uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 534 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 338-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 162-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 534 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 6 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.10% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.85% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 901 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 619 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 534
Obunachilar
-124 soatlar
-167 kunlar
+630 kunlar
Postlar arxiv
ፕሮጀክቶችን የማማከር አቅም እያደገ መጥቷል ……..///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በራስ ኃይል የማማከር አቅም እያደገ መምጣቱን በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የበቆጂ የፕሮጀክት የሳይት ሱፐርቫይዘር ሲሳይ አዱኛ እንዳስታወቁት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በቆጂ ከተማ እየተገነባ ያለውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማማከርና ቁጥጥር ስራዎች በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ በኩል እየተከናወነ ነው፡፡ በኢንጂነሪንግ ዘርፍ ከአፈር ምርመራ ጀምሮ የቁፋሮ፣ የዲዛይን፣ የግንባታ ስራዎች እንዲሁም ኮንትራክተሩ በተቀመጠለት ጊዜና የጥራት ደረጃ ስለመከናወኑ ቁጥጥር የሚደረግበት ዘርፍ መሆኑን ሱፐርቫይዘሩ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በበቆጂ ባለ 230 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በራስ አቅም የማማከር፣ የዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች ማከናወኑ ለውጭ ኮንትራክተሮች ሊያውጣ የሚችለውን የውጭ ምንዛሬ ከማስቀረቱ በተጨማሪ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ መርሃ ግብርና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ የሚያስችል መሆኑን ሱፐርቫይዘሩ አስረድተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ ጠቅልል አበሻ በበኩላቸው እስካሁን የአንከር ቦልት እና የትራንስፎርመር ሀዲድ ግንባታዎች የተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ጣበያው ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ሁለት ትራንስፎርመሮች፣ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና 10 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ይኖሩታል፡፡ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከበቆጂ ከተማ በ100 ኪሎ ሜትር ዙሪያ መለስ ያሉ አካባቢዎች በቂና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለው የበቆጂ ባለ 230 ኪቮ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 216 ሚሊየን ብር ለፕሮጀክቱ ግንባታ በጀት ተመድቦለታል፡፡ የግንባታ ስራው በተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ የሚከናወን ሲሆን የተቋሙ ኢንጂነሪንግ ዘርፍ ደግሞ በአማካሪነት እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ የተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ በርካታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን የማማከር ሰፊ ልምድ ያለው ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ የማማከር ሥራ እየሰራ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል በሚደረገው ዘመቻ ዘርፈ ብዙ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ……////…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚደረገው ዘመቻ ዘርፈ ብዙ ምላሽ እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ߵߵየማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይ ቪ መከላከልߴߴ በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የፀረ ኤድስ ቀን ዛሬ በውይይትና በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀግብር አክብረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ቀኑን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር እንደገለፁት የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት በአብዛኛው የሚታየው በአምራቹ የህብረተሰብ ክፍል ላይ በመሆኑ የሀገርን ኢኮኖሚ በእጅጉ ይጎዳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ የሆኑ ፕሮጀክቶችን የሚያከናውንና በዘርፉ በርካታ የሰው ኃይል የያዘ ተቋም በመሆኑ የጤና ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር እንደሆነ ኃላፊው ጠቅሰዋል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛ ለተላላፊ እና ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች ተጋላጭ እንዳይሆን ጥንቃቄ በማድረግ የራሱንና የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ ማሳካት እንደሚኖርበት አሳስበዋል፡፡ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት፣ የስኳርና የሆርሞን ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ረድኤት አምባቸው በበኩላቸው እንደስኳር፣ ደም ግፊት እና ካንሰር ያሉት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች አሳሳቢነታቸው እየጨመረ የመጡ የጤና ችግሮች መሆናቸውን ገልጸዋል። እንደ ረዳት ፕሮፌሰሯ ገለፃ በቅርብ በተደረገ ጥናት በዓለም 537 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ ከስኳር በሽታ ጋር ሲኖር 6 ነጥብ 7 ሚሊየን ህዝብ ደግሞ በስኳርና ተያያዥ በሽታዎች ለሞት ተዳርጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ከአስሩ ሰው አንዱ ስኳር እንዳለበት ሲገመት ከሁለት የስኳር ታማሚዎች አንዱ ደግሞ ስኳር እንዳለበት እንኳን አለማወቁ የችግሩን አሳሳቢነት እንዲጨምር ማድረጉን ነው ረዳት ፕሮፌሰሯ የተናገሩት።  እንቅስቃሴ አልባ የአኗኗር ዘይቤ ለበሽታዎች መጨመር ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ያሉት ረዳት ፕሮፌሰር ረድኤት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የታሸጉ ምግቦችን አለማዘውተር እና በየጊዜው የቅድመ ምርመራና ጤና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ መክረዋል፡፡ በተቋሙ የጤና አገልግሎት የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከል አስተባባሪ አቶ አለምሰገድ ባስሊዮስ በበኩላቸው የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመቀነስ በሚደረገው ሁሉን አቀፍ ዘመቻ ተቋሙ የበኩልን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች በኤች አይ ቪ ኤድስ ወላጆቻቸውን ላጡ ህጻናት የሚያደርጉት የገንዘብና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተቋሙ ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚደረገው ዘመቻ የሚሰጠው ምላሽ አንዱ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ37ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ36ኛ ጊዜ ߵߵየማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይ ቪ መከላከልߴߴ በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ከተላላፊ እና ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች ስርጭት ጋር የተያያዙ የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ውይይት አድርገዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች የኦፕሬሽን ሥራዎችን አስተማማኝነት እያሳደጉ ይገኛሉ ………///………. በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚከናወነው የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ የኃይል ማመንጨት ሥራውን አስተማማኝ እንዲሆን እያገደረገ መሆኑን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የቴክኒክ ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ባይለየኝ እንዳስታወቁት መምሪያው በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን፣ የጥገና፣ የመልሶ ግንባታ እና የማዘመን ሥራዎች ሲከናወኑ የቴክኒክ ድጋፎችን ያደርጋል፡፡ መምሪያው የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽንና የጥገና አስተዳደርን የሚያዘምኑ፤ የግድብ ደህንነትን የሚያረጋግጡ፤ የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦትን የሚያቀላጥፉ፤ የውል አስተዳደርን የሚያሻሽሉ፤ የተለያዩ የጥገና እና ሌሎች በርካታ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሆነ አቶ ዘላለም ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የቴክኒክ ድጋፍ የሚፈልጉ ዝርዝር ሥራዎችን ለይቶ መመሪያ በማዘጋጀት እና በማስፀደቅ እንዲሁም ዝርዝር የአሰራር ሥርዓት በመዘረጋት የኦፕሬሽን ሥራውን እየደገፈ ይገኛል፡፡ የቴክኒካል ድጋፍ ሥራው የኦፕሬሽን ሥራዎች በተቀመጠላቸው የአሰራር ስርዓት መሠረት እንዲከናወን በማድረግ ኃይል የማመንጨት ሥራው ያለችግር እንዲከናወን እያደረገ እንደሚገኝ ነው አቶ ዘላለም የተናገሩት፡፡ ድጋፉ ለጥገና ሥራ የሚያስፈልጉ የመለዋወጫ ዕቃዎች እና ሌሎች ግብአቶች እንዲሟሉ በማድረግ የጥገና ሥራዎች በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት እንዲከናወኑ እያገዘ መሆኑንም ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች በዓለምአቀፍ የአሰራር ስርዓት ጥራት መስፈርት መሰረት መከናወናቸውን በማረጋገጥ፣ በመደገፍ እና በመከታተል የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችንና ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሚረዳ አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ዘላለም ገለጻ እየተከናወነ ያለው የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ የባለሙያዎችን ዕውቀትን በማሳደግ፣ ወጪን በመቀነስና የኃይል መቆራረጥን በማስቀረት ለተቋሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ የጥገና አስተዳደሩን በዘመነ የቴክኖሎጂ ስርዓት እንዲመራ ለማድረግ ዝግጅት መጀመሩንና ከሌሎች ዓለምአቀፍ ተቋማት የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲኖር ለማስቻል ዝርዝር የስልጠና ፍላጎት የያዘ ሰነድ በመዘጋጀት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 17ቀን 2016 ዓ.ም

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደቡ መጠሪያ፤- ቻይልድ ኬር አድሚኒስትሬቲቭ አሲስታንት 1ኛ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ኮሌጅ ዲፕሎማ ወይም 10+3 ወይም በደረጃ IV) በመምህርነት፣ በማኔጅመንት፣ በሰው ሀብት አስተዳደር እና በማርኬቲንግ የትምህርት ዘርፍ ያጠናቀቀች፤ ሲኦሲ ሰርተፊኬት ያላት ሆኖ የልጆች እንክብካቤና አያያዝ ስልጠና ሰርተፊኬት ያላት ቢሆን ይመረጣል፡፡ (የስራ ልምድ አይጠይቅም) ወይም ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ 12/10ኛ ክፍል ያጠናቀቀች 6 ዓመት በልጆች አያያዝ ወይም በልጆች ማቆያ የስራች ሆኖ የልጆች እንክብካቤና አያያዝ ስልጠና ሰርተፊኬት ያላት ቢሆን ይመረጣል፡፡ የሥራ ደረጃ፡ ጂ1 ደመወዝ ፡ 5,237.00 (አምስት ሺ ሁለት መቶ ሰላሳ ሰባት ብር) ብዛት፡ እንደ አስፈላጊነቱ የሥራ ቦታ ፡ በተቋሙ ዋና መ/ቤት የቅጥር ሁኔታ፡ ቋሚ ጾታ ፡ ሴት ማሳሰቢያ ፡- • የመመዝገቢያ ቀን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡ • ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች የትምህርት እና የሥራ ማስረጃ ኮፒ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት የሠራተኛ ቅጥርና ምደባ ቢሮ በአካል በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ መሪነቱን የሚያጠናክር ድል አስመዘገበ ........///........ በስምንተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የኦሮሚያ ፖሊስን 2ለ1 በማሸነፍ መሪነቱን አስቀጥሏል። ጨዋታው በተጀመረ በሶስተኛው ደቂቃ ጎል ያስተናገደው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በጎሉ ሳይደናገጥ ተረጋግቶ በመጫወት በ16ኛው ደቂቃ በአጥቂው አቤል ሀብታሙ አማካኝነት የአቻነት ጎል ማስቆጠር ችሏል። በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጠንካራ ፉክክር በታየበት በዚህ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ይበልጥ ተጭኖ በመጫወት ከዕረፍት በፊት በ28ኛው ደቂቃ የማሸነፊያዋን ሁለተኛ ጎል በቢኒያም ካሳሁን አማካኝነት በተቃራኒው ቡድን መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል። የኦሮሚያ ፖሊስ ቡድን ረጃጅም እና ኃይል የተቀላቀለበት አጨዋወት ይዞ በመግባት ለማሸነፍ አልያም ነጥብ ተጋርቶ ለመውጣት ቢሞክርም ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአጭር ቅብብል እና በፈጣን የማጥቃት እንቅስቃሴ ጨዋታውን በመቆጣጠር ሦስት ነጥብ ይዞ ለመውጣት ችሏል። ከተጀመረ ሁለት ወራትን ባስቆጠረው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሀግብር ኢትዮ -ኤሌክትሪክ ካከናወናቸው ስምንት ጨዋታዎች ስድስቱን አሸንፎ፣ በሁለቱ ተሸንፎ በ18 ነጥብ እና በሰባት ንፁህ ጎል ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመጪው እሁድ ታህሳስ 21 ቀን 2016 ዓ.ም.  ከይርጋጨፌ እግር ኳስ ክለብ ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ዘጠነኛ ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ታህሳስ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የኢትዮ - ታንዛኒያ የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ሊፈረም ነው ........///…….... በኢትዮጵያ እና በታንዛኒያ መካከል የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን በቅርቡ ሥምምነት እንደሚፈረም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንደገለፁት ከኢትዮጵያ፣ ኬኒያ እና ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የሦስትዮሽ ውይይት በናይኖቢ አካሂደዋል። ውይይቱም በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የህግ ማዕቀፎች፣ የኃይል ሽያጭ እና ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተናግረዋል። በኢትዮጵያ እና በታንዛኒያ መካከል የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ለማድረግ ተደጋጋሚ ድርድሮች ሲካሔዱ መቆየታቸውን ነው አቶ ህይወት ያስታወሱት። በኬኒያ በተደረገው የሦስትዮሽ ውይይት በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከሥምምነት መደረሱን የገለፁት ዳይሬክተሩ አንድ የማጠቃለያ ውይይት ከተደረገ በኋላ የፊርማ ሥምምነቱ እንደሚካሄድ ጠቁመዋል። እንደ አቶ ህይወት ገለፃ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተካሔደ ያለው ድርድር የኬኒያን ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠቀም የሚከናወን በመሆኑ ከባለፉት የኃይል ሽያጭ ሥምምነቶች ለየት ያደርገዋል። ከኃይል ሽያጭ ድርድሩ ጎን ለጎን በኬኒያው የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ኩባንያ (ኬትራኮ) እና በታንዛኒያው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ኩባንያ (ታኒስኮ) መካከል የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኪራይ ሥምምነት ለማካሄድ ውይይቶች በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል። የኃይል ሽያጭ እና የማስተላለፊያ መስመር ኪራይን አስመልክቶ በሦስቱ ሀገራት መካከል ሥምምነት (EKT Interconnection Agreement ) መፈፀሙን የጠቀሱት አቶ ህይወት ሥምምነቶቹ ወደፊት ከኤሌክትሪክ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት እንደሚያግዝም አስታውቀዋል። የኬኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ኩባንያ (ኬትራኮ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶ/ር ኢንጂነር ጆን ማቲቮ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እንደገለፁት የሦስቱ ሀገራት ውይይት ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስሩን እውን ለማድረግ ማሳያ ነው። ከሦስቱ ሀገራት የተውጣጡት ባለሙያዎች በኬኒያ ድንበር ላይ የሚገኘውን የኢስኒያን ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝተዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ቀጣይ ለሚደረገው የኃይል ሽያጭ ሥምምነት ዝግጁ መሆኑንም በጉብኝቱ ወቅት መታዘባቸውን ተናግረዋል። የኢትዮ- ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሥምምነት የሚፈረም ከሆነ የኬኒያን ግሪድ በመጠቀም የኢትዮ-ኬኒያ- ታንዛኒያ የኃይል ትስስር እንደሚፈጠር ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

ፕሮጀክቱ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል ………..///………. የበቆጂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክቱ የሳይት አስተባባሪና ተቀጣሪዎች ተናገሩ፡፡ አስተባባሪው አቶ እንዳልካቸው ጃንቦ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በጥበቃ፣ በፅዳትና በተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ለ87 ወንዶችና ለ29 ሴቶች ጊዚያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ፕሮጀክቱ ከተጠናቀቀ በኋላም እስከ 30 ለሚደርሱ ወጣቶች ቋሚ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አስተባባሪው ጠቁመዋል፡፡ በበቆጂ ከተማ ዙሪያ ነዋሪ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጋዲሳ ለብዙ ዓመታት ሥራ ፍለጋ አብዛኛውን የሀገሪቱ ክፍል ሲያዳርሱ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ የሚያገኙት ገቢ ከራሳቸው ልብስና ጉርስ አልፎ ቤተሰብን ለማገዝ ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው እንደነበር አስታዉሰዋል። የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ በትውልድ ቀያቸው መጀመሩ የሥራ ዕድል ስለፈጠረላቸው ከቤተሰባቸው ጋር በደስታ እየኖሩ መሆኑን ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ በአካባቢው የነበረውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር የሚያስቀር ከመሆኑም በላይ ለወጣቶች ትልቅ የሥራ ዕድል በመፍጠሩ ደስተኛ ነኝ ያሉት አቶ ደጀኔ ወደ ፊትም በተመሣሣይ ፕሮጀከት ለመሥራት መነሳሳት ፈጥሮብኛል ብለዋል። በፕሮጀክቱ በመስራት ላይ የምትገኘው ወ/ሮ ውዴ ደሜ በበኩሏ እርሷና ቤተሰቧ ኑሯቸውን የሚገፉት በትንሽ የእርሻ ሥራና ጉልት ሽጠው በሚያገኙት ገቢ እንደነበር ጠቅሳ ፕሮጀክቱ በአካባቢዋ ከተጀመረ ወዲህ ግን የሥራ ዕድል እና ተጨማሪ ገቢ ማግኘቷን ተናግራለች። የፕሮጀክቱ ፎርማን አቶ ገበየው ፌንሳ በበኩላቸው ሠራተኞቹ ለፕሮጀክቱ ያላቸው አመለካከት እንዲሁም በሥራ ላይ የሚያሳዩት ቅንነትና ተሳትፎ የሚደነቅ መሆኑን ገለጸዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚያከናውናቸው የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ግንታዎች ለበርካታ ወጣቶች ቋሚና ጊዚያዊ የሥራ ዕድል እየፈጠረ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

በፕሮጀክቱ ላይ ያጋጠመው የድንጋይ ክምችት የቁፋሮ ሥራውን ፈታኝ ቢያደርገውም ቁፋሮው በስኬት እየተጠናቀቀ ነው ……....///……... የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ላይ አጋጥሞ የነበረው ከባድ የዐለት ክምችት የቁፋሮ ሥራውን ፈታኝ ቢያደርገውም በስኬት እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የሳይት አስተባባሪ አቶ እንዳልካቸው ጃምቦ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በሚገነባበት ቦታ ላይ ከባድ የዐለት ንጣፍ እንዲሁም ጥቁር አፈር መኖሩ የቁፋሮ ሥራውን አስቸጋሪና ጊዜ እንዲወስድ አድርጎታል። ፕሮጀክቱን ከተያዘለት የ12 ወራት ጊዜ ቀደም ብሎ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ ወደ ሳይት ቢገባም በጣቢያው ላይ ያጋጠመው ከባድ የዐለት ክምችት ግን ከተገመተው በላይ ፈታኝ እንደነበር አስተባባሪው አንስተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት አስቸጋሪ የሆኑ የቁፋሮ ሥራዎች እየተገባደዱ መሆኑን የገለፁት አቶ እንዳልካቸው ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ተናግረዋል። በፕሮጀክቱ ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት የታየው ቁርጠኝነት እና የቡድን ሥራ የተቋሙን እምቅ አቅምና ጥንካሬ ያሳየ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሲቪል መሀንዲስ ሱራፌል ሲያምረኝ በበኩሉ ፕሮጀክቱን ለመገንባት የመሬት ጥናትና የአፈር ምርመራ ሲደረግ በቀላሉ ሊወጣ የሚችል የድንጋይ ክምችት መኖሩ ይታወቅ እንደነበር አንስተዋል፡፡ ይሁንና የቁፋሮ ሥራው ሲጀመር ከሚገመተው በላይ የሆነና እስከ 3 ሜትር ስፋት ያለው ግዙፍ የዐለት ክምችት በማጋጠሙ የቁፋሮ ሥራው አስቸጋሪ እንዲሆን እንዳደረገው ጠቅሰዋል። የሲቪልና ኤሌክትሮ መካኒካል ዕቃዎች መትከያ መሠረት ለማውጣት 1 ነጥብ 4 ሜትር ድረስ የሚቆፈር ቢሆንም የድንጋዩ ጥልቀት ከዚያ በላይ በመሆኑ ሳቢያ መልሶ ለመሙላት እና መሰረት ለማውጣት እልህ አስጨራሽ ጉልበት መጠየቁን ገልፀዋል፡፡ የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍልና ስዊች ያርድ በሚያርፉበት ቦታ ላይ ጥልቀት ያለው ጥቁር አፈር ማጋጠሙ ሌላው ፈታኝ ችግር እንደነበርም ነው መሀንዲሱ የገለፁት፡፡ ጥቁር አፈር በባህሪው ክብደት የመሸከም አቅም እንደሌለው የገለፁት አቶ ሱራፌል ጥቁር አፈሩን ሙሉ በሙሉ በማንሳትና መልሶ በጠቅጠቅ የመሰረት ማውጣት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በፕሮጀክቱ የኤክስካቫተር ሾፌር የሆነው ወጣት ዳግም ደገፋ በ12 ዓመት የአገልግሎት ዘመኑ እንደ አሁኑ ያለ አስቸጋሪ የቁፋሮ ሥራ ገጥሞት እንደማያውቅ ተናግሯል፡፡ የዐለት ንጣፉ የተያያዘና በጣም ከባድ በመሆኑ በተደጋጋሚ የማሽን ብልሽት እንዳጋጠመው የገለፀው የኤክስካቫተር ሾፌሩ ድንጋዩን ወደ ሌላ ቦታ ለመግፋት በአንድ ማሽን ጉልበት የማይቻል እንደነበር አንስቷል፡፡ በፕሮጀክቱ ትልቅ የቡድን ስሜት መኖሩ ችግሮችን በጋራ ለማለፍ እንዳስቻላቸው የፕሮጀክቱ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች ገልፀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

የፌደራልና የክልል መንግሥት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ …….....///……….. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ የተለያዩ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ ፕሮጀክቱ ስላለፈበት ሂደትና አሁን ስለደረሰበት ደረጃ ገለፃ አድርገዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ዋና ግድብ ግንባታ ከመሬት ወለል 74 ሜትር ከፍታ ላይ መድረሱንና ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን፣ የትርፍ ውሃ ማስተንፈሻ ቦይ ወይም ስፒል ዌይ ግንባታ 11 በመቶ መከናወኑን፣ የኃይል ማመንጫ ቤት የሲቪል ግንባታም 55 ነጥብ 6 በመቶ ላይ እንደሚገኝ፣ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 62 በመቶ መድረሱን ገልፀውላቸዋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ4 ሺህ 5 መቶ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩንም ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል። በአፍሪካ በግዙፍነቱ ሦስተኛ ደረጃ የያዘው የኮይሻ የታዳሽ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ያለበት ደረጃ አበረታች መሆኑን አመራሮቹ በጉብኝታቸው ገልፀዋል። የኮይሻ ግድብ በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በቅርብ ርቀት የሚገኝ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ የኢኮኖሚ አቅምና የመልማት ዕድል የሚፈጥር ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡ በጉብኝቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

40 በመቶ የሚሆነው የግድቡ ግንባታ በጥቅጥቅ አርማታ ተሞልቷል …………///………. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ 40 በመቶ የሚሆነው በጥቅጥቅ አርማታ መሞላቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ኢንጂነር አባይነህ ጌትነት እንደገለጹት ዋናውን ግድብ ለመሙላት ከሚጠበቀው 7 ነጥብ 6 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ ጥቅጥቅ አርማታ ውስጥ 3 ነጥብ 2 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ ጥቅጥቅ አርማታ ተሞልቷል፡፡ ለዋናው ግድብ ግንባታም 6 ነጥብ 4 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ ልል አፈር የማንሳት ሥራ ተከናውኗል ብለዋል፡፡ ከግድቡ ግንባታ በተጓዳኝ የኃይል ማመንጫ ቤትና የውሃ ማስተንፈሻ ወይም ስፒል ዌይ ግንባታ በመከናወን ላይ መሆኑን ምክትል ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ከመላው ኢትዮጵያ ለተውጣጡ ከ4 ሺህ 5 መቶ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ ከ85 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ መገንባቱን እንዲሁም በጎፋ ዞን የመለኮዛ ወረዳና በኮንታ ዞን የኮንታ ወረዳን የሚያገናኝ 175 ሜትር ርዝመት ያለው ድልድል በፕሮጀክቱ መሰራቱን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሚፈጠረው 129 ኪሎ ሜትር የሚተኛ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ለአካባቢው ተጨማሪ የቱሪዝም መስህብ የመሆን ዕድል አለው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content