uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 553 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 395-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 164-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 553 obunachiga ega bo‘ldi.

22 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 5 ga, so‘nggi 24 soatda esa 1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.99% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.38% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 043 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 393 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 23 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 553
Obunachilar
+124 soatlar
+47 kunlar
+530 kunlar
Postlar arxiv
“የህዳሴው ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል” ዛዲግ አብርሃ .......///...... የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከአንገት መድፋት ወደ ደረት መንፋት አሸጋግሮናል ሲሉ የአፍሪካ አመራት ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። ፕሬዝደንቱ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች በተቋሙ ዋና መ/ቤት የአመራርን ስልጠና ሲሰጡ እንደተናገሩት የህዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጫነት ባሻገር ለኢትዮጵያውያን ያለው ትርጉም የላቀ ነው። “የህዳሴ ግድብ የሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የማዕዘን ድንጋይ ነው።” ያሉት አቶ ዛዲግ ግድቡ ለሀገር ከሚያስገኘው የኢኮኖሚ ጥቅም በላይ ለዓለም የከባቢ አየር ጥበቃ ድርሻው ጉልህ መሆኑን ተናግረዋል። የውሃ ኃይል ግድቦች በሩቅ ምስራቋ ቻይና በዓለም የመጀመሪያው ሀገረ መንግስት ግንባታ እንዲጀመር መሰረት መሆናቸውን ጠቅሰው የሚመነጨው ኃይል ከኢኮኖሚ ጥቅም በላይ መሆኑን አሳይቷል ብለዋል። አቶ ዛዲግ እንዳሉት የታላቁ ህዳሴ ግድብ የብሄራዊ ኩራት ምንጭ በመሆኑ ግድቡ ከታሪካዊ ማንነታችን ጋር በጥብቅ በተሳሰረው የአባይ ወንዝ ላይ መገንባታችን ኩራቱን ከፍ እንደሚያደርገው ገልፀዋል። ግድቡ በሚያመነጨው ኃይል፣ በሚያስገኘው የውጭ ምንዛሪ እና በሚፈጥረው ትስስር ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላት የወሳኝነት ሚና እንዲጎለብት የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል። የአባይን ውሃ እንዳንጠቀም ብዙ ሴራ ቢሸረብብንም ያንን ሁሉ አልፈን የወሰንነው ውሳኔ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እርምጃ ነው ሲሉ የግድቡን የሉዐላዊነት መገለጫነት አስረድተዋል። ግድቡ ኢትዮጵያ ልማቷን ለማረጋገጥ የምትሄደውን ረዥም ርቀት ያሳየም ነው ብለዋል። ስለትውልዳዊ ቅብብሎሽ ሲያነሱም “ጀምሮ ያለመጨረስ ታሪካችን የሁል ጊዜም አለመሆኑን በህዳሴው ግድብ አረጋግጠናል” ሲሉ ተደምጠዋል። ይህ ትውልድ ከአፄ ዳዊት ጀምሮ የነበረውን አባይን የመገደብ ህልም ከግብ ማድረስ የቻለ አኩሪ ትውልድ መሆኑን የተናገሩት አቶ ዛዲግ “የቀደመውን ትውልድ ህልም ተቀብሎ እውን የማድረግ ተግባር አስቀጥለን ለትውልድ ማስተላለፍ ከቻልን ኢትዮጵያን ለሁልጊዜም የታላላቅ ጅምሮች እና የታላላቅ ፍጻሜዎች ሀገር እናደርጋታለን” ሲሉ እምነታቸውን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ አቅም አውጥቶ መጠቀም እንደሚገባ የገለጹት ፕሬዝደንቱ ይህንን ለማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትልቁን ኃላፊነት እንደሚወስድ አስረድተዋል። በመሆኑም የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ እያንዳንዱ ቤት የሚገባ በመሆኑ አፈጻጸሙ በሀገረ መንግስት ግንባታው ላይ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል። “የኤሌክትሪክ ኃይልን ተጠቃሚነት ማሳደግ ኢትዮጵያ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገው ሽግግር ወሳኝ በመሆኑ ለኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ሽግግር መክፈቻ ቁልፉ መብራት ኃይል ጋር ነው ያለው ማለት ይቻላል” ሲሉ ተናግረዋል። በመሆኑም ተቋሙ ወደ ውጪ ሀገራት በሚልከው ኢነርጂ ምክንያት የዲፕሎማሲ ሥራ እየሰራ ነው ሊባል እንደሚችል ጠቅሰዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ለተቋሙ የሥራ መሪዎች በተቋም ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየተሰጠ ነው  ........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር በአመራር እና የተቋም ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ የሦስት ቀን ሥልጠና ለተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች መስጠት  ጀመሯል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይና የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ገብረ ኪዳን በስልጠናው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገሪቷ እና ለቀጣናው አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ  ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው። አመራሩ የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣ እና የመፈጸም አቅሙ እንዲጎለብት ሥልጠና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። ስለሆነም አመራሩ ሥልጠናውን በንቃት በመከታተል የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል አቅም እንዲገነባ  አሳስበዋል። ሥልጠናው ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛዲግ አብርሃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የመሪነት ሚና ላይ ያተኮረ ሥልጠና በመስጠት ላይ ናቸው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ፕሮጀክቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የማህበራዊ ኃላፊነት ድጋፍ አደረገ .......///...... የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች እና ሠራተኞችን በማስተባበር ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ከ600 ሺህ ብር በላይ የማህበራዊ ኃላፊነት ድጋፍ ማድረጉን  የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌቱ ያደታ እንዳስታወቁት በፕሮጀክቱ ዙሪያ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ለሚኖሩ 33 ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው አቅመ ደካሞች የስንዴ፣ ጤፍ፣ የኤሌክትሪክ ምጣድ፣ ዘይት እና የድንችድጋፍ ተደርጓል። ድጋፉ ፕሮጀክቱ በኢተያ ወረዳ በዕቅድ ከሚያከናውናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች በተለየ በሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች እና ሠራተኞች በጎ ፈቃደኝነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የአካባቢው ማህበረሰብ ለፕሮጀክቱ ግንባታ መጠናቀቅ አወንታዊ አስተዋፅኦ በማበርከቱ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ለማህበረሰቡ ያላቸውን አጋርነት በተግባር ያሳዩበት እንደሆነም ነው ያብራሩት። በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው የዞንና የወረዳ መስተዳድር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ሥራ አስኪያጁ አረጋግጠዋል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት 20 ተርባይኖችን ወደ ሥራ በማስገባት 69 ሜጋ ዋት ኃይል ወደ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ቋት በማስገባት ላይ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+5

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 1ኛ እና በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ሰኔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን
+3
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 1ኛ እና በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ሰኔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በፋርማሲስት 1ኛ እና በፋርማሲስት 2ኛ የስራ መደብ የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተራ ቁጥር 1 (አንድ) ላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ከነሐሴ 09 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ እና የሙያ ፈቃድ (License) ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ..…..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት የመንግስት የልማት እና ኢነርጂ ፖሊሲዎችን ታሳቢ ያደረገ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙ ባለፉት ስድስት ዓመታት ብቻ በኃይል ማመንጨት ዘርፉ ላይ ያከናወናቸው ሥራዎች በ128 ዓመታት ከተከናወኑ ሥራዎች የ48 በመቶ ድርሻ አላቸው፡፡ ተቋሙ ባለፉት ስድስት ዓመታት ባከናወናቸው የግንባታ ሥራዎች ሀገራዊ የማመንጨት አቅሙን በ3 ሺህ 784 ሜጋ ዋት ማሳደግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት የፕሮጀክት አስተዳደር አቅምን በማሳደግ ተቋሙ ግንባታቸው የተጀመሩ የማመንጫ፣ የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን በመከታተል እና በመቆጣጠር እንዲሁም የተጠናቀቁትን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን እና የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር የአይሻ፣ የኮይሻ እና የአሉቶ ጅኦተርማል ፕሪይም ፕሮጀክቶችን በመከታተልና በመቆጣጠር አፈፃፀማቸውን ለማሻሻል ዕቅድ ተይዞ ለተግባራዊነቱ እንቅስቃሴ መጀመሩን አብራርተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ፣ የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን፣ የባህር ዳር-ወልድያ- ኮምቦልቻ እና የአዋሽ-ወልዲያ የባቡር ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክቶችን ጨምሮ አስር የማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት እንደሚሰራ ነው ያነሱት፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የኢትዮ-ጂቡቲ 2ኛ ሰርኪዩት እና የጎንደር-ዳንሻ-ሁመራ-ባዕከር አግሮ ኢንዱስትሪ የኃይል አቅርቦት እንዲሁም የመቀሌ-ዳሎል የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን ጨምሮ የሰባት ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማስጀመር ዕቅድ ተይዟል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ የኃይል አማራጮች 38 ሺህ 120 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት መታቀዱንና ከዚህም ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የ45 ነጥብ 21 በመቶ ድርሻ እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ደንበኞች 31 ሺህ 600 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል  በማቅረብ እንዲሁም ከልዩ ልዩ ገቢዎች በአጠቃላይ 109 ነጥብ 54 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ለ2018 በጀት ዓመት ለሥራ ማስኬጃ 251 ቢሊየን ብር በጀት የያዘ ሲሆን 55 ነጥብ 1 ከመቶ ከኃይል ሽያጭና ልዩ ልዩ ገቢዎች፣ 31 ነጥብ 4 ከመቶ ከሀገር ውስጥ ብድርና እርዳታ እንዲሁም 13 ነጥብ 5 ከመቶ ከዓለም አቀፍ  ብድርና እርዳታ እንደሚሸፈን ተገልጿል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከተያዘው 251 ቢሊየን ብር ውስጥ 71 በመቶ ለፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ እንደሚውል የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው 118 ቢሊዮን ብር በግንባታ ሂደት ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች፣ 29 ቢሊዮን ብር ለአዳዲስ ፕሮጀክቶች ማስጀመሪያ እና 10 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመልሶ ግንባታ ሥራ እንዲሁም ቀሪው 17 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብሩ ለመለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ እና ለሲቪል ጥገና ክፍያዎች መመደቡን አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት የተነሳ በምዕራብ ጎንደር ዞን ኃይል ተቋርጧል ……..///……. በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ጭልጋ ከተማ አካባቢ በስርቆት ምክንያት በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት ከአዘዞ-ሸኽዲ በተዘረጉ ሦስት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በዚህም ምክንያት ከሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት በጊዜያዊነት እንደተቋረጠባቸው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ በላይነህ ገለፃ ከአዘዞ-ሸኽዲ በተዘረጉ አስር ተጨማሪ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የስርቆት ወንጀል በመፈፀሙ የመውደቅ አደጋ ላይ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች ዳግም ለመጠገን እንቅስቃሴ መጀመሩን  ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የወደቁትን ሦስት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአፋጣኝ መልሶ በመትከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የኃይል አቅርቦቱን ለማስቀጠል ጥረት ይደረጋል፡፡ በመሆኑም ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ የአካባቢው ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የአዘዞ-ሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ከፍተኛ የሥርቆት ወንጀል እየተፈጸመ እንደሆነ ገለፁት ሥራ አስኪያጁ ህብረተሰቡና የፀጥታ አካላት ለኃይል መሠረተ ልማቱ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በዞኑ በስርቆት እና ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ለ20 ቀናት ተቋርጦ የቆየውን ኃይል በጊዜያዊነት በ87 የእንጨት ምሰሶዎች በመተካት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ መደረጉ አይዘነጋም፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሁናዊ ገፅታ 📌 ከአፍሪካ ሙሉ በሙሉ ታዳሽ ኃይል በመጠቀም 3ኛ የግሪድ አስተዳዳሪ ተቋም ነው። 📌 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴን እና አሰላ የንፋስ ኃይል ፣ማመንጫን ጨምሮ 20 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል። 📌 ከ20 ሺህ 700 ሰርኪዩት ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው 308 የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን አሉት። 📌 ከ132 ኪሎ ቮልት እስከ 500 ኪሎ ቮልት የቮልቴጅ መጠን ያላቸው 145 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በኦፕሬሽን ላይ ይገኛሉ።  📌 በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከ31 ሺህ 400 በላይ ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው 361 ትራንፎርመሮች አሉት። 📌 ከ40 ሺህ በላይ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች አሉት። 📌 በአሁኑ ወቅት ካፒታሉ 586 ቢሊየን ብር እንዲሁም አጠቃላይ ሀብቱ ደግሞ 709 ቢሊዮን ብር ደርሷል። 📌 ከአፍሪካ ከውኃ ኤሌክትሪክ ኃይልን በማመንጨት አቅም አንደኛ ነው። 📌 በ2017 በጀት ዓመት 7 ሺህ 910 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም የነበረው ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ተጠግኗል …..///…... ለወራት ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ የቆየው የለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን 1 አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር ኢንጂነር ደረጀ ገዛኸኝ እንደተናገሩት በማከፋፈያ ጣቢያው አቅራቢያ በሚጣለው ቆሻሻ ላይ የሚሰባሰቡ አሞራዎች የጣቢያው አንድ ትራንስፎርመር እንዲቃጠል አድርገው ነበር። በዚህ እና ከስርጭት መስመር ጋር በተያያዙ ቴክኒካል ችግሮች በተደጋጋሚ ኃይል ይቋረጥ እንደነበር ኢንጂነር ደረጀ አንስተዋል። የኃይል መቋረጡን በዘላቂነት ለመፍታት እና የጣቢያውን አቅም ለማሳደግ አንድ መቶ ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለመትከል የማጓጓዝ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል። ትራንስፎርመሩ ተጓጉዞ ማከፋፈያ ጣቢያው እንዲደርስ እገዛ ያደረጉትን የአዲስ አበባ እና የሸገር ከተማ ፖሊስን አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊ የሥራ መደቦች፡- • ሶሺዮሎጂስት • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ
#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊ የሥራ መደቦች፡- • ሶሺዮሎጂስት • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር (ዲ1) በመሆኑም ከላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች የሚከተሉትን ሊንኮች መጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። Link 1 👉 https://forms.gle/dHiiFD2w3ubSs3ZK9 18 Link 2፡ 👇 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfA1P8Oc9OymnrSYLNUUq2v0ulr_ZgFUth2qBP1WC7DmHo6aQ/viewform?usp=dialog 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

#Vacancy የቃለ-መጠይቅ ፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በChange Management Officer III (D4) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 06 ቀን 2017 ዓ
#Vacancy የቃለ-መጠይቅ ፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በChange Management Officer III (D4) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና መፈተኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ 50 እና ከዚያ በላይ ያገኛችሁ ከተ.ቁ 1 እስከ 6 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ የቃለ መጠይቅ (Interview) ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል ልማት ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚፈልግ ነው …..///…... የኃይል ልማት ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚፈልግ በመሆኑ በተቋሙ አቅም ብቻ ሊሸፈን እንደማይችል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን አስመልክቶ ዓመታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠበት ወቅት ከታሪፍ ማሻሽያ እና ከኃይል አቅርቦት ተደራሽነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ተነስተዋል፡፡ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተቋሙ ከአስር ዓመታት በላይ የታሪፍ ማሻሽያ ሳያደርግ በከፍተኛ ብድር የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድጉ የኃይል መሰረተ ልማት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ በዚህም ተቋሙ የህልውና አደጋ ውስጥ በመግባቱ በመንግሥት በኩል የሀገር ውስጥ ዕዳ ጫና ስረዛ እንደተደረገለት አስታውሰዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ የፋይናንስ ቁመናውን ለማሻሻል፣ የኃይል ሽፋንን ለማሳደግ እና  የአገልግሎት ጥራትን ለማዘመን እንዲሁም የኦፕሬሽንና የፕሮጀክት ወጪዎችን ለመሸፈን በጥናት ላይ ተመስርቶ የታሪፍ ማሻሻያ መተግበሩን ተናግረዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያው በየሩብ ዓመቱ ተከፋፍሎ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን ያስታወሱት ኢንጂነር አሸብር የታሪፍ ማሻሻያው ከጎረቤት ሀገራት አንፃር ሲታይ አሁንም እጅግ ዝቅተኛና የተቋሙን ወጪ መሸፈን የማይችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በየዓመቱ የሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት በአስር በመቶ እያደገ በመሆኑ ከታሪፍ ማሻሽያው ጎን ለጎን በዘርፉ ያለውን የኃይል ስብጥር ለማሳደግና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ያለው ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ የታሪፍ ምጣኔ የግል አልሚዎችን የሚያበረታታ ባለመሆኑ እስከ አሁን የሚፈለገው ውጤት አለመገኘቱን ገልፀዋል፡፡ የተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ40 በመቶ በላይ ለሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል ኤሌክትሪክ ተደራሽ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡ ያልተቆራረጠ ኃይል ለማህበረሰቡ ለማዳረስ እና የኃይል ሽፋኑን ለማሳደግ ከፍተኛ የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎች የሚጠይቁ በመሆናቸው የታሪፍ ማሻሻያው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተግባራዊ መደረጉን አንስተዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የህብረተሰብ ክፍል ታሳቢ ያደረገ ነው ያሉት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጭማሪው በቀን ሲሰላ ከ55 ሳንቲም ያልበለጠ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያውን አስመልክቶ የሚነሱ የተሳሳቱ አመለካከቶችን በማረም በኩል መገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ነው ያስረዱት፡፡ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት ተቋሙ ከዓመታዊ በጀቱ አብዛኛውን ለካፒታል ፕሮጀክቶች በመመደብ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከአሁን ቀደም ተቋሙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወስዶት የነበረውና በተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ የቆየውን ብድር መንግሥት ወደ ራሱ መውሰዱን የጠቆሙት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ተቋሙ የመክፈል አቅሙንና ገቢውን ያገናዘበ ብድር ከባንኩ በመውሰድ ፕሮጀክቶችን በራሱ አቅም ለማስፈፀም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በግንባታ ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች ማስኬጃ ከ261 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከራስ ፋይናንስ መሸፈኑንም ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ከያዘው 251 ቢሊየን ብር በጀት ውስጥ 71 በመቶ ለፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ እንደሚውል የጠቆሙት አቶ ደመረ በጀቱ ከኃይል ሽያጭ፣ ከመንግሥት ከሚገኝ ድጋፍ፣ ከአገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ከሚገኝ ብድርና ድጋፍ የሚሸፈን መሆኑን አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4