uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 548 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 340-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 158-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 548 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.05% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.01% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 053 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 491 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 548
Obunachilar
-724 soatlar
+147 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
በሪሁ አረጋዊ በዳይመንድ ሊግ የ5 ሺህ ሜትር አሸናፊ ሆነ ........///........ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነው በሪሁ አረጋዊ ባሳለፍነው ሌሊት በቤልጂየም ብራስልስ በተከናወነው የ5ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ሩጫ ድል ቀንቶታል። አትሌት በሪሁ ርቀቱን 12 ደቂቃ 43 ሰከንድ ከ66 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 1ኛ በመውጣት አሸናፊ ሲሆን የሀገሩ ልጆች አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት እና አትሌት ጥላሁን በቀለ ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል። የዳይመንድ ሊግ በአትሌቲክስ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛውን የገንዘብ ሽልማት የሚያስገኝ ውድድር ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በበጀት ዓመቱ አምስት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ታቅዷል …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ጨምሮ አምስት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት የአላማጣ - ኮምቦልቻ - ለገጣፎ ባለ 230 ኪሎ ቮልት 2ኛ ሰርኪዩት ዝርጋታ፤የበቆጂ እና ደብረ ታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ፤ የኮተቤ ግቢ ዕድሳት እና ማሻሻያ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ በተጨማሪም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዕድሳት እና የማሻሻያ ሥራ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ እና የገዳ ስፔሻል ኢኮኖሚክ ዞን 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክቶችን 75 በመቶ ለማድረስ እንደሚሰራም ነው የገለፁት፡፡ በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 99.4 በመቶ፤ የኮይሻ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት 73.96 በመቶ፤ የአይሻ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን 95.58 በመቶ ለማድረስ መታቀዱንም ነው አቶ አሸብር ያስታወቁት፡፡ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ የኃይል መቆራረጥን ከመቀነስ ባሻገር የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን እንደሚያሳድጉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ለበቆጂ ታሪክና የመልማት ፍላጎት ዕውቅና የሰጠ ነው ……..//……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የሚገነባው የበቆጂ ባለ230/33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ለበቆጂ ታሪክና ለነዋሪዎቿ የመልማት ፍላጎት ዕውቅና የሰጠ መሆኑን የከተማው አስተዳደር ገለጸ፡፡ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ ብርሃኔ ለገሠ እንደገለጹት በቆጂ ባፈራቻቸው ብርቅዬ አትሌቶች በዓለም አደባባይ የምትታወቅ ታሪካዊ ከተማ ብትሆንም እስከአሁን ድረስ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት አልነበራትም፡፡ ይህም ኢንቨስተሮች ወደ አካባቢው መጥተው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዳያፈሱና ከተማዋም በታሪኳና በመልማት አቅሟ ልክ እንዳትለማ እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ የአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት የአካባቢው ሕዝብና መስተዳድር ተደጋጋሚ ጥያቄ እንደነበር የተናገሩት ከንቲባ ብርሃኔ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄውን ለመመለስ የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያን በራስ አቅም እየገነባ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በፍጥነት እንዲጠናቀቅና አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ሕዝቡና መስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ከማከፋፍያ ጣቢያው ግንባታ ጋር ተያይዞ አሁን ላይ ከተማዋ በልማትና ዕድገት እንድትሮጥ የሚያስችሉ በርካታ ባላሀብቶች ኢንቨስት ለማድረግ ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለአካባቢው የረጅም ጊዜ የመብራት ጥያቄ በተሰጠው ምላሽ መደሰታቸውን የሚናገሩት ከንቲባዋ በተለይም ፕሮጀክቱ በራስ አቅም በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑ ልዩ ኩራት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የሳይቱ አስተባባሪ አቶ እንዳልካቸው ጃምቦ በበኩላቸው የበቆጅ 230/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እና የአንድ ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ከሚያዚያ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በራስ ኃይል እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን ላይ የስዊችያርድ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው የተከላና መስመር ዝርጋታዎች እንዲሁም የቅድሚያ ፍተሻና ሙከራ ሥራ ተጠናቆ የመጨረሻውን የፍተሻና የሙከራ ሥራ ለመስራት በዝግጅት ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ከሚገነቡት አራት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ውስጥ የሦስት ምሰሶዎችን የመትከል ሥራ መጠናቀቁንና የቀሪው ሥራም እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ እንዳልካቸው ገለጻ ከውስጥ ለውስጥ መንገድ እና ከኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚቀሩ ሥራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የማካካሻ ዕቅድ አውጥተውና አስፈላጊ ዕቃዎችን አሟልተው እየሰሩ ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትዕግስት በለው እንደገለጹት የፕሮጀክቱ የሲቪልም ሆነ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ በተቋሙ የራስ ኃይል የሚከናወን ሲሆን በፕሮጀክቱ ላይ እየተሳተፉ ያሉ ሠራተኞች በሕዳሴ ግድብ ላይ ጭምር አሻራቸውን ያኖሩ ናቸው፡፡ 8 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና 19 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞለት የሚገነባው የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያና የ1 ኪሎ ሜትር ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሲጠናቀቅ ለአካባቢው ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ስበትን የሚያመጣና ኢኮኖሚውን የሚያነቃቃ ነው ብለዋል፡፡ የበቆጅ ማከፋፍያ ጣቢያ በ230 ኪሎ ቮልት ከመልካ ዋከና ተቀብሎ 10 ወጭዎች በ33 ኪሎ ቮልት ያለው ሲሆን እስከ 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝና ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www
+6
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም

ተቋሙ የመፈጸም አቅሙን በማሳደግ ተወዳዳሪ የኃይል ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው ........//....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጣዊ የመፈጸም አቅሙን በማሳደግ ለሀገር ዕድገት አለኝታ የሆነና በአፍሪካ ተወዳዳሪ የኃይል ማዕከል ለመሆን እየሠራ መሆኑን አስታወቀ። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሐ ጌታቸው እንደገለጹት ተቋሙ አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ተወዳዳሪ ለመሆን የመፈጸም አቅሙን በማሳደግ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በራስ ኃይል እያከናወነ ይገኛል። ቀደም ሲል በውጭ ኮንትራክተሮች ብቻ ይገነቡ የነበሩ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና የማስተላለፊያ መስመሮች አሁን ላይ በተቋሙ የራስ አቅም እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ፍስሐ ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ተቋሙ ከ1970ዎቹ ጀምሮ በራስ ኃይል የተለያዩ የጥገና ስራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በግንባታ ላይ የሚገኙትን የበቆጂ፣ የገዳ ልዮ የኢኮኖሚ ዞናና የደብረታቦር ማከፋፈያ ጣቢያዎች መገንባቱ የተቋሙ ውስጣዊ አቅም ለመገንባቱ ማሳያ ነው። የኦፕሬተር መኖሪያ ቤቶችን፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ እና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ጥገና በተቋሙ ባለሙያዎች እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ፍስሐ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የተለያዩ ዘርፎች ላይ ጭምር የተቋሙ ባለሙያዎች እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም ተቋሙ ጊዜንና ገንዘብን በቆጠበ መልኩ ጥናቶችን መሠረት በማድረግ በተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት፣ የሕብረተሰቡን የመልማት ጥያቄዎች በዘላቂነት ለመፍታትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመስጠት እንዳስቻለው አብራርተዋል። በማመንጫ፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ችግር ሲያጋጥም ከውጭ ሀገር ባለሙያ እስኪመጣ ድረስ ይከሰት የነበረውን የኃይል ብክነትና የሚወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን በማዳን በኩልም ሚናው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ራዕይ ለማሳካት እና የመፈጸም አቅሙን ለማሳደግ ለሰው ኃይል ግንባታው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚህም ከኤሌክትሮ ሜካኒካል ጋር በተያያዘ የአጭር ጊዜ ሥልጠና የሚሰጥበት የራሱ ማሰልጠኛ ተቋም እንዳለው የገለጹት አቶ ፍስሐ ከዚህ በተጨማሪም በየጊዜው የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ስልጠናዎችን በማመቻቸት፣ ልምድ ያላቸው ሠራተኞቹን ከአዲሶቹ ጋር በማቀናጀት እና በቴክኖሎጂ የታገዙ አዳዲስ አሰራሮችን በመተግበር እየሠራ ይገኛል ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ለአዲስ ዓመት በቂ ኃይል በማቅረብ የኃይል መቋረጥ እንዳይከሰት አድርጓል ………/////……… በ2017 አዲስ ዓመት ዋዜማ እና በዕለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ያለምንም እጥረት መቅረቡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ ማዕከሉ እንደገለፀው በበዓሉ ዋዜማና በበዓሉ ዕለት ከ4 ሺህ 2 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል በላይ ዝግጁ የተደረገ ቢሆንም ጥቅም ላይ የዋለው 3 ሺህ 737 ሜጋ ዋት ኃይል ብቻ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ዝግጁ በማድረጉ በትግራይ ክልል እና በኮምቦልቻ ከሚገኙ ፋብሪካዎች በስተቀር ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀሙ ፋብሪካዎችና ኤክስፖርት የሚደረግባቸው ሀገራት ጭምር ያለምንም የኃይል አቅርቦት ችግር እንደመደበኛው ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘታቸውንም ማዕከሉ ገልጿል፡፡ በክረምቱ ዝናብ የተነሳ የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ የያዘውን ከፍተኛ ውሃ ለማስተንፈስ ሲባል ሥራ አቁሞ የነበረው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በበዓሉ ዋዜማ ሥራ እንዲጀምር በመደረጉ በትግራይ ክልል አንዳንድ ከተሞች ተከስቶ የነበረው የኃይል መቋረጥ እንዲስተካከል መደረጉንም ማዕከሉ አስታውቋል፡፡ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የኃይል መቋረጥ እንዳያጋጥም የየዘርፉ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት ተገቢውን ትኩረት ሰጥተው ሰርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content

የዋዜማ የኃይል አጠቃቀም ከፍተኛ ጭነት 3737 ሜጋ ዋት ሆኖ ተመዝግቧል .........///........ የ2017 ዓ.ም አዲስ ዓመት ዋዜማ የኃይል አጠቃቀም ከፍተኛ ጭነት 3737 ሜጋ ዋት ሆኖ ተመዝግቧል። የኃይል ፍላጎቱ 3 ሺህ 9 መቶ ሜጋ ዋት እንደሚደርስ ተተንብዮ የነበረ ሲሆን መጠባበቂያ ኃይልን ጨምሮ እስከ 4 ሺህ 2 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ ተደርጎ ነበር። አዲሱ ዓመት የሠላም እና የደስታ ይሁንልዎ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙ ሠራተኞች በዓልን ጨምሮ ዓመቱን በሙሉ 24 ሠዓት በሥራ ላይ ናቸው .........///........ በኃይል ማመንጫ እና በማከፋፈያ ጣቢያ እና በማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኦፕሬሽንና ጥገና ሠራተኞች በዓላትን ጨምሮ ዓመቱን በሙሉ 24 ሠዓት  በሥራ ማሳለፍ የዘወትር ተልዕኳቸው ነው። የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ ያሉት ኃይል ማመንጫዎች የሚያመነጩትን ኃይል በማመጣጠን ወደሚፈለገው አካባቢ የማድረስ ሥራ ይሰራሉ። የ 24 ሠዓት ሥራ የተቋሙ ሠራተኞች የዘወትር ተልዕኮ ቢሆንም እንደ አዲስ ዓመት ያሉት የህዝብ በዓላት በደስታ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ደግሞ በልዩ ትኩረት ያለማቋረጥ በፈረቃ ይሰራሉ። የዕለት ተዕለት ሥራቸው ከሚከውኑት ባለሙያዎች በተጨማሪ በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የኃይል መቋረጥ እንዳያጋጥም እና ድንገተኛ የኃይል መቋረጥ ቢያጋጥም እንኳ የአስቸኳይ ጥገና ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ግብረ ኃይል መቋቋሙ ማሳያ ተደርጎ ሊጠቀስ ይችላል። አዲሱ ዓመት የሠላም እና የደስታ ይሁንልዎ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ወደፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ እን
እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ወደፊት እንድንጓዝ የሚያደርግ እንዲሆን በአግባቡ ማቀድና በትጋት መሥራት ይጠይቃል፡፡ እንደ ተቋም በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ የያዝነውን ተቋማዊ ዕቅድ ለማሳካት የምንተጋበት፤ "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ራዕያችንን እውን ለማድረግ የምንሠራበት፣ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ስኬት የምናስመዘግብበት እንዲሁም በግል ያቀድናቸውን ውጥኖች ከግብ የምናደርስበት የሠላም፣ የደስታና የስኬት ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ!! መልካም አዲስ ዓመት! አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

ለአዲስ ዓመት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል ………////……… ለ2017 አዲስ ዓመት 4 ሺህ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ ማዕከሉ እንደገለፀው በየጊዜው ከሚታየው የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ በመነሳት በዘንድሮ አዲስ ዓመት እስከ 3 ሺህ 9 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያስፈልግ ተተንብይዋል፡፡ ይሁንና ከሰሞኑ የተከዜ ግድብን ለማስተንፈስ በተለቀቀው ውሃ እና በአላማጣ - ባህር ዳር የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በደሰረ ጉዳት ምክንያት ኃይል በተቋረጠባቸው የአማራ እና የትግራይ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች የኃይል መቆራረጥ ሊኖር ቢችልም የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫን ወደ ሲስተም ለማስገባትና አካባቢዎቹ ለአዲስ ዓመት ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በኃይል ማመንጫዎች፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ አስቀድሞ የፍተሻ እና የጥገና ሥራ የተከናወነ ሲሆን ድንገተኛ ችግር ቢያጋጥም አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ቡድን ዝግጁ ተደርጓል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ለአዲስ ዓመት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል ………////……… ለ2017 አዲስ ዓመት 4 ሺህ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆ
ለአዲስ ዓመት የኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል ………////……… ለ2017 አዲስ ዓመት 4 ሺህ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት ኃይል ዝግጁ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ ማዕከሉ እንደገለፀው በየጊዜው ከሚታየው የኃይል አጠቃቀም አዝማሚያ በመነሳት በዘንድሮ አዲስ ዓመት እስከ 3 ሺህ 9 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያስፈልግ ተተንብይዋል፡፡ ይሁንና ከሰሞኑ የተከዜ ግድብን ለማስተንፈስ በተለቀቀው ውሃ እና በአላማጣ - ባህር ዳር የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በደሰረ ጉዳት ምክንያት ኃይል በተቋረጠባቸው የአማራ እና የትግራይ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች የኃይል መቆራረጥ ሊኖር ቢችልም የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫን ወደ ሲስተም ለማስገባትና አካባቢዎቹ ለአዲስ ዓመት ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በኃይል ማመንጫዎች፣ በማከፋፈያ ጣቢያዎችና በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ አስቀድሞ የፍተሻ እና የጥገና ሥራ የተከናወነ ሲሆን ድንገተኛ ችግር ቢያጋጥም አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ቡድን ዝግጁ ተደርጓል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8