uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 546 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 351-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 178-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 546 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.76% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.84% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 005 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 463 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 546
Obunachilar
+824 soatlar
-227 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ውሃ ወደ ግድቦች እየገባ ነው ....... /// ...... በተያዘው የክረምት ወቅት ወደ ኃይል ማመንጫ ግድቦች እየገባ ያለው የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እንደሚያስችል የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ። በጽ/ቤቱ የፕላኒንግ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ ግድቦች በቂ ውኃ መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ወደግድቦች እየገባ ያለው የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ለማሳካት እንደሚያስችል ታይቷል ብለዋል። እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት የአምስት ግድቦች የውሃ መጠን ከፍተኛ እንዲሁም የሦስቱ ደግሞ በቂ በሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጇ ጠቁመዋል። በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የቅድመ መከላከል ጥገናዎችን ከግድብ ውሃ አጠቃቀም ጋር አቀናጅቶ በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በማከናወን የኃይል መቋረጥን ለመቀነስ እቅድ መያዙንም አመልክተዋል፡፡ በተያዘው ክረምት ከፍተኛ የውሃ መጠን ያከማቹ የማመንጫ ጣቢያዎች ከፍተኛ ኃይል እንዲያመነጩ በማድረግ አነስተኛ ውሃ የያዙ ግድቦች የሚኖራቸውን ጫና ቀንሶ ውሃ በተገቢው መጠን እንዲይዙ ለማድረግ መታቀዱን ስራ አስኪያጇ ተናግረዋል፡፡ በለስ፣ ፊንጫ፤ ገናሌ ዳዋ 3፤ ግልገል ጊቤ 1ኛ እና አመርቲ ነሼ የውሃ ማመንጫ ጣቢያዎች የውሃ እጥረት ስለማያጋጥማቸው በሙሉ አቅማቸው ያመነጫሉ ተብሎ የታሰበ ሲሆን በግቤ 3ኛ ማመንጫ ጣቢያ ግድብ ላይ በቂ ውሃ ለመያዝ ሲባል ጭነቱን በተወሰነ መልኩ ለመቀነስ መታሰቡንም ጠቁመዋል፡፡ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በራስ አቅም የጥገና ስራዎችን በማከናወን ለረጅም ጊዜ የቆሙ የተለያዩ ማመንጫ ጣቢያ ዩኒቶችን ወደ ኦፕሬሽን መመለስ እንደተቻለ ያስታወሱት ወ/ሮ ጥሩወርቅ በተያዘው በጀት ዓመትም ተመሳሳይ ስራዎችን በመስራት የማመንጫ ዩኒቶች በአግባቡ ኃይል እንዲያመርቱ ለማድረግ እና ተቋሙ ለጥገና ስራ የሚያወጣውን ወጪ ለመቀነስ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የማመንጫ ጣቢያዎችን የመለዋወጫ እቃ እጥረት ለመፍታትና በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ የመለዋወጫ እቃዎችን በማዕቀፍ የግዥ ስርዓት ለማከናወን እየተሰራ ካለው ስራ በተጨማሪ ለ11 ማመንጫ ጣቢያዎች የሚያገለግል የመለዋወጫ ዕቃ በቀጥታ ግዢ ለመፈፀም በሂደት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የዘርፉን የኦፕሬሽንና የጥገና ሠራተኞች ክህሎት ለማሳደግ ዓለም አቀፍ ልምድ ያላቸውን ኩባንያዎች በሀገር ውስጥ በማምጣት ለሠራተኞች ሥልጠና እንዲሰጡ ለማድረግ ዕቅድ መያዙንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

ኢትዮጵያ በኮሎምቢያ ካሊ የተካሄደውን የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 1 ነሃስ በድምሩ በ12 ሜዳሊያ ከአፍሪካ በአንደኝነት አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ውድድሩን
ኢትዮጵያ በኮሎምቢያ ካሊ የተካሄደውን የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 1 ነሃስ በድምሩ በ12 ሜዳሊያ ከአፍሪካ በአንደኝነት አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ውድድሩን ከአሜሪካ እና ጃማይካ በመቀጠል በሶስተኛነት በማጠናቀቋ እንኳን ደስ አላችሁ፣እንኳን ደስ አለን! እንላለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2014 ዓ.ም

የፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመል
+2
የፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 05 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ተቋሙ የራሱን ክሊኒክ ማቋቋሙ ለሠራተኞች ህክምና የሚወጣውን ወጪ ለመቀነስ ያግዛል ……./////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራሱን መካከለኛ ክሊኒክ ማቋቋሙ ለሠራተኞቹ የህክምና አገልግሎት ሲያወጣ የነበረውን ወጪ ለመቀነስ እንደሚያግዘው የተቋሙ የጤና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሰረት ሙሉጌታ ገለጹ፡፡ ስራ አስኪያጇ እንደገለጹት ተቋሙ የራሱ የህክምና ክሊኒክ የሌለው በመሆኑ ሠራተኞቹ የህክምና አገልግሎቶችን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከለኛ ክሊኒክ ሲያገኙ ቆይተዋል፡፡ ክሊኒኩ በላብራቶሪና በመድሃኒት ያልተደራጀ በመሆኑ የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለማግነት የሚፈልጉ ሠራተኞች ወደ ውጪ ሪፈር የሚላኩበት ሁኔታ እንደነበር ያነሱት ኃላፊዋ ይህም ተቋሙን ለከፍተኛ ወጪ ሲዳርገው እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ የራሱን መካከከለኛ ክሊኒክ ማቋቋሙ የምርመራ፣ የላቦራቶሪና የመድሃኒት አገልግሎቶችን በራሱ ለመስጠት ስለሚያግዘው ለህክምና የሚወጣውን ወጪ እና የሠራተኞችን እንግልት በመቀነስ ሲነሱ የነበሩ የተለያዩ ቅሬታዎችን ለመፍታት ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ መሰረት ገለፃ የክሊኒኩ መቋቋም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ውስጥ የሚገኙ 13 ክሊኒኮችን በባለሙያ፣ በመድሃኒትና በላቦራቶሪ መሳሪያዎች ለማጠናከር፣ የተለያዩ የሙያ ድጋፎችን ለመስጠትና ስልጠናዎችን ለማመቻቸት ይረዳል፡፡ በክሊኒኩ ከፍተኛ ሜዲካል ላቦራቶሪ ቴክኖሎጂስት የሆኑት አቶ ዳዊት ሳህሌ በበኩላቸው ክሊኒኩ በሰውነት ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን፤ በሽንትና በሰገራ ውስጥ ያሉ ጥገኛ ትላትሎችን፤ በደም ምርመራ ሊለዩ የሚችሉ እንደ ኮሌስትሮል፣ ጉበትና ኩላሊት ላይ ያሉ ኬሚካሎችን ለመለየት የሚያግዙ እና ለሌሎች የላቦራቶሪ ስራዎችን ለማከናወን የሚረዱ የተለያዩ የላቦራቶሪ መሳሪያዎች እንደተሟሉለት ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ የሆርሞን ምርመራ እና የረጅም ጊዜ የጤና ክትትል ለሚያደርጉ የላቦራቶሪ ምርመራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በክሊኒኩ ውስጥ ለደም ግፊት፤ ለስኳር፣ ለሆርሞን፣ ለቆዳ፣ ለመተንፈሻ አካልና ለህመም ማስታገሻ የሚያገለግሉ እንዲሁም የቫይታሚን መድሃኒቶች መሟላታቸውን ጠቁመዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በተለየዩ ዘርፎች የህክምና አገልግሎት ከሚሰጡና ከአገልግሎቱ ጋር ስምምነት ካደረጉ 30 የህክምና ተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ ሲሆን በ2016 በጀት ዓመት በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግና ጥራት ካላቸው የጤና ተቋማት ጋር ተቋሙ በራሱ ስምምነት በማድረግ የህክምና አገልግሎቱን ለመስጠት እቅድ ተይዟል፡፡ ክሊኒኩ ደረጃቸውን የጠበቁ የላብራቶሪ መሳሪያዎችና ዋና ዋና መድሃኒቶች እንደተሟሉለት ያነሱት ኃላፊዋ የረጅም ጊዜ የህክምና አገልግሎት ለሚከታተሉ ሠራተኞች የሚያገለግሉ መድሃኒቶችን ለማሟላት በግዥ ሂደት ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ክሊኒኩ አራት የምርመራ ክፍል፣ የላቦራቶሪ፣ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት መስጫ፣ ለህክምና አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችና መድሃኒቶች የሚቀመጡበት መጋዘን፣ የአልጋ እንዲሁም አገልግሎት የሰጡ የህክምና መሳሪያዎች የሚቀመጡበት ክፍሎች አሉት፡፡ በክሊኒኩ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ሰባት ባለሙያዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ተጨማሪ ባለሙያዎችን ለማሟላት በቅጥር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙ መካከለኛ ክሊኒክ ተመረቀ ……….////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያስገነባው መካከለኛ ክሊኒክ በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምረ፡፡ ክሊኒኩን ከትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን ሥራ አስፈፃሚ ጋር መርቀው በይፋ ሥራ ያስጀመሩት የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ተቋሙ የራሱ ክሊኒክ እንዲኖረው ለማድረግ የተሰራውን የመልሶ ግንባታ ሥራ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል፡፡ ከዚህ ቀደም የተቋሙ ሠራተኞች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከለኛ ክሊኒክ የህክምና አገልግሎት ሲያገኙ እንደነበር የጠቀሱት ኃላፊው ላለፉት ስምንት ዓመታት ለተቋሙ ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ ለቆየው ክሊኒክና ግንባታውን በሚፈለገው የጥራት ደረጃ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ ላደረጉት አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍዴል በበኩላቸው ተቋሙ የተጣለበትን ተልዕኮ እንዲወጣ ለማድረግ የሠራተኛውን ጤንነት ለመጠበቅ ትኩረት ተሠጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የክሊኒኩ አገልግሎት መስጠት መጀመር የሠራተኛውን ጤንነት በቅርበት ለመከታተል ያግዛል ነው ያሉት፡፡ ክሊኒኩ በአሁኑ ወቅት በሰው ኃይልና በአገልግሎት መስጫ መሳሪያዎች ሥራ ሊያስጀምር በሚችል መልኩ የተደራጀ እንደሆነና በቀጣይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በወቅቱ በመፍታት ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ያሉትን ክሊኒኮች ለማጠናከር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡ ስድስት ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት መካከለኛ ክሊኒክ በተቋሙ የኮተቤ ግቢ ውስጥ ቀደም ሲል ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ሲጠቀምበት የነበረውን ህንጻ መልሶ በመገንባት ለአገልግሎት እንዲውበቃ የተደረገ ነው፡፡ የመልሶ ግንባታ ሥራው በራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ እንዲሁም የማማከርና የዲዛይን ሥራው ደግሞ በኢንጂነሪንግ መምሪያ መከናወኑን በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የተቋሙ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የክሊኒኩን የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ተዘዋውረው በመጎብኘት በባለሙያዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

በተያዘው በጀት ዓመት እስከ 19 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት የሚደርስ ኃይል ለማመንጨት ታቅዷል ……..////…… በተያዘው የ2015 በጀት ዓመት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች 18 ሺህ 994 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት መታቀዱን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ በጽ/ቤቱ የፕላኒንግ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት ከታቀደው ውስጥ 18 ሺህ 228 ነጥብ 48 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከውሃ፣ 705 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከነፋስ እንዲሁም 60 ነጥብ 54 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከደረቅ ቆሻሻ የሚመረት ነው፡፡ ዕቅዱን ለማሳካትም የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማሟላት፤ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን የውሃ አጠቃቀም እና አስተዳደር ለማሻሻል፣ የመለዋወጫ ዕቃዎች ግዢ እና አቅርቦትን ለማስተካከል እንዲሁም የፍተሻና ጥገና ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲከናወኑ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ዩኒቶቻቸው ጥገና በሚፈልጉት በፊንጫ፣ በአመርቲ ነሼ፣ በቆቃና የአዋሽ እንዲሁም በረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አስፈላጊውን ጥገና በማከናወን በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኢነርጂ አቅርቦትን አስተማማኝ ሊያደርግ የሚችል ደረጃዉን የጠበቀ የቅድመ መከላከል፤ የፍተሻ፣ የትንተና እና የሁኔታዎች አመላካች የጥገና ሥራ ለማከናወን እቅድ መያዙንም አመልክተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለፃ ለኬንያ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት መጠናቀቁ፣ በተያዘው ክረምት በሁሉም የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በቂ የውሃ መጠን እየገባ መሆኑ፤ እንዲሁም የህዳሴ 2ኛ ዩኒት እና አይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት እየተሰራ ያለው ስራ በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ለማሳካት እንደ መልካም አጋጣሚ የሚወሰዱ ናቸው፡፡ በበጀት ዓመቱ 17 ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል ያመነጫሉ ተብለው ዕቅድ የተያዘላቸው ሲሆኑ ከእነዚህም በአማካይ 3 ሺህ 862 ሜጋ ዋት ዝግጁ የሆነ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖራል ተብሎ ታቅዷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

ማህበሩ ሲያካሄድ የነበረውን ጉባኤ አጠናቀቀ ………////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ከሐምሌ 25 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ያካሄደውን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ አጠናቀቀ፡፡ ማህበሩ በሁለት ቀናት ቆይታው በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ ቁልፍ ጉዳዮች እና በቀጣዩ በጀት ዓመት ሊሰሩ በታቀዱ ሥራዎች ላይ በሰፊው ተወያይቶ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል። ከሠራተኛ ዕድገት አሰጣጥ፣ ዝውውር፣ ከጥቅማጥቅም እና ከሰራተኞች ደህንነት ጋር ተያይዞ ሊስተካከሉ ይገባቸዋል ያሏቸውን ጉዳዮች በማንሳት ማኔጅመንቱ ትኩረት ሰጥቶ እንዲቀርፋቸው ጠይቀዋል፡፡ በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ምላሽ ይፈልጋሉ ተብለው በተለዩ ጉዳዮች ላይ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ሀብት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ ከሠራተኛ እድገት፣ የሥራ አፈጻጸም፣ ጥቅማጥቅም፣ ደመወዝ እና ሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ በተነሱት ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ሰጥተዋል። ሥራ አስፈፃሚው በምላሻቸው ማህበሩ ለሰራተኛው በየጊዜው የሚጠይቃቸው የተለያዩ የአበል ጥያቄዎች የተቋሙን የፋይናንስ አቅም ባገናዘበ አግባብ በጥናት እየታየ ምላሽ እንደሚያገኝ ገልፀዋል፡፡ የዓመታዊ ጭማሪና የማትጊያ አበል የተቋሙን የፋይናንስ እና ፊዚካል አፈጻጸም እንዲሁም የሠራተኛውን የሥራ አፈጻጸም ውጤት ግምት ውስጥ በማስገባት እንደሚታይም ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የሚስተዋሉ ተገቢ ያልሆኑ የዕድገትና ዝውውር ሂደቶችን በማረም ህብረት ስምምነቱ በሚፈቅደው መሰረት እና ግልጽ በሆነ መንገድ መከናወን እንዳለበት ያነሱት ሥራ አስፈጻሚው ለዚህም ተገቢ የሆነ ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። ከማህበሩ አባላት በግንባታ፣ በኦፕሬሽን፣ በንብረት እና አስተዳደር እንዲሁም በሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው በተያዘው በጀት ዓመት 1 ሺህ 736 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል ……………///………… የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2015 በጀት ዓመት 1 ሺህ 736 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን አስታወቀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ባንተያምራል መኮንን እንደገለፁት ማመንጫ ጣቢያው ካሉት ሶስት ተርባይኖች መካከል በሁለቱ 170 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ላይ ይገኛል፡፡ ወደ አንደኛው ዩኒት ውሃ እንዲገባ የሚያስችለው የዋናው በር ፒስተን ላይ ችግር በማጋጠሙ ምክንያት አንዱ ተርባይን ለጊዜው አገልግሎት እየሰጠ አይደለም ብለዋል፡፡ ይሁንና ያጋጠመውን ችግር ኃይል ማመንጫውን የገነባው ተቋራጭ ሲ.ጂ.ጂ.ሲ የተባለው የቻይና ኩባንያ ኃላፊነቱን ወስዶ ለማስተካከል እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ኩባንያ የፒስተን ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ባንተያምራል ከገቢዎችና ጉምሩክ ፈቃድ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች እንዳለቁ ወደ ጣቢያው የማጓጓዝና የመትከል ሥራዎች እንደሚጀመሩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የጥገና ሥራውን በተቻለ ፍጥነት አጠናቆ ተርባይኖቹ በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመርቱ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

ማህበሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሠራተኛውን ጥያቄ የሚመልሱ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ …….////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር በ2014 በጀት ዓመት የሠራተኛውን ጥያቄ የሚመልሱና ጥቅሙንም የሚያስጠብቁ ሥራዎች ማከናወኑን ገለፀ፡፡ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ የማህበሩን ዓመታዊ ሪፖርት ሲያቀርቡ እንደገለፁት በህብረት ሥምምነት እንዲሻሻሉ ማህበሩ ያቀረባቸውን የህክምና ወጭዎች፣ በአዋጁ ያልተካተቱ የጥቅማ ጥቅምና አስተዳደራዊ ጉዳዮች፣ ዕድገትና ዝውውር፣ የዓመታዊ ጭማሪና የሠራተኛውን ጥቅም በሚያስጠብቁ ሌሎች ጉዳዮች ላይ በትኩረት ሲሰራ ነበር፡፡ ማህበሩ የሠራተኛውን መብት፣ ጥቅምና ፍላጎት ለማሟላት በቦርድ፣ በማኔጅመንትና በተለያዩ ውሳኔ በሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ የሠራተኛውን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ መሳተፉን ሊቀመንበሩ ተናግረዋል፡፡ በሥራ ላይ ሁነው ትምህርታቸውን ያሻሻሉ የተቋሙ ሠራተኞች በተመረቁበት ሙያ ተመዝነው በመረጡት ቦታ እንዲመደቡ መደረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ በጥበቃ፣ በፅዳትና በአትክልተኛ የሥራ መደቦች ላይ የሚገኙ እና የመንጃ ፈቃድ ያላቸው ሠራተኞች ሥልጠና አግኝተው ፈተናውን ያለፉ ሠራተኞችን የመመደብ ሥራ መከናወኑን ሊቀመንበሩ ተናግረዋል፡፡ የሴቶችን ተጠቃሚነትና ውሳኔ ሰጭነት ለማሳደግ የቀረበን የድጋፍ እርምጃን የህብረት ሥምምነቱ አካል እንዲሆን ለማድረግ ሰፊ ሥራ መሰራቱን የገለፁት ሊቀመንበሩ በዋናው መሥሪያ ቤት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን የህፃናት ማቆያ ሥራ እንዲጀመር ለማድረግም የማህበሩ ሚና የጎላ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡ በዋናው መስሪያ ቤት፣ በፕሮጀክቶች፣ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተቋሙ እና በሠራተኛው መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሠላም በመፍታት ጤናማ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ማህበሩ ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ ማህበሩ አሁን ላይ የ2014 በጀት ዓመት ጥቅማ ጥቅም ድርድርን ጨምሮ የአበልና ሌሎች የሠራተኛውን ጥቅም በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን በሪፖርቱ ተጠቁሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው ……..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ አባላት አራተኛ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀ
+3
የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው ……..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ አባላት አራተኛ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀምሯል። ማህበሩ ሐምሌ 25 እና 26 ቀን 2014 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጠቅላላ ጉባኤ በ2014 በጀት ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች እና የማህበሩ የሒሳብ ሪፖርት ላይ ውይይት ይደረግበታል። የማህበሩ የ2015 በጀት ዓመት ዋና ዋና ዕቅዶች ላይም ውይይት በማድረግ እና ዓመታዊ በጀቱን በማጽደቅ ይጠናቀቃል ረብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ ዕሴቶች፣ ተግባርና ኃላፊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተሻሻው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 381/2008 መሰረት የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ሲሆን የተቋቋመባቸው ዓላማዎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራዎች የአዋጭነት ጥናት፣ የንድፍ እና የቅየሳ ሥራዎች ማከናወን፣ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በአማካሪ ማሠራት፤ 2. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎች፣ ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታና የማሻሻያ ሥራዎችን ማከናወን፤ እንደአስፈላጊነቱ እነዚህኑ ሥራዎች በሥራ ተቋራጭ ማሠራት፤ 3. ከብሔራዊ ግሪድ ጋር የተያያዙ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጪያ ጣቢያዎችን፣ ከ66 ኪሎ ቮልት ኃይል በላይ የመሸከም አቅም ያላቸውን የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ማስተዳደር፣ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን ማከናወን፤ 4. ከ66 ኪሎ ቮልት ደረጃ በላይ በሆኑ መስመሮች የኤሌክትሪክ ኃይልን በጅምላ መሸጥ እና መግዛት፤ 5. ከ66 ኪሎ ቮልት በላይ የሆኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ሊዝ ማድረግ፤ 6. የሚሸጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል በተመለከተ የታሪፍ ማሻሻያ ሀሳብ ማቅረብ፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ ማድረግ፤ 7. የገንዘብ ሚኒስቴር የሚያወጣውን መመሪያና የፖሊሲ አቅጣጫ መሠረት በማድረግ ቦንድ መሸጥና በዋስትና ማስያዝ እና ከአገር ውስጥ፣ ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የብድር ውል መደራደርና መፈራረም፤ 8. ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ የሆኑ ሥራዎችን ማካሄድ፤ ራዕይ ለሀገር ዕድገት አለኝታ የሆነና ለአህጉራዊ ትስስር መሠረት የሚጥል ዓለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋም ሆኖ ማየት፤ ተልዕኮ ታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረት በማድረግ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ መሠረተ ልማቶችን የአዋጭነት፣ የቅየሣ ዲዛይን፣ የመገንባት የማሻሻል የማስተዳደር ተግባራትን ማከናወን፣ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጅምላ በመሸጥና በመግዛት ለአገር ብልፅግናና ለአህጉራዊ ትስስር መሠረት የሚሆን አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ፤ እሴቶች • ቀጣይነት ያለዉ ልህቀት • የአገልግሎት አስተማማኝነትና ጥራት • ፕሮፌሽናሊዝም • ተጠያቂነት • ማህበራዊ ኃላፊነት • የሙያ ደህንነትና ጤንነት • መደመር ተቋማችንን የማይመለከቱ ተግባራት • ከላይ በዝርዝር ከተገለፁት የመ/ቤቱ ዓላማዎች ውጭ ያሉ ተግባራት ማለትም፦ • ለደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የመስጠት፤ • የኤሌክትሪክ ጥገና አገልግሎት ተግባራትን የማከናወን፤ • ደንበኞች የተገለገሉበትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ስሌት የማንበብ፤ • ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሒሳብን የማስከፈል፤ • የኤሌክትሪክ ሥርጭት እና ተያያዥነት ያላቸው ተግባራትን የማከናወን መብቶችና • ግዴታዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተግባርና ኃላፊነቶች መሆናቸውንም ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሐምሌ 22 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content