uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 545 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 351-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 178-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 545 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.76% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.84% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 005 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 463 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 545
Obunachilar
+824 soatlar
-227 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
photo content

የሰንደቅ ዓላማ ቀን ሲከበር ሁሉም ሠራተኛ መደበኛ ሥራቸውን በብቃት በመወጣት ሊሆን ይገባል ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ሲያከብሩ መደበኛ ሥራቸውን በብቃት በመፈፀም መሆን እንዳለበት የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኽኝ አሳሰቡ፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች 15ኛውን ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ሰንደቅ ዓላማችን የብዝኃነታችን መገለጫ፣የሉዐላዊነታችን ምሰሶ ነው በሚል መሪ ቃል በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት አክብረዋል፡፡ በበዓሉ ላይ አቶ ሙላት ገዛኽኝ እንደተናገሩት ሀገራችን በውስጥ ባንዳዎችና በውጭ ኃይሎች የእጅ አዙር ጦርነት ውስጥ በገባችበትና ይህን የውክልና ጦርነት በመቀልበስ ህልውናዋን ለማረጋገጥ በምታደርገው የመጨረሻ ምዕራፍ ትግል ላይ መከበሩ ልዩ ያደርገዋል፡፡ ዛሬ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዓሉን ለማክበር የታደለው ሀገራችን በመኖሯ ነው ያሉት ኃላፊው ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን እና ሌሎች የፀጥታ ኃይሎች እየከፈሉት ላለው አገር የማዳን ተጋድሎ ትልቅ ክብርና ምስጋና ያስፈልጋቸዋል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሁሉም ሠራተኛ ለሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ፈጣን ምላሽ በመሥጠት የሀገሩን ሉዐላነት በንቃት መጠበቅ እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በመላው ሀገሪቱ በተለያዩ ዝግጅቶች ለ15ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+4

የተሰረቁ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችና ብረታ ብረቶች በጭነት መኪና ያጓጓዙ ተጠርጣሪዎች ተያዙ ………./////……… የተሰረቁ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ብረታ ብረቶችና ሽቦዎችን በጭነት መኪና ሲያጓጉዙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በደሴ ጢጣ ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ ተያዙ፡፡ ከወልድያ እንደተነሳ የተገመተው የጭነት መኪና ጢጣ ኬላ ላይ በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ተይዞ ሲፈተሽ የተለያዩ የታወር አካላት የሆኑ ብረቶች፣ ሳይላ ካቦና ብሎኖች ተገኝተውበታል፡፡ የጭነት መኪናው ከፊትም ከኋላም ሰሌዳ ያልለጠፈ ሲሆን አሽከርካሪውም በወቅቱ ሲያዝ ምንም ዓይነት መንጃ ፈቃድ እንዳልነበረው ታውቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ደሴ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ ተደርጎ ምርመራ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መምሪያ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ ገልፀውልናል፡፡ በወልዲያ - ኮምቦልቻ መስመር ተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት እያጋጠመ ሲሆን በቅርቡም በመርሳ ከተማ ቀበሌ 01 እና በሀርቡ ወረዳ ጃሜ መንደር ውስጥ ሥርቆት መፈፀሙን የባህር ዳር - ወልዲያ -ኮምቦልቻ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሪፖርት ይጠቁማል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

ባለሙያዎች በሕግ አግባብ በመሥራት የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ እንዲሰሩ ተጠየቀ ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሕግ ባለሙያዎች የተጀመሩ ክርክሮች በህግ አግባብ እልባት እንዲያገኙ በመሥራት የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ በትኩረት እንዲሰሩ የተቋሙ የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አሳሰቡ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ መርክነህ ይገዙ በመምሪያው በሥራ ላይ ለሚገኙና ተቋሙን ለተቀላቀሉ አዳዲስ የሕግ ባለሙያዎች በተዘጋጀው እና በህግ እና የቡድን ሥራ ግንባታ ላይ ባተኮረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ላይ እንደገለፁት የተቋሙን ጥቅም ለማስከበር በውል አስተዳደር ላይ አመርቂ ሥራ ተሰርቷል፡፡ ይሁንና ባለሙያዎች በተቋሙ ላይ የሚነሱ ክርክሮችን በብቃት ለመመለስ እንዲያስችላቸው በሕግና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉ መዝገቦችን በመዳሰስና በመመርመር አቅማቸውን የበለጠ ማጎልበት እንዳለባቸው ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡ በፕሮጀክቶች ላይ ከተቋራጮች ጋር በሚኖሩ ውሎች እና ከካሳ ክፍያ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በርካታ መዝገቦች መኖራቸውን የጠቀሱት አቶ መርክነህ ፋይሎችን በጥንቃቄ በመመርመር ሕግና መመሪያን ተከትሎ በመስራት የተቋሙን ጥቅምን ማስከበር ይገባል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የሕግ ባለሙያዎች የሚቀርቡላቸውን ጉዳዮችን በንቃት በመከታተል የቅድመ መከላከል ሥራ ለመሥራት ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ውጤታማ ሥራዎችን ለማከናወን የቡድን ግንባታ ሥራ ወሳኝ በመሆኑ ባለሙያዎች ሥራቸውን በጋራ በማከናወን ለራሳቸው እርካታ፣ ለተቋማቸው ብሎም ለሀገራቸው በትብብር መንፈስ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል፡፡ የቡድን ግንባታ ሥራን ለማጎልበት መልካም ትብብርና ተግባቦት ወሳኝ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ ሁሉም ባለሙያ ከሌሎችባለሙያዎች ጋር የሚኖረውን ተግባቦት ማሻሻልና ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በበጀት ዓመቱ ሦስት ወራት 411 ጊጋ ዋት ሰዓት አመንጭቷል ……….//////………. በ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ከመነጨው አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 10 በመቶ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ በጽ/ቤቱ የዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሺፈራው እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከመነጨው 4 ሺህ 98 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ውስጥ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 411 ጊጋ ዋት ሰዓት አመንጭቷል፡፡ በቅርቡ ኃይል ማመንጫት የጀመሩት የግድቡ ሁለት ዩኒቶች እያንዳንዳቸው ኃይል 375 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን በጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ብቻ 411 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማመንጨት ወደ ብሔራዊ ኃይል ቋት ማስገባት መቻላቸውን ሥራ አስኪያጇ ገልፀዋል። ኃይል ማምረት ከጀመሩት ሁለት ዩኒቶች መካከል ዩኒት 9 በየካቲተ 2014 ዓ.ም፤ ዩኒት 10 ደግሞ በነሀሴ 2014 ዓ.ም. በይፋ ኃይል ማመንጨት መጀመራቸው ይታወሳል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ከፍታው ከመሬት 145 ሜትር፣ ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ የዋናው ግድብ መደረት የግርጌ ውፍረት 130 ሜትር፥ የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦትን በማሳደግ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ውህደት እውን እንዲሆን እየሰራች ነው ……….//////……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅሙንና ተደራሽነቱን ለማሳደግ እና በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ውህደት እውን እንዲሆን እየሰራ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተናገሩ፡፡ ከምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት አባል ሀገራት የተወጣጡ ከፍተኛ የኢነርጂ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች የተሳተፉበትን መድረክ ሲከፍቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነት ሽፋኗን ለማሳደግ እየሰራች ነው፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና የማስተላለፊያ መስመሮችን በማስፋፋት በ2025 የኤሌክትሪክ ሽፋኑን መቶ በመቶ ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቀጣናው የኃይል አቅርቦት እጥረትን በማስወገድ ክፍለ አህጉራዊ ውህደት እውን እንዲሆን እየሰራች መሆኗን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከሱዳን እና ከጅቡቲ የኃይል ትስስር መፈጠሩን እንዲሁም በቅርቡ ከኬንያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በቀጣይም ከተቀሩት የቀጣናው ሀገራት ጋር የኃይል ትስስሩን ለማስፋት የሚያስችሉ ሥራዎችን በመሥራት ለምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ዓላማ መሳካት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ዋና ፀሐፊ ኢንጂነር ሌቢ ቻንጉላ በበኩላቸው ቀጠናዊ የኃይል ትስስሩ ከተመሰረተ የቆየ ቢሆንም አባል ሀገራቱ በኃይል ማመንጨት፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ በሚፈለገው ደረጃ አለመጓዛቸው ትግበራውን በሚፈለገው መጠን እንዳላፋጠነው ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ኢትዮጵያ ከጅቡቲ እና ከሱዳን ጋር የጀመረችው እና በቅርቡም ከኬንያ ጋር የምታደረገው የኃይል ትስስር እንዲሁም ኬንያ- ታንዛኒያ-ዛምቢያ እና ኬንያ-ዑጋንዳ-ሩዋንዳ-ቡሩንዲ የሚያደረጉት የኃይል ትስስር ፕሮጀክት በቀጣናዊ የኃይል ትስስር የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ አበረታች ስራዎች ማሳያ ናቸው ብለዋል ፡፡ በዚህም የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ቀጣናዊ ትስስር ሀገራቱን በማማከር እና አቅጣጫ በመስጠት ሚና እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ በመድረኩ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን ጨምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የልህቀት ማዕከል፣ አዲሱ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል እና የዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ የዲዛይን ሀሳቦች ዙሪያ ለመድረኩ ታዳሚዎች ገለፃ ተሰጥቷል፡፡ ተሳታፊዎቹ በቅርቡ የተመረቀውን ብሑራዊ የሳይንስ ሙዚየም ጎብኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

የተቋሙ የስድስት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ከኦዲት ግኝት ትችት ነፃ ሆኗል ……..//////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ2008 እስከ 2013 ዓ.ም ያለው የሂሳብ ሪፖርቱ በውጪ ኦዲተሮች ተመርምሮ ከኦዲት ትችት ነፃ መሆኑ ተገለፀ፡፡ የአይ ኤፍ አር ኤስ ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪጅ አቶ ሕሊና ገዛኸኝ እንደገለጹት በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ሥርዓት (IFRS) የተሠራው የተቋሙ የሂሳብ ሪፖርት የ IFRS ስታንዳርዶች፣ IFRSን በሀገሪቱ ለመተግበር በወጡ አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች እንዲሁም የሀገሪቱ የአይ ኤፍ አር ኤስ የሂሳብ አያያዝ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ በተቀመጡ መመዘኛዎች በውጪ ኦዲተሮች ተመዝኖ ከኦዲት ትችት ነፃ ሆኗል፡፡ የተቋሙ የሂሳብ ሪፖርት በኢትዮጵያ የኦዲት አገልግሎት ኮርፖሬሽን ተመዝኖና ተመርምሮ በአይ ኤፍ አር ኤስ ስታንዳርድ መሰረት መሠራቱን እና ከኦዲት ግኝት ነጻ መሆኑን የሚገልጽ ማረጋገጫ እንደተሰጠውም አስታውቀዋል፡፡ በኦዲት ሥራ ሂደት ከሁሉም ነገሮች ነፃ የሆነ (unqualified clean report)፣ በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ግኝት ያለበት (qualified)፣ ድርጅቱ ሂሳቡን ቢሰራም የተቀመጠውን ስታንዳርድ በግልጽ የማያሳይ (disclaimer) ወይም ከተቀመጠው ስታንዳርድና መርህ ውጭ ተሰርቷል (adverse) የሚባሉ የኦዲት ሪፖርት ደረጃዎች እንዳሉ ያስረዱት አቶ ሕሊና ተቋሙ ከሁሉም ትችት ነፃ የሆነ የኦዲት ሪፖርት ደረጃ ማግኘቱን አመልክተዋል፡፡ ሪፖርቱ ተቋሙ እያካሄዳቸው ያሉ ሥራዎችን፣ እየሰጣቸው ያሉ አገልግሎቶችን፣ ያለውን ንብረት እና ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች በተቋሙ ላይ ፍላጎት ላላቸው አካላት በማሳወቅ ግልጽነቱንና ተጠያቂነቱን ለማሳየት እንዲሁም ለመንግስት የረጅም ጊዜ ዕቅድ በግብዓትነት እንደሚያግዝ አቶ ሕሊና ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ከዚህ በፊት ሪፖርቱን GAP በተባለ ሲስተም ሲያከናውን ከኦዲት ትችት ነፃ የሆነ አስተያየት ቢሰጠውም በሪፖርቱ ለተቋሙ ከፍተኛ አመራር መስተካከል አለባቸው የሚባሉ ጉዳዮች እየተጠቀሱ (with management letter) ሲሰጥ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የተሰጠው ከኦዲት ግኝት ትችት ነጻ የሆነና መሻሻል አለባቸው የሚባሉ ጉዳዮችና አስተያየቶች ያልተካተቱበት (without management letter) እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ሪፖርቱ ከኋላ ያሉ መረጃዎችን በማጥራት እና የIFRS አሰራር መርህን መሰረት አድርጎ በመሰራቱ በምዘናው ላይ ችግር እንዳላጋጠመም ነው የተናገሩት፡፡ የንብረት ክለሳና IFRS ሪፖርቲንግ ፕሮግራም መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ይርጉ ኃይሉ በበኩላቸው በIFRS መመዘኛ መሰረት የተሰራዉ የሂሳብ ሪፖርት በውጪ ኦዲተሮች እንዲረጋገጥ ቀርቦና ተፈትሾ በተቀመጡ ስታንዳርዶች መሰረት መሰራቱ በመረጋገጡ ከኦዲት ትችት ነፃ መሆኑን ማረጋገጫ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ የስድስት ዓመት የሂሳብ ሪፖርት ከኦዲት ግኝት ነፃ መሆኑ ተቋሙ ከሌሎች ተመሳሳይ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ተወዳዳሪ ለመሆን እና ያለውን ንብረት በማስያዝ የፋይናንስ ምንጭ የሚያገኝበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አቶ ይርጉ ተናግረዋል፡፡ አቶ ይርጉ እንዳሉት ሪፖርቱ ተቋሙ ራሱን የፈተሸበትና ኢንቨስተሮች፣ አበዳሪዎችና ተጠቃሚዎች በተቋሙ ላይ የመተማመን ሁኔታ እንዲኖራቸው እና በተቋሙ ያሉ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ ለማድረግ ዕድል ይፈጥራል፡፡ የስድስት ዓመቱ የሂሳብ ሪፖርት በIFRS ሲሰራ ረጅም ሂደቶችና ውጣ ውረዶች እንደነበሩት ያነሱት ኃላፊዎቹ በሂደቱ ውስጥ ያሉ ጫናዎችን በመቋቋምና ሠራተኛውን በማስተባበር ከዚህ በፊት የነበረውን ወደ ኋላ በመመለስ በአንድ ዓመት ውስጥ የሦስት ዓመት የኦዲት ሪፖርት መስራት ተችሏል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ተቋሙ ከኦዲት ግኝት ትችት ነፃ እንዲሆን የሁሉም ሠራተኛና የሥራ መሪዎች አስተዋጽዖ እንደነበረው ያነሱት ኃላፊዎቹ ይህንን ለማስቀጠል ሁሉም ሠራተኛና የሥራ መሪ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 02 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የሐረር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ አቅም ተፈጥሮለታል ……./////……. በሐረር ቁጥር 3 የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ የከተማውንና በዙሪያው ያሉ ከተሞችን የኃይል አቅርቦት እንዳስተካከለ የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ፡፡ ኃላፊው አቶ ቴዎድሮስ ታመነ እንዳስታወቁት አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት ኤምፒር አቅም የነበረው የሐረር ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ማሟላት አልቻለም ነበር፡፡ ይህንን ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት 50 ሜጋ ቮልት ኤምፒር አቅም ያለው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር በማስመጣት የማስፋፊያ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ በተከናወነው የማስፋፊያ ሥራም የሐረር እና አካባቢው ህዝብ እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች በቂ ኃይል እየቀረበላቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለሐረር እና አወዳይ ከተሞች ኃይል የሚያቀርቡ ባለ 33 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው አራት ወጪ መስመሮች እንዲሁም ለፊቅና ጂግጂጋ ከተሞች ባለ 132 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ የሐረር ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለምሥራቁ የሀገሪቱ ክፍል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የገለፁት ኃላፊው ለሐሮማያና ሐረር ከተሞች 66 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው ተጨማሪ ሁለት መስመሮች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች አዲስ ሰራተኞችን ለመቅጠር ሐምሌ 28 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ / የፅሁፍ ፈተና የሚሰጥ ስለለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን ፡፡

ለጎረቤት ሀገራት ከ13 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚገመት የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተከናውኗል ……..////……… በተያዘው በጀት ዓመት ሁለት ወራት ለሱዳንና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል ከ13 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ሽያጭ መከናወኑን በማርኬቲንግና ቢዝነስ ዲቨሎፕመንት መምሪያ የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ምኒሊክ ጌታሁን እንደገለጹት ባለፉት ሁለት ወራት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ከ349 ነጥብ 56 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ከ18 ነጥብ 55 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ሽያጭ ለማከናወን ታቅዶ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሁለቱ ወራት 232 ነጥብ 76 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የ13 ነጥብ 04 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሽያጭ በማከናወን የዕቅዱን 70 ነጥብ 29 በመቶ ብቻ ነው ማሳካት የተቻለው፡፡ እንደ አቶ ምኒሊክ ገለጻ በሁለቱ ወራት ለሱዳን 112 ነጥብ 36 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል በማቅረብ የ5 ነጥብ 61 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጅቡቲ 120 ነጥብ 39 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የ7 ነጥብ 42 ሚሊዮን ዶላር ሽያጭ ተከናውኗል፡፡ ለጅቡቲ ለማቅረብ በዕቅድ ከተያዘው ኃይል የ12 ነጥብ 29 በመቶ ብልጫ ያለው ኃይል የቀረበ ሲሆን ለሱዳን ደግሞ የዕቅዱን 46 ነጥብ 36 በመቶ ብቻ መሸጥ እንደተቻለ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የተከናወነው ሽያጭ ከዕቅዱ አንጻር ሲታይ የ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወይም የ29 ነጥብ 71 ቅናሽ ያለዉ ሲሆን የተሸጠው ኃይል ደግሞ ከዕቅዱ 116 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ወይም የ33 ነጥብ 42 በመቶ ቅናሽ ያለው ነው፡፡ ምንም እንኳን ለሁለቱ ሀገራት የተከናወነው ሽያጭ በጥቅል ሲታይ ከዕቅዱ በታች ቢሆንም ከጅቡቲ የተገኘው ገቢ ግን ከዕቅዱ የ15 ነጥብ 38 በመቶ ብልጫ ያሳየ ነበር፡፡ ከሱዳን ይገኛል ተብሎ ታቅዶ የነበረውን ሽያጭ ማሳካት ያልተቻለው በሁለቱ ወራት የሱዳን የኤሌክትሪክ ኩባንያ ኃይል የመግዛት ፍላጎቱ በመቀነሱ እንደሆነ አቶ ምኒሊክ አስታውቀዋል፡፡ በሁለቱ ወራት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ ከተገኘው ገቢ በተጨማሪ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር በላይ መገኘቱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም

1538155948.webp0.19 KB