uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 528 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 328-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 528 obunachiga ega bo‘ldi.

06 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 6 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.84% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.05% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 323 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 492 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 07 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 528
Obunachilar
-324 soatlar
-97 kunlar
+630 kunlar
Postlar arxiv
ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ከ66 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ .......................................................//................................................... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2012 በጀት ዓመት ለሱዳንና ጅቡቲ ካቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ከ66 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን የማርኬቲንግና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ቢሮ አስታወቀ፡፡ ቢሮው በ2012 በጀት ዓመት 56 ነጥብ 92 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ከ66 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ሰብስቧል፡፡ ይህም የዕቅዱን 116 ነጥብ 5 በመቶ በማከናወን ከዕቅድ በላይ ገቢ መገኘቱ ተገልጿል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከተሰበሰበው ገቢ 37 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ከጅቡቲ እና ቀሪው 29 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ከሱዳን የተገኘ ነው ተብሏል፡፡ በዚህ ዓመት ከሁለቱ ሀገራት የተገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ገቢ ከ2011 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ11 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ብልጫ እንዳለው ተነግሯል፡፡ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በቂ ውኃ መያዛቸውና የኃይል መቆራረጥ መቀነሱ ለዕቅዱ መሳካት አስተዋፅኦ ማድረጉ ተብራርቷል፡፡ በቅርቡም ለኬኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ እና የኤሌክትሪክ ኮንቨርተር ጣቢያ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከሦስቱ ሀገራት በተጨማሪ በቀጣይ ከሶማሌ ላንድ፣ ከታንዛኒያ እና ደቡብ ሱዳን ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ለመፍጠር የሁለትዮሽ ግንኙነት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡

eep.mp477.93 MB

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቀቀ። .................///.................. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ግድቡ በመጀመሪያው ዙር 4.9 ቢሊዬን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በመያዝ በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል። ይህ በግድቡ የተያዘው ውሃ በመጪው ዓመት በሁለት ተርባይኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ያስችላል።

የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሊትና ግንባታ ጎን ለጎን ይከናወናል …………………..//////………………………. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሊትና ግንባታ ጎን ለጎን እንደሚከናወን የው
+1
የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሊትና ግንባታ ጎን ለጎን ይከናወናል …………………..//////………………………. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሊትና ግንባታ ጎን ለጎን እንደሚከናወን የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ገለጹ፡፡ የግድቡ ከፍታም በዚህ ዓመት ከ525 ወደ 560 በማደጉ በመጀመሪያው ሙሊት ለማከናወን የታቀደውን የ4.9 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚያዝ መሆኑን ሚኒስትሩ አመልክተዋል፡፡ ከቴክኒክ አንጻር የውሃ አሞላሉና አስተዳደሩ፣ በድርቅ ጊዜ የሚኖረው የውሃ አለቃቀቅና አስተዳደር በሚመለከት የሚዘጋጀው የህግ ማዕቀፍ ወይም መመሪያ ላይ ድርድሮች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ የሚዘጋጀው የህግ ማዕቀፍ የዛሬውንም ሆነ የወደፊቱን ትውልድ ጥቅም ተገቢ ባልሆኑ አንቀጾች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በማይታሰርበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በድርድሩም ሂደት መግባባት ላይ የተደረሰባቸው ነጥቦች መኖራቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ባልተግባቡባቸው ነጥቦች ዙርያ የየሀገራቱ ሪፖርቶች ለአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ፕሬዘዳንት ቀርበዋል ብለዋል፡፡ ሪፖርቶቹን የተደራዳሪዎቹ ሀገራት መሪዎቹ ተመልክተው በሚያስተላልፏቸው መመሪያዎች ድርድር የሚቀጥልበት ሁኔታ መኖሩን ከሚኒስቴሩ ማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡ ባለፈው ሰኞ በቆመውና 11 ቀናትን ባስቆጠረው ድርድር ከኬንያ፣ ከኮንጎ፣ ከማሊ፣ከናይጀሪያ፣ ከዙምባቡዌ፣ ከማዳጋ ስካር ፣ከደቡብ አፍሪካ፣ ከአውሮፓ ህብረትና ከአሜሪካ የተውጣጡ 11 ኤክስፐርቶችና ታዛቢዎች የድርድሩን ሂደት በበይነ መረብ ሲከታተሉ እንደነበር ክቡር ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል፡፡ የውሃ ሙሊቱን በተመለከተ በሳተላይት የሚታዩት ምስሎችም ትክክለኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡

Different media reported that Ethiopia will not start filling GERD without reaching an agreement between the lower riparian c
Different media reported that Ethiopia will not start filling GERD without reaching an agreement between the lower riparian countries. The fact on the ground is Ethiopia is finalizing the construction to start impounding and will start filling the dam two weeks later. It wants to see the impoundment and negotiation process as a separate process. Reaching to an agreement is not a prerequisite to fill the dam. If the three countries agreed on the disputing points within two weeks, Ethiopia will be pleased. If not reaching to an agreement, filling the dam will proceed as planned. The time frame is an indication as to when the filling will start, scheduled by Ethiopia.

ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ ባይደረስም የውሃ ሙሌቱን ታከናውናለች! ኢትዮጵያ በጋራ የመጠቀም እና አብሮ የማደግ መርህን የምትከተል ሀገር ናት፡፡ ይሁንና በራሷ የተፈጥሮ ሀብት ለመጠቀም የሌሎችን ፈቃድ ወይም ይሁንታ የማግኘት ግዴታ የለባትም፡፡ በዘንድሮው የክረምት ወቅት ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ውሃ ለመያዝ የምትሰራው ስራ 60 በመቶ የሚሆነው የሃገራችን ህዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ የተጀመረውን ጥረት ያግዛል፡፡ በአንፃሩ በጋራ ተጠቃሚነት ለማታምነው ግብፅ ‹‹ከእኔ ብቻ ልኑር›› የዘመናት ግትር አስተሳሰቧ እንድትወጣና በፍትሃዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነት ምህዋር ላይ እንድትሽከረከር ያደርጋታል፡፡ ግብፅ በቀጠናውም ሆነ በአህጉሪቱ ላይ ሁለንተናዊ ብልጫን መያዝ ስለምትፈልግ ግድቡ ውሃ እንዳይያዝ ዓለም አቀፍ ተቋማትን በመጠቀም ተፅዕኖ ለማሳደር ስትሞክር ትታያለች፡፡ ይህም ድርጊቷ የሃገራችንን ውሳኔ የሚቀለብስ ባይሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ በሃገራቱ መካከል ፍጥጫ እየተካረረ እንዲመጣ አድርጓል፡፡ የአፍሪካ ህብረት ኃላፊነቱን ወስዶ የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ መሪዎችን በመጋበዝ ዓርብ ምሽት ሰኔ 19 ቀን 2012 ዓ.ም ውይይት ማድረጋቸው በዚህ መነሻነት ነው። ውይይቱ የሃገራትን የተናጠል ፍላጎት ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት ለማምጣት ያለመ ሲሆን የግብፅ ሚዲያዎች ግን ከውይይቱ መንፈስ ውጪ ‹‹ኢትዮጵያ ስምምነት ላይ ሳይደረስ የውሃ ሙሌቱን ላለመጀመር ተስማማች›› የሚል የተሳሳተ ወሬ በመንዛት ላይ ይገኛሉ። ይህንንም የአፍሪካ ህብረት ተችቶታል፡፡ እውነታው ግን እነሱ እንደሚሉት ሳይሆን ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ የምታከናውነውን ቀሪ ስራና የራሷን ጥቅምና ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ እንጂ በፍራቻና በተፅዕኖ የራዘመም የሚራዘምም የውሃ ሙሊት የማይኖር መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡ ሁሉም ሰው እንደሚያውቀው በዘንድሮው ክረምት ውሃ እንይዛለን ተባለ እንጂ በየትኛው ቀን ላይ ውሃ የመያዝ ስራው እንደሚጀምር ቀድሞውንም ይፋ አልተደረገም። ሐምሌ የሚለው ወር የተመረጠው ክረምቱ የሚገባበት ወር በመሆኑ ሐምሌ 1 የመሙላት ሁደቱ ይጀመራል ተብሎ አልተነገረም፡፡ ስለሆነም እስከቀሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ድረስ ኢትዮጵያ ግድቡን በውኃ ላለመሙላት የተስማማችበትን ምክንያት አንሻፎ ማቅረብ ህዝባችን በግድቡ ላይ የያዘውን ወጥ አቋም በመሸርሸር ህዝባዊ ድጋፉን ለማሳጣት ከማለም ውጭ ሌላ የተለየ ትርጉም አይሰጠውም፡፡ በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት የሚለው ቃል የተመረጠው በዘፈቀደ ሳይሆን ውሃ ለመያዝ ወሳኝ የሚባሉ የግድቡ ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅና በዚህ ዓመት4 ነጥብ 9 ቢሊየን ሜ.ኪ. ውሃ የሚተኛበትን መሬት በማፅዳት የደን ምንጣሮ ሥራውን በፍጥነት ለመከናወን ሲባል ነው፡፡ ይህ ውሳኔ እንደሀገር ውሃውን ለመያዝ አሁንም ጽኑ አቋም እንዳለን የሚያሳይ እንጂ የግብፅ ሚዲያዎች እንደሚሉት የኢትዮጵያን ተሸናፊነትና የግብጽን አሸናፊነት አያሳይም፡፡ ድርድሩን ከግድቡ ውሃ መሙላት ጋር ማያያዝ ተገቢ እንዳልሆነ ከሚያሳዩን ጉዳዮች አንዱ ሦስቱ ሀገራት እ.ኤ.አ. በ2015 ማርች ላይ የተስማሙበት የመርሆዎች ስምምነት ኢትዮጵያን የግድቡን ግንባታ እያከናወነች ውሃ ለመያዝ የሚከለክላት አለመሆኑ ነው፡፡ የግድብ ግንባታው ደግሞ ኮንክሪት ሞልቶ መተው ሳይሆን ውሃ ይዞ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ስለሆነ ኢትዮጵያ በዚሁ ስሜት እተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡በመሆኑም ሁላችንም የሃገራችንን ጥቅምና ፍላጎት ከፍ በሚያደርግ መልኩ ሃገራዊ አንድነታችንን ማጠናከር ይኖርብናል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የተጀመረው ውይይትም አጀንዳውን ዓለም ባንክና ከአሜሪካ እጅ አውጥቶ አፍሪካዊ በማድረግ ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለማምጣት የታሰበውን የህብረቱን ዓላማ የሚደግፍ ነው፡፡ ኢትዮጵያም በአፍሪካ ወንድሞቿ ፊት በተፈጥሮ ሀብቷ ለመበልፀግ የምታደርገው በፍትሐዊ ተጠቃሚነትና በጋራ የመልማት ፍላጎትን ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለማሳየት ከፍተኛ ዕድል ይሰጣታል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሁላችንም አንድ መሆን ከቻልን የማንሻገረው ፈተና እና የማንወጣው ችግር ስለማይኖር በሀገራዊ አጀንዳዎቻችን ላይ የጋራ አቋም መያዝ ይኖርብናል!

የሕዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት አልተራዘመም። የሙሌቱን ስራ ለማከናወን የሚደረገው ዝግጅት እንደተጠናቀቀ በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ ሙሌቱ ይጀመራል።
የሕዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት አልተራዘመም። የሙሌቱን ስራ ለማከናወን የሚደረገው ዝግጅት እንደተጠናቀቀ በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ ሙሌቱ ይጀመራል።

በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በዘራፊዎች የተቋረጠው መስመር ተጠገነ ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ከሰኔ 17
+3
በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በዘራፊዎች የተቋረጠው መስመር ተጠገነ ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ከሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ/ም ጀምሮ ላለፉት አምስት ቀናት ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠግኖ አካባቢው ኃይል ማግኘት ጀምሯል፡፡ በአካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ኃይል ተቋርጦ የቆየ ሲሆን ችግሩ በተከሰተበት አካባቢ 20 ምሰሶዎችን በማቆም መስመሩን ለማገናኘት ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ የተቋማችን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የጥገና ባለሙያዎች ችግሩን ለመቅረፍ ለቀናት ሲያደርጉት የነበረው ጥረት እየጣለ ባለው ዝናብ ምክንያት አስቸጋሪ የነበረ ቢሆንም ዛሬ አካባቢው ኃይል እንዲያገኝ ማድረግ አስችሏል፡፡ በኢንደስትሪ መንደሩና ከዚህ ጋር በተገናኘ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ያላችሁ ነዋሪዎች የችግሩን ግዝፈት በመረዳት ኃይል መልሰን እስከምናገናኝ በትዕግስት ስለጠበቃችሁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ ሰኔ 21 ቀን 2012 ዓ/ም

የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢውን ኃይል መልሶ ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በ
+2
የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢውን ኃይል መልሶ ለመቀጠል ርብርብ እየተደረገ ነው ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት የተቋረጠውን ኃይል መልሶ ለማገናኘት ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች በሌላ የእንጨት ምሰሶዎች በመተካት አካባቢዎቹን ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ከትላንት ጀምሮ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን እስካሁንም 20 ምሰሶዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ጉድጓዶች ተቆፍረው ስድስት ምሰሶዎች ተተክለዋል፡፡ የሁሉም ምሰሶዎች ተከላ እንደተጠናቀቀም መስመሩን የማገናኘት ስራ የሚሰራ ይሆናል፡፡ በትናንትናው ዕለት 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ በሌላ ምሰሶ ላይ ተጨማሪ ጉዳት በማድረሱ የቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል እንደተቋረጠ መግለፃችን ይታወሳል፡፡ የፌስቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ሰኔ 18 ቀን 2012 ዓ/ም

በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው ኃይል ተቋረጠ ................///////.................. በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደርና አካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት በኢንደስትሪ መንደሩና በአካባቢው ኃይል ተቋርጧል። 132 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ በዘራፊዎች ተፈቶና ተቆርጦ በመውደቁ በሌላ ምሰሶ ላይ ተጨማሪ ጉዳት በማድረስ ነው ኃይል የተቋረጠው። በዚህም የኢንደስትሪ መንደሩን ጨምሮ በሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ በቦሌ አራብሳ፣ በአየር መንገድ ማህበር፣ በጎሮ፣ በአይሲቲ ፓርክ፣ በገርጂ ወረገኑና በገርጂ ካሳንቺስ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጣል። ችግሩ እንደተከሰተ የተቋማችን የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የጥገና ባለሙያዎች ችግሩን ለመቅረፍ እንቅስቃሴ ቢጀምሩም ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ምሰሶውን መልሶ በማቆም መስመሩን ማገናኘት አልተቻለም። የተሰረቁትን የምሰሶ አካላት በሌላ ተክቶ መልሶ ለማቆም መለዋወጫና በርካታ ቀናት የሚፈልግ ቢሆንም ሌላ ተለዋጭ የእንጨት ምሰሶ በመትከል መስመሩን ለማገናኘት ጥረት ተጀምሯል። በመሆኑም በኢንደስትሪ መንደሩም ሆነ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል መልሰን እስከምናገናኝ ድረስ ህብረሰተቡ በትዕግስት እንዲጠብቀንና ሌሎች የኃይል አማራጮችን እንዲጠቀም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሳስባል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከቦሌ ለሚ መስመር ጋር የተገናኘው የቃሊቲ አካባቢ መስመር ተጠግኖ ኃይል መስጠት ጀምሯል። በዚህ አጋጣሚ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት የሚያደርሰው ተፅዕኖ ሰፊ በመሆኑ ህብረተሰቡ ንብረቱን እንደራሱ ንብረት እንዲጠብቅና ድርጊቱን የሚፈፅሙ ግለሰቦችንም ለፍትህ አካላት እንዲጠቁም ጥሪያችንን እናቀርባለን። የፌስቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። https://www.facebook.com/320447995296707/posts/556093998398771/ ሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ/ም

የኮቪድ -19 ወረርሽኝን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት ተካሄደ ………………………/////……………….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮሮና ወረርሽኝ መከላከያ መንገዶች ዙሪያ ሜክሲኮ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤቱ ትናንት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡ መድረኩ የተዘጋጀው “ቤተሰባችን፣ድርጅታችን እና ሃገራችን ስለሚፈልጉን እንጠነቀቃለን፤ እናተም ተጠንቀቁ! ’’ በሚል መሪ ቃል ነው፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል በተለያዬ መንገድ መልዕክት ቢተላለፍም በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ እየመጣ አይደለም፡፡ በመሆኑም ለአፍታም ሳንዘናጋ ርቀታችንን በመጠበቅ፣ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብልን በማድረግ እና እጆቻችንን ቶሎ ቶሎ በመታጠብ ወይም በሳታይዘር በማጽዳት ከአላስፈላጊ የጤና ጉዳትና የህይወት መስዋዕትነት ራሳችንን መጠበቅ ይገባል ብለዋል፡፡ ‘‘ጤናችን በምናደርገው ጥንቃቄ ይጠበቃል፣ የታላቁ ህዳሴ ግድባችንም በምናደርገው ያላሰለሰ ጥረትና ድጋፍ ይጠናቀቃል’’ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ለተጨማሪ https://www.facebook.com/Ethioelectric/posts/555267431814761

የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች እና አመራሮች ደም ለገሱ …………………/////………………… የፊንጫ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች እና አመራሮች በደም እጥረት የሚሞቱ ሰዎችን እናድን በሚል
+4
የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች እና አመራሮች ደም ለገሱ …………………/////………………… የፊንጫ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች እና አመራሮች በደም እጥረት የሚሞቱ ሰዎችን እናድን በሚል መሪ ቃል ደም ለገሱ፡፡ የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ ሹመት በላይ እንደተናገሩት ከነቀምት ከተማ የጤና ባለሙያዎችን በማስመጣት 38 የድርጅቱ ሠራተኞች እና በጣቢው የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት ደም ለግሰዋል፡፡ የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፤ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፣ አባይ ጮመን ወረዳ የሚገኝ ሲሆን 134 ሜጋ ዋት ኃይል በማመንጨት ላይ ይገኛል፡፡ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። https://t.me/EEPCommuication ሰኔ 14 ቀን 2012 ዓ.ም.

ለአዋሽ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ ………………../////…………….. ለአዋሽ - ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት የሚያገለግ
ለአዋሽ ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ ………………../////…………….. ለአዋሽ - ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት የሚያገለግል የከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ስራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ስምምነቱ ለባቡር ፕሮጀክቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ባለ 230/132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ነው። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የቻይናው ፒንጋኦ ግሩፕ ኦቨርሲስ ማርኬቲንግ ዳይሬክተር ዣይ ያንቢን (Zhai Yanbin) ተፈራርመዋል፡፡ የባቡር ፕሮጀክቱ ካለው ሃገራዊ ጠቀሜታ አኳያ የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራ በተያዘለት የጊዜ መርሃ ግብር ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ እንዳለበት ዋና ስራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የመስመር ዝርጋታውን ለማጠናቀቅ ብቻ 11 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር እና 133 ነጥብ 48 የኢትዮጵያ ብር ተመድቧል፡፡ መንግስት የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ በሰጠው ትኩረት መሰረት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሸፈን መደረጉን ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ ሚስተር ዣይ በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ስለተገነዘብን ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ፣ ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡ 206 ኪ.ሜ ርዝመት የሚኖረው የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ግንባታ በ12 ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። የባቡር ፕሮጀክቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ስምምነት ሚያዚያ 30 ቀን 2012 ዓ/ም መፈረሙን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የአዋሽ - ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቆ ኃይል ብቻ ይጠብቃል።

የአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቀቀ **************** በአላማጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በትራንፎርመር ላይ የደረሰው ብልሽት ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ ኃይል በፈረቃ ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎች ያልተቆራረጠ ኃይል ማግኘት ጀምረዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመር ላይ ሚያዝያ አጋማሽ ላይ የደረሰው ችግር በአላማጣ፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ እና ማይጨው ከተሞችና አካባቢያቸው የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥና በከፊል የፈረቃ ስርዓት ውስጥ እንዲገቡ አድርጎ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ችግሩን በጊዜያዊነት ለመቅረፍ ቀድሞ የነበረውን የ66 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ባለ 20 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር በ12 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር በመቀየር ጥገና የተከናወነ ቢሆንም የተጠገነው ትራንፎርመር ኃይል የመሸከም አቅም እስከ ሰባ አምስት በመቶ በመሆኑ የፈረቃ አሰራርን ለማስቀረት አላስቻለም ነበር፡፡ ይሁንና ተጨማሪ ባለ 12 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንፎርመር በመትከል በከተሞቹ የፈረቃ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማስቀረት የሚያስችል ስራ ተሰርቷል፡፡ ተጨማሪ ትራንስፎርመሩ የማከፋፈያ ጣቢያውን አቅም ቀድሞ ከነበረው የተሻለ እንዳደረገውም ተገልጿል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የገጠመውን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሳምንታት በትዕግስት ለጠበቃችሁን የአላማጣ፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ እና ማይጨው ከተሞችና አካባቢያቸው ነዋሪዎች የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። https://t.me/EEPCommuication ሰኔ 12 ቀን 2012 ዓ.ም

ከሌሎች ምንጮች - EBC የስዊዝ መተላለፊያ ቦይ ዘመናዊ ግብጽን እንደገነባ ሁሉ፣ ታላቁ የሕዳሴ ግድብም ለኢትዮጵያ ከድህነት መውጫ መንገዷ ነው ተባለ ******************************* ግብጽ ከአስዋን ግድብ እና ሌሎች የኤሌክትሪክ ምንጮች ሕዝቧን ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ፣ ውጤታማ የሆነ የግብርና ውኃ አጠቃቀም፣ ቱሪዝም እና ሌሎች ዘርፎች ተጠቃሚ ማድረጓን ሚዲየም ዶት ኮም ላይ የወጣ ዘገባ አመልክቷል። የስዊዝ መተላለፊያ ቦይ ዘመናዊቷን ግብጽ እንደገነባ ሁሉ፣ በኢትዮጵያ ሙሉ ባለቤትነት ስር የሚተዳደረው እና ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን መሠረታዊ የሆኑ የድህነት እና ድርቅ ችግሮች ይፈታል ተብሎ ይጠበቃል ብሏል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለአገሪቱ የኤሌክትሪክ ብርሃን ማምጣት ብቻ ሳይሆን ለሌሎች አገራትም ጠቀሜታ እንዳለውም ገልጿል። ግድቡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም የምሥራቅ አፍሪካ አገራት በሆኑት ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛንያ የሚገኙ 70 ሚሊየን ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ጠቅሷል። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አንድን አገር ብቻ ሳይሆን የቀጠናውን አገራት ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ሲል መረጃው አመልክቷል። ኢትዮጵያ ከግድቡ ጋር በተያያዘ አሁን እያደረገች ያለው ግብጽ እ.አ.አ 1956 ላይ የስዊዝ መተላለፊያ ቦይን ከብሪታኒያ እና ፈረንሳይ አስተዳደር በመውሰድ የግብጻውያን አንጡራ ሀብት እንዳደረገችው ያለ ተግባር ብቻ ነው ሲል ዘገባው አትቷል።

ከሌሎች ምንጮች «እንደ ናይል የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት በበላይነት ተቆጣጥረው የሚጠቀሙበት ወንዝ በዓለም የለም» - ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ የአ.አ ዩ. መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ****
ከሌሎች ምንጮች «እንደ ናይል የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት በበላይነት ተቆጣጥረው የሚጠቀሙበት ወንዝ በዓለም የለም» - ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ የአ.አ ዩ. መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ************************************* (ኢ.ፕ.ድ.) እንደ ናይል የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት በበላይነት ተቆጣጥረው የሚጠቀሙበት ወንዝ በዓለም እንደሌለ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ አስታወቁ፡፡ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት፤ በዓለም ላይ ከ240 በላይ ወንዞች ሁለትና ከዚያ በላይ ሀገራትን አቋርጠው ያልፋሉ፡፡ አንዳንድ ምሁራን ደግሞ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ቁጥር 215 አካባቢ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ አብዛኞቹን ወንዞች የላይኞቹ እና የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ህብረት ፈጥረው እና ተባብረው ወንዞችን እንደሚጠቀሙ የገለጹት ፕሮፌሰር ያዕቆብ፤ በአንዳንድ ተፋሰሶች ግን የውሃው አመንጪ የሆኑ እና አቅም ያላቸው ሀገሮች አብዛኛውን ውሃ እየተጠቀሙ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር ያዕቆብ ማብራሪያ ሀገራት ህብረት ፈጥረው እያለሙ ካሉት ወንዞች መካከል ኢንዱስ ወንዝ ተጠቃሽ ነው፡፡ ይህንን ወንዝ ሕንድ እና ፓኪስታን ህብረት ፈጥረው እየተጠቀሙት ነው፡፡ በአውሮፓ የሚገኘውና 13 ሀገራትን የሚያቋርጠው ዳኑብ ወንዝም ሀገራት በትብብር እያለሙት ካሉት ወንዞች ተጠቃሽ ነው፡፡ በተመሳሳይ ስምንት ሀገራትን የሚያቋርጠው ራይን ወንዝም በተመሳሳይ ሀገራቱ በትብብር ያለማሉ፡፡ በምዕራብ እና በደቡብ አፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ወንዞችንም እንዲሁ ሀገራት ተግባብተው እንደሚያለሙ የጠቀሱት ፕሮፌሰሩ፤ ለአብነት ያህል ሴኔጋል ወንዝን ሴኔጋል፣ ማሊ እና ሞሪታኒያ የሦ

ርእሳነ መስተዳድሮቹ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ ...........................//////.................. የሰባት ክልል ርእሳነ መስተዳድሮች የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ
+4
ርእሳነ መስተዳድሮቹ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ ...........................//////.................. የሰባት ክልል ርእሳነ መስተዳድሮች የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጎበኙ። የአፋር፣ የአማራ፣ የኦሮሚያ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ የደቡብ ብ/ብ/ህዝቦች፣ የጋምቤላና የሶማሌ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮችና ምክትል ርዕሳነ መስተዳድሮች በኢኖቬቭንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢንጂነር አብርሃም በላይ እና በተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በመመራት የግድቡን ግንባታ ጎብኝተዋል። ዶ/ር አብርሃም በግድቡ ላይ ስለተከናወኑት ተግባራትና በመጪው ክረምት ውሃ ለመያዝ የሚሰሩትን ስራዎች በተመለከተ ገለፃ አድርገውላቸዋል። በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትልልቅ ስራዎች በሚሰሩበት ጊዜ ርዕሰ መስተዳድሮቹ ግድቡን መጎብኘታቸው የተለየ ትርጉም እንደሚሰጠውም ዶ/ር አብርሃም ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሮቹና ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮቹ በበኩላቸው የግድቡ ወቅታዊ የግንባታ ሂደት አበረታች እንደሆነ መመልከታቸውን ገልፀዋል። ይህም ስለግድቡ ለሚመሩት ህዝብ በተገቢው ሁኔታ ለመግለፅና በተለያዩ ወገኖች የሚሰነዘሩ አሉታዊ አስተያየቶችን ለማክሸፍ ያስችለናል ብለዋል። ርዕሰ መስተዳድሮቹና ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮቹ ከጉብኝቱ በኋላ ግድቡ እየተገነባ ባለበት ስፍራ ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመሃከለኛው ክፍል የኮንክሪት ሙሊት ለዓመታት ከነበረበት ከባህር ጠለል በላይ ከ525 ሜትር አሁን ላይ 552 ሜትር ደርሷል። ውሃ ለመያዝም ስምንት ሜትሮች ብቻ ቀርተውታል። የግድቡ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 74 በመቶ ደርሷል። ሰኔ 07 ቀን 2012 ዓ/ም

"መከላከል ከመታከም ይቀላል፣ ቤት መቆየት ሆስፒታል ከመተኛት ይሻላል፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ አድርጎ መተንፈስ በማሽን ከመተንፈስ ይልቃል፣ ስለሆነም እነዚህን እንዲሁም ሌሎችን የመከላከያ መንገዶችን ሳንዘናጋ በመተግበር እራሳችንን እና የምንወዳቸውን ከኮሮና ቫይረስ በሽታ እንጠብቅ" ዶ/ር ሊያ ታደሰ (የኢፌዲሪ የጤና ሚኒስትር)

የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሠራተኞች የደም ልገሳና የችግኝ ተከላ አካሄዱ ……………………/////……………… የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሠ
+4
የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሠራተኞች የደም ልገሳና የችግኝ ተከላ አካሄዱ ……………………/////……………… የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሠራተኞች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ የደም ልገሳና የችግች ተከላ አካሄዱ፡፡ በመርሐ ግብሩ መክፈቻ ላይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ሁሉም ሰው ራሱንና ሌላውን ከበሽታው ለመጠበቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት፡፡ በተለያየ ምክንያት ደም የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህብረተሰቡ ደም መለገስ መቀነሱን ከግምት ውስጥ በማስገባት በፈቃደኝነት ደም ለመለገስ የተገኙትን የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱንና የተጠሪ ተቋማትን አመራሮችና ሰራተኞች አመስግነዋል፡፡ እንደ ሀገር በ2012 ዓ.ም 5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በተራቆቱ አካባቢዎች ብቻ ሳይሆን በየደጃፋም ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ አሻራን የማሳረፍ ሥራ ርቀትን በመጠበቅ መከናወን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ችግኝ በመትከል ደም ለግሰዋል፡፡ ሰኔ 4 ቀን 2012 ዓ.ም