uz
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis abeba Ethiopia

Ko'proq ko'rsatish
4 770
Obunachilar
-23224 soatlar
-1 7917 kunlar
-3 26430 kunlar
Postlar arxiv
#አድማስ_ዲጅታል_ሎተሪ ! የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር የአድማስ ድጅታል ሎተሪ የአንደኛ ዙር ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን 2014 ዓ/ መውጣቱን ገልጿል። የወጡ ዕድለኛ የሚያደርጉ ቁጥሮች ፡- 👉 የ1ኛ ዕጣ
#አድማስ_ዲጅታል_ሎተሪ ! የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር የአድማስ  ድጅታል ሎተሪ የአንደኛ ዙር ዛሬ ነሐሴ 13 ቀን 2014 ዓ/ መውጣቱን ገልጿል። የወጡ ዕድለኛ የሚያደርጉ ቁጥሮች ፡- 👉 የ1ኛ ዕጣ የ1.5 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002031699514 👉 2ኛ ዕጣ  የ800 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002294990063 👉 3ኛ ዕጣ የ350 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002318579148 👉 4ኛ ዕጣ የ200 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002210849268 👉 5ኛዕጣ የ160 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002133487616 👉 6ኛ ዕጣ የ120 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002305487051 👉 7ኛ ዕጣ የ90 ሺህ ብር የሚያሸልመው ዕጣ  ቁጥር -002137548817 ሌሎችም በርካታ ዕጣዎች መውጣቱን የገለፀው ብሄራዊ ሎተሪ ሙሉውን ዝርዝር በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

#ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ ሱዳን፤ ሙሌቱን ተከትሎ በህዳሴው ግድብ ላይ እርምጃ ትወስዳለች መባሉን አስተባበለች አሁንም አሳሪ ስምምነት ላይ መደረስ አለበት በሚለው አቋሟ እንደጸናች መሆኗንም ነው
#ታላቁ_የኢትዮጵያ_ሕዳሴ_ግድብ ሱዳን፤ ሙሌቱን ተከትሎ በህዳሴው ግድብ ላይ እርምጃ ትወስዳለች መባሉን አስተባበለች አሁንም አሳሪ ስምምነት ላይ መደረስ አለበት በሚለው አቋሟ እንደጸናች መሆኗንም ነው የገለጸችው ሱዳን በሮዜርየስ ግድብ፣ በመስኖ እና በሌሎች የሃይድሮ ኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶቿ የውሃ ይዞታ ላይ ችግር ካጋጠመ ሶስተኛ ዙር ሙሌቱ ከሰሞኑ በተጠናቀቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ እርምጃ ትወስዳለች መባሉን አስተባበለች። የሃገሪቱ የመስኖ እና የውሃ ሃብት ሚኒስቴር ጉዳዩን በማስመልከት መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው የግድቡ ተደራዳሪ ቡድን የቴክኒክ ኮሚቴ መሪ እንደተናገሩት ተደርጎ በተወሰኑ ሚዲያዎች የቀረበው ዘገባ የተሳሳተ እና ከእውነት የራቀ ነው ብሏል፤ ቡድን መሪው ጉዳዩን በማስመልከት የተናገሩት ነገርም ሆነ የሰጡት መግለጫ እንደሌለም በመጠቆም። አሁንም የግድቡን ሙሌትና አስተዳደር በተመለከተ ከአሳሪ የሶስትዮሽ ስምምነት ላይ ይደረስ በሚለው አቋሙ እንደጸና መሆኑንም ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው። በሙሌቱ መጠናቀቅ ማብሰሪያ ስነ ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሙሌቱ የታችኞቹ የተፋሰሱ ሃገራት የሚያገኙ የውሃ መጠን ሳይቀንስ መጠናቀቁን በመግለፅ ግብጽን ጨምሮ ሶስቱም ሃገራት ለፍትሐዊ ተጠቃሚነት በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል።  የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ከሱዳን የመስኖ እና የውሃ ሃብት ሚኒስትር ዳው አብደል ራህማን መንሱር እና ከደቡብ ሱዳን የመስኖ እና የውሃ ሃብት ሚኒስቴር ተወካይ አምባሳደር ዴንግ ኦቤድ ጋር ተገናኝተው ጥሩ ጊዜ ማሳለፋቸውን በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል። ሆኖም መቼ እና የት እንደተገናኙ ተገናኝተው ምን እንዳወሩም አልገለፁም።

#EthiopiaCheck Monitoring በኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET343 የተከሰተው ምንድን ነበር? በያዝነው ሳምንት መጀመርያ ሰኞ እለት በበረራ ቁጥር ET343 ከካርቱም ወደ አዲስ
#EthiopiaCheck Monitoring በኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET343 የተከሰተው ምንድን ነበር? በያዝነው ሳምንት መጀመርያ ሰኞ እለት በበረራ ቁጥር ET343 ከካርቱም ወደ አዲስ አበባ ሲበር የነበረ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ማረፊያው አዲስ አበባ ደርሶ እያለ ከበረራ ተቆጣጣሪዎች ጋር ግንኙነቱ ተቋርጦ እንደነበር በአለም አቀፍ የአቪዬሽን ሚድያዎች ሲዘገብ ነበር። እንደ "Aviation Herald" ያሉ ሚድያዎች አውሮፕላኑ ግንኙነት ካለማድረጉ በተጨማሪም ለማረፍ ከፍታውን ሳይለቅ አዲስ አበባ መድረሱን የዘገቡ ሲሆን ጉዳዩን ከኢትዮጵያ የበረራ ቋት ማዕከል ማረጋገጣቸውን ፅፈዋል። በዚህ ዙርያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ መግለጫ ያወጣ ሲሆን በተባለው ጉዳይ ዙርያ ሪፖርት እንደደረሰው እና የበረራው ፓይለቶች ኋላ ላይ ከአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጋር ግንኙነት ፈጥረው አውሮፕላኑ በሰላም እንዳረፈ አስታውቋል። አክሎም በረራውን ሲያከናውኑ የነበሩ ፓይለቶች ከስራ ታግደው ምርመራ እየተካሄደ እንደሆነ አስታውቋል። በምርመራው ውጤት መሰረትም አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ ጨምሮ አስታውቋል። ፎቶ: ፋይል (ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን) ©EthiopiaCheck

አሜሪካ ለዩክሬን ተጨማሪ 800 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ አጸደቀች ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሩሲያ ጋር ቀጥታ ጦርነት ውስጥ ላለችው ዩክሬን ተጨማሪ 800 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የጦር መሳሪያ ድጋፍ ፈርመዋል። አሜሪካ የጦር መሳሪያውን ድጋፍ ያደረገችው ዩክሬን የኑክሌር ጥቃት ከሩሲያ ሊያጋጥማት ይችላል በሚል እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል። የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 176ኛ ቀኑ ላይ ሲገኝ ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል። ✍️ ቤተሰብ ይሁኑ! 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter

የታላቁ የህዳሴ ግድብ ከፍታ ስንት ነው? የሶስተኛው ዙር የውሀ ሙሌት ያጠናቀቀው የታላቁ የህዳሴ ግድብ በ600 ሜትር ከፍታ በአሁኑ ወቅት 22 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሀ መያዝ ችሏል። በአጠቃላይ ከሚ
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ከፍታ ስንት ነው? የሶስተኛው ዙር የውሀ ሙሌት ያጠናቀቀው የታላቁ የህዳሴ ግድብ በ600 ሜትር ከፍታ በአሁኑ ወቅት 22 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር ውሀ መያዝ ችሏል። በአጠቃላይ ከሚጠበቀው ከፍታ 45 ሜትር ገደማ ይቀራል። በተለየ አገላለጽ ደግሞ የግድቡ ከፍታ 145 ሜትር መሆኑም በተደጋጋሚ ይነሳል። ለመሆኑ 645 እና 145 የሚሉት ቁጥሮች አረዳድ ምንድን ነው ? በተደጋጋሚ እንደሚገለፀው የሚገነባው ግድብ ከፍታ 145 ሜትር ነው። ግድቡ 645 ሜትር ከፍታ ይኖረዋል ሲባል ከባህር ወለል በላይ የሚኖረው ጠቅላላ ከፍታ ነው። ግድቡ እየታነፀ ያለበት የጉባ አከባቢ ከባህር ወለል በላይ 500 ሜትር ከፍታ ያለው ነው። በዚህ ከፍታ ላይ 145 ሜትር ያለው ግድብ በመገንባት ላይ በመሆኑ የሁለቱ ድምር ግድቡን ከባህር ወለል በላይ እስከ 645 ሜትር ከፍ እንደሚል ልብ ይለዋል። በአሁኑ ወቅት 600 ሜትር ከፍታ ላይ ነው ሲባልም አሁን ግድቡ 100 ሜትር የሚሆነው ከፍታው ተገንብቷል ማለት ነው። ቀሪውም 45 ሜትር ብቻ ይሆናል። ባለፈው አመት የተገነባው የግድቡ ክፍል ከፍታ 75 ሜትር ነበር። ወይም የግድቡ ከፍታ 575 ሜትር ነበር። በዚህ አመት 25 ሜትር ከፍታ ተጨምሮ 100 ሜትር ከፍታ ላይ ደርሷል። ወይም 600 ሜትር ከፍታ። ይህ የመካከለኛው የግድቡ ክፍል ገፅታ ነው። በግራ እና በቀኝ ያሉት ደግሞ ከፍታቸው ባለፈው አመት 585 ሜትር ወይም የ85 ሜትር ከፍታ የነበራቸው ሲሆን በተያዘው አመት ከፍታቸው 611 ሜትር ደርሰዋል፤ ወይም 111 ሜትር የሚሆነው ግንባታ ተከናውኗል። በመጭዎቹ ሁለት ወይም ሁለት አመት ተኩል የቀረው የግድቡ ክፍል ግንባታ ይጠናቀቃል ተብሎም ይጠበቃል። [Balageru TV]

“ከኢንሳ ነው የመጣነው” ብለው በማስፈራራት 260 ሺሕ ብር የተቀበሉት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ሠራተኞች በእስራት ተቀጡ “የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ነው የመጣነው” ብለው በማስፈራራት 260 ሺሕ ብር የተቀበሉት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ሠራተኞች በእስራት መቀጣታቸው ተገለጸ። 1ኛ ተከሳሽ ዋና ሳጅን ፈቃዱ ዘውዴ (በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአስተዳደር ዘርፍ ሥር ሾፌር)፣ 2ኛ ተከሳሽ ረ/ኢ/ር ይስሃቅ ዳካ (በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአስተዳደር ዘርፍ ሥር ሾፌር) 3ኛ ተከሳሽ ረ/ኢ/ር ደሴ ደጆ (በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአስተዳደር ዘርፍ በተሸከርካሪ ጥገና ዳይሬክቶሬት የገበያ ጥናት ጉዳይ አስፈፃሚ ማስተባበሪያ ሃላፊ) ሆነው በሚሰሩበት ጊዜ ከ4ኛ ተከሳሽ ዳዊት ዳዲ በዳኔ ጋር በመመሳጠር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተገን በማድረግ እና ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀማቸው ነው እስራቱ የተወሰነባቸው፡፡ የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያሳየው፤ ተከሳሾች ተጠርጣሪን የመያዝ እና የማቆየት ስልጣን ሳይኖራቸው በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ዲአፍሪካ ሆቴል አካባቢ ወደሚገኘው የግል ተበዳይ አሉላ አለነ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች ሱቅ 2ኛ ተከሳሽ ለሥራ በተሰጠው መኪና በመሄድ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች መኪና ውስጥ ሆነው ሲጠብቁ 1ኛ ተከሳሽ በር ላይ ቆሞ ሽፋን ሲሰጥ፣ 4ኛ ተከሳሽ ሱቁ ውስጥ በመግባት የግል ተበዳይን ”ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) ነው የመጣነው፤ ለወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ለጥያቄ ስለምንፈልግህ ዉጣ“ በማለት የግል ተበዳይን ከሱቁ ያስወጡታል። በማስከተልም፤ ለገሃር አካባቢ ከወሰዱት በኋላ “አንድ ሚሊዬን ብር አምጣ ካለሆነ ለኦሮሚያ ፖሊስ አሳለፈን እንሰጥሃለን” ብለው በማፈራራት 260 ሺሕ ብር ወደ 4ኛ ተከሳሽ ሂሳብ እንዲያስተላልፍ ካደረጉ በሗላ ገንዘቡን በመከፋፈል ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው በዋና እና ልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸው ነበር፡፡ ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ ናቸው በማለት ነሐሴ 11 ቀን 2014 በዋለው ችሎት አራቱም ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በ3 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ2000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑን የፍትሕ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡ የሙስና ወንጀል ጉዳዮቸ ዐቃቤ ሕግ በውሳኔው ላይ ይግባኝ ለመጠየቅ የውሳኔ ግልባጭ ጠይቆ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የኢትዩትዩብ ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ። ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

የቻይና ፕሬዝደንት ዢ ጅንፒንግ እና የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን የቻይና እና የሩሲያ መሪዎች በኢንዶኔዥያው የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ሊካፈሉ ነው በኢንዶኔዥያው ስብሰባ ላይ የአሜሪካው ፕ
የቻይና ፕሬዝደንት ዢ ጅንፒንግ እና የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን የቻይና እና የሩሲያ መሪዎች በኢንዶኔዥያው የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ሊካፈሉ ነው በኢንዶኔዥያው ስብሰባ ላይ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደንም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል የቻይና ፕሬዝደንት ዢ ጅንፒንግ እና የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በመጭው ህዳር ወር በሚካሄደው የኢንዶኔዥያው የቡድን 20 አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ሊሳተፉ ነው፡፡ ሮይተርስ የኢንዶኔዥያ ፕሬዝደንት ጆኮ ዊዶዶ አማካሪን ጠቅሶ እንዘገበው የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ስብሰባውን ይካፈላሉ፡፡  አማካሪው ኢዲ ዋድጃጃንቶ ሁለቱ መሪዎች እንደሚገናኙ ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ ጆ ባይደን፤ ሩሲያ ከቡድን 20 አባልነት “መሰረዘ አለባት” አሉ የናሽናል ሬዚለንስ ኢንስቲቲዩትን የሚመሩት ዊድጃጃንቶ ፕሬዝደንቱ ሁለቱ መሪዎች ወደ ኢንዶኔዥያ ባሊ ከተማ መጥተው ስብሰባውን እንደሚያካሄዱ ነግረውኛል ብለዋል፡፡ ፕሬዝደንት ጆኮ ዊዶዶ ቀደም ሲል ሁለቱ መሪዎች በቡድን 20 ሀገራት ስብሰባ እንደሚካፈሉ ለብሉምበርግ አረጋግጠዋል፡፡ ሮይተርስ መሪዎቹ ስለመሳተፋቸው ከሩሲያ ሆነ ከቻይና ምላሽ አለማግኘቱን ዘግቧል፡፡ በቡድን 20 ሀገራት ስብሰባ ላይ የዩክሬኑ መሪ ዘለንስኪ ተጋዘብዋል፤ የኢንዶኔዥያው ፕሬዝደንት ጆኮ ዊዶዶ በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል ያለውን ግጭት በሽምግልና ለመፍታት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት፣ ሩሲያ አሜሪካን ጨምሮ ከምእራባውያን ጋር ወታደረዊ ፍጥጫ ውስጥ የገባች ሲሆን ቻይና ደግሞ በታይዋን ጉዳይ በተለይም ከቻይና ጋር ወደታራዊ ትብብር እስከማቋረጥ የደረሰ ቅራኔ ውስጥ ገብታለች፡፡

ማሊ፤ ፈረንሳይን ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ከሰሰች ምዕራብ አፍሪካዊቷ ማሊ፤ ፈረንሳይ የአየር ክልሌን በመጣስ ለታጣቂዎች ጦር መሳሪያ እያቀረበች ነው ስትል ከሰሰች። የማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሁኔ
ማሊ፤ ፈረንሳይን ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ከሰሰች ምዕራብ አፍሪካዊቷ ማሊ፤ ፈረንሳይ የአየር ክልሌን በመጣስ ለታጣቂዎች ጦር መሳሪያ እያቀረበች ነው ስትል ከሰሰች። የማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሁኔታውን በማስመልከት ለተመድ የጸጥታው ምክርቤት ደብዳቤ ጽፏል። በደብዳቤው የሃገሪቱ የአየር ክልል በዚህ ዓመት ብቻ ከ50 ለሚበልጡ ጊዜያት በዋናነትም በፈረንሳይ ወታደራዊ ድሮኖች፣ የጦር ሄሊኮፕተሮች እና የጦር ጄቶች መጣሱን ገልጿል እንደ ሮይተርስ ዘገባ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዕድለኞች መልካም ዜና ይዞ መጥቷል #የ1.1_ትሪሊየን ትርፍ #ያጋሩ ይሸለሙ https://t.me/CommercialbankEthiopia እንኳን ደስ አላቸችሁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀብት 1.1 ትሪሊየን ትርፍ ምክንያት በማድረግ የባንካችን ፕሬዝዳንት #አቶ_አቢ_ሳኖ እስከ መስከረም_5 ብቻ የሚቆይ #የቴሌግራም_ገፅ ማነቃቂያ የሚሆን ሽልማቶች ተዘጋጅቷል። https://t.me/CommercialbankEthiopia እስከ_መስከረም_5 ድረስ የሚቆይ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም አዘጋጅቷል። በዚህም መሰረት እድለኞችን በርካታ # ስጦታዎችን ለመሸለም ተዘጋጅተናል! # 1ኛ . ለ200 እድለኞች ከ300,000 ብር በላይ ዋጋ የሚያወጡ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎችና እያንዳንዳቸው ከ50,000 ብር በላይ ግምት ያላቸው ሙሉ የቤት እቃዎች # 2ኛ . ለ 220 እድለኞች 50ሺ ብር እና እያንዳንዳቸው ከ15,000 ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የማቀዝቀዣ ፍሪጆች፤ # 3ኛ . ለ 245 እድለኞች 10ሺ ብር እና እስከ 7,000 ብር የሚያወጡ Infinix ሞባይል ቀፎዎች # 4ኛ . ለ 150 እድለኞች 10ሺ ብር እና የTECHNO SPARK የሞባይል ቀፎዎች # 5ኛ . ለ 100 እድለኞች 5ሺ ብር እና የTechno spark የሞባይል ቀፎች እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ የአዲስ አመት ስጦታዎችን አዘጋጅተናል። #ይፍጠኑ እስከ #መስከረም_5 2014 ድረስ የእነዚህ አጓጊ ሽልማቶች ባለ እድል ይሁኑ። ልብ ይበሉ! በሽልማት ፕሮግራሙ ከመሳተፍዎ በፊት # በጥንቃቄ መመሪያዎችን ያንብቡ! ለመሸለም እነዚህን መመሪያዎች በጥንቃቄ ይከተሉ። 1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/CommercialbankEthiopia 2. በመቀጠል ይህንን መልዕክት ከ50 በላይ ለሆኑ ሰዎች በፍጥነት ሼር ( Forward) ያድርጉ፤ (ልብ ይበሉ! ብዙ ሰዎችን # add ባደረጉ ቁጥር የሽልማት ዕድልዎን ያሠፋሉ!) https://t.me/ComercialbankofEthiopia ✍️ ቤተሰብ ይሁኑ! 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/CommercialbankEthiopia

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነዳጅ ግብይት የሚፈጸምበት የሞባይል መተግበሪያ ጥቅም ላይ ሊያውል ነው። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በኢግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መካከል የነዳጅ ግብይትን መፈፀም የሚያስች
+2
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነዳጅ ግብይት የሚፈጸምበት የሞባይል መተግበሪያ ጥቅም ላይ ሊያውል ነው። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በኢግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መካከል የነዳጅ ግብይትን መፈፀም የሚያስችል ‘Nedaj’ (‘ነዳጅ’) የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ ጥቅም ላይ ለማዋል ዛሬ ነሀሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ስምምነት ተፈርሟል፡፡ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዳህላክ ይገዙ ባንኩ የሀገራችንን የነዳጅ ግብይት በማዘመን ለተሽከርካሪ ባለቤቶች፣ ለነዳጅ ማደያዎች እና ለነዳጅ ተቆጣጣሪ የመንግስት አካላት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለውን የሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ መቻሉን ጠቁመዋል። በሀገራችን በቀን ከ11.2 ሚሊዮን ሊትር በላይ ነዳጅ ሽያጭ የሚፈፀምና ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ክፍያ እንደሚንቀሳቀስ የኢግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ በእርሱፈቃድ ጌታቸው ጠቁመዋል። የተሽከርካሪ ባለቤቶች እና ነዳጅ ማደያዎች 'Nedaj' (ነዳጅ) የተሰኘው መተግበሪያ ሞባይላቸው ላይ ጭነው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር አግልግሎቱን መጠቀም የሚችሉ ሲሆን፣ በባንኩ ሂሳብ የሌላችው ደግሞ የተቀማጭ ሂሳብ ወይም የሲቢኢ ብር ሂሳብ በመክፈት የአግልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዕድለኞች መልካም ዜና ይዞ መጥቷል #የ1.1_ትሪሊየን ትርፍ #ያጋሩ ይሸለሙ https://t.me/CommercialbankEthiopia እንኳን ደስ አላቸችሁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀብት 1.1 ትሪሊየን ትርፍ ምክንያት በማድረግ የባንካችን ፕሬዝዳንት #አቶ_አቢ_ሳኖ እስከ መስከረም_5 ብቻ የሚቆይ #የቴሌግራም_ገፅ ማነቃቂያ የሚሆን ሽልማቶች ተዘጋጅቷል። https://t.me/CommercialbankEthiopia እስከ_መስከረም_5 ድረስ የሚቆይ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም አዘጋጅቷል። በዚህም መሰረት እድለኞችን በርካታ # ስጦታዎችን ለመሸለም ተዘጋጅተናል! # 1ኛ . ለ200 እድለኞች ከ300,000 ብር በላይ ዋጋ የሚያወጡ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎችና እያንዳንዳቸው ከ50,000 ብር በላይ ግምት ያላቸው ሙሉ የቤት እቃዎች # 2ኛ . ለ 220 እድለኞች 50ሺ ብር እና እያንዳንዳቸው ከ15,000 ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የማቀዝቀዣ ፍሪጆች፤ # 3ኛ . ለ 245 እድለኞች 10ሺ ብር እና እስከ 7,000 ብር የሚያወጡ Infinix ሞባይል ቀፎዎች # 4ኛ . ለ 150 እድለኞች 10ሺ ብር እና የTECHNO SPARK የሞባይል ቀፎዎች # 5ኛ . ለ 100 እድለኞች 5ሺ ብር እና የTechno spark የሞባይል ቀፎች እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ የአዲስ አመት ስጦታዎችን አዘጋጅተናል። #ይፍጠኑ እስከ #መስከረም_5 2014 ድረስ የእነዚህ አጓጊ ሽልማቶች ባለ እድል ይሁኑ። ልብ ይበሉ! በሽልማት ፕሮግራሙ ከመሳተፍዎ በፊት # በጥንቃቄ መመሪያዎችን ያንብቡ! ለመሸለም እነዚህን መመሪያዎች በጥንቃቄ ይከተሉ። 1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ። https://t.me/CommercialbankEthiopia 2. በመቀጠል ይህንን መልዕክት ከ50 በላይ ለሆኑ ሰዎች በፍጥነት ሼር ( Forward) ያድርጉ፤ (ልብ ይበሉ! ብዙ ሰዎችን # add ባደረጉ ቁጥር የሽልማት ዕድልዎን ያሠፋሉ!) https://t.me/ComercialbankofEthiopia

ትህነግ እንዲህ ሲጨንቀው ነው የሚደራደር! ዛሬ ለድርድር በርካታ ቅድመ ሁኔታ የሚዘረዝረው ጌታቸው ረዳ፣ ድሮ መንገድ ላይ ያገኘውን ጎረምሳ ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲያውም ግብዣ በእኔ ሆኖ እንደራደር እያለ ይለምን ነበር😂 በእርግጥ ዲያስፖራዎ በቆረጣ ገብቶበት ሲጨንቀው ነው። ትህነግ ወደ ድርድር ሊመጣ የሚትለው እንዲህ ሲጨንቀው ብቻ ነው። የሚያስጨንቅ ሲያገኝ ጋብዧችሁ ልደራደር ይላል።

#ፊንላንድ ከወደ ፊንላንድ የተሰማ ... በእድሜ ወጣት የሆኑት የ36 ዓመቷ የፊንላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር በአንድ ፓርቲ ላይ ሲጨፍሩ የሚያሳይ ቪድዮ ሾልኮ ከተለቀቀባቸው በኃላ ከፍተኛ ትችት እየደረሰባ
+1
#ፊንላንድ ከወደ ፊንላንድ የተሰማ ... በእድሜ ወጣት የሆኑት የ36 ዓመቷ የፊንላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር በአንድ ፓርቲ ላይ ሲጨፍሩ የሚያሳይ ቪድዮ ሾልኮ ከተለቀቀባቸው በኃላ ከፍተኛ ትችት እየደረሰባቸው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ሳና ማሪን ሾልኮ በወጣው ቪድዮ ከዝነኛ ፊላንዳውያን ጓደኞቻቸው ጋር ሲጨፍሩ እና ሲዘፍኑ ታይተዋል። ከዚህም በኃላ የጠቅላይ ሚኒስትሯን ድርጊት በተለይ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ዘንድ ከፍተኛ ትችት አስከትሎባቸዋል። አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ጠቅላይ ሚኒስትሯ " የአደንዛዥ እጽ ምረመራ ይደረግላቸው " ሲሉ ጠይቀዋል። ሌሎች ደግሞ ብዙ ሀገራዊ ጉዳይ እያለ ስለጭፈራ ማውራቱ ጊዜው አይደለም ሲሉ ተችተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሯ ግን " አደንዛዥ እጽ አልወሰድኩም " ያሉ ሲሆን አልኮል መጠጣታቸውን እና በሙሉ ኃይላቸው በፓርቲው ላይ መጨፈራቸውን ግን ተናግረዋል። ቪዲዮ እየተቀረጹ መሆኑን እንደሚያውቁ የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሯ " ለሕዝብ ዕይታ መቅረቡ ግን ያበሳጫል " ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። " ደንሻለሁ፣ ዘፍኛለሁ እንዲሁም ፓርቲ አድርጊያለሁ ሁሉም ሕጋዊ ናቸው። እኔ ወይም በአካባቢዬ አደንዛዥ እጽ በሚወሰድበት ቦታ ሆኜ አላውቅም " ሲሉም አክለዋል። በተጨማሪ " የቤተሰብ ሕይወት አለኝ፣ የሥራ ሕይወት አለኝ፣ እንዲሁም ከጓደኞቼ ጋር የማሳለፈው ነጻ የምሆንበት ጊዜ አለኝ። በእኔ የዕድሜ ክልል ውስጥ እንደሚገኙ ከሌሎች ሰዎች ጋር ተመሳሳይ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። መሪን ከእ.አ.አ. 2019 መጨረሻ ጀምሮ ፊንላንድን እየመሩ ሲሆን አሁንም ድረስ ከፓርቲያቸው ጠንካራ ድጋፍ እንዳላቸው ቢቢሲ አስነብቧል።