uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 544 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 333-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 158-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 544 obunachiga ega bo‘ldi.

27 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 10 ga, so‘nggi 24 soatda esa -16 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.06% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.33% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 895 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 539 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 7 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 28 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 544
Obunachilar
-1624 soatlar
-97 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+2

photo content
+9

የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ላይ ተሳተፉ ..........///........... የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሥራ አመራሮችና የሆለታ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች በሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግቢ ውስጥ በዛሬው ዕለት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉት የትራንስሚሽን ሰብሰቴሽን ኦፐሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደተናገሩት ተቋሙ በሀገር ደረጃ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ላይ በስፋት እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ ተቋሙ ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነውን ኃይል እያመነጨ የሚገኘው ከውሃ እንደሆነ ጠቅሰው የአረነጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ የማመንጫ ጣቢያዎችን ከደለል በመከላከልና በቂ ውሃ እንዲይዙ በማድረግ አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት ያስችላል ብለዋል፡፡ ከዚህም በመነሳት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እየተካሄደ እንደሚገኝ ነው የተናገሩት፡፡ እየተተከሉ ያሉ ችግኞች የጣቢያዎችን ግቢ ከማስዋብ በተጨማሪ ለምግብነት የሚውሉ በመሆኑ በቀጣይ የጣቢያ ሠራተኞችን ተጠቃሚ እንደሚ ያደርግ አንስተዋል፡፡ እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የሚተከሉ ችግኞች በማከፋፈያ ጣቢያዎች በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የእሳት አደጋዎችን በመካለከል አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል፡፡ የሆለታ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ጥላሁን አዘዘው በበኩላቸው በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ ከ2 ሺህ በላይ ችግኞች መተከላቸውን ጠቁመው ይህም በጊቢው ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተሳተፉት የሰበታ 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አየልኝ በበኩላቸው ችግኞቹን መትከል ብቻ ሳይሆን ለፍሬ እስኪበቁ ድረስ መንከባከብም እንደሚገባ አሳስበዋል። ባለፈው ዓመት ከተተከሉት ችግኞች ከ85 በመቶ በላይ የሚሆኑት መጽደቃቸውንም ጠቁመዋል፡፡   "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በሲኒይር ጂአይኤስ ኤክስፐርት (Senior GIS Expert-D5) እና ጂአይኤስ ኤክስፐርት (GIS Expert-D4) የስራ መደብ ተመዝግባችሁ ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አምስት ኪሎ ካምፖስ (Addis Ababa University Institute of Technology) የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

የጽሁፍ ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በኦፊስ ሰርቪስ ፐርፎርመር -1ኛ እና በሴክረተሪ -1ኛ የስራ መደብ እንዲሁም ሚያዚያ 08 ቀን 2016 ዓ.ም በእንግዳ ተቀባይ-1ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ንግድ ስራ ኮሌጅ (ኮሜርስ) የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ኢትዮጵያ በማራቶን ወርቅ አገኘች! የ2022 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ታምራት ቶላ በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል። እንኳን ደስ አለን! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የሴት ሠራተኞችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል ……….//………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህብረት ስምምነት እና ሌሎች የአሰራር መመሪያዎች አማካኝነት የሴት ሰራተኞችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን የተቋሙ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደተገሩት ማሻሻያዎች ከመደረጋቸው በፊት ሴቶችን በፍትሀዊነት አሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርጉ አሰራሮች ባለመዘርጋታቸውና የግንዛቤ ክፍተት በመኖሩ በየደረጃው ያለው የሴት ሠራተኞች ቁጥርና የተሳትፎ ሁኔታ እጅግ በጣም ዝቅተኛ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት በህብረት ስምምነቱና ሌሎች የተቋሙ የአሰራር መመሪያዎች ላይ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነትን የሚያረጋግጡ ጉዳዮች በመካተታቸው የተሻሉ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በዚህም ከ2013 ዓ.ም በፊት በተቋሙ 14 በመቶ የነበረውን የሴት ሠራተኞች ድርሻ ወደ 17 በመቶ እንዲሁም በተለያዩ የአመራር ደረጃዎች 9 በመቶ የነበረውን 11 በመቶ ማሳደግ ተችሏል፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ ሴቶች ሥራቸውን ተረጋግተው እንዲሰሩ በዋናው መ/ቤት እና በአዳማ 1 የንፋስ የኃይል ማመንጫ የህጻናት ማቆያ መቋቋሙን አስታውሰው በቀጣይም በሌሎች የሥራ አካባቢዎች የሕጻናት ማቆያ ለማቋቋም በእቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የሴቶችን የአመራር ክህሎት ለማጎልበትና የውሳኔ ሰጪነት አቅም ለማዳበርም ተቋሙ በቀረጸው የልዩ ድጋፍ መሰረት በየዓመቱ 55 ሴት ሠራተኞች ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ድግሪ ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መመቻቸቱን ኃላፊዋ ጠቁመዋል፡፡ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መምሪያው ከሁሉም የሥራ ክፍሎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተባብሮ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ በህብረት ስምምነቱና በሌሎች የተቋሙ መመሪያዎች ላይ የድጋፍ እርምጃው ያስፈለገው ሴቶች ተደራራቢ ኃላፊነቶች ያሉባቸው መሆኑን ተገንዝቦ ሁሉም አመራርና ሠራተኛ ለመመሪያዎቹ መፈፀም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2016 ዓ.ም

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ አቅም የተገነቡ 13 ፕሮጀክቶች ተጠናቀዋል ……..///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘርፍ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 13 የተለያዩ ፕሮጀክቶችን የግንባታ ሥራ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንዳስታወቁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመምሪያው ስር በሚገኙ የሥራ ክፍሎች በተለያዩ ጊዜያት የተጀመሩ 28 ፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ሲከናወን ነበር። ከእነዚህ ውስጥ መምሪያው በበጀት ዓመቱ የ18 ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ አቅዶ 13ቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃቱን ተናግረዋል፡፡ ቀሪዎቹ አምስት ፕሮጀክቶች በፀጥታ እና በዕቅዱ ያልተያዙ ተጨማሪ ሥራዎች በመምጣታቸው ምክንያት በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት አለመጠናቀቃቸውን ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት፡፡ እንደ አቶ ሰለሞን ገለፃ የአዋሽ 2 እና 3 ማመንጫ ጣቢያዎች የአፈር መሸርሸር መከላከያ፣ የራይቱ - ጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር የሁለት ምሶሶዎችን ቦታ የመቀየር፣ የሆለታና ሰበታ ዕቃ ግምጃ ቤት ሥራዎች ከተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች መካከል ይጠቀሳሉ። በበጀት ዓመቱ ከተጠናቀቁት ፕሮጀክቶች ውስጥ አምስቱ በፕሮጀክት ማኔጅመንት አንድ ቢሮ፣ ሦስቱ በፕሮጀክት ማኔጅመንት ሁለት እንዲሁም አምስቱ በሲቪል ጥገና ቢሮ የተከናወኑ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በተያዘላቸው መርሃ ግብር ካልተጠናቀቁ አምስት ፕሮጀክቶች መካከል አራቱ አፈፃፀማቸው ከ85 በመቶ በላይ መድረሱን አስታውቀዋል። አቶ ሰለሞን እንዳሉት መምሪያው በዕቅድ ከያዛቸው ሥራዎች በተጨማሪ ኦፕሬሽን ላይ ባሉ ከፍተኛ የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን የጥገና እና የሌሎች ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሥራዎችን አከናውኗል፡፡ የፕሮጀክቶቹ የግንባታ ሥራ በራስ ኃይል መከናወኑ የሠራተኛውን የእኔነት ስሜት በማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሪንና ተጨማሪ ወጪን በማስቀረት እንዲሁም ለሀገሪቱ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በራስ አቅም በተከናወኑ ሥራዎች ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመምሪያው እየተከናወኑ ከሚገኙ 15 ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት የሦስት ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን የግንባታ ሥራ ለመጀመር ዕቅድ መያዙንም አቶ ሰለሞን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የቲክቶከረ ገፅን በመከታተል አባል የረሁኑ! ተጨማሪ መረጃዎችንም ያግኙ ↠https://tiktok.com/ethio_power

የ13 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ተከላ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል ........///......... በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ በኢተያ ከተማ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከሚተከሉ 29 ተርባይኖች የ13ቱ ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ ገለፁ፡፡ ባለሙያው አቶ ይድነቃቸው ደሳለኝ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 61 በመቶ ደርሷል። በፕሮጀክቱ ከሚተከሉት 29 የንፋስ ማማዎች ውስጥ የ23ቱ የመሰረት ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን አፈፃፀሙም 80 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል። 16 የንፋስ ማማዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ዕቃዎች ከወደብ ተጓጉዘው ሳይት መድረሳቸውንም ነው አቶ ይድነቃቸው የገለፁት። እንደ ባለሙያው ገለፃ የአንድ የንፋስ ተርባይን ማማ የመሰረት ሥራ ለማከናወን ከሰባት እስከ 12 ቀናት የሚወስድ በመሆኑ ቀሪ የመሰረትና የተከላ ሥራዎችን በቀጣዮቹ ጊዜያት በማጠናቀቅ በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም ኃይል እንዲያመነጭ ለማድረግ በዕቅድ እየተሰራ ነው። 27 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የውስጥ ለውስጥ የጠጠር አስፓልት መንገድ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ይድነቃቸው አፈፃፀሙም 45 በመቶ መድረሱን ጨምረው ገልፀዋል። 100 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 465 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 ተርባይኖች አሉት፡፡ ለግንባታው 145 ሚሊዮን ዩሮ በጀት የተያዘለት ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ስጦታ እየተሸፈነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። ግንባታውን በዋናነት ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ የተባለ ኩባንያ እያከናወነው ሲሆን ዳር አል ሃንዳሳህ ሼር እና ፓርትነር የተሰኘ ኩባንያ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግ ዘርፍ በአጋርነት በማማከር ሥራው ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ይገኛሉ። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ሀገሪቱ ከንፋስ የምታገኘውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 544 ሜጋ ዋት ያሳድገዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 30 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

በፕሮጀክቱ የዕቃ ግምጃ ቤት የካይዘን ፍልስፍና ተግባራዊ እየተደረገ ነው ………///…….. በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የዕቃ ግምጃ ቤቶች ላይ የካይዘን የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ዊ ቢውልድ ኩባንያ ገለፀ። በኩባንያው የዕቃ ግምጃ ቤቶች ሱፐርቫይዘር አቶ በርገና ባዴቦ እንደገለፁት ለፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ የሚያገለግሉ ግብዓቶች፣ ለሥራ ላይ ደህንነት መሳሪያዎች እና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች ተለያይተው በካይዘን ፍልስፍና የአሰራር ስርዓት መሠረት በአግባቡ ተደራጅተዋል። ይህም የዕቃዎቹን ደህንነት በማረጋገጥና ሥራ ተቋራጩን ከአላስፈላጊ ወጭ በማዳን የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ማድረጉን ነው ያስታወቁት። ለፕሮጀክቱ ሥራ የሚያስፈልጉ ዕቀዎች በፕሮጀክቱ ዕቃ ግምጃ ቤት በዓይነታቸው እና በገቡበት ጊዜ ተለይተው እንደሚቀመጡም አቶ በርገና ተናግረዋል። ዕቃ ግምጃ ቤቱ ላይ የሚደራጁ ዕቃዎች በሚሰጣቸው መለያ መሠረት በዳታ ቤዝ ተመዝግበው እንደሚቀመጡ ጠቁመው ይህም በግምጃ ቤቱ ያሉ እና ወጪ እንዲሆኑ የሚጠየቁ ዕቃዎችን ክትትል ለማድረግና ለጠያቂው አካል በቀላሉ ለማቅረብ ማስቻሉን አመልክተዋል። እንደ ሱፐርቫይዘሩ ገለፃ ግምጃ ቤቶቹ በካይዘን የአሰራር ስርዓት መሠረት መደራጀታቸው ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እና ዕቃዎችን ከተለያዩ ጉዳቶች በመጠበቅ በአግባቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል። አቶ በርገና እንዳሉት በካይዘን ፍልስፍና መደራጀቱ ዕቃ ወጪ ሲደረግ ዕቃዎችን ለመፈለግ የሚወስደውን ጊዜ ለማስቀረት እና አዲስ የሚገቡ ዕቃዎች በማን እንደታዘዘ፣ ለምን ዓላማ እንደሚውል እና ዕቃዎቹን ለአዘዘው አካል በአግባቡ ለማቅረብ እንደሚያስችል ተናግረዋል። በዕቃ ግምጃ ቤቶቹ ላይ በየስድስት ወሩ ቆጠራ እንደሚከናወን ያነሱት ሱፐርቫይዘሩ ይህም የጎደሉ ዕቃዎችን በቀላሉ በመለየት ለማሟላት እና የሚገቡ ዕቃዎችን በዓይነታቸው ለማስቀመጥ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል። ድርጅቱን ከአላስፈላጊ ወጪ ለመታደግ ቀድመው የገቡ ዕቃዎች ጥቅም ላይ ሳይውሉ አዲሶቹን መጠቀም እንደማይቻል ሱፐርቫይዘሩ አስረድተዋል። ሥራውን በአግባቡ ለማከናወንና ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጅ ጋር ለመራመድ በዕቃ ግምጃ ቤቱ ላይ ለሚገኙ ሠራተኞች ሙያዊ ስልጠናዎች በኩባንያው እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። ካይዘን ለዕይታ ማራኪ የሥራ ቦታ እንዲኖር የሚያስችል ወጪ፤ ጊዜና ጉልበትን የሚቆጥብ ከጃፓን የተቀዳ የአሰራር ሥርዓት ፍልስፍና ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 29 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

የኢትዮ-ኤሌክትሪኩ በሪሁ አረጋዊ ለሀገሩ የብር ሜዳሊያ አስገኘ ……….///………. በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ አትሌት የሆነው አትሌት በሪሁ አረጋዊ በወንዶች 10 ሺህ ሜትር ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ አስገኝቷል። ከትናንት በስቲያ በተካሄደው የፍፃሜ ውድድር አትሌት በሪሁ ርቀቱን 26 ደቂቃ ከ43 ሰከንድ ከ44 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሁለተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ዩጋንዳዊው ጆሽዋ ቼፕቴጌ 26 ደቂቃ 43 ሰከንድ ከ14 ማይክሮ ሰከንድ በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያውን ወስዷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሀምሌ 28 ቀን 2016 ዓ.ም