ፣ ለሕጉ ተገዥ ሳንኾን ከየትም ከየትም መጥተን እግዚአብሔርን የምናስቀይም ነው የምንኾነው፤ ያልተቀጣ ልጅ ኹልጊዜ እንደሰረቀ ይኖራል፤ ልቡናው በእግዚአብሔር ቃል እና ምስጢር ያልተቀጣ ሰውም ኹልጊዜ እንደበጠበጠ ይኖራል፤ ፖለቲካ ከቤተ ክርስቲያን ይውጣ፤ እውነት ይገለጥ ቅዱስ አባታችን፤ ስለእውነት እንቁም፤ በአራቱ ማዕዝን ጥያቄ ተቀስሯል፤ ስለ ሃይማኖት ጥያቄ እየተነሣ ነው፤ ጥያቄውን የሚመልሰው ማን ነው? ብዙ ችግሮች ቀርበዋል፤ የሚፈታቸው ማን ነው? አእምሮ ያስባል፤ ጆሮ ይሰማል፤ ድኻ ተበደለ፤ ፍርድ ተጓደለ፤ የሚል አባት ከሌለ ትርጉሙ ምንድን ነው? ዙሪያውን ሰይፍ ተመዞ እየተብለጨለጨ የደነዘዘውን አእምሮ እናስወግደው፤ ቃሉን እንጠይቀው፡፡ ሕጉ ይከበር፤ ስም ብቻ አንያዝ፤ ሕጉን ወደ ኋላ አሽቀንጥረን ትተን እንዴት መምራት እንችላለን? ተንኰል ይቅር፤ በውሸት አንመን፤ በዝባዥ ይጋለጥ፤ ጨርሻለኹ፡፡ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ 2008 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ የብፁዕነታቸው ቡራኬ አይለየን !
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.