የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Kanalga Telegram’da o‘tish
5 576
Obunachilar
-40724 soatlar
-2 4147 kunlar
-2 42630 kunlar
Postlar arxiv
https://youtu.be/2UG2h7X8nS8?si=xPYUDl9cU4aA_I77
የሶማሊያው ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ 🇪🇹+🇸🇴
+3
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ተወያዩ።
የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በአምስት አመቱ ተቋማዊ ሪፎርምና በውጪ ጉዳዮች ሰላምና ደህንነት ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል።
ከተቋማዊ ለውጡ በመነሳት ተቋሙ ከለውጡ በፊት የነበረበትን ከፍተኛ የሆነ ችግር በመቅረፍ ሠራዊቱን ከሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች ተዋፅኦ እንዲኖረው በማድረግ፣ ሃገራችንን በሚመጥን መልኩ እንደ ኢትዮጵያ እንዲያስብ ተደርጎ እየተገነባ ያለ መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገልፀዋል።
በአዲሱ ስትራቴጂ ከለውጡ በፊት የነበሩትን መመሪያዎች በመፈተሽ እና እንደ አሥፈላጊነቱ በመቀየር የሠራዊቱን ኑሮና ሌሎች መሠረታዊ ነገሮች በማሻሻል፣ ሠራዊቱ ከየትኛውም የፖለቲካ አመለካከት ከሃይማኖትና ከብሄርተኝነት ነፃ የሆነ አስተሳሰብ እንዲኖው የማድረግ ሥራ መሠራቱን አንስተዋል። አየር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና ምድር ሃይልን በማጠናከር ፕሮፌሽናል በሆነ መንገድ ሠራዊቱን መገንባት መቻሉንም አሥረድተዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፀረ ሰላም ሃይሎች ሠላም መርጠው በሰላም እጃቸውን እንዲሰጡ እየተሰራ ያለ መሆኑን ጠቅሰው ሠራዊቱ ልምድ ያለው በመሆኑ ከሀገርም አልፎ በቀጠናው አገራት እንዲከበር አድርጎታል ነው ያሉት።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትም ሰፋ ያሉ ጉዳዩች ላይ ሃሳብ አንስተው የተወያዩ ሲሆን አጠቃላይ ስለተደረገላቸው አቀባበልና ሠፊ ገለፃ ምስጋና አቅርበዋል።
+4
የኮማንዶ ክፍለ ጦር ከዞኑ ጋር በመተባበር ለወራት ያሰለጠናቸውን ሚሊሺያዎች አስመረቀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 02 ቀን 2017 ዓ.ም
ክፍለ ጦሩ የተሰጠዉን ሀገራዊ ግዳጅ ከመወጣት ጎን ለጎን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አሥተዳደር የቀጠናውን ሰላም ለማፅናት የአካባቢ ሚሊሺያዎችን ከዞኑ ጋር በመቀናጀት አሰልጥኖ አስመርቋል።
በምርቃቱ የተገኙት የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል እሸቱ መንግስቴ የሚሊሺያ ሀይል ከሁሉም የፀጥታ አካላት በተሻለ ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበት የሚኖር በመሆኑ የህዝቡን ችግሮች በፍጥነት በመፍታት የአከባቢውን ሰላም ማረጋገጥ ይችላል፤ በመሆኑም ይህ ሀይል በእኩልነት ህዝብን የሚያይና ያለምንም መድሎ ችግሮችን በመፍታት የአካባቢውን ሰላም የሚያረጋግጥ ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡
የኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ በበኩላቸው ነፃ አውጭ ነን በሚል የውሸት ትርክት ጫካ በመግባት ህዝብን በመዝረፍና በማንገላታት ነፃነቱን የገፈፉ ኃይሎች በሠራዊቱ በተወሰደባቸው እርምጃ በአካባቢው አንፃራዊ ሰላም መስፈኑን አውስተዋል።
አሁን ሰልጥነው የተመረቁ የፀጥታ አካላትም ይህንን ሰላም የማፅናት ታላቅ ሃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን አውቀው በዚህ ልክ መስራት አንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የኬሚሴ ከተማ አስተዳደር ሚሊሺያ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እንድሪስ አሊ በበኩላቸዉ ሚሊሺያዎች የሚሰጣቸዉን የሰላም ማስከበር ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችላቸው ሥልጠና መውሰዳቸውን ገልፀው በቀጣይ የዞኑን የፀጥታ አቅም ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ዘገባው የክፍለጦሩ የሠራዊት ሥነ ልቦና ግንባታ ነው።
#Ethiopia🇪🇹
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.force
አፋር - ዱለቻ ወረዳ ዶፋን ተራራ ላይ የተከሰተው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ
