uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 559 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 384-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 165-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 559 obunachiga ega bo‘ldi.

23 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 0 ga, so‘nggi 24 soatda esa -2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.89% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.48% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 026 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 408 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 24 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 559
Obunachilar
-224 soatlar
-37 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar
Postlar arxiv
የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም የማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው …….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጂን ሥር የሚገኘውን የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ እንድሪስ አህመድ እንደገለፁት የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ በባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ ነው። በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ  የቆየውን ኤር ኢንሱሌትድ ስዊች ጊር ወደ  ጋዝ ኢንሱሌትድ ስዊችጊር ብሬከር  የመቀየር ሥራ መሰራቱ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል። የብሬከር ቅየራው አሁን ላይ 70 በመቶ መድረሱንና ሲጠናቀቅ የጣቢያውን ኃይል የማቅረብ አቅም አስተማማኝና የተቀላጠፈ እንደሚያደርገው ጠቅሰዋል። የሪጂኑ ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሙሀመድ አብዱ በበኩላቸው የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ብሬከር ቅየራ ለሠመራ፣ ለሎጊያ፣ ለሚሌ፣ ለአሳይታ፣ ለዱብቲ ከተሞችና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝ ኃይል ማቅረብ ያስችላል ብለዋል። የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ 230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል። አንድ ገቢ መስመርና ሁለት ወጪ መስመሮች ያሉት የሰመራ ማከፋፈያ ጣቢያ በ2003 ዓ.ም  ተገንብቶ ለክልሉ በዋነኛነት ኃይል በማቅረብ እያገለገለ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቀየረው ትራንስፎርመር ሥራው ጀምሯል ………..///……… በአዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ገጥሞት በሌላ የተተካው ትራንስፎርመር ሥራ መጀመሩን የማዕከላዊ ሦስ
የተቀየረው ትራንስፎርመር ሥራው ጀምሯል   ………..///……… በአዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ገጥሞት በሌላ የተተካው ትራንስፎርመር ሥራ መጀመሩን የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ የጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ  ታደሰ  ገብሬ እንዳስታወቁት የትራንስፎርመር ፍተሻና ሙከራ ሥራ በሥኬት በመጠናቀቁ ትራንስፎርመሩ ሥራ እንዲጀምር ተደርጓል፡፡ የትራንስፎርመሩ ሥራ መጀመር ከጣቢያው ኃይልሲያገኙ በነበሩ አካባቢዎች ለሳምንታት በፈረቃ ሲሰጥ የቆየውን አገልግሎት እንደሚያስቀር ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ትራንስፎርመሩ በሙሉ አቅሙ መሥራት ሲጀምር የሚፈጠረውን የኃይል ጭነት ለማቃለል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል አንድ ወይም ሁለት የሥርጭት መስመሮችን በቅርብ ወደሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች  የማዛወር ሥራ ሊሰራ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ4 ቀን 2017 ዓ.ም

በጣቢያው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራው ተጠናቋል   ………..///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አዲስ ዌስት የኮልፌ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ብልሽት ያጋጠመውን ትራንስፎርመር የመቀየር ሥራ መጠናቀቁን የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን አስታወቀ፡፡ በሪጅኑ የጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ  ታደሰ  ገብሬ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች በአንዱ ላይ ብልሽት በማጋጠሙ ምክንያት ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ከመጋቢት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል በፈረቃ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ችግሩ እስኪፈታ ድረስም ኃይል ለተቋረጠባቸው የምዕራብ አዲስ አበባ አካባቢዎች በቀሪው አንድ ትራንስፎርመር ኃይል በፈረቃ ሲቀርብ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ብልሽት ያጋጠመው ትራንስፎርመር የቅየራ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የፍተቫና የሙከራ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ የፍተሻና ሙከራ ሥራው በስኬት ከተጠናቀቀ ዛሬ ማምሻውን አልያም ነገ ጠዋት በፈረቃ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ወደ መደበኛ የኃይል ሥርጭት እንደሚመለሱ ተናግረዋል፡፡ አቶ ታደሰ ያጋጠመው ችግር እስኪፈታ በትዕግስት ለጠበቁ ነዋሪዎችም ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የጣቢያው የፍተሻና የሙከራ ሥራው በስኬት ተጠናቋል ……..///…….. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የፍተሻና የሙከራ ሥራ በስኬት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌቱ ያደታ እንዳስታወቁት ማከፋፈያ ጣቢያው ከሦስት አቅጣጫ በአራት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እንዲገናኝ በማድረግ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ጣቢያው ከቆቃ፣ ከመልካዋከና እና ከበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጋር ለማገናኘት የሁለት የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎችና የሽቦ ዝርጋታ ሥራ በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ መከናወኑንም ነው አቶ ጌቱ የጠቆሙት። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የኮሙዩኒኬሽን፣ የስካዳ እና የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶች በተቋሙ ባለሙያዎች ተሰርተው ትራንስፎርመሮቹ ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮችና 4 ገቢ መስመሮች እንዳሉትም ነው የጠቀሱት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በቀጣይ 40 በመቶ የቅድመ ፍተሻ ሥራ የተከናወነላቸውን የንፋስ ተርባይኖች ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ጋር በማገናኘት ኃይል እንዲያመነጩ ይደረጋል። በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በየሳምንቱ 10 ሜጋ ዋት በድምሩ 80 ሜጋ ዋት ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት ለማስገባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነም ነው አቶ ጌቱ የገለፁት። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ እንደ ሀገር ከንፋስ የሚመነጨውን ኃይል ከ404 ሜጋ ዋት ወደ 504 ሜጋ ዋት ከፍ በማድረግ የኃይል ስብጥሩን ለማሳደግና አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸመውን ስርቆት መከላከል ይገባል .....///...... በኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈጸመው ተደጋጋሚ ስርቆት ለመከላከል የሚያስችል ውይይት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት ከተማ ተካሄደ። በውይይቱ ላይ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማን ጨምሮ የአካባቢው የሃይማኖት አባቶች፣ የጎሳ መሪዎች እና የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል። መስመሩ የኢትዮጵያ የወጪ እና ገቢ ዕቃዎች የሚጓጓዙበት መሆኑን በውል መረዳት እንደሚያስፈልግ ኃላፊዎቹ አስረድተዋል። በባቡር መስመሩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ በሚፈጸም ተደጋጋሚ ስርቆት የተነሳ የባቡር መስመሩን ሙሉ አቅም ለመጠቀም እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን ገልፀዋል። ይህም ገቢ እና ወጪ ዕቃዎች እንዲዘገዩ በማድረግ በዓለምአቀፍ ገበያ ላይ ተወዳዳሪነትን በመቀነስ እና የዋጋ ንረትን በማስከተል በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚያስከትል ተናግረዋል። በመሆኑም ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት፣ ማህበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በባቡር መስመሩ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለመከላከል ከመንግሥት ጎን በመሆን የማጋለጥ ስራ እየሰሩ መሆኑን እና ይሄን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል። በአዋሽ-ወልዲያ-ሃራ ገቢያ የባቡር የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ላይ በአስር ቀናት ውስጥ ብቻ ከ80 ኪሎ ሜትር በላይ የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ እና 25 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ለስርቆት መዳረጉን መዘገባችን ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ማከፋፈያ ጣቢያው አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ ነው ........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰበታ ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ አቅሙን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አየልኝ እንደገለጹት በባለ 400 ኪሎ ቮልት በሀገሪቱ የመጀመሪያው የነበረው ማከፋፈያ ጣቢያው በ2002 ዓ.ም ወደ ሥራ ሲጀምር በዋናነት የግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ኃይል ተቀብሎ ለማስተላለፍ ነው። ጣቢያው ከግልገል ጊቤ 2 በገላን ማከፋፈያ ጣቢያ በኩል እንዲሁም ከጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት አራት ገቢ መስመሮች ሲኖሩት ካራ ቆሬ አካባቢ ለሚገኘው ሰበታ አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ  እንዲሁም ለኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መስመር በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ኃይል እንደሚሰጥ ተናግረዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችና ለፋብሪካዎች በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከ34 በላይ ወጪ መስመሮች እንዳሉት ገልጸዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮች እንዳሉት የጠቆሙት አቶ ሙሉጌታ በሦስት መስመር ወደ 60 ሜጋ ዋት አካባቢ ኃይል ለዳታ ማይኒንግ ድርጅት እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡ የሰበታ ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ በ 400 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመነጨውን ኃይል ከሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀብሎ ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እያስገባ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በቀጣይም የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር አንድ ተጨማሪ አውቶ ትራንስፎርመር እና ለአካባቢው ማሕበረሰብ አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ፓወር ትራንስፎርመር ከውጪ ለማስገባት በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በማመንጫ ጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት የካይዘን አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዕቃ ግምጃ ቤቶች የካይዘን አሰራር ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ጣቢያው አስታወቀ። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ አቶ እሸቱ አበራ እንደተናገሩት የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ለማቀላጠፍ የሚያግዝ የካይዘን የአሰራር ሥርዓትን በዕቃ ግምጃ ቤቶች ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል። የካይዘን የአሰራር ሥርዓት ከመተግበሩ በፊት የዕቃ ግምጃ ቤቶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁና ዕቃዎቹም በተለያዩ ቦታ በዘፈቀደ የተቀመጡ እንደነበረ አስታውሰዋል። በዚህም ዕቃዎቹ በሙቀትና በተለያዬ ምክንያቶች በአጭር ጊዜ ከመበላሸታቸውም በተጨማሪ ለሥራ ሲፈለጉ በቀላሉ የማይገኙ በመሆኑ ውጤታማ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን አዳጋች ነበር ብለዋል። ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት በካይዘን የአሰራር ሥርዓት ግንዛቤ ያላቸው ባለሙያዎች ተመድበው ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመዋል። እንደ ባለሙያው ገለጻ በጣቢያው በሚገኙ ሦስት የዕቃ ግምጃ ቤቶች ላይ የሚሰሩና የሚወገዱ የመለዋወጫ ዕቃዎችና መሣሪያዎችን በመለየት በዓይነታቸውና በአገልግሎት ዘመናቸው መሰረት ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል። ይህም ጣቢያው ያሉትንና የሌሉትን የመለዋወጫ ዕቃዎች ለይቶ እንዲያውቅ በማስቻሉ ቀደም ሲል ዕቃዎቹን ለመፈለግ ይወስድ የነበረውን ጊዜና በብልሽት ምክንያት ያጋጥም የነበረውን አላስፈላጊ ወጭ ማስቀረት መቻሉን ተናግረዋል። የጣቢያው የዕቃ ግምጃ ቤት ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ  ማርታ ጉንቴ በበኩላቸው ከሦስት ወር በላይ ጊዜ በመውሰድ የተደራጁት ዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝር መረጃዎች መለያ ተሰጥቷቸው ተመዝግበው መቀመጣቸውን ገልጸዋል። ይህም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያሉ ዕቃዎችን ለማወቅ፣ ያለቁ ዕቃዎችን ለማሟላት እና የሚገቡ ዕቃዎችን በዓይነታቸው አደራጅቶ በማስቀመጥ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ማስቻሉን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአራት ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ካይዘን ኢንስቲትዩት ጋር የካይዘን ትግበራ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ሪጅኖች ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሊያከናውኑ ይገባል ........///........ ሪጅኖች ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ የኦፕሬሽን ሥራዎችን ሊያከናውኑ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አሳሰበ። ዘርፉ የሪጅኖችን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም በመገምገም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫ ሰጥቷል። በተቋሙ የትራንስሚሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ሲዓ እንደተናገሩት ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲያስችለው ተቋማዊ ለውጥ እየተገበረ ይገኛል። በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ውጤታማ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያልተከናወኑ ተግባራትንና በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ለማከናወን የታቀዱ ሥራዎችን በማካተት የመቶ ቀን ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ እንዲገባ አሳስበዋል። ዕቅዱን በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ የጋራ በማድረግ ወደ ሥራ እንዲገባ ያሳሰቡት አቶ አንዷለም ዕቅዱ ሪጅኖች ያሉበትን የአፈጻጸም ደረጃ የለየ፣ ችግሮችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀመጠ፣ የሥራ ቅደም ተከተልንና ባለቤት የለየ ሊሆን ይገባል ብለዋል። በመቶ ቀን ዕቅዱ በተለያዩ ምክንያቶች የግሪድ መሳሳት ባጋጠሙ ቦታዎች ላይ አስፈላጊ ሥራዎችን በመስራት ግሪዱን ወደነበረበት አቅምና አቋም ለመመለስ ትኩረት እንዲሰጥ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራዎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈጸም ሪጅኖች ከሠራተኞች ጋር መግባባት መፍጠርና መፍጠንን ማዕከል በማድረግ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። የማዕከላዊ አንድ ሪጅን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኸኝ እንደገለጹት የግምገማ መድረኩ ተቋማዊ ለውጡን ሪጅኖች በምን መልኩ ማስኬድ አለባቸው በሚለው ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ የፈጠረ ነው። መድረኩ በሪጅኖች ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያጋጠሙ ችግሮችን ለይቶ በቀጣይ ለመፍታት እና በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የተሻለ ለውጥ ለማስመዝገብ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል። የሰሜን ምስራቅ ሁለት ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ሀሰን ሙሐመድ በበኩላቸው የግምገማ መድረኩ የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበት እንዲሁም የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር በቀጣይ በምን መልኩ መሰራት አለበት በሚለው ዙሪያ በቂ ግንዛቤ ያገኘንበት ነው ብለዋል። እንደሪጅን ያሉ ችግሮችን እና መልካም አጋጣሚዎችን በመለየት የአጭርና የረጅም ጊዜ መፍትሄዎችን አስቀምጦ ስጋቶችን በቀነሰ መልኩ ለተቋማዊ ለውጡ ስኬት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማቀላጠፍ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር መስራት አለባቸው …..///…. የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራ በማቀላጠፍ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር መስራት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ። የትራንስሚሽን ቢዝነስ 13ቱም የሪጅን ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ አንዷለም ሲዓ እንደተናገሩት ግምገማው የሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራ ያለበትትን ደረጃ ለማወቅ፣ እርስ በእርስ ለመማማር፣ ከኦዲት ጋር ተያይዞ የተሰሩ ማሻሻያዎችን ለማየት እና አመራሩ በአፈፃፀሙ ላይ የጋራ ግንዛቤ ኖሮት ሥራዎችን እንዲሰራ ዕድል ለመፍጠር ነው፡፡ ዘርፉ እንደ አዲስ ከተዋቀረ በኋላ ቀደም ሲል በችግር መልክ ሲነሱ የቆዩና መፍትሄ ያላገኙ ጉዳዮችን በመለየት በዘላቂነት ለመፍታት እንዲሁም የኦፕሬሽን አሰራሮችን ለማዘመንና ለማሻሻል ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አንዷለም አክለውም ሪጅኖች የኦፕሬሽን ሥራዎችን በማቀላጠፍ እንዲሁም ከአካባቢ መስተዳድር አካላትና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪክት ኃላፊዎች ጋር በመቀናጀት የኃይል ተደራሽነቱን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የዘርፉ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የዕቅድና ክትትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ታገል ደገፉ ቀርቧል፡፡ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ የሚያስችሉ የቅድመ መከላከል፣ የትንበያ፣ የፍተሻ ጥገና ሥራዎች በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፍያ ጣቢያዎች ላይ መከናወናቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ በሰመራና በአዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በጭነት ልዩነት ወቅት ቮልቴጅን ለመቀጣጠር የሚረዳ መሣሪያ (shunt reactor) በመትከልና ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት የአፋር ክልልና የጅቡቲን የኤክስፖርት ኮሪደር እንዲሁም የባቡር ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን አስተማማኝና ያልተቆራረጠ ኃይል እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉም ተጠቁሟል፡፡ የዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ብሬከሮች ተከላ እንዲሁም በስርቆት ምክንያት የሚወድቁ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን መልሶ የመገንባት ሥራዎች በራስ አቅም በማከናወን ወጭና ጊዜ መቆጠብ መቻሉም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ የመለዋወጫ እቃዎች ተመዝግበው መቀመጣቸው፣ በአስራ ስድስት ማከፋፈያ ጣቢዎች ላይ ላይ የፕሮቴክሽን ማሻሻያ ሥራዎችን በመስራት የብሔራዊ የኃይል ቋቱን ደህንነት ከፍ በማድረግ አላስፈላጊ የኃይል መቆራረጦችን መቀነስ ተችሏል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት መጨመር፣ በጸጥታ ችግር ምክንያት የተለያዩ መስመሮች ለረዥም ጊዜ ተቋርጠዉ መቆየት፣ የከፍተኛ ኃይል ትራንስፎርመር እጥረት እና በማሰራጫ መስመሮች ላይ በሚያጋጥም አደጋ ምክንያት የሚወጡ መስመሮች እና ትራንስፎርመሮች መጨመር በዘጠኝ ወራት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች መሆናቸውም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አበባው ያለው በበኩላቸው ግምገማውን ማድረግ ያስፈለገበት ዋና ምክንት በተቋሙ እየተከናወኑ ካሉ ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች ጋር ተያይዞ በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ መዘናጋት እንዳይኖር ያለበትን ደረጃ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት በ36 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የማሻሻያና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በራስ አቅም እየተከናወኑ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ኃይል ያላገኙ አካባቢዎችን ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም ኃይል ባገኙ አካባቢዎች አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ የዘርፉን አፈፃፀም ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አበባው የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማዘመን እና አሰራሮችን ለማሻሻል እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ግምገማው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ዘርፉ የዘጠኝ ወር የሥራ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነው .....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን የ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው። ግምገማው የሪጅኖችን የዘጠኝ ወራት ክንውን፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰዱ የመፍትሄ ርምጃዎች እንዲሁም ቀጣይ የትኩረት አቅጣዎች ላይ ያተኮረ ነው። በግምገማው ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ ተቋሙ እያደረገ ካለው ሪፎርም ጎን ለጎን የኦፕሬሽን ሥራዎችን በአግባቡ በማከናወን የተቋሙን ግቦች ማሳካት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ ለሚደርሱ ጥፋቶች እና ሌሎች አስተዳደራዊ ክፍተቶችን ለማረም ተጠያቂነት ከማስፈን ጎን ለጎን ቀድሞ መከላከል ላይ ያተኮረ አሠራር መዘርጋት አስፈላጊ ነው ብለዋል። ለዚህም ሁሉም ሪጅኖች  ከመስተዳድር አካላት እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ተቀራርቦ በመስራት እና ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት አስተማማኝ ኃይል ለህብረተሰቡ ማድረስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በዘጠኝ ወራት ውስጥ  የማስተላለፊያ መስመሮች፣ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ዘርፉን ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያዉ በዞኑ የተሰማሩ የኢንቨስተሮችን የኃይል ፍላጎት መልሷል ……..///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወልቂጤ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በጉራጌ ዞን  ለተሰማሩ ከ315 በላይ የሚሆኑ ኢንቨስተሮችን የኃይል ፍላጎት በተሟላ መልኩ መመለስ መቻሉን የዞኑ አስተዳደር የኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቁ፡፡ የመምሪያው ልዩ አማካሪ አቶ ዳርጌ ተረፈ እንዳስታወቁት የወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው መኖሩ ኢንቬስተሮችን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያበረከተ ነው፡፡ በአካባቢው ሰላማዊ እና ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ከመኖሩ ባሻገር በቂ የኃይል አቅርቦት መኖሩ ባለሀብቶቹን በመሳብ በኩል ያለውን ዕድል ማስፋቱን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ዳርጌ ገለፃ የኢንቨስትመንት ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ከኃይል አቅርቦት ጋር ለተገናኙ ችግሮች ማከፋፈያ ጣቢያዉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት የድርሻዉን እየተወጣ ነው፡፡ በአካባቢዉ እየተነቃቃ የመጣዉን ኢንቨስትመንት አጠናክሮ ለማስቀጠል በቅርቡ የኢንዱስትሪ መንደር ለማቋቋም ዝግጅቶች መጠናቀቃቸዉን አማካሪው ጠቁመዋል፡፡ ባለሀብቶች ዞኑ ባሉት የኢንቨስትመት አማራጮች ላይ ለመሰማራት ሲመጡ በአካባቢው ምንም ዓይነት የኃይል እጥረት እንደማይገጥማቸዉ ልዩ አማካሪው አረጋግጠዋል፡፡ የጉራጌ ዞን አስተዳደር በ10 ወረዳዎች እና በአምስት የከተማ መስዳድሮች የተዋቀረ ሲሆን አካባቢዉን ምቹ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድርግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆኑ ተመላክቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም