uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 528 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 328-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 528 obunachiga ega bo‘ldi.

06 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 6 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.84% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.05% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 323 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 492 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 07 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 528
Obunachilar
-324 soatlar
-97 kunlar
+630 kunlar
Postlar arxiv
ፓርቲው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ ...............//////................ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ( ኢዜማ) ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የግማሽ ሚሊዮን ብር ስጦታ አበረከተ። በድጋፍ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በልዩነት ብቻ የተመሰረተውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ በማሻሻል በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ፓርቲው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያደረገው ድጋፍም የትብብሩ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ እንዳሉት ስጦታው በሀገር ውስጥና በሀገር ውጭ ከሚኖሩ የፓርቲው አባላት ለዚሁ ዓላማ የተሰበሰበ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ባለፈው ታሪካችው በሀገራዊ የጋራ አጀንዳዎች ላይ የማይደራደሩ መሆናቸውን አስታውሰው ሁሉም ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በልዩነት ምክንያት ሀገራዊ ጥቅማቸውን ለአፍታም ቢሆን አሳልፈው መስጠት እንደሌለባቸው አሳስበዋል፡፡ ኢዜማ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የማያወላውል አቋም እንዳለውና ወደፊትም ድጋፉን እንደሚቀጥል ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አረጋግጠዋል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ብራሄራዊ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ታገል ቀኑብህ በበኩላቸው ኢዜማ ያደረገው ድጋፍ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አንድ መሆን እንዳለባቸው ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ከአሁን በፊት ፓርቲዎች በእንደዚህ ዓይነት ሀገራዊ ልማት ላይ የሚያሳዩት ተሳትፎ ብዙም እንዳልነበር አቶ ታገል ጠቁመዋል፡፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነገ መንግሥት ሆነው ቢመረጡ የሚያስተዳድሩት አሁን በልዩነት ሁነው የሚሰሩትን መልካም ሥራ በመሆኑ በጋራ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የጋራ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour መስከረም 12 ቀን 2013ዓ/ም

ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የቢሾፍቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ ………………..///……………… ከአዲስ አበባ በ45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በቢሾፍቱ ከተማ የተገ
+3
ከ25 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የቢሾፍቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ ………………..///……………… ከአዲስ አበባ በ45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በቢሾፍቱ ከተማ የተገነባው ባለ 400/230/15 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ ዳዊት ገብረ እግዚአብሄር ገለጹ፡፡ አቶ ዳዊት እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ስራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፡፡ ከነባሩ አቃቂ - ገላን ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ እስከ ቢሾፍቱ ማከፋፈያ ድረስ 46 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም ተከናውኗል፡፡ የፕሮጀከቱ የሳይት ተቆጣጣሪ መሃንዲስ አቶ ዘውዱ ለገሰ እንደገለፁት ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለት ባለ 600 ሜጋ ቮልት አምፒር እና ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትንስፎርመሮች ተተክለውለታል፡፡ ጣቢያው ጥንድ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና ሁለት ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት እንዲሁም 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ የማከፋፋያ ጣቢያውን የገነባው ላርሰን ኤንድ ቱብሮ የተባለ የህንድ ኩባንያ ሲሆን ግንባታው ለመጨረስ ከ25 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበታል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በቢሾፍቱ ከተማ እና በዙሪዋ ለሚገኙ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎችና የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲሁም ለህብረተሰቡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል ተብሎ ይታመናል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም.

ፎርቲስኪው በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት አለው ……………../////……………….. በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በሃይድሮጂን ምርት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራው ፎርቲስኪው በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት እንዳለው አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ በማዕድን ልማት፣ በማዳበሪያ አቅርቦትና በሃይድሮጂን ምርት ሲሰማራ የሚያስፈልገውን ኃይል በራሱ ከማሟላት ባሻገር የሚያመርተውን ኃይል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የኃይል ቋት በመጠቀም እስከ 25 ጊጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት አለው፡፡ የፎርቲስኪው እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ በማሻሻል ኤሌክትሪክ ለሁሉም ለማዳረስ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ታምኖበታል፡፡ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን በሀገሪቱ የተጀመረውን የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ በማሳካት በአህጉሪቱ በቀዳሚነት ለመሰለፍ ማለሙን ይፋ አድርጓል፡፡ መስከረም 08 ቀን 2013 ዓ/ም

25 ጊጋ ዋት ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት ካለው ድርጅት ጋር ውይይት ተካሄደ ...................////............ ፎርቲስኪው የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው አስታወቀ፡፡ የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በሸራተን አዲስ ሆቴል ከድርጅቱ ተወካዮች ጋር በተካሄደው ውይይት ላይ እንደገለፁት መንግስት 45 በመቶ ብቻ የሆነውን የኃይል ተደራሽነት ለማሻሻል የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ማከናወኑን ገልፀዋል። በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኃይል ተደራሽነት ለማሳደግ ንፁህና ታዳሽ ኃይል በማልማት ፣ ዘርፉንም ፋይናንስ በማድረግና የግሉን ባለሃብት በማሳተፍ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማትን የመገንባት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለልዑካኑ አብራርተውላቸዋል፡፡ እ.አ.አ. በ2030 ኢትዮጵያ ለዜጎቿ መቶ በመቶ ኃይል ለማቅረብ የያዘችውን ዕቅድ ለማሳካት ድርጅቱ ያሳየው ተነሳሽነት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል እያቀረበች እንደሆነና 350 ሜጋ ዋት የደረሰው የኃይል ሽያጭ በጥቂት ዓመታት ወደ 700 ለማሳደግ መታቀዱንም ገልጸውላቸዋል፡፡ በተለይ በከተሞች አካባቢ እየጨመረ የመጣው የኢንዱስትሪዎች መስፋፋትና የኃይል ፍላጎት መጨመር ለግል ባለሀብቱ ትልቅ ዕድል እንደሆነም ጠቅሰውላቸዋል፡፡ ሚኒስትሩ ንጹህና ታዳሽ ኃይል ማልማት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ምቹ እንደሆነችና ሰፊ አማራጮችም እንዳሏት ነግረዋቸዋል፡፡ በተለያዩ ዓለም ሀገራት ንጹህና ታዳሽ ኃይል በማመንጨት ግንባር ቀደም የሆነው ፎርቲስኪው የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ልዑካን ድርጅታቸው በኢትዮጵያ በ10 ቢሊዮን ዶላር 15 ጊጋ ዋት ከውሃና 10 ጊጋ ዋት ከጂኦ ተርማል ኃይል ለማመንጨት ፍላጎት እንዳለው ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል። ውይይቱም በኢትዮጵያ የኃይል ልማቱን ለመጀመር ያለንን ተነሳሽነት ለማሳየት ሲሆን ይህን ድርጅቱ በአውስትራሊያ በጊኒና በሌሎችም ሃገራት ተመሳሳይ ሥራ በመሥራት ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል። የሚሠሩትም የልማት ሥራ በርካታ ሥራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና በተለይም ሴቶችን ያሳተፈ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡ ሚኒስትሩም የድርጅቱ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋዩን ማፍሰስ ዘርፈ ብዙ ትልቅ እድል ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ፎርቲስኪው በማዕድን ፣ በማዳበሪያ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የተሰማራ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው፡፡ መስከረም 07 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+2

እንኳን ለ2013 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ!! አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንልን ከልቤ እመኛለሁ!! 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊 🌻🌻 መልካም 🌻🌻 🌻🌻 አዲስ 🌻🌻 🌻🌻 ዓመት 🌻🌻 🌻🌹⁣🌾🌻💐🌷🌻 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊

እንኳን ለ2013 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ!! አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤናና የብልፅግና እንዲሆንላችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይመኛል!! 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊 🌻🌻 መልካም 🌻🌻 🌻🌻 አዲስ 🌻🌻 🌻🌻 ዓመት 🌻🌻 🌻🌹⁣🌾🌻💐🌷🌻 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊

ስመ ጥር ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የሀገራችንን አቋም የሚያሳይ ቪድዮ ተለቀቀ።

አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ …………./////……….. በእንቦጭ አረም በመዘጋቱ አገልግሎት ለጊዜው አቋርጦ የነበረው የአዋሽ II የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ የእንቦጭ አረሙ የውሃ መቀየሻ ግድብ ላይ በመተኛቱ የተነሳ የውሃ መቀበያው (water intake) አገልግሎቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ አረሙን ከወንጂ ስኳር ፋብሪካ በተገኘ ኤክስካቫተር የማንሳት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ የውሃ መቀበያው በመከፈቱ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአርብ ነሐሴ 29 ጀምሮ ዳግም ኃይል ማምረት ጀምሯል፡፡ 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው አዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1966 ዓ.ም ነበር፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም

የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ *****************//////***************** የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ2012 ዓ
የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ *****************//////***************** የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሰራተኞች የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆኑ። ሽልማቱ የተበረከተው የግድቡ መሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ከመጋቢት 24/2004 ዓ.ም ጀምሮ በጉባ በሥራ ላይ ለሚገኙ የግድቡ ሰራተኞችና ጸጥታውን ለሚቆጣጠሩ የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፓሊስ አባላት ነው። በጉባ የሚገኙ ሰራተኞችን ወክለው የታላቁ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሽልማቱን ተረክበዋል፡፡ በአባይ ፖለቲካ ላይ የተለያዩ ጥንቶችን ያደረጉት ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ የጤና ባለሙያዎችና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች እንዲሁም የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአረብኛ የኢትዮጵያን አቋም በተለያዩ መድረኮች በማንፀባረቅ የሚታወቀው መሀመድ አል አሩሲ የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ጳጉሜ 02 ቀን 2012 ዓ.ም

የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዓለምአቀፍ ትኩረት ስቧል ……………/////……….. የኤሌክትሪክ ዘርፍ ተሸላሚው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክን ለሁሉም ለማዳረስ እገዛ እያደረገ መሆኑን ፓወር የተሰኘው በኃይል ላይ በማተኮር የሚዘጋጀው ዓለምአቀፍ መጽሔት ዘግቧል፡፡ ከህዝቦቿ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኤሌክትሪክ የማያገኙባት ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተሻሻለች መምጣቷን መጽሔቱ በዝርዝር አትቷል፡፡ መፅሔቱ ይፋ እንዳደረገው የገናሌ ዳዋ 3 ፕሮጀክት መንግስት እ.ኤ.አ እስከ 2025 በመላው ሀገሪቱ ኤሌክትሪክ ለማስፋፋት የሚደረገውን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እገዛ ማድረግ ጀምሯል፡፡ በ3 ተርባይኖች 254 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የገናሌ ዳዋ 3 የኃይል ማመንጫ ተመርቆ ስራ የጀመረው በተያዘው ዓመት አጋማሽ ላይ ነበር፡፡ ይህን ሊንክ በመጫን ዝርዝር ዘገባውን ማግኘት ይችላሉ፡፡ https://www.powermag.com/award-winning-hydropower-project-helps-electrify-ethiopia/

ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት እጥረት የጣቢያው ስጋት እየሆኑ ነው ተባለ --------------/////////---------------- የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ
+5
ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት እጥረት የጣቢያው ስጋት እየሆኑ ነው ተባለ --------------/////////---------------- የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተንሳፋፊ ሳርና የመለዋወጫ አቅርቦት ስራውን እያስተጓጎለበት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡ ኃላፊው አቶ ፍቃዱ ደምሴ እንደገለፁት ወደ ጣቢያው የውሃ መቀበያ እየተገመሰ የሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ለኃይል ማመንጫው የኦፕሬሽን ሥራ ከፍተኛ ስጋት እየሆነ ነው፡፡ ተንሳፋፊ ሳሩ ከሐምሌ 9-11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን እስከማስቆም ደርሶ እንደነበረ የገለፁት ኃላፊው ባለፈው ዓመትም በተንሳፋፊ ሳሩ ምክንያት ከ10 ቀን በላይ ጣቢያው መቆሙን አስታውሰዋል፡፡ ጣቢያውን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ኤክስካቬተር በመከራየትና ዋና በሚችሉ የጣቢያው ሠራተኞችን በመጠቀም የኃይል ማመንጫውን ውሃ መቀበያ የዘጋውን ተንሳፋፊው ሣር ለጊዜውም ቢሆን በማስወገድ ሥራ ማስጀመር መቻሉን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡ ጣቢያውን ከተንሳፋፊ ሳር ለመጠበቅ የሚያግዝ መከላከያ (Taff Boom) ያለው ቢሆንም በዘንድሮ ዓመት ከሃይቁ ዳር እየተገመሰ የሚመጣው የሳር ደሴት መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ ቀደም ሲል የተገጠመው መከላለያ ሊመልሰው አልቻለም፡፡ በመሆኑም በየጊዜው ወደ ኃይል ማመንጫው ለሚመጣው ተንሳፋፊ ሳር ዘላቂ መፍትሄ ካልተሰጠው በቀር ጣቢያውን እስከ መዘጋት ሊያደርሰው እንደሚችል አብራርተዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 27 ቀን 2012 ዓ.ም.

አዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለጊዜው አገልግሎቱን አቋረጠ …………./////……….. በአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ በማጋጠሙ ከቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 201
+3
አዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለጊዜው አገልግሎቱን አቋረጠ …………./////……….. በአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ በማጋጠሙ ከቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ጣቢያው ለጊዜው አገልግሎት ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ II እና III ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዲሳሳ ገልሜሳ አስታውቀዋል፡፡ ላለፉት 49 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውና 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በውሃ መጥለቅለቅ አደጋ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ አገልግሎት መስጠት አቁሟል፡፡ ከተርባይን ወለል እስከ ተርባይን ሮተር ማገናኛ ዘንግ (Turbine Rotor Coupling Shaft) ድረስ ያሉት የኤሌክትሮ-መካኒካል እቃዎች በውሃ በመዋጣቸው የጉዳቱን መጠን ለማወቅ እንዳልተቻለ አቶ ዲሳሳ ተናግረዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 26 ቀን 2012 ዓ.ም.

የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል አግኝቷል ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ምክንያት የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ሲደረግ የነበረው ርብርብ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። በምሰሶው መውደቅ ምክንያት በአካባቢው ላለፉት ሁለት ቀናት ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል። በእነዚህ ቀናት ከነበረው ከባድ ዝናብና የመብረቅ ብልጭታ ከሚፈጥረው ከባድ ንዝረት ጋር በመታገል መስመሩን ላገናኙ የጥገና ባለሙያዎቻችን ላቀ ያለ ምስጋናችንን እያቀረብን የአካባቢው ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችም በትዕግስት ስለጠበቃችሁን ከልብ እናመሰግናለን። የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም.

የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል የተጀመረው ርብርብ በከባድ ዝናብ ውስጥም ቀጥሏል ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና በአካባቢው የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል እየተደረገ ያለውን ርብርብ በአካባቢው እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብና መብረቅ እያስተጓጎለው ቢሆንም ርብርቡ ቀጥሏል። አካባቢው ኃይል ያገኝ የነበረበትን የቀድሞ መስመር ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት እስከ ማምሻው ድረስ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ይሁንና እየጣለ ያለው ዝናብ እና የመብረቅ ብልጭታ በመስመሩ ውስጥ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ንዝረት በመፍጠር የጥገና ባለሙያዎች ስራቸውን በተገቢው እንዳያጠናቅቁ እንቅፋት እየሆነ ነው፡፡ መስመሩን ለማገናኘት አሁንም ጥረት የቀጠለ መሆኑን በመገንዘብ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.

በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ
+2
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ምክንያት ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ የተቋረጠውን ኃይል ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው። የአካባቢው መስመር ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት እስከ ማምሻው ድረስ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም.

በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋርጧል ................///////.................. ትናንት ማምሻውን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደ
+2
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋርጧል ................///////.................. ትናንት ማምሻውን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር በወንዝ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የባለ 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በጎርፍ በመውደቁ ዛሬ ከእኩለ ቀን ጀምሮ በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል፡፡ የወደቀውን የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በሌላ ለመተካት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ የወደቀውን ምሰሶ ሙሉ በሙሉ ለማቆም ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም ከኮተቤ ከሚወጣ መስመር ጋር በጊዜያዊነት በማገናኘት አካባቢው ነገ ኃይል እንዲያገኝ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ በኢንደስትሪ መንደሩና ከዚህ ጋር በተገናኘ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ያላችሁ ነዋሪዎች ችግሩን ለመፍታት የጀመርነውን ጥረት በመገንዘብ በትዕግስት እንድትጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪውን ያቀርባል፡፡ አሁን ችግር በደረሰበት አካባቢ ሰኔ ወር አጋማሽ ላይ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸው ለ‹‹ገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት›› ለገሱ ……………………//////……………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸው ለ‹‹ገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት›› ለገሱ ……………………//////……………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የአንድ ወር ደሞዛቸው ለ‹‹ገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት›› ሰጡ፡፡ የተቋሙ ስራ አመራር አባላትና የተጠሪ መምሪያ ኃላፊዎች ከሠራተኞች ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ የአንድ ወር ደሞዛቸውን ለመስጠት ወስነዋል፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ሰራተኞቹና አመራሮቹ በ‹‹ገበታ-ለሀገር›› ፕሮጀክት ለሚከናወኑት ልማቶች የወር ደመወዛቸውን በፍቃደኝነት ለመስጠት በመወሰናቸው አመስግነዋል፡፡ በ‹‹ገበታ-ለሀገር›› ከሚከናወኑት ሶስት ፕሮጀክት መካከል አንዱ በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ አካባቢ የሚከናወን ነው፡፡ ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም

ከ1 ሺህ 3 መቶ ኪ.ሜ በላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና 14 የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ …………………..//////………………… በ2013 በጀት ዓመት የ1 ሺህ 304 ነጥብ 2 ኪ.ሜ የማስተላለፊያ መስመርና 14 የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ኃላፊ ወ/ሮ ጽዮን ብርሃኑ እንዳስታወቁት በአሁኑ ሰዓት በመላው ሀገሪቱ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 14 የማስተላለፊያ መስመር እና 34 የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በግንባታ ላይ ከሚገኙት የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶች መካከል 433 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ባለ 500 ኪ.ቮ፣ 1045 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ባለ 400 ኪ.ቮ፣ 949 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪ.ቮ እና 191 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ባለ 132 ኪ.ቮ ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ የሚገነቡት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ደግሞ አንድ ባለ 500 ኪ.ቮ፣ አምስት ባለ 400 ኪ.ቮ፣15 ባለ 230 ኪ.ቮ እና 13ቱ ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ 132 ኪ.ቮ ናቸው፡፡ በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል አራቱ በራስ ኃይል በመከናወን ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ወ/ሮ ጽዮን ገልጸዋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች መካከልም የ14 ማከፋፈያ ጣቢያ እና የ1 ሺህ 304 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባትን በ2013 በጀት ዓመት በማጠናቀቅ ወደ ስራ ለማስገባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል አራቱ በራስ ኃይል በመከናወን ላይ የሚገኙ ናቸው ተብሏል፡፡ ከአዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ በተጨማሪ በአንዳንድ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ አቅም የማሳደግ ስራ በመከናወን ላይ እንደሚገኝም ነው ወ/ሮ ጽዮን የተናገሩት፡፡ እንደ ወ/ሮ ጽዮን ገለፃ የፕሮጀክቶችን ግንባታ በተያዘላቸው መርሃ ግብር ለማከናወን የወሰን ማስከበር ችግር፣ የፀጥታ ሁኔታ፣ የግብኣት አቅርቦት ችግር፣ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የእንቅስቃሴ ገደብ መደረጉ፤ የሙከራና ፍተሻ ስራ በወቅቱ አለመከናወኑ ተግዳሮቶች ነበሩ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በግንባታ ላይ የሚገኙት የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ለ2 ሺህ 661 ያህል ዜጎች የስራ እድል መፍጠር ችለዋል፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመት በአማራ፣ በደቡብ እና ኦሮሚያ ክልሎች አምስት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጀመርና የአራት ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ስራ እንደሚሰራ ኃላፊዋ ተናግረዋል፡፡ በ2013 በጀት ዓመቱ የታቀዱ ስራዎችን በመርሃ ግብራቸው ለማከናወን የካሳ ክፍያ ጥያቄ፣ የፀጥታ ሁኔታ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ኮሮና ቫይረስ እና ከታክስ ጋር በተገናኘ ከዕቃ ማጓጓዝ ላይ የተጫነው የታክስ አዋጅ እንደ ስጋት የተለዩ ችግሮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመምሪያው ከሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በተቋሙ የራስ ኃይል ቢሮ በርካታ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ከ18 ሺህ 8መቶ ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመርና ከ2 መቶ በላይ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 21 ቀን 2012 ዓ.ም.

ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል …………………..//////………………… በተያዘው የ2013 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመት 12 ነጥብ 9 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት(12 ሺህ 900 ጊጋ ዋት ሰዓት) የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ውስጥ ተጠቃሚዎች በማቅረብ 8 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል፡፡ ከመምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ገቢው የሚሰበሰበው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጅምላ ከሚቀርብ የኃይል ሽያጭ፣ ከከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች፣ ኢትዮ ቴሌኮም ከሚጠቀምበት የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ እና ከኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የኃይል አቅርቦት ነው፡፡ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ካቀደው ውስጥ 89 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብሩ ኢትዮ ቴሌኮም ከሚጠቀምበት 8,443 ኪሎ ሜትር የፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) ኪራይ፣ 7 ነጥብ 46 ቢሊዮን ብሩ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚቀርብ የጅምላ ኃይል ሽያጭ፣ 987 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብሩ ለከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንደስትሪዎች እንዲሁም 47 ነጥብ 88 ሚሊዮን ብሩ ለኢትዮ- ጅቡቲ ምድር ባቡር ከሚቀርበው የኃይል ሽያጭ ለመሰብሰብ የታቀደ ነው፡፡ ተቋሙ በ2013 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ለመሰብሰብ የያዘው እቅድ ከ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ ያለው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ተቋሙ በ2012 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ6 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ በመሰብሰብ የእቅዱን 102 ነጥብ 2 በመቶ ማሳካት እንደቻለ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ በ2006 በጀት ዓመት ከነበረበት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በየዓመቱ እያደገ የሚገኝ ሲሆን በ2011 በጀት ዓመት 7 ቢሊዮን ብር እንዲሁም በ2012 በጀት ዓመት መጨረሻ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ሊደርስ ችሏል፡፡ በ2013 በጀት ዓመት ከሀገር ዉስጥ ኃይል ሽያጭ፣ ከኃይል ኤክስፖርት እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ገቢ በመሰብሰብ ዓመታዊ ገቢውን ወደ 13 ቢሊዮን ለማድረስ ታቅዶ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ቆጣሪ በመግጠም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር አዲስ የኃይል ሽያጭ ስምምነት በማዘጋጀት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት እና ተጨማሪ የገቢ ምንጮችን በመለየት የአዋጭነት ጥናት ማካሄድ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ በዕቅዱ ተካቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የታቀደውን ገቢ በአግባቡ ለመሰብሰብ ከማመንጨት እስከ ደንበኛ ድረስ ባለው ሰንሰለት ለኃይል ብክነት መንስኤ የሚሆኑ ጉዳዮችን በመለየት መፍትሔ እንዲያገኙ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም.