uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 534 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 338-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 162-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 534 obunachiga ega bo‘ldi.

29 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 6 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.10% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.85% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 901 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 619 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 534
Obunachilar
-124 soatlar
-167 kunlar
+630 kunlar
Postlar arxiv
በማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ የከተማዋን ኢንቨስትመንት እያነቃቃ ነው ………...//…….... የጅግጅጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ የከተማዋን ኢንቨስትመንት እያነቃቃ መምጣቱን የምስራቅ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አብዱላሂ አብሽር እንደገለፁት ከ2014 ዓ.ም በፊት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የአካባቢውን የኃይል ፍላጎት ማሟላት ባለመቻሉ በከተማዋ የነበረው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ተዳክሞ ቆይቷል። ይሁን እንጂ በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ በተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ በኃይል አቅርቦት እጥረት ተዘግተው የነበሩ ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መመለሳቸውን ተናግረዋል። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምለው ተሾመ በበኩላቸው በጣቢያው በተከሰተ የአቅም ማነስ ምክንያት ከተማዋ የኤሌክትሪክ ኃይል በፈረቃ የምታገኝበት አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሮ ቆይቷል። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በተከናወነው የአቅም ማሻሻያ ሥራ በባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ ለሚሆኑ መስመሮች 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው ትራንስፎርመር በመትከል ችግሩን ሙሉ በሙሉ መቅረፍ እንደተቻለ አመልክተዋል። ጣቢያው የአቅም ማሻሻያ ሥራ ከተከናወነለት በኋላ 59 ሜጋ ዋት ኃይል የማቅረብ አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት ለደንበኞች እየቀረበ ያለው የኃይል መጠን ግን 22 ሜጋ ዋት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል። የአቅም ማሳደግ ሥራው በሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች መከናወኑ ከዕውቀት ሽግግር አንፃር የጎላ ጠቀሜታ እንደነበረውም ነው ሥራ አስኪያጁ የገለፁት። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ከተከናወነው የአቅም ማሳደግ ሥራ በተጨማሪ የመቆጣጠሪያ ክፍሉን ሊያዘምን የሚችል በጋዝ የሚሰራ መቆጣጠሪያ ወይም ጂ.አይ.ኤስ (Gas Insulated System) ቅየራ ለማከናወን በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም አቶ ደምለው ጠቅሰዋል። በ1997 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በ132 ኪሎ ቮልት ከሐረር ቁጥር ሦስት ኃይል ተቀብሎ በባለ 33 ኪሎ ቮልት አራት ወጪ መስመሮች ለቀብሪበያህ፣ ቶጎ ጫሌ፣ ጭናክሰን፣ ፋፈን እና በጅግጅጋ ዙሪያ ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች እንዲሁም በባለ 15 ኪሎ ቮልት አራት ወጪ መስመሮች ለጅግጅጋ ከተማ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 12 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንደነበሩት ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 05 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ- ኤሌክትሪክ  በከፍተኛ ሊግ ጨዋታ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናገደ .........///......... በስድስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም  በንብ እግር ኳስ ቡድን አንድ ለባዶ ተረቷል። በውድድር ዓመቱ አምስት ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ በጥሩ ግስጋሴ ላይ የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ85ኛው ደቂቃ በተቆጠረበት ጎል በሊጉ የመጀመሪያውን ሽንፈት አስተናግዷል። በመከላከል እና መልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት ወደ ሜዳ የገባው  የንብ እግር ኳስ ቡድን ዕቅዱን ማሳካት የቻለ ሲሆን በአንፃሩ ሙሉ በሙሉ በማጥቃት ላይ የተመሠረተ ጨዋታ ይዞ የተጫወተው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በተደጋጋሚ ያገኘውን በርካታ የጎል ዕድል አምክኗል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሽንፈት ቢገጥመውም በ15 ነጥብ እና በሰባት ንፁህ ጎል የከፍተኛ ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል፡፡ ክለቡ በመጪው እሁድ  ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ. ም. ከጂማ አባ ቡና ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በድራጊስት (ኤች-3) የስራ መደብ ላይ ባለሙያ ለመቅጠር መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ታህሳስ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ የሠራተኛ ምደባ ቢሮ የጽሑፍ ፈተና የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

በክልሉ ከግሪድ ኤሌክትሪክ የሚያገኙ ከተሞችና ቀበሌዎች ቁጥር እያደገ መጥቷል ……...///……... በሶማሌ ክልል ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በመገንባታቸውና የአቅም ማሻሻያ ሥራዎች በመከናወናቸው ከግሪድ ኤሌክትሪክ የሚያገኙ ከተሞችና ቀበሌዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መሐመድ የሱፍ ሮብሌ እንደገለፁት በክልሉ እያደገ የመጣውን የልማት ጥያቄ ተከትሎ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው። ባለፉት አምስት ዓመታትም የክልሉን ፍላጎት ሊያስተናግዱ የሚችሉ ሁለት አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሥራ መጀመራቸውን ገልፀዋል። በክልሉ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎች በመገንባታቸው እና በነባሮቹ ላይ የአቅም ማሻሻያ ሥራዎች በመከናወናቸው ምክንያት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሳይሆኑ የቆዩ ከተሞችና ቀበሌዎች ከግሪድ ኃይል ማግኘት መጀመራቸውን ነው የተናገሩት። በዚህም በክልሉ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ20 በላይ ከተሞች እና ከ40 በላይ ቀበሌዎች የኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን አቶ መሐመድ ጠቁመዋል። እንደ አቶ መሐመድ ገለፃ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎችና የአቅም ማሻሻያ ሥራዎች ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና ለኑሮና ለሥራ ምቹ ያልሆኑ አካባቢዎችን ምቹ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። ከክልሉ የህዝብ አሰፋፈር እና የቆዳ ስፋት አንፃር ሁሉንም አካባቢዎች ከግሪድ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን መስራት እንደሚጠይቅም ተናግረዋል። በዚህም ለዋና ዋና ከተሞችና ለወረዳ ማዕከላት ቅድሚያ በመስጠት ከግሪድ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መሐመድ ከግሪድ ርቀው የሚገኙ አካባቢዎች ደግሞ በፀሐይ ኃይልና በሌሎች አማራጮች ኃይል እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙት በተጨማሪ የምስራቁን ግሪድ የሚያጠናክሩ ከፍተኛ የኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩን ያነሱት ኃላፊው ፕሮጀክቱ ክልሉ ከሁለት አቅጣጫ የሚያገኘውን ኃይል በአንድ ለማስተሳሰር እንደሚያግዘው ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ መገንባት በክልሉ ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉና በመስኖ ልማት የሚተዳደሩ አርሶ አደሮች ሥራቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል በመጠቀም እንዲያከናውኑ አቅም ይፈጥራል። የፕሮጀክቱ መገንባት በክልሉ ሁለት ተጨማሪ አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲኖሩት የሚያስችል እና ይህም በክልሉ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቁጥር ወደ ሰባት እንደሚያሳድገው ጠቁመዋል። ተቋሙ በክልሉ ለሚያከናውናቸው የመሠረተ ልማት ግንባታዎች የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ያነሱት አቶ መሐመድ ድጋፉ በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን የመመለስ አቅም አለው ………..///………… የሐረር ቁጥር ሦስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚፈልጉ ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ተጨማሪ አቅም እንደተፈጠረለት የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ። ኃላፊው አቶ ቴዎድሮስ ታመነ እንደገለጹት የማከፋፈያ ጣቢያው ሁለት ባለ 132፣ ሁለት ባለ 66፣ አራት ባለ 33 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ከድሬዳዋ ኃይል ተቀብሎ በባለ 132 ኪሎ ቮልት ሁለት ወጪ መስመሮች ለጅግጅጋ፣ ለደገ ሃቡርና ፊቅ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በባለ 15 ኪሎ ቮልት አምስት ወጪ መስመሮች በክልሉ ለሚገኙ ወረዳዎች፣ የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞች ኃይል እያቀረበ ይገኛል ብለዋል። በ66 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ በሐረር ከተማ ለሚገኘው ለነባሩ ማከፋፈያ ጣቢያ እና በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ለሚገኙት ለሀሮማያ፣ ለደደር፣ ለካራ ሚሌ፣ ለጨለንቆ ከተሞችና አካባቢዎች እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለበዴሳ፣ ለፈዲስ፣ ለሐረር ከተማ ውሃ አገልግሎት እና በከተማዋና በዙሪያዋ ለሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ ኃላፊው አብራርተዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ባሉት ሦስት ትራንስፎርመሮች 80 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማቅረብ አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት እያቀረበ የሚገኘው 48 ሜጋ ዋት ብቻ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በመሆኑም ማከፋፈያ ጣቢያው ወደፊት ሊመጡ የሚችሉ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚችል 32 ሜጋ ዋት ተጨማሪ አቅም እንዳለው ኃላፊው ገልጸዋል። ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ከ51ሜጋ ዋት የማይበልጥ አቅም እንደነበረው የጠቆሙት አቶ ቴዎድሮስ በዚህም በሐረር ከተማና በአካባቢው በየጊዜው እያደገ ለመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ባለመቻሉ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል በፈረቃ እንዲያገኙ ሲደረግ እንደነበር አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ ከአንድ ዓመት በፊት በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የተደረጉ አቅም የማሳደግ ሥራዎች ኃይል የመጫን አቅሙን በፊት ከነበረው በ56 ነጥብ 9 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል። ይህም በፈረቃ ሲሰጥ የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከማስቀረቱም በተጨማሪ ወደፊት የሚመጣውን የኃይል ፍላጎት ሊያስተናግድ የሚችል ተጨማሪ አቅም ፈጥሮለታል ብለዋል። ጣቢያው በቅርቡ በ15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ለሐረር ከተማ ተጨማሪ ኃይል ለመስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመሩን አቶ ቴዎድሮስ አስታውቀዋል። ከጣቢያው በሚወጡ የማሰራጫ መስመሮች ላይ በሚያጋጥሙ ችግሮች ምክንያት የኃይል መቆራረጥ እንዳይስተዋል ከክልሉ እና ምስራቅ ሀገርጌ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም የጣቢያው ኃላፊ አመልክተዋል። የሐረር ቁጥር ሦስት ማከፋፈያ ጣቢያ ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 03 2016 ዓ.ም

photo content
+8

ማህበሩ ከዳሽን ባንክ ጋር የዱቤ አለ አገልግሎት ስምምነት ተፈራረመ -------///-------- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ከዳሽን ባንክ ጋር የዱቤ አለ አገልግሎት ስምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እና በዳሽን ባንክ የኮተቤ 02 ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም መንገሻ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ የማኅበሩ አባል የሆኑት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች አቅማቸው የሚፈቅደውን የዕቃ ዓይነቶች በረጅም የክፍያ ጊዜ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑ በፊርማ ሥነ- ስርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡ የማኅበሩ ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደተናገሩት በስምምነቱ መሰረት ሠራተኛው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማህበሩ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ ማህበሩ ከባንኩ ጋር ስምምነት ላይ እንዲደርስ ድጋፍ ላደረጉ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በዳሽን ባንክ የዲጂታላይዜሽን ባንኪንግ ዳሬክተር አቶ ብሩክ ኃ/መስቀል እንደገለፁት የዱቤ አለ አገልግሎትን ዲጂታላይዝ በማድረግ የመግዛት አቅም ለሌላቸው ሠራተኞች የፋይናንስ አቅም በመፍጠር ዕቅዳቸውን እንዲያሳኩ የሚያደርግ አሰራር መቅረቡ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ማህበሩ የግል ባንክ ከሆነው ዳሸን ባንክ ጋር የደረገው ስምምነት ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ባንኩ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይወሰን በመላ ሀገሪቱ ለሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች አገልግሎቱን እንዲያቀርብ የጠየቁት ሥራ አስፈጻሚው ስምምነቱ በፋይናንስ አከፋፈል ሥርዓቱ ላይ ችግር የማያስከትል በመሆኑ በስኬት ለመስራት ያስችላል ብለዋል፡፡ ስምምነቱ የማህበሩ አባል ለሆኑ ሠራተኞች እስከ 700 ሺህ ብር ድረስ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው ሲሆን ከሶስት ወር እስከ አንድ ዓመት የሚቆይ የአከፋፈል ጊዜ ይኖረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 02 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የተከናወነው የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራ ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ዕድል ፈጥሯል ………..///………... በሐረር ቁጥር ሦስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ የተከናወነው የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራ ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ እንዳስቻለ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሐረሪ ክልል ጽ/ቤት አስታወቀ። በአገልግሎቱ የሐረሪ ክልል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፈሪድ አብዱልሰላም እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች ከመከናወናቸው በፊት የነባር ደንበኞችን የኃይል ፍላጎት በአግባቡ ማስተናገድ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሶ ነበር። ከአንድ ዓመት በፊት የተከናወነው የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራ በክልሉ ሲነሱ የቆዩትን የኃይል መቆራረጥ ችግሮች መፍታት እንዳስቻለ ጠቅሰዋል። የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራው የኃይል መቆራረጥ ችግሮችን ከመቅረፉም ባለፈ አዳዲስ ተጨማሪ ደንበኞችን ለማስተናገድ ዕድል መፍጠሩንም ነው የተናገሩት። ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ የነበረው የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር ከ25 ሺህ እንደማይበልጥ ያስታወሱት አቶ ፈሪድ በጣቢያው በተደረገው አቅም የማሳደግ ሥራ የደንበኞች ቁጥር በአሁኑ ወቅት ወደ 52 ሺህ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የተከናወኑ የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች በክልሉ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት እገዛ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል። ሐረር የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ በአሁኑ ሰዓት ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ለፋብሪካዎች እና ለሌሎች ደንበኞች አስተማማኝ ኃይል እየቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በከተማዋና በዙሪያዋ የሚገኙ አርሶ አደሮችም የመስኖ ልማት ሥራዎችን ለማከናወን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠቀም በመጀመራቸው ምርታማነትን በማሳደግ የራሱን አስተዋፅዖ እያበረከተ እንደሆነም አመልክተዋል። እንደ አቶ ፈሪድ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ከተማ ለሚመጣው የውሃ መስመር አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ በከተማዋ ይስተዋል የነበረውን የውሃ አቅርቦት ችግር እንዲቀረፍ አስችሏል። የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራው የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን እርካታ እያሳደገ እንደሚገኝ መሆኑን የገለፁት ሥራ አስፈፃሚው በ2015 በጀት ዓመት በተከናወነ የዳሰሳ ጥናት የእርካታ መጠኑ 72 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 2016 ዓ.ም

photo content
+7

በማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍል ውስጥ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ……….///…….... በሐረር ቁጥር ሦስት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ 1 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የቴክኒካል ድጋፍ ባለሙያ አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንደገለፁት እየተከናወነ የሚገኘው የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን የሚያግዝ ነው። የአቅም ማሳደግና የማሻሻያ ሥራው በማከፋፈያ ጣቢያው ቀደም ሲል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩትን መቆጣጠሪያዎች በሌላ መቆጣጠሪያ ለመቀየር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ቴዎድሮስ እንደገለፁት ቀደም ሲል የነበረው የጣቢያው መቆጣጠሪያ በአየር የሚሰራ (vacume switchgear ) ሲሆን በአሁኑ ወቅት እየተለወጠ ያለው መቆጣጠሪያ ደግሞ በጋዝ የሚሰራ ጂ.አይ.ኤስ (Gas Insulated System) ነው፡፡ የማሻሻያ ሥራው በ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ላይ እየተከናወነ እንደሚገኝ ያነሱት አቶ ቴዎድሮስ ይህም የጣቢያውን የቁጥጥር ሥራ ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ለማከናወን ያስችላል ብለዋል። የጂ.አይ. ኤስ መቆጣጠሪያ ብሬከር ገጠማ ሥራው ሲጠናቀቅ በአንድ ላይ ይወጡ የነበሩ ሁለት ወጪ መስመሮች በተናጠል እንዲወጡ ከማድረጉም ባሻገር የ33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን ቁጥር ከአራት ወደ ስድስት ከፍ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል። ሁለቱ መስመሮች በአንድ ላይ ወጪ በሚሆኑበት ጊዜ በታቀዱ የጥገና ሥራዎች እና ድንገት በሚያጋጥሙ ችግሮች ሳቢያ የኃይል መቆራረጥን ከማስከተሉም በተጨማሪ በኢነርጂ ሜትር ላይ አሉታዊ ጫናዎች ያሳድራሉ። በአየር የሚሰራው መቆጣጠሪያ በነበረበት ወቅት ችግሮች ሲያጋጥሙ የጥገና ሥራ በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናወን ረዘም ያለ ጊዜ ይወስድ እንደነበር ባለሙያው አስታውሰዋል። የመቆጣጠሪያው መቀየር የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚረዳም ነው ባለሙያው የተናገሩት። በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ የሚገኘው የጥገና ሥራ የኃይል አቅርቦቱ ሳይቋረጥ እየተከናወነ እንደሆነም አመልክተዋል። የጣቢያውን መቆጣጠሪያ የመቀየር ሥራ በምስራቅ አንድ እና ሁለት ሪጅን የጥገና ባለሙያዎች በራስ አቅም መከናወኑ በቀጣይ በጥገና ሥራዎች ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት፣ ዕውቀትን ለማሸጋገር እና ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ለማዳን ያግዛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 01 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዘገበ .........///........ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር አምስተኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኮልፌ ክፍለ ከተማን ሁለት ለባዶ በማሸነፍ በሊጉ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል። ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ጎል አዳኙ መሳይ ሰለሞን እና ናትናኤል ሰለሞን ሁለቱን ጎሎች አስቆጥረዋል። በጨዋታው ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው የኢትዮ-ኤሌክትሪኩ ተጫዋች ናትናኤል ሰለሞን የጨዋታው ኮከብ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ መሆን ችሏል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በዚህ የውድድር ዓመት ያደረጋቸውን አምስት የሊግ ጨዋታዎች ሁሉንም በማሸነፍ ብቸኛው ክለብ ሲሆን በ15 ነጥብ እና በ8 ንፁህ ጎል በሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ትናንት የተከናወነውን ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስን በመቆጣጠር እና ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ በመድረስ የተጋጣሚውን በር ፈትሿል። በአንፃሩ ኮልፌዎች አልፎ አልፎ ወደ ፊት ለመምጣት ከመሞከራቸው በስተቀር ሙሉ በሙሉ በመከላከል ላይ የተመሠረተ አጨዋወት ሲተገብሩ ታይተዋል። የከፍተኛ ሊግ 6ኛ ሳምንት መርሀግብር በመጪው ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከንብ እግር ኳስ ክለብ ጋር ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 27 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+9

ከጥቃት ነፃ የሆን ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም የመፍትሔው አካል ሊሆን ይገባል ………///………. ዓለም አቀፍ የፀረ ፆታ ጥቃት ቀን “መቼም፣ የትም፣ በምንም ሁኔታ ፆታዊ ጥቃትን ዝም አንበል” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ተከብሯል፡፡ በመርሀ ግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኻኝ እንደተናገሩት የሴቶችን ጥቃት ለማስቆም ሰላምን ማስፈን ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል፡፡ ከጥቃት ነፃ የሆን ትውልድ ለመፍጠር ሁሉም ከቤት ጀምሮ በሥራ ቦታው በኃላፊነት ስሜት በመንቀሳቀስ የመፍትሔ አካል እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተናገሩት የፀረ - ፆታዊ ጥቃት ዘመቻ በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል በመሆኑ ሁሉም ሀገራዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡ የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር አባል ወ/ሮ ሰናይት ጣሰው በስነስርዓቱ ላይ ባቀረቡት የውይይት ሰነድ በሴቶች እና ህፃናት ላይ ስነ ልቦናዊ፣ ወሲባዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊና አካላዊ ጥቃቶች እንደሚፈፀሙ አብራርተዋል፡፡ ጥቃቶቹን ለመከላከል ግንዛቤ መፍጠርና የወጡ ህጎችን በአግባቡ ማስፈፀም እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡ በውይይቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የተቋሙ ሠራተኞችም አስተማሪና አመለካከት ለዋጭ የሆኑ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች እንደሚያስፈልጉ ገልፀው ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡ ዓለም አቀፍ የፀረ ፆታ ጥቃት ቀን በዓለም ለ32ኛ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ18ኛ ጊዜ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም