uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 539 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 340-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 161-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 539 obunachiga ega bo‘ldi.

28 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 24.98% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.34% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 882 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 539 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 29 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 539
Obunachilar
-424 soatlar
-147 kunlar
+130 kunlar
Postlar arxiv
ተቋሙ "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሃሳብ ውይይት እያካሄደ ነው ......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሃሳብ በተቋሙ አዳራሽ ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ፀጋዎቿን በመጠቀም ለቀጣዩ ትውልድ ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ለማስተላለፍ የተቋሙ የሥራ አመራርና ሠራተኛ ሌት ተቀን መሥራት አለባቸው። ውይይቱ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመዳሰስ ፈተናዎችን ወደ ዕድል ለመቀየር፣ ለሀገር ዕድገት እና ለሕዝቦች ተጠቃሚነት በጋራ የሚሰራ የተቋም ሀብት ለመፍጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ተግዳሮቶቿን ተቋቁማ በለውጥ ጎዳና ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር ጥረት እያደረገች መሆኑን ጠቁመው የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በዚህ የለውጥ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አበርክቶ ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢትዮጵያን ብልፅግና ዕውን ለማድረግ ሁሉም የተቋሙ የሥራ መሪና ሠራተኛ በንቃት መስራት እንደሚጠበቅበት የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሀብት መፍጠር ሂደት የሚኖረው ድርሻ ምን ሊሆን እንደሚገባ በውይይቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለፃ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ማስቀጠል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ነው። በውይይቱ ላይ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በሀብት ፈጠራና ሀገራዊ የብልፅግና ጉዞ ላይ የጋራ መግባባት ላይ ይደረሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 01 ቀን 2016 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ

photo content
+5

በማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……...///…….. በከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚከሰቱትን የእሳት አደጋዎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከአቅም በላይ በሆኑ የኃይል ጭነቶች ምክንያት የእሳት አደጋዎች እንዳይከሰቱ በትኩረት እየተሰራ ነው። በጣቢያዎቹ የሚከሰቱትን የእሳት አደጋዎች ለመከላከል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለሪጅኑ የኦፕሬሽን ሠራተኞች ሥልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው በእሳት አደጋ መከላከያ መሳሪያዎች አጠቃቀም ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ የተሰጠው ሥልጠና በማከፋፈያ ጣቢያዎች የእሳት አደጋዎችን ቢከሰቱ በፍጥነት ለመቆጣጠር ያግዛል። የሥልጠናው ተካፋዮች ያገኙትን የንድፈ-ሃሳብና የተግባር እውቀቶች ለሌሎች የሥራ ባልደረቦቻቸው ማካፈል እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። ሥልጠናውን በነፃ ለሰጠው ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ዳይሬክተሩ ምስጋና አቅርበዋል። በሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ገብሬ በበኩላቸው ሥልጠናው ሪጅኑ በሚያስተዳድራቸው 19 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ለሚሰሩ ከ60 በላይ የኦፕሬሽን ሠራተኞች መሰጠቱን ገልፀዋል። እንደ አቶ ታደሰ ገለፃ ሥልጠናው ዝቅተኛ የቮልቴጅ መጠን ባላቸው የማሰራጫ መስመሮች ላይ በሚከሰት የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ሽቦዎች መጣመር ምክንያት በተደጋጋሚ የሚስተዋሉትን የእሳት አደጋዎች በፍጥነት ለመቆጣጠር ይረዳል። ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ሥልጠና ላይ ሰልጣኞቹ የንድፈ-ሃሳብ እውቀትና የተግባር ልምምድ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ለጎረቤት ሀገራት የ47 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተከናውኗል ……..///…….. ባለፉት 6 ወራት ለጎረቤት ሀገራት የ47 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ መከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ምኒልክ ጌታሁን እንዳስታወቁት ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 6 ወራት ለጅቡቲ፣ ሱዳንና ኬንያ 1 ሺህ 82 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ 66 ነጥብ 27 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ ለማከናወን አቅዶ ነበር፡፡ ከዕቅዱ ውስጥ 762 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ የ47 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የተከናነው ሽያጭ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ15 በመቶ ዕድገት ቢኖረውም ከዕቅድ አንጻር ግን የተከናወነው ሽያጭ የዕቅዱን 71 ነጥብ 7 በመቶ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ በስድስቱ ወራት ለጅቡቲ የ20 ነጥብ 9 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ ለማከናወን ታቅዶ የ19 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱ 92 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት ቢቻልም ለሱዳንና ኬንያ የተከናወነው ሽያጭ ግን ከዕቅዱ ዝቅ ማለቱን አብራርተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ በግማሽ ዓመቱ ለሱዳን 11 ነጥብ 8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ ለማከናወን ቢታቀድም በሀገሪቱ ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት መሸጥ የተቻለው 8 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው፡፡ በኬንያ በኩልም በ 6 ወራት ውስጥ የ33 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽያጭ ለማከናወን ዕቅድ ቢያዝም የተሸጠው ግን 20 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ተቋም የታቀደውን ኃይል ለማቅረብ አቅሙና ዝግጁነት ቢኖርም በሱዳንና ኬንያ በኩል የታሰበውን ያህል ኃይል ባለመውሰዳቸው እና ፍላጎታቸው ወጥ ባለመሆኑ አፈፃፀሙ ዝቅ ማለቱን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በሁለተኛው አጋማሽ በሀገር ውስጥ ኃይል በዶላር ለመግዛት ፍላጎት ካላቸው ተቋማት ጋር ስምምነት በመደረጉ፣ ከጅቡቲ፣ ሱዳንና ኬንያ በተጨማሪ ለታንዛኒያ ኃይል ለማቅረብ መታቀዱን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የወሰን ማስከበር ችግር ለኦፕሬሽን ሥራ ፈተና እየሆነ መጥቷል .........///............ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጂን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ የወሰን ማስከበር ችግር በኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ ፈተና እየሆነበት መምጣቱን አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንደገለጹት የማስተላለፊያ መስመሮች በሚያልፉባቸው አካባቢዎች የሚቀርቡት የካሳ ይገባኛል ጥያቄዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች በወቅቱ እንዳይከናወኑ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ችግሩ በሪጂኑ ከጂማ ዞን እስከ ጋምቤላ በተዘረጉ የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እንደሚስተዋል ገልፀው ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች የፍተሻና የጥገና ሥራ ለማከናወን ፈተና እየሆነ መምጣቱንም ገልፀዋል። በካሳ ጥያቄ የተነሳ ኃይል የማስተላለፍ ሥራ እየተስተጓጎለ እንደሆነና በቅርቡም የጊቤ 2 - ሰኮሩ መስመር ለአራት ቀናት ኃይል ማስተላለፍ ተቋርጦ መቆየቱን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ አቶ ጌታሁን እንዳሉት የወሰን ማስከበር ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳደር አካላት ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በተመሳሳይ የማስተላለፊያ መስመሮች በሚያልፉባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የታወር አካላት ስርቆቶች ለሪጂኑ የኦፕሬሽን ሥራ ስጋት መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ከጊቤ 2 - ወላይታ ሶዶ በተዘረጋው መስመር ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት እንደሚያጋጥም አስታውሰው ከመስተዳደር አካላት ጋር በተከናወነ የትብብር ሥራ ባለፉት ሦስት ወራት ስርቆቱ የመቀነስ አዝማሚያ ማሳየቱን ገልፀዋል፡፡ ይሁንና በአሁኑ ወቅት ከመቱ - በደሌ እና መቱ -ጋምቤላ በተዘረጉ መስመሮች ላይ እየተፈፀመ ያለው ተደጋጋሚ ስርቆት መፍትሄ ባለማግኘቱ በኦፕሬሽን ሥራው ላይ ስጋት መደቀኑን ነው አቶ ጌታሁን የተናገሩት፡፡ እስከ አሁን በመስመሮቹ በስርቆት ምክንያት ኃይል ተቋርጦ እንደማያውቅ የጠቆሙት አቶ ጌታሁን በሁለቱ መስመሮች ላይ እየተፈጸመ ያለው ስርቆት በዚህ ከቀጠለ ግን ወደፊት ኃይል እስከማቋረጥ ሊያደርስ ይችላል ብለዋል፡፡ የታወር ስርቆት እና የወሰን ማስከበር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጥር  29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የአይ ሲ ቲ ድጋፎችን ወጥነት ባለው መልኩ ለመስጠት የሚያስችል ዘመናዊ አሰራር ተዘርግቷል .........///......... ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የሚቀርቡ የአይ ሲ ቲ ድጋፍ ጥያቄዎችን ወጥነት ባለው መልኩ ለማስተናገድ የሚያስችል ዘመናዊ መተግበሪያ መልማቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ አክሊሉ እንዳስታወቁት የሥራ ክፍሉ ሲስተሞችን ከማልማት አንስቶ ከአጠቃቀምና ከኔትወርክ ጋር የተያያዘ ድጋፍ ለሥራ ክፍሎች እየሰጠ ይገኛል፡፡ ድጋፍ የሚፈልጉ የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ ክፍሎች ጥያቄዎቻቸውን ወጥነት ባለው መልኩ እንዲያቀርቡ ለማድረግ እና ድጋፉንም ወጥነት ባለው መልኩ ለመስጠት "OS ticket" የተሰኘ መተግበሪያ መልማቱንም አስታውቀዋል። የተቋሙ ሠራተኞች ችግር ሲያጋጥማቸውና የባለሙያ ድጋፍ ሲፈልጉ በአካል፣ በስልክ እና በውስጥ ማስታወሻ ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ እንደነበር ያስታወሱት ዳይሬክተሩ አዲሱ መተግበሪያ ተጠቃሚው አካል ድጋፉን በሥራ ቦታው ሆኖ በቀላሉ ለማቅረብ የሚያስችለው ነው ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ብዙአየሁ ገለጻ አሰራሩ ምላሽ ያገኙና ያላገኙ የድጋፍ ጥያቄዎችን ለማወቅ፣ ድጋፍ የሚሰጠው ባለሙያ በአግባቡ እየሠራ መሆኑን ለመቆጣጠር እና ድጋፉ በአግባቡ መሰጠቱን ከተጠቃሚው በቀላሉ እርካታ ለመቀበል የሚያስችል ነው፡፡ በመምሪያው የሲስተም አድሚኒስትሬሽን ባለሙያ አቶ ፍቃዱ ቃበታ በበኩላቸው ሲስተሙ ተግባራዊ ሲደረግ የአይ ሲ ቲ ድጋፍ ጥያቄዎችን https://eepticket.eep.com.et/ በሚለው ሊንክ በመግባት ማቅረብ የሚችሉበት አሰራት መዘርጋቱን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሲስተሙ ተሞክሮ ውጤታማ እንደሆነና ስለ አጠቃቀሙ ለሠራተኞች ግንዛቤ ከተሰጠ በኋላ ወደ ትግባራ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ የአሰራር ስርዓቱን ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ባለሙያው አሰራሩ ሲተገበር የድጋፍ ፈላጊውን እንግልት ለመቀነስ እና ድጋፉን በወቅቱ ለመስጠት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡ በተቋሙ እየተካሄዱ ያሉ የዲጂታላይዜሽን ትግበራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ለሠራተኞች የተለያዩ የአቅም ማሳደጊያ ሥልጠናዎች እየተሰጡ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ በተቋሙ የተለያዩ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር በሚሰራው ሥራ ላይ በሥራ ክፍሉ ያሉ ባለሙያዎች የእርስ በርስ የመማማር ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱም ተገልጿል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 28 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌቲክስ ቡድን ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ .........///....... በ 53ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌቲክስ ቡድን በ 216 ነጥብ አጠቃላይ ውጤት ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። ከጥር 21-26 ቀን 2016 ዓ.ም ሲካሄድ በሰነበተው ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌቲክስ ቡድን በ360 ነጥብ አንደኛ፣ የመቻል አትሌቲክስ ቡድን ደህሞ 253 ነጥብ በማግኘት ሁለተኛ በመሆን የውድድሩ አሸናፊዎች ሆነዋል። በሻምፒዮናው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በሴቶች 10 ሺህ ሜትር፤ በሴቶች እና በወንዶች 400 ሜትር፤ በወንዶች እና በሴቶች 5 ሺህ ሜትር፤ በወንዶች 100 ሜትር እንዲሁም በሴቶች አራት በ 400 ሜትር ዱላ ቅብብሎሽ በድምሩ ሰባት የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘት ችሏል። በሴቶች 200 ሜትር፤ በወንዶች 100 ሜትር እንዲሁም በሴቶች የ400 ሜትር ሪሌ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሶስት የብር ሜዳሊያዎችን የግሉ አድርጓል። በተጨማሪም በከፍታ ዝላይ፤ በሴቶች 200 እና 100 ሜትር ፤ በስሉስ ዝላይ፣ በወንዶች 800 ሜትር፣ በወንዶች 110 ሜትር መሠናክል፤ በወንዶች 400 ሜትር ዱላ ቅብብሎሽ እና በወንዶች 10 ሺህ ሜትር በአጠቃላይ ስምንት የነሐስ ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ችሏል። በውድድሩ ከ1 ሺህ 100 በላይ አትሌቶች የተሳተፉ መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታውቋል። በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ትናንት በተከናወነው የመዝጊያ መርሐግብር የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፤ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ጣቢያው ባለፉት 6 ወራት ከ238 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማመንጨት ችሏል .........///.......... የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት 6 ወራት 238 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ተረፈ ሞገስ እንደገለፁት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ በኦፕሬሽን፣ በጥገና እና በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። ጣቢያው በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ለማመንጨት ካቀደው 354 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 238 ነጥብ 58 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 67 ነጥብ 2 በመቶ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ47 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ያነሰ መሆኑንም ነው አቶ ተረፈ የጠቀሱት። ባለፉት 6 ወራት ለበርካታ ቀናት ውሃ የመልቀቅ ሥራዎች በመሰራታቸው፣ ከባለፈው ዓመት በተለየ የማመንጫ ተርባይኖች ላይ ተደጋጋሚ ብልሽቶች በማጋጠማቸው እንዲሁም የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት በአፈፃፀሙ ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን ተናግረዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት የተበላሹ የኃይል ማመንጫ ተርባይኖችን  በመጠገን  ወደ ሥራ ለማስገባት  የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በቀጣይ 6 ወራትም የታቀደውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በትኩረት እንደሚሰራ ነው አቶ ተረፈ ያስታወቁት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የመድን ህንጎችን አተገባበር ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ………///……….. የመድን ህጎችን በአግባቡ ለመተግበር የግንዛቤ ሥራዎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ በኢንሹራንስ ህጎችናአተገባበር ላይ የተሰጠው ሥልጠና የተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያ መድን ድርጅት አዘጋጅነት በኢንሹራንስ ህጎችና አተገባበራቸው ላይ በማተኮር ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ለሁለት ሳምንት የተሰጠው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ በስልጠናው ላይ ከተሳተፉት መካከል የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል ማመንጫ ሥራ አሰኪያጅ አቶ ከማል አህመድ እንደተናገሩት ስልጠናው የኢንሹራንስ ህጎችንና አተገባበራቸውን ፣ኢንሹራንስ የተገባባቸውንና ያልተገባባቸውን የኢንሹራነስ ዓይነቶችን ለይቶ ለማወቅና ለመተግበር ያግዛል፡፡ በንብረት አስተዳደርና ጥገና መምሪያ የንብረት ሪስክና ኢንሹራንስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳህሌ ደግፍ በበኩላቸው ሥልጠናው በኢንሹራንስ ህጎችና አተገባበራቸው ዙሪያ ቴክኒካዊና ህጋዊ አካሄዶችን ለይቶ ለማወቅ እንዳስቻላቸው ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በመድን ዋስትና ላይ አብረውት ከሚሰሩ ድርጅቶች ጋር በመድን ዋስትና አፈፃፀም ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ያዘጋጀው ሥልጠና ለሁለቱም ተቋማት ጠቃሚ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተሳታፊዎቹ አሳስበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 25 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በምጣኔ ሀብትና በዲፕሎማሲ መስክ ለተመዘገቡ ውጤቶች የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) .........///........ በ2016 በጀት የመጀመሪያ ስድስት ወራት እንደ ሀገር በምጣኔ ሀብትና ዲፕሎማሲ መስክ ለተመዘገቡ ውጤቶች የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረጉን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የ2016 የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ተቋማት የጋራ ጉባዔውን በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው። በመድረኩ ባለፉት ስድስት ወራት በሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በጋራ እየተገመገመ ነው። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር  ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) መድረኩን ሲከፍቱ እንደገለጹት የበጀት ዓመቱ የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ በተደራጀ መንገድ ወደ ሥራ የገባበት ነው። ባለፉት ስድስት ወራት መንግሥት ትኩረት ባደረገባቸው የምጣኔ ሀብት ምሶሶዎች በርካታ አመርቂ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። የሕግ የበላይነትና መልካም አስተዳደር በማስፈን፣ አዎንታዊና ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ እንዲሁም በዲፕሎማሲና ሌሎች ዘርፎችም አበረታች ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል። በእነዚህ ዘርፎች እንደ ሀገር ለተመዘገቡ ውጤቶች የሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ዘርፉ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል ነው ያሉት።  ያም ሆኖ የሐሰተኛ መረጃዎችን ጨምሮ ሌሎች ተግዳሮቶችም እንደነበሩ ጠቅሰው በቀጣይ የተሻለ ለመሥራት መረባረብ እንደሚጠይቅ ማስገንዘበቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ጥር  24 ቀን 2016 ዓ.ም