uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 368-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 174-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 10 ga, so‘nggi 24 soatda esa -6 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 24.86% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.87% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 862 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 620 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-624 soatlar
-207 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+4

አስተዳደሩ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመስክ ምልከታ እያካሄደ ነው ........///........ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመስክ ምልከታ እና ውይይት አካሄደ። አስተዳደሩ አስቀድሞ በላከው የመስክ ምልከታና ክትትል ቼክ ሊስት መሰረት ከተመረጡ የሥራ ዘርፎች ጋር ውይይት ተደርጓል። በዚህ መሰረት ከአስተዳደሩ የተወከሉ ባለሙያዎች ከመስከረም 21 ቀን 2016 ጀምሮ በ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት፣ በኮርፖሬት ፋይናንስ አስተዳደር፣ በውስጥ ኦዲትና ቁጥጥር ፣ በሠራተኞች የሥራ አፈፃፀም ምዘና እንዲሁም በፕሮጀክቶች ክትትልና ግምገማ ዙሪያ ከሚመለከታቸው የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች እና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። በመስክ ምልከታው ላይ የዕቅድ ዝግጅቱ ሠራተኞችን ያሳተፈ ስለመሆኑ እና ዕቅዱ በየደረጃው ተመንዝሮ ወደሠራተኛው ስለመውረዱ፣ የተቋሙ የ2015 በጀት ዓመት ሂሳብ በዓለምአቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት ማድረጊያ ስርዓት ወይም (IFRS) ስለመዘጋቱ ፣ ስለፕሮጀክቶች ክትትል እና ግምገማ ሂደት የአስተዳደሩ ባለሙያዎች ጥያቄዎችን አቅርበው ምላሽ ተሰጥቷቸዋል። የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሙያዎች በሰጡት አስተያየት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ልምድ እና መማማሪያ እንዲሆን ሂደቱ ተሰንዶ እንዲቀመጥ ምክረሀሳብ አቅርበዋል። ተቋማዊ ስጋቶችን አስቀድሞ በመለየት መፍትሔ ለመስጠት ትኩረት እንዲደረግ እና እንደተቋም የተጀመሩ የለውጥ ሥራዎች በታሰበው መንገድ እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ሂደቱ እንዲገመገም አስተያየት ሰጥተዋል። በተቋሙ የሥራ አፈፃፀም ምዘና በጥሩ ጅምር ላይ ያለ ቢሆንም የአፈፃፀም ጥራትን ለማሻሻል ትኩረት እንዲሰጥ እንዲሁም የሥልጠና ማዕከሉን ቀድሞ ወደነበረው ስምና ዝና ለመመለስ ጥረት እንዲደረግ አሳስበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ተቋሙ በራሱ ጋራዥ ተሽከርካሪዎቹን በመጠገን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን ችሏል ………///……… ተቋሙ በራሱ ጋራዥ የተሽከርካሪ ጥገናዎች በማከናወኑ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሸከርካሪ ስምሪት እና አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት ተቋሙ በራሱ ጋራዥ የተሽከርካሪዎች ሞተር ዕድሳትን ጨምሮ የተለያዩ የተሸከርካሪ ማሽነሪዎች ጥገና እያከናወነ ነው፡፡ የጋራዥ አገልግሎቱን ወደ መካከለኛ ደረጃ ለማሳደግ መታቀዱን የገለፁት አቶ ኃይላይ ጋራዡን የተሟላ መለዋወጫ እንዲኖው እና በብቁ ባለሙያዎች እንዲደራጅ በማድረግ ተሽከርካሪዎች የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ ተሽከርካሪዎች በተቋሙ ጋራዥ የጥገናና ዕድሳት አገልግሎት ማግኘታቸው ወጪን ከመቀነስ ባሻገር ኦርጂናል የመለዋወጫ ዕቃዎች እንዲገጠሙላቸው አስችሏል ብለዋል፡፡ ከጥገና ሥራዎች ባሻገር ወጥ የሆነ የተሽከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪት ተግባራዊ ለማድረግ ለ600 የተቋሙ ተሽከርካሪዎች የጂፒኤስ ገጠማ መከናወኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወቁት፡፡ የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት ሱፐርቫዘር የሆኑት አቶ ጌቱ ዘላለም በበኩላቸው በ2015 በጀት ዓመት ከ2 ሺህ 1 መቶ በላይ የተቋሙ ተሽከርካሪዎች የጥገናና ዕድሳት አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀዋል፡፡ ተሽከርካሪዎቹ በተቋሙ ጋራዥ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉ ወጪ ከመቀነስ ባለፈ ተሽከርካሪዎች በአጭር ጊዜ እንዲጠገኑ እና በፍጥነት ወደ ስራ እንዲመለሱ በማድረግ ከፍተኛ ተቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋራዥ የሞተር ዕድሳት፣ የቀለም ቅብ፣ የመኪና አካል ወይም ቦዲ፣ የኤሌክትሪክ ሲስተም እና የጊር ቦክስ ጥገናና ዕድሳት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም

ተቋሙ የታገቱ ሠራተኞችን ለማስለቀቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል ...///... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአሉቶ ላንጋኖ የጂኦተርማል ፕሮጀክት ለሥራ ሲንቀሳቀሱ ባልታወቁ
ተቋሙ የታገቱ ሠራተኞችን ለማስለቀቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል ...///... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከአሉቶ ላንጋኖ የጂኦተርማል ፕሮጀክት ለሥራ ሲንቀሳቀሱ ባልታወቁ ሰዎች የታገቱ የፕሮጀክቱን ሠራተኞች ጉዳይ በቅርበት እየተከታተለው ይገኛል። እገታው መፈፀሙ ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ የታጋቾች ቤተሰቦች ሳይረበሹ ታጋቾችን ለማስለቀቅ ጉዳዩን ለሚመለከታቸው አካላት የማሳወቅ ሥራ ሰርቷል። በአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች እና አባገዳዎች በኩል የታገቱት ሠዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲለቀቁ ለማድረግ በቅርበት እየሰራ ይገኛል። ይሁንና "ተቋሙ ምን እንደተፈጠረ እንኳ አልጠየቀም" በሚል በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተዘዋወረ ያለው መረጃ የተሳሳተ፣ ለታጋች ቤተሰቦች ስሜት ጥንቃቄ ያላደረገ እና ተቋሙ እያደረገ ያለውን ጥረት ከግምት ውስጥ ያላስገባ ሆኖ አግኝተነዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታገቱት ሠራተኞች ደህንነት ተጠብቆ ወደቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ ለማድረግ የተቻለውን ሁሉ የሚያደርግ መሆኑን ይገልፃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

photo content
+3

ለቢሮ ኪራይ ይወጣ የነበረ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለ27 ዓመታት በሌላ ተቋም ተይዞበት የቆየውን ይዞታ በማስመለስ እና የጥገና ሥራ በማከናወን ዋና መስሪያ ቤቱን ወደ ኮተቤ ማዛወሩን የንብረት አስተዳደር እና ጥገና አገልግሎት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ታደሰ ዳዲ እንደገለፁት በዓመት ለቢሮ ኪራይ ይወጣ የነበረውን ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል፡፡ ተቋሙ በ2015 በጀት ዓመት ጥቅም ላይ የማይውሉ ብረታብረቶችን በማስወገድ ከ113 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ታደሰ ገለፃ ገቢው የተገኘው ጥቅም ላይ የማይውሉ ቁርጥራጭ ብረቶች፣ ሽቦዎች፣ በርሜሎች እና እንጨቶች በጨረታ በመሸጥ ነው፡፡ የቀድሞ የኢፌዲሪ ብረታብረት እና ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን ወይም ሜቴክ ከተቋሙ ጋር ለነበረው ሥራ ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባቸውን ብረታብረቶን እና ማሽነሪዎች በመረከብ አገልግሎት ላይ የሚውሉት እና መወገድ ያለባቸውን ንብረቶች የመለየት ስራ መጀመሩንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ደህንነት እና ጥራት ለመጠበቅ የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮች ለመተግበር እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ታደሰ ንብረቶችን ሳፕ በተባለ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የመመዝገብ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በተቋሙ የፋሲሊቲ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ በበኩላቸው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ወደ ኮተቤ መዛወሩ ምቹ የስራ ሁኔታ ከመፍጠሩ ባሻገር ሁሉንም የስራ ክፍሎች በአንድ ግቢ ውስጥ በማድረግ የሥራ ትስስርን እንዲጠናከር ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ በዋና መስሪያ ቤት ግቢ ውስጥ ያልተጠናቀቁ መሠረተ ልማቶችን ለማጠናቀቅ፣ የግቢ ማስዋብ፣ የአትክልት እና ፍራፍሬ ተከላ እንዲሁም የመንገድ ሥራዎች እንደሚከናወኑ አቶ ከሊል አስታወቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የፕሮጀክቱ የመቆጣጠሪያ ክፍል የጣሪያ ኮንክሪት ሙሌት ዛሬ ተከናወነ ..........///........... የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የሳይት መሀንዲስ አስታወቁ። መሀንዲሱ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለፁት የባለሙያዎች መኖሪያ ቤት ግንባታ 40 በመቶ ሲጠናቀቅ የጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል ጣሪያ የኮንክሪት ሙሊት ዛሬ ተከናውኗል። የማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል በ500 ካ.ሜ. ቦታ ላይ ያረፈ መሆኑን የጠቆሙት መሀንዲሱ የፕሮጀክቱ አማካይ አፈፃፀም 18 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች የዲዛይን ሥራ ሲጠናቀቅ የሥራው አፈፃፀም አሁን ካለው እንደሚፈጥን መሀንዲሱ ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ ለሜሣ ረጋሣ እንደገለፁት የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ኘሮጀክት በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት ደረጃ እየተከናወነ ነው። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ዳይሬክተር ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው በዛሬው ዕለት የተከናወነው የመቆጣጠሪያ ክፍል የኮንክሪት ሙሌት ሥራ ፕሮጀክቱን ከአዋጭነት ጥናት ጀምሮ እስከማጠናቀቂያ ጊዜ ድረስ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ለማከናወን የተያዘው ዕቅድ በተያዘለት መርሃግብር እየተከናወነ ለመሆኑ ማሳያ ነው። ኘሮጀክቱ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ሲሆን ለሌሎች ፕሮጀክቶች ሞዴል እንዲሆን ተደርጎ እየተገነባ እና ክትትል እየተደረገበት ስለመሆኑ ተናግረዋል። በሞጆ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት ለ26 ሰዎች ቋሚ፣ ለ150 ሰዎች ደግሞ ጊዜያዊ የስራ ዕድል ፈጥሯል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡ መልካም በዓል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች  በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡ መልካም በዓል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2016 ዓ.ም

ለመላው የእስልምና ተከታዮች በሙሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንኳን ለ1498ኛው የነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል - መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ልባዊ ምኞቱን ይገልፃል፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የአብ
ለመላው የእስልምና ተከታዮች በሙሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንኳን ለ1498ኛው የነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል - መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ እያለ ልባዊ ምኞቱን ይገልፃል፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ ይመኛል፡፡ ኢድ ሙባረክ! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 15 ቀን 2016 ዓ.ም

ለክቡራን የተቋማችን ሠራተኞች እና ደንበኞቻችን ከዚህ ቀደም በህትመት ብቻ ወደእናንተ ሲደርስ የነበረው ወርሃዊ መጽሔታችንን በሶፍት ኮፒ በተቋማችን ቴሌግራም እና ድረገጽ ላይ የምታገኙበትን ተጨማሪ ምቹ ሁኔታ ፈጥረናል፡፡ በመሆኑም በየወሩ ተቋማችንና ዘርፉን የሚመለከቱ ቁልፍ ዜናዎች በዚህኛው አማራጭ እንድትከታተሉ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡ መልካም ንባብ! ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ

photo content
+3

ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም በመገንባት በ2015 በጀት ዓመት 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም በመገንባት በ2015 በጀት ዓመት 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ማዳን መቻሉን የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ እንደገለጹት የተቋሙ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ እስከ 400 ኪሎ ቮልት የሚደርሱ የማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እና የውጪ ሥራ ተቋራጮች በማይገቡባቸው አካባቢዎች የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ መምሪያው በ2015 በጀት ዓመት ሲያከናውናቸው ከነበሩ 23 ፕሮጀክቶች መካከል 18ቱን አጠናቆ ያስረከበ ሲሆን ቀሪዎችን በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለማስረከብ እየሰራ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም በማከናወን የውጭ ምንዛሬን ከማዳኑ በተጨማሪ በቀጣይ ጊዜያት አቅሙን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት ማቀዱንም ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ የተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ ፕሮጀክቶችን በጥራትና በጊዜ አጠናቆ በማስረከብ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማድረግ እየተሠራ ነው፡፡ ራዕዩን ለማሳካትም የአመራሩና የሠራተኛው ሚና የጎላ መሆኑን የተናገሩት ሥራ አስፈፃሚው ለዕውቀት ሽግግር ቅድሚያ በመስጠት በትጋት፣ በትብብርና በኃላፊነት ስሜት መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ዘመናዊ የግንባታ መሳሪያዎች እጥረት፣ ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታ እና የግብዓት አቅርቦት ችግሮች መምሪያው ለሚያከናውናቸው የፕሮጀክት ግንባታዎች ተግዳሮት የነበሩ ቢሆንም ችግሮችን በዘለቄታው ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቶች በሚገነቡበት አካባቢ ለሚኖረው ማህበረሰብ ቅድሚያም በመስጠት በየፕሮጀክቶቹ ከ200 እስከ 300 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የሥራ ዕድል እንደተፈጠረም ጠቅሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በራስ ኃይል በሚከናወኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ውስጥ ዘርፉ የዲዛይንና የማማከር እንዲሁም የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን እያከናወነ ነው ብለዋል፡፡ የተቋሙን የራሥ ኃይል አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ በማሳደግ ሀገሪቱ ለውጭ ተቋራጮች የምትሰጠውን የግንባታ ኮንትራት ለማስቀረት አልሞ እየሠራ መሆኑን አቶ ውድነህ ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ዘርፉ ከመምሪያው ጋር በቅንጅት እየሠራ ፕሮጀክቶቹ በጥራትና በጊዜ እንዲጠናቀቁ እገዛ እያደረገ ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የሥራ አመራር ቡድኑ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ጎበኘ .........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን የበላይነህ ክንዴ ሜታል ኢንጂነሪንግ ፋብሪካን ጎበኘ። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ  የተመራው ቡድን በገላን ከተማ የሚገኘውን በፋብሪካው የመኪና መገጣጠሚያ ወርክሾፕ የተገጣጠሙ  የኤሌክትሪክ፣ የከባድ ደረቅ ጭነት እና የፈሳሽ ጭነት ተሽከርካሪዎችን የገጠማ ሂደት ተመልክተዋል። የበላይነህ ክንዴ ብረታብረት ኢንጂነሪንግ ስራ አስኪያጅ በሱፍቃድ ሸዋዬ እንደገለፁት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹ በአንድ ጊዜ ቻርጅ ብቻ ከ270 እስከ 350  ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ። ፋብሪካው ላመረታቸው ተሽከርካሪዎች ባትሪ የስምንት ዓመት እንዲሁም  ለሞተር  የአምስት ዓመት ዋስትና ይሰጣል። የመለዋወጫ አቅርቦት ዝግጁ መደረጉን እና ከሽያጭ በኃላ ሰርቪስ ማድረጊያ ቦታ ቄራ አካባቢ መዘጋጀቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ፋብሪካው አስራ አምስት ቻርጂንግ ማድረጊያዎችን አስመጥቶ ለሙከራ ቢገጥምም ባለሦስት ፌዝ የኤሌክትሪክ መስመር የሚፈልግ  በመሆኑ ቻርጅ ማድረጊያዎችን በተለያዩ አካቢዎች በጋራ መትከል የሚቻልበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቀዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው ፋብሪካው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መግጠም የጀመረበት ሰዓት  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጨማሪ ዩኒቶች ወደሥራ በሚገቡበትና እንደሀገር ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትኩረት በተሰጠበት ወቅት ነው። በመሆኑም የሁለቱ ተቋማት አጋርነት በተሽከርካሪ ብቻ ሳይገደብ በሚያድግበት ሁኔታ ላይ ለመስራት ተቋሙ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል። የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በሰጡት አስተያየት ፋብሪካው  የውጭ ምንዛሪ የሚያድን እና የስራ ዕድል የሚፈጥር  መሆኑን  በጉብኝቱ መመልከታቸውን ተናግረዋል። የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ እና የቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰጠኝ እንግዳው እንደተናገሩት ፋብሪካው ከብክለት የፀዳ ሀገር ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ  ነው። በዚህ ሂደት ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  ከግሩፑ ጋር አብሮ እንደሚሰራ  ያላቸውን ጽኑ እምነት ገልፀዋል። የበላይነህ ክንዴ ብረታብረት ኢንጂነሪንግ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ1400 በላይ የከባድ ደረቅ ጭነት እና የፈሳሽ ጭነት  ተሽከርካሪዎችን እንዲሁም 216 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሚኒባሶችን ገጣጥሟል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 09 ቀን 2016 ዓ.ም

EEP Communication - Telegram kanali @eepcommuication statistikasi va tahlili