uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 546 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 351-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 178-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 546 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.76% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.84% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 005 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 463 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 546
Obunachilar
+824 soatlar
-227 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
በተቋሙ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ታግዞ ለመፍታት የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀመረ ………/////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ ዘርፎች የሚያጋጥሙትን ችግሮች በጥናት ላይ ተመስርቶ ለመፍታት የሚያስችለው ኮሚቴ አዋቅሮ በይፋ ሥራ ጀመረ፡፡ የተቋሙ የምርምርና ሥርፀት ዳይሬክተር አቶ ሚራጅ ፈረጃ እንደገለፁት ኮሚቴው የተዋቀረው በታዳሽ የኃይል ምንጮች፣ በኢነርጂ ውጤታማነት እና የኃይል ጥራት፣ በኢነርጂ ሀብቶች ስርጭት፣ በፕሮጀክት አስተዳደር እና በሌሎች መስኮች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጥናት ለይቶ በመፍታት የተቋሙን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን ነው፡፡ ጥናቶችን በውስጥ ባለሞያ በማካሄድ የድርጅቱን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት መታሰቡንም የገለፁት አቶ ሚራጅ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ጥናቶችን አብሮ ለመስራት በዕቅድ መያዙንም ጠቁመዋል፡፡ ጥናት ቢደረግባቸው ተብለው የተለዩ ችግሮችን በማቅረብ ከምርምርና ሥርፀት ኮሚቴ አባላት ጋር ኮሚቴውን ሥራ ለማስጀመር ውይይት መደረጉን የገለፁት ዳይሬክተሩ መብራራት ያለባቸው ሀሳቦች ተብራርተው፣ የሚስተካከሉ እና መቀነስ ወይም መጨመር ያለባቸው ጉዳዮች ተለይተው ሰፊ ውይይት መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ የኮሚቴ አባላቱም በተቋሙ ውስጥ አንገብጋቢ የሆኑና አፋጣኝ መፍትሄ ይሻሉ የተባሉ ጉዳዮች ከመለየት ባሻገር ሌሎች የጥናት ጭጦችና ለጥናቱ በተሞክሮነት የተመረጡ ተቋማትን ልምድ በዝርዝር በማንሳት ውይይት አድርገዋል፡፡ ከኮሚቴው የተገኙ ግብዓቶችን በማካተት እና በማስተካከል ወደ ተግባር እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ስርዓት (IFRS) ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ ………/////………. በፋይናንስ የሥራ ዘርፍ ለተሰማሩ 83 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ስርዓት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ። ለሶስት ቀናት በቆየው ስልጠና ለፋይናንስ አሠራር ልህቀት የሚያግዝ ፅንሰ ሀሳብና ተግባራዊ ልምድ ማግኘታቸውን የስልጠና ተሳታፊዎች ተናግረዋል። የስልጠና ተሳታፊዎች እንዳሉት የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ሥርዓት ስልጠና በመውሰዳቸው ለቀጣይ ሥራቸው ተጨማሪ አቅም ተፈጥሮላቸዋል። በተቋሙ የአይ ኤፍ አር ኤስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ይርጉ ሀይሉ እንደተናገሩት ተግባራዊ የተደረገው የፋይናንስ ስርዓት በየጊዜው የሚሻሻል በመሆኑ ሰልጣኞች በየጊዜው ከዚህ አሠራር ጋር የሚራመድ ዕውቀት እና ክህሎት ሊታጠቁ ይገባል። ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ስርዓት (IFRS) በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተግባራዊ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ ተቋሙ በአይ ኤፍ አር ኤስ መመዘኛዎች ተለክቶ ለተከታታይ ዓመታት ከሒሳብ ትችት ነፃ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተከታታይነት ባለው መልኩ የሚሰጥ ሲሆን በቅርቡ በፋይናንስ የሥራ ዘርፍ ለተሠማሩ ተጨማሪ ባለሙያዎች ስልጠና ለመስጠት ታቅዷል። ስልጠናውን የሰጠው ፕራይስ ወተር ሀውስ ኮፐርስ አሶሼትስ አፍሪካ ሊሚትድ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ተቋም ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ተቋሙን ለተቀላቀሉ አዳዲስ ሠራተኞች የትዉዉቅ መርሐግብር ተዘጋጀ .........../////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ለተቀላቀሉ አዳዲስ የኤሌትሪካል እና የመካኒካል መሐንዲሶች የትውውቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር ተካሄደ። የመርሃግብሩ ዋና ዓላማ የተቋሙን ራዕይ፣ ተልዕኮ እንዲሁም ተቋሙ ሊያሳካ የሚፈልጋቸውን ግቦች ለአዳዲስ ሠራተኞች ለማስተዋወቅ ነው፡፡ የተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሣ ስለ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ታሪክ፣ አደረጃጀት ፣የሥራ ባህል ፣ ስለ ተቋሙ ራዕይና ተልዕኮ እንዲሁም ተግባርና ኃላፊነት ለሠራተኞቹ ገለጻ አድርገዋል። ለተቋማዊ ባህል ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ተግባራትን ማከናወን፣ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር ካፒታልን ማሳደግ፣ የበጀት አጠቃቀምን በማሻሻል ወጭን መቀነስ እንዲሁም ማህበራዊ ኃላፊነትን በአግባቡ በመወጣት የተቋሙን እሴት ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎች መስራት ከሠራተኞች እንደሚጠበቅ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ሠራተኞች በተመደቡበት ቦታ ሁሉ ሙያቸውን በሚገባ ተጠቅመው ሥራቸውን በኃላፊነት እንዲወጡና የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ተግተው እንዲሰሩ ዶ/ር ወንድወሰን አሳስበዋል። በትውውቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ እንደተናገሩት ተቋሙን የተቀላቀሉ አዳዲስ ሠራተኞች የቡድን ሥራን በማዳበር በትምህርት ያገኙትን ዕውቀት በተግባር ማዋልና የግንኙነት ክህሎታቸውንም ማሳደግ አለባቸው። ሠራተኞች በኃይል ማመንጫዎች፣ በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን የሥራ ክፍሎች የሚመደቡ ይሆናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ አዲሶቹ ሠራተኞች የተቋሙን መተዳደሪያ ደንብ አውቀው መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የተቋሙ የህግ አገልግሎት መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ አጥናፌ አሳስበዋል። ተቋሙም ለቀጠራቸው ሠራተኞቹ በውሉ መሰረት ተገቢውን የሥራ መሳሪያ፣ ደመወዝ፣ ህክምና፣ ጥቅማጥቅም እና ሠብዓዊ ክብርን የመጠበቅ ግዴታ እንዳለበት አቶ ደረጀ ገልፀዋል። ተቋሙ በሚመድባቸው  የተለያዩ የሥራ ቦታዎች በቅንነት ማገልገል እንዲችሉ ለሠራተኞቹ ምቹ ሁኔታ መፍጠር አለበት ብለዋል ። በተቋሙ የሥነ ምግባር እና የሥልጠና ከፍተኛ ባለሞያ አቶ ሳምሶን ጨነቀ በበኩላቸው የሙያ ሥነ ምግባር  ለተቋም ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው አዲስ ሠራተኞችም ይህን ማክበር እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል ። ሠራተኞች ከህግና ሥነ ምግባር በተጨማሪ ስለኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን የሥራ አካባቢ፣ የሥራ ሁኔታ፣ መልካም አጋጣሚ እና ፈታኝ ሁኔታዎች ገለፃ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+8

photo content

ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በሎየር 1ኛ፣ በፕሮፌሽናል ነርስ 3ኛ፣ በፕሮፌሽናል ነርስ 2ኛ፣ በላብራቶሪ ቴክኖሎጂስት 3ኛ እና በድራጊስት የስራ መደቦች በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው የፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ መስከረም 09 ቀን 2014 ዓ.ም በዋናው መ/ቤት ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ 2ኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡

በስርዓተ-ጾታ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር የአመለካከት ለውጥ የሚያመጣ ሥራ ይሰራል ……..////…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በስርዓተ-ጾታ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት አቅዶ እየሰራ መሆኑን የተቋሙ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወይዘሮ ሌንሴ ኤደኢ እንደገለፁት በተያዘው በጀት ዓመት በዋናው መስሪያ ቤት፣ በሪጅኖች እና በኤሌክትሪክ ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚገኙ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ግንዛቤን በመፍጠር ጾታዊ ተጽእኖን ለመቀነስ አቅዶ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ መምሪያው በተቋሙ ሁለንተናዊ አሰራር የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ በቅጥር፣ በዕድገት፣ በዝውውር፣ በትምህርትና ሥልጠና ለሴቶች የተፈቀዱት የአወንታዊ ድጋፍ እርምጃዎች በአግባቡ ተግባራዊ እንዲሆኑ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ በተቋሙ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የገለፁት ወ/ሮ ሌንሴ የአመራር ክህሎት ማሻሻያና የህይወት ክህሎት ሥልጠና በመስጠት ሴቶችን ወደ አመራርነት ለማምጣት ታቅዷል ብለዋል፡፡ በተቋሙና በሠራተኞች ድጋፍ ለችግር የተጋለጡ ህፃናትን በመርዳት የተቋሙን ማሕበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ባህሉን የበለጠ ለማሳደግ ጥረት እንደሚደረግ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ በተያያዘ ዜና በዋናው መስሪያ ቤት ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የህጻናት መዋያ ማዕከል የተቋሙን የሴት ሠራተኞችን ችግር እያቃለለ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ ማዕከሉን የበለጠ በማስፋፋትና የጎደሉ ቁሳቁሶችን በማሟላት ከአራት ወር እስከ አራት ዓመት የሆኑ ህጻናት ልጆች ላሏቸው የተቋሙ ሴት ሠራተኞች በሙሉ የህጻናት ማቆያ አገልግሎት በተሟላ መልኩ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል እየተሰራ ይገኛል፡፡ በ2014 ዓ.ም ስምንት ህጻናትን ብቻ ተቀብሎ ያስተናግድ የነበረው ማቆያው ተጨማሪ ሞግዚቶቸን በመቅጠር የህፃናት አያያዝና ስነ ልቦናዊ ክብካበቤ ስልጠና በመስጠት ተጨማሪ 25 ህፃናትን ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በተያዘው በጀት ዓመት በሪጅኖችና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የህጻናት ማቆያ ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ወ/ሮ ሌንሴ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

የሳፕ ሲስተም መተግበሩ የፋይናንስ ሥራዎችን አቃልሏል ……..////……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጡ አገልግሎቶችንና አሰራሮችን ለማዘመንና ለመምራት የተተገበረው ሳፕ የተሰኘው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ውስብስብ የፋይናንስ አሰራሮችን እያቀለለ መምጣቱን የተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ተግባራዊ መሆን በጀመረው የሳፕ ሲስተም ከኮስት ማዕከል ጋር የተገናኙ ስድስት ንዑሳን ሞጁሎች እንዲሁም ከግምጃ ቤት ሰነድ አስተዳደር፣ ከሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ ከተሰባሳቢ እና ተከፋይ ሂሳብ፣ ከካሽ፣ ባንክ እና ቋሚ ሀብት አስተዳደር ጋር የተያያዙ ሞጁሎች በመጀመሪያው ምዕራፍ ሥራ ላይ እንዲውሉ ተደርገዋል፡፡ ከገንዘብ አስተዳደር፣ ከፈንድ አስተዳደር፣ ከንብረት ኪራይ ጋር የተያያዙ ሞጁሎች በሁለተኛው የሳፕ ትግበራ ምዕራፍ ላይ እንደሚተገበሩ ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የሳፕ ሲስተም በተቋሙ ውስጥ መተግበሩ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት እንዲኖር ፣ ወቅታዊ ታማኝነት ያለው ሪፖርት ለሚመለከተው አካል ለማቅረብ እና ሥራን በቀላሉ ለማቀላጠፍ እያገዘ ነው፡፡ በተለይም ለዕቃ ግዢ የሚውል በጀት ለመመደብና ለመልቀቅ እንዲሁም የደመወዝ አከፋፈል ሥራዉን በማቀላጠፍ መረጃዎችን በማጥራት በኩል ከፍተኛ ሚና በመጫወቱ ሲስተሙ በጀትን ለመቆጣጠርና ወጪን ለመቀነስ እንዳስቻለ አስረድተዋል፡፡ ተቋሙ ከዚህ በፊት ሲጠቀምበት የነበረው "የአግሬሶ" ሲስተም የሂሳብ ሪፖርት የሚያወጣው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስፈፃሚው የሳፕ ሲሰተም በየወሩ ያለውን የሂሳብ ሪፖርት ለማውጣትና ለመዝጋት ስለሚያስችል የተቋሙን የፋይናንስ ሁኔታ በየወሩ ለማወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ደመረ ገለጻ የሳፕ ሲስተም የየሥራ ክፍሎችን የበጀት አጠቃቀም በቀላሉ ክትትል በማድረግ ከበጀት አጠቃቀምና ከሌሎች የፋይናንስ አሰራሮች ጋር በተያያዘ ችግር ሲያጋጥም ችግሩ የት ላይና በማን እንደተፈጠረ ለማወቅና ችግር የፈጠረውን አካል ተጠያቂ ለማድረግ እንደሚያግዝ ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በማኑዋል የሚከናወኑ ሥራዎችን በሂደት የሳፕ ሲስተሙ ወደ ሙሉ ትግበራ ሲገባ መረጃዎችን ወደ ሲስተሙ የማስገባት ሥራ ለማከናወን ትኩረት እንደሚሰጥ ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይ በሌሎች የሥራ ክፍሎች የሚተገበሩት ከሰዓት መቆጣጠሪያና ከአበል አከፋፈል ጋር እንዲሁም ከግዥ ጋር በተያያዘ አገልግሎት የሚተገበሩ ሞጁሎች የፋይናንስ ሥርዓቱን እንደሚያቀሉት እምነት አለኝ ብለዋል፡፡ የሁለኛው ምዕራፍ የሳፕ ሲስተም ትግበራ በመጀመሪያው ምዕራፍ የታዩ ችግሮችን በመቅረፍና በሞጁሎች ላይ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር በመሆን በማስተካከል በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ እንደሚጀምር አቶ ደመረ አስታውቀዋል፡፡ በተቋሙ በሁለት ምዕራፍ ተግባራዊ ለማድረግ የተጀመረውን የሳፕ ሲሰተም በአግባቡ ተግባራዊ ለማድረግ ከአማካሪው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ በመሆን እየተሰራ ሲሆን ሲስተሙ ሙሉ በሙሉ ሲተገበር የወረቀት ሥራዎችን ያስቀራል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ የሳፕ ሲሰተምን በአግባቡ ለመተግበር ሠራተኞች ቴክኖሎጂውን በአግባቡ ያለመላመድና በአግባቡ ተግባራዊ ያለማድረግ፣ ሲስተሙን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር በሁሉም የተቋሙ የሥራ ቦታዎች መሰረተ ልማቶች ያለመሟላት እና ችግር ሲያጋጥም ከአማካሪው ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመቅረፍ ጊዜ የመውሰድ ሁኔታዎች መኖራቸው በመጀመሪያው ዙር የሳፕ ሞጁሎች ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ዋና ዋና ችግሮች መሆናቸዉም ተጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ለአዲስ ዓመት በቂ ኃይል በማቅረብ የኃይል መቋረጥ እንዳይከሰት አድርጓል ………/////……… በ2015 አዲስ ዓመት ዋዜማ እና በዕለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ያለምንም እጥረት ማቅረቡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በበዓሉ ዋዜማና በዓሉ ዕለት 3183 ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ የተደረገ ቢሆንም ጥቅም ላይ የዋለው 2 ሺህ 500 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ ነው፡፡ ተቋሙ ያዘጋጀው የኤሌክትሪክ ኃይል ከበቂ በላይ በመሆኑ በበዓሉ ዕለት ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀሙ ፋብሪካዎች ጭምር ያለምንም የኃይል አቅርቦት ችግር እንደመደበኛው ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘታቸውንም ሥራ አስፈፃሚው አረጋግጠዋል፡፡ እንደ ስራ አስፈፃሚው ገለፃ ሱዳንና ጅቡቲም በቂ ኃይል ሳይቆራረጥ ማግኘት ችለዋል፡፡ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የኃይል መቆራረጥ እክል እንዳይገጥማቸው የየዘርፉ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት 24 ሰዓት በትጋት መስራታቸውንም ሥራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል፡፡ በተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንዴሳ በበኩላቸው በበዓሉ ወቅት የኃይል እጥረት እንዳይከሰት በሀገሪቱ ከፍተኛ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጨምሮ ሁሉም ኃይል ማመንጫዎች የሚፈለገውን ኃይል በበቂ መጠን ማመንጨት መቻላቸውን ገልፀዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለት ዩኒቶች ኃይል ማመንጨት መጀመራቸው ለኃይል አቅርቦቱ ማደግ መጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

በ2015 በጀት ዓመት የስምንት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ይጀመራል ………/////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2015 በጀት ዓመት ስምንት የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የግንባታ ስራ ለመጀመር ዕቅድ መያዙን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ እንዳስታወቁት በተያዘው በጀት ዓመት በውጪ ሥራ ተቋራጮችና በተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የሚከናወኑ ስምንት የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ለመጀመር ታቅዶ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በበጀት ዓመቱ ይጀመራሉ ተብለው በዕቅድ ከተያዙ ፕሮጀክቶች መካከል የበቆጂ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት እና ደብረ ታቦር ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም በአዳማ ከተማ ይገነባል ተብሎ ለታሰበው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ የሚገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታቸው በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ የሚከናወኑ ይሆናል፡፡ ግንባታቸው በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ ለሚከናወኑት ፕሮጀክቶች የሚያስፈልጉ የግንባታ ዕቃዎች በሌሎች አቅራቢ ኩባንያዎች የሚቀርብ መሆኑንም ሥራ አስፈፃሚው አንስተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለበቆጂና ደብረ ታቦር ጣቢያዎች የግንባታ ሥራ ለማከናወን ከግንባታ ዕቃ አቅራቢው ኩባንያ ጋር ስምምነት በማድረግ የተለያዩ ሥራዎች መጀመራቸው ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የደቡባዊ ኤሌክትሪክሲቲ ግሪድ የማስፋፊያ ፕሮጀክት እና የቡታጅራ - ወራቤ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች በውጭ ሥራ ተቋራጮች የሚገነቡ መሆናቸውን ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የበቆጂና ደብረታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በበጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ 68 ነጥብ 4 በመቶ እንዲሁም የደቡባዊ ኤሌክትሪክሲቲ ግሪድ የማስፋፊያ ፕሮጀክት አፈፃፀምን 26 ነጥብ 3 በመቶ ለማድረስ ታቅዷል፡፡ ለፕሮጀክቶች የተያዘው በጀት ከተለያዩ አበዳሪ ባንኮችና በሌሎች የልማት አጋር አበዳሪ ተቋማት፣ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተቋሙ ገቢ ይሸፈናል ተብሎ እቅድ ተይዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

መስከረም የአዲስ ዓመት መግቢያ ናት፤ መስከረም አደይ የሚፈካባት፣ በክረምቱ ዝናብ የደፈረሱ ወንዞች የሚጠሩበት፣ ሰዎች የተስፋ ስንቅ የሚሰንቁበት የአዲስ ዓመት መባቻ ናት፡፡ እንኳን ለ2015 ዓ. ም በሰላም አደረሳችሁ! አዲሱ ዓመት ተስፋ ሰንቀን የምንጓዝበትና በተሰማራንበት መስክ ሥኬት የምናስመዘግብበት እንዲሆን ከልብ እንመኛለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et

ተቋሙ ለመጪው አዲስ ዓመት በቂ የኃይል አቅርቦት ማዘጋጀቱን አስታወቀ ……..////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመጪው አዲስ ዓመት በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ዝግጅት ማጠናቀቁን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በበዓሉ ዕለት በአማካኝ 2707 ሜጋ ዋት እንደሚያስፈልግ የኃይል ፍላጎት ቅድመ ጥናት ያሳየ ቢሆንም ተቋሙ እስከ 3183 ሜጋ ዋት ኃይል አዘጋጅቷል፡፡ የተዘጋጀው የኤሌክትሪክ ኃይል ከሚፈለገው አንፃር ሲታይ ከበቂ በላይ በመሆኑ በበዓሉ ዕለት ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀሙ ፍብሪካዎች እና ሌሎች ተቋማት እንደመደበኛው ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙ ይሆናል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በቂ ኃይል ዝግጁ በመደረጉ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ የሆኑት ሱዳንና ጅቡቲም ሳይቆራረጥ ኃይል የሚያገኙ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ ገለፃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለት ዩኒቶች ኃይል ማመንጨት መጀመራቸው ለኃይል ማመንጨት አቅም መጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ በበዓል ዕለት የኃይል መቆራረጥ እንዳያጋጥም በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ዝግጁ መሆናቸውን የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው የዘርፉ ኃላፊዎችና ሠራተኞችም የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንዴሳ በበኩላቸው በበዓል ወቅት የኃይል እጥረት እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል፡፡ በሀገሪቱ ከፍተኛ ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የጊቤ 3 ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጨምሮ የሁሉም ኃይል ማመንጫዎች ዩኒቶች ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በበዓል ወቅት ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል መጨናነቅ እና የመቆራረጥ ችግር ለማስወገድ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 04 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+7

በተለያዩ ውድድሮች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች ሽልማት ተበረከተ ……..////……. ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የማበረታቻ ሽልማት አበርክቷል። በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው የሽልማት መርሐ ግብር ላይ አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች እንዳስመዘገቡት ውጤት ከ አምስት ሺህ እስከ 3 መቶ ሺህ ብር የሚደርስ የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የኢትዮ - ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነችውና በ18ኛው የኦሪጎና የዓለም ሻምፒዮና በሴቶች ማራቶን ለሀገሯ የወርቅ ሜዳልያ ያስገኘችው ጎቲቶም ገብረስላሴ ልዩ ተሸላሚ በመሆን የ300 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላታል። ክለቡ በ2014 ዓ.ም የውድድር ዘመን በአትሌቲክስ፣ በሴቶች እግር ኳስ፣ በብስክሌት እና በጠረጴዛ ቴኒስ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች የገንዘብና የምስክር ወረቀት በማበርከት ለቀጣይ ውድድር ሞራል እንዲሰንቁ አድርጓል። የኢትዮ - ኤሌክትሪክ ክለብ ፕሬዚዳንት አቶ ጫላ አማን የክለቡ አትሌቶች በአፍሪካ ሻምፒዮና፣ በአዋቂዎች የዓለም ሻምፒዮና እንዲሁም በወጣቶች የአለም ሻምፒዮና ተሳትፈው ለሀገራቸው የወርቅ ሜዳልያ በማስገኘታቸው ክለቡ በእጅጉ መደሰቱን ገልፀዋል። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን በ2014 ዓ.ም በፕሪሚየር ሊጉ ብርቱ ተፎካካሪ በመሆን የብር ሜዳልያ በማግኘቱም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት የክብር ዶክተር ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ኢትዮ- ኤሌክትሪክ ስፓርት ክለብ ለክለቡና ለሀገርም ብርቅዬ አትሌቶችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የክለቡ ጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው የክለቡ ስፖርተኞች በዓመቱ በሁሉም የስፖርት ዘርፎች የላቀ ውጤት በማስመዝገብ ዓመቱን በልዩ ሁኔታ ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። ተሸላሚ ስፖርተኞች እና የኮቺንግ ስታፍ አባላት በቀጣይም ጠንክረው በመስራት ክለቡንና ሀገራቸውን በዓለም መድረክ ከፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። በእውቅናና ሽልማት መርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚና የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የስፖርት ክለብ ጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ተሊላ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ አሰፋ ንጉሴ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጫላ አማን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 04 ቀን 2014 ዓ.ም