uz
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis abeba Ethiopia

Ko'proq ko'rsatish
5 066
Obunachilar
-25624 soatlar
-1 8217 kunlar
-3 02830 kunlar
Postlar arxiv
ኢትዮጵያ በሱዳን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና ትጫወታለች ኢትዮጵያ በሱዳን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና እንደምትጫወት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ
ኢትዮጵያ በሱዳን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና ትጫወታለች ኢትዮጵያ በሱዳን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ገንቢ ሚና እንደምትጫወት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል፡፡በውይይታቸው ሀገራቱ የቆየ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይም መክረዋል፡: ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቀጠናው የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮችን መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

👉 ፕሬዚዳንት ባይደን የአሜሪካ ኤምባሲ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው ከሱዳን መውጣታቸውን አረጋገጡ‼️ ♦ ኢትዮጵያን፣ ጂቡቲንና ሳዑዲ አረቢያን አመስግነዋል‼ ♦️ በስድስት አውሮፕላኖች መውጣታቸው ታውቋል
👉 ፕሬዚዳንት ባይደን የአሜሪካ ኤምባሲ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው ከሱዳን መውጣታቸውን አረጋገጡ‼️ ♦ ኢትዮጵያን፣ ጂቡቲንና ሳዑዲ አረቢያን አመስግነዋል‼ ♦️ በስድስት አውሮፕላኖች መውጣታቸው ታውቋል‼️ ♦️ የፈጥኖ ደራሹ ኃይል የአሜሪካን ዜጎች ለቀው እንዲወጡ ከአሜሪካ ኃይሎች ጋር ተቀናጅተን ሰርተናል ብሏል‼️ ዓለም አቀፍ አደራዳሪዎች የገቡበት የሱዳኑ ተኩስ አቁም ስምምነት ፈርሶ ውጊያው ከቀጠለ በኋላ፤ የካርቱም ሰማይ በከባድ መሣሪያዎች ጭስ ታፍኖ ሰማዩ ጠቁሯል። ውጊያው ሁለተኛ ሳምንቱን በመያዙ አሜሪካ ዜጎቿን አስወጥታለች። በዚህ የተቀናቃኝ ኃይሎች ውጊያ በብዙ መቶዎች ሲሞቱ ብዙ ሺሕ ሕዝብ ቆስሏል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባይደን "በእኔ ትእዛዝ የአሜሪካን ሠራዊት የአሜሪካ መንግስት ሠራተኞችን ከካርቱም የማስወጣት ዘመቻ አካሂዷል" በማለት መግለጫ ሰጥተዋል። ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያና ሳኡዲ አረቢያ ዘመቻውን ለማሳካት ረድተውናል ሲሉ አመስግነዋል። በሔሚቲ የሚመራው የፈጥኖ ደራሹ ኃይል እዝ ከአሜሪካ ሠራዊት ግዳጅ ፈጻሚ አካላት ጋር በመቀናጀት በስድስት አውሮፕላኖች የአሜሪካን ዲፕሎማቶችና ቤተሰቦቻቸው ከሱዳን ለቀው እንዲወጡ ማድረጉን ገልጿል። የሌሎችም ሀገራት ዜጎች ካርቱምን ለቀው በመውጣት ላይ ይገኛሉ። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ለሁሉም ዲፕሎማቲኮች ከሙሉ ትብብር ጋር ጥበቃና ከለላ በመስጠት በሠላም ወደሀገራቸው እንዲመለሱ እናደርጋለን ብሏል። ©አልጀዚራ ቤተሰብ ይሁኑ! ቴሌግራም፦ #ሼር #Join https://t.me/CommandoAndAirborneCommand You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

“ሄሮን ቲፒ (Heron TP)” ድሮን “ሄሮን ቲፒ” አደገኛው የእስራኤል የውጊያ ድሮን በሰዓት በሰዓት 370 ኪ.ሜ የሚጓዘው ድሮኑ ለ30 ሰዓታት አየር ላይ መቆየት ይችላል። “ሄሮን ቲፒ (Heron
“ሄሮን ቲፒ (Heron TP)” ድሮን “ሄሮን ቲፒ” አደገኛው የእስራኤል የውጊያ ድሮን በሰዓት በሰዓት 370 ኪ.ሜ የሚጓዘው ድሮኑ ለ30 ሰዓታት አየር ላይ መቆየት ይችላል። “ሄሮን ቲፒ (Heron TP)” ድሮን የእስራኤል አየር ኃይል ከታጠቃቸው አደገኛ የአውደ ውጊያ መሳሪያዎች ውስጥ በቀዳሚነት ዪጠቀስ ነው። በእስራኤል ኤሮስፔስ ኢንዱስትሪ የተመረተው ድሮኑ በተለያዩ ወታደራዊ ትልእኮዎች ላይ መሳተፍ ብቃቱን ማስመስከር እንደቻለ ይነገርለታል። ሄሮን ቲፒ ድሮንን ከእስራኤል በተጨማሪ እንደ ጀርመን፣ አውስትራሊያ፣ ፈረንሳይ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ካናዳ ያሉ ሀገራት እንደታጠቁጥ ይነገራል። “ሄሮን ቲፒ (Heron TP)” ድሮንን ምን የተለየ ያደርገዋል…ʔ ሄሮን ቲፒ ድሮን በየትኛውም አይነት የአየር ፀባይ ለ30 ሰዓታት ያክል መስራ ይችላ የተባለ ሲሆን፤ በሰዓት 370 ኪሎ ሜትር ፍጥነት መጓዝ እንደሚችልም ተነግሯል። ድሮኑ ለተልዕኮ በሚሰማራበት ወቅት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከባህር ጠለል በላይእስከ 45 ሺህ ጫማ ድረስ ከፍ ብሎ በመብረር ከራዳር እይታ ውጪ ጥቃት መሰንዘር ይችላል። ያለ ሰዎች ንክኪ በራሱ መነሳት እና ማረፍ የሚችው ድሮኑ፤ የሳተላይተ ግንኙነት ቴክኖሎጂ ስለሚጠቀምም ከመቆጣጠሪያ ጣያው ከ1 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ ርቆ መጓዝ ይችላ ተብሏል። ቤተሰብ ይሁኑ! ቴሌግራም፦ #ሼር #Join ለተጨማሪ መረጃዎች You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 14 ቀን  2015 ዓ.ም ለዘላቂ ሠላም የሠራዊት ግንባታ ሂደትን በተመለከተ፦ ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከመከታ መፅሄት ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፡፡ መከታ ፦ የሐገራችንን ሰላም በዘላቂነት ለማስከበር የሰራዊታችን ዝግጁነት በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? የኢፌዲሪ ጦር ሐይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፦  በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ የነበረውን ጦርነት በሰላም  ስምምነት ለመቋጨት ጥረት ከማድረግ ጎን ለጎን በቀጣይ ሐገሪቱን ሌላ ጦርነት እንዳይቃጣባት የሚያደርግ ጦርነትን በሩቅ የሚያስቀርና ጦርነት ከተከፈተብንም በአጭር ጊዜና በአነስተኛ ኪሳራ መመከት የሚያስችል የዝግጁነት ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ሠራዊታችን ከለውጡ በፊት የነበረው ዝግጁነትና አቅም አሁን ከደረሰበት ብቃትና ደረጃ ጋር በፍፁም የማይነፃፀር የሰማይና የምድር ያህል ልዩነት ያለው ነው፡፡ "አየር ሐይልን ብቻ ብንመለከት ዝግጁ የምትባል አንዲት ቢጫ ሄሊኮኘተር ነበረች። የሚበሩ ጄቶች አልነበሩም። ቢበሩም የአብራሪዎች ከፍተኛ እጥረት ነበር። በምድር ሐይልም ቢሆን ኢትዮጵያን የምታክል ትላቅና ታሪካዊ ሀገር የሚመጥን ሠራዊት አልነበረም። የተወሰኑ ክፍለጦሮችና ለስም ብቻ የተደራጁ ዕዞች ነበሩ። በአስተሳሰብ ከፍተኛ ችግሮች ነበሩ። ከሀገራዊ ጉዳይና ህዝባዊ ዓላማ ይልቅ የብሔር አጀንዳና የፓለቲካ ፓርቲ ውግንና ጉዳይ የሚያሳስበው ሠራዊት ነበር። በእነዚህ አሳሪ አስተሳሰቦች የታጠረ ሠራዊት ይዞ ሠራዊቱ ዝግጁ ነበር ማለት አይቻልም።  ለአብነት ያህል በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ጦርነት ሲቀሰቀስ ሙሉ በሙሉ ከብሔርና ከፓርቲ አስተሳሰብ ያልተላቀቁ አባላት ከህውሐት ጋር መቀላቀላቸው ራሱን የቻለ ማሳያ ነው ። እዚህ የቀሩትም ከአስተሳሰቡ የፀዱ ስላልነበሩ የሚያስከትሉትን ጫና ለመቀነስ ለጊዜው እንዲለዩ ተደርጓል።  መከላከያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሪፎርም አካሄዷል።  ሠራዊቱን ከብሔርና ፖለቲካ አስተሳሰብ ማላቀቅ  ከአንኳር አንኳር የሪፎርሙ ተግባራት ውስጥ ይጠቀሳል። በውጤቱም አንድ ዓይነት ሀገራዊ አስተሳሰብ ያለው ሠራዊት መገንባት ተችሏል። ሪፎርሙ ለተቋማችን መከላከያ በርካታ ፀጋዎችን ይዞ መጥቷል። ከእነዚህ ውስጥ የሠራዊቱን የመኖሪያ ካምፖች መገንባት የተሻለ የስራና የሕይወት ዋስትና እንዲኖረው ማድረግ፡፡ የኑሮ ማሻሻል ሥራዎችና የአደረጃጀት ለውጦች ይጠቀሳሉ። ጦርነትን እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀም ከተቻለ መልካም ውጤቶች እንደሚኖሩት ያለፉትን ዓመታት የሠራዊቱን ተሞክሮ  ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በአብነት ያነሳሉ። "መከላከያ ጦርነቱን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሰው ሐይል፣ በአደረጃጀት፣ በትጥቅ መሠረታዊ ለውጥ አምጥቷል። እየተዋጉ ሠራዊት መገንባት ከባድ ቢሆንም ተቋሙ ግን  ይህንን ማሳካት ችሏል። ለጦርነት ዝግጁ የሆነ እዚህ ግባ የሚባል ትጥቅም ሆነ አደረጃጀት እንዲሁም አስተሳሰብ ካልነበረበት ሁኔታ ተነስቶ  አሁን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። አየር ሐይል ሄሊኮኘተሮችንና ጄቶችን በእስኳድሮን ደረጃ ታጥቋል። ምድር ሐይል በሰው ሃይል የተጠናከረ፣ በዕውቀት ያደገ፣ በክህሎት የዳበረና በስነ ልቦና ዝግጁነት የላቀ ሆኖ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ ተደራጅቷል። ዘመኑ የደረሰበትን የዕድገት ደረጃ እንዲሁም ከባቢያዊና ዓለም ዓቀፋዊ ሁኔታዎችን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ መከላከያ በቀጣይነት ለመንገባት የአሥር ዓመት ስትራቴጂካዊ እቅድ ተዘጋጅቶ በመተግበር ላይ ይገኛል።   በዘመናዊ ሠራዊት ግንባታ ታሪካችን በርካታ ሂደቶች ታልፈዋል። በደርግ ዘመን ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር ተብሎ ግዙፍ ሠራዊት መገንባቱ ይታወሳል።  ይሁንና በብዛትም ሆነ በጥራት አሁን ያለውን የኢፌዲሪ መከላከያን የሚያክል ሃይል አልተገነባምና በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን የሚያሰጋት ሐይል የለም"ይላሉ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ፡፡ መከታ  ፦ "የሠራዊታችን ውስጣዊ አንድነትና የተልዕኮ ግልፀኝነት በምን ሁኔታ ላይ ይገኛል ? ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ፦ ሠራዊታችንን ለመከፋፈል፣ ከተልዕኮውና ከቆመለት ዓለማ እንዲወጣ ለማድረግ የሚቃጡ ሙከራዎች  ቢታዩም ይሕ  ፈፅሞ የሚሳካ አይደለም፣ ሙከራውን የሚያደርገት ወገኖችም የሰራዊታችንን ውስጣዊ ሁኔታ ካለመገንዘብ የሚያካሒዱት ሙከራ ነው፡፡ ሠራዊቱ የሀገሩን ዳር ድንበርና ሉዓላዊ ክብር ለመጠበቅ በብሔራዊ ሠንደቅ ዓላማው ፊት ቃል የገባ ፤የብሔር አጀንዳና የፖለቲካ ወገንተኝነትን አራግፎ የጣለ፤ በወርቃማ እሴቶች የተገነባና እሴቶቹን ወደ እምነት የቀየረ ሀይል ነውና ለአፍራሽ ኘሮፓጋንዳ ሰለባ የሚያደርገው ስብዕና የለውም። በግለሰብ ደረጃ ሠለባ የሚሆን እንኳን ቢኖር ሠራዊቱ የሚያርምበትና ችግሩ ሥር ሳይሰድ ፈጥኖ  የሚያስተካክልበት አሠራር አለው  ሠራዊቱ እንዲፈርስ የሚፈልጉት የሀገራችን ቀንደኛ ጠላቶችና ባንዳዎች ናቸው። እንደሚታወቀው ባንዳ ባለቤት አለ፤ አባት አለው። ሀገራችን ጠንካራ ሠራዊት እንዲኖራት የሚፈልጉ ሃይሎች ሠራዊቱ በብሔርና በፖለቲካ እንዲከፋፈል ባንዳዎችን በጥቅም ይገዛሉ። ባንዳ እንደ ዕቃ ህሊናው ለመሸጥ ዝግጁ የሆነ ዜጋ ነው።ለሀገር ክብር፣ ለወገን ሠላምና ደህንነት የሚቆረቆር አይደለም ባንዳ፡፡ "የኢትዮጵያ ጠላቶች ሠራዊታችን ተከፋፍሎ እንዲዳከም ከመሥራት በተጨማሪም ሠራዊቱን ከመንግስት ጋር ለማጋጨትም የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርጉ ይታያሉ::በነውጥ ሐገረ መንግስቱን አፍርሰው ስልጣን ለመያዝ የሚፈልጉ ወገኖች ለዚሕ ዕኩይ ዓላማቸው እንድንተባበራቸው ይፈልጋሉ::እኛ ግን ይሕ መንገድ አሸናፊና ተሸናፊ የሌለበት ሕዝብን ወደ ማያቋርጥ ዕልቂት የሚያስገባ ስለሆነ አንተባበርም::ይልቁንም ሙከራውን በፅናት እንመክተዋለን፡፡ ሠራዊቱ የሚተባበረው ህጋዊ አካሄድን ከሚከተል ጋር ብቻ ነው። ተልዕኳችን በህገመንግስቱ መሠረት የተቋቋመን መንግስት ማገልገል ነው ። ከዚህ ውጭ የመጣን ሐይል እንመክታለን። ለአፍራሽ ኘሮፓንጋንዳ ጆሮ አንሠጥም። ከብሔር አስተሳሰብና ፖለቲካ ውግንና ነፃ የሆነ ሠራዊት ገንብተናል። ህገመንግስቱ ስልጣን የሚያዝበትን አግባብ ግልፅ አድርጎታል። የፖለቲካ ውድድር የሚደረግበትን አግባብና መንግስት የሚቀየርበትን አሠራር አስቀምጧል። በህጉ መሠረት የመጣን መታዘዝ ግዴታችን ነው። በሌላ በኩል ህገወጥን አካል ሠራዊቱ አይታገስም"፡፡ በጦር ሐይሎች ጠቅላይ መምሪያ በየሦስት ወሩ የሚታተመው መከታ መፅሔት ቁጥር 1 ዕትም የተወሰደ

ዶርትመንድ መሪነቱን ተረክቧል ! በጀርመን ቡንደስሊጋ ሀያ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዶርትመንድ ከ ፍራንክፈርት ጋር ያደረገውን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት መረከብ ችሏል። የ
ዶርትመንድ መሪነቱን ተረክቧል ! በጀርመን ቡንደስሊጋ ሀያ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዶርትመንድ ከ ፍራንክፈርት ጋር ያደረገውን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን መሪነት መረከብ ችሏል። የዶርትመንድን የማሸነፊያ ግቦች ማለን 2x ፣ ቤሊንግሀም እና ሁመልስ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል። ዶርትመንድ በዘንድሮው የውድድር አመት ባደረጋቸው ሀያ ዘጠኝ የሊግ ጨዋታዎች አስራ ዘጠኙን በአሸናፊነት የተወጣ ሲሆን በሊጉ ብዙ ድል ያስመዘገበ ክለብም ያደርገዋል። ቦርስያ ዶርትመንድ ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ነጥቡን #ስልሳ በማድረስ የሊጉን መሪነት ከባየር ሙኒክ መረከብ ችሏል።

ለተጨማሪ መረጃዎች You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
ለተጨማሪ መረጃዎች You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 14 ቀን 2015 ዓ.ም "ጀነራል ሠአረ መኮንን በመከላከያ ሠራዊታችን ታሪክ ውስጥ ሁሌም ታስቦ የሚኖር ጀግና መሪ ነው።" ዶ/ር አብርሐም በላይ የቀድሞው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ለነበሩት ጀኔራል ሠአረ መኮነን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቦሌ ሩዋንዳ ድልድይ ሐውልታቸውን አቁሞላቸዋል። በሐውልት የምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከለከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሐውልቱን መርቀው ከፍተዋል። በዕለቱም የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ እንደተናገሩት በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ  በአንዳንድ እኩይ ተግባራት ላይ በተሠማሩ ኃይሎች በተለያዩ ጊዜ የተፈፀሙ አሰቃቂ ግድያዎች የታሪካችን የጥቁር መገለጫዎች ሆነዋል። ለጥፋት እና ለኪሳራ፣ ለመጥፋት እና ለመገዳደል ለመሳደድና ለማሳደድ የሚፈልጉ ነገር ግን ከነዚህ የመጥፎ የታሪክ ልምምድ ባለመማር እና ማስተዋስ ባለመቻላችን ጭምር የመጣ መሆኑን ገልፀዋል። የገባንበት የዕርስ በዕርስ ጦርነት እና የጥቁር መጋረጃ ታሪኮችን እንደ ሀገር እና እንደተቋም የማያዳግም ትምህርት የምንወስድበት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ከጥቁር የታሪክ ምዕራፎች በመማር በከፍተኛ ቁርጠኝነት እና ዝግጁነት በዘላቂ እርቅ ፈጣሪ ፍቱን ጉዟችን የማቅናት ጅምር ጎዳና ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልፀዋል። ሚኒስትሩ ለሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ባስተላለፉት መልዕክት ጥቁር የታሪክ መጋረጃዎችን በፍትህ እና በይቅርታ፣ ዘላቂ ሽረት የሚያገኝበት አግባብ እንዲመጣ አንድነታችሁን በማጠናከር የህዝበችሁን እና የሀገራችሁን ኢትዮጵያ ፅኑ ዋስትና በመሆናችሁ የተጣለባችሁ ኃላፊነት ከባድ ነው ብለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው ጀኔራል ሠዓረ የተሠዋው ጀግና በመሆኑ እና ወታደራዊ ዲሲፒሊን የተላበሰ የኢትዮጵያ ወታደር በመሆኑ ነው ብለዋል። ጀኔራል ሠአረ መኮነን ወታደር ብሔር የለውም በማለት ለሌሎች በማስተማር እና በመምራት ገለልተኛነቱን በተግባር ያረጋገጠ ለትውልዱ ተምሳሌት የሆነ ጀግና መሪ መሆኑንም ገልፀዋል። ጀኔራል ሠአረ ህልፈተ ህይወቱ ቢያሳዝንም የሞተለት አላማ  ለወጣቱ፣ ለመከላከያ ሠራዊቱ እና ለአመራሩ ማስተማሪያ ይሆናል ያሉት ከንቲባዋ ከተማ አስተዳደሩ ሐውልት እና በስሙ መንገዶችን ከመሠየም በተጨማሪ ታሪኩን እናስተምርበታለን  ከጀነራል ሠአረ መኮንን ቤተሰቦች እና ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር በጋራ በመሆን የሚጠበቅብንን ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል። የጀኔራል ሠዓረ መኮንን ባለቤት ኮሎኔል ፅጌ ዓለማየሁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ሩዋንዳ ድልድይ ለጄኔራሉ ጀግንነቱን የሚመጥን ሐውልት በስሙ ስላቆመ ምስጋና አቅርበዋል።

የጄኔራል ሰዓረ መኮንን መታሰቢያ ፓርክና ሐውልት ተመረቀ የቀድሞ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን መታሰቢያ ፓርክና ሐውልት ዛሬ በአዲስ አበባ ተመረቀ። በምርቃቱ ላይ
+4
የጄኔራል ሰዓረ መኮንን መታሰቢያ ፓርክና ሐውልት ተመረቀ የቀድሞ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን መታሰቢያ ፓርክና ሐውልት ዛሬ በአዲስ አበባ ተመረቀ። በምርቃቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ ጀኔራል መኮንኖች፣ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ የጄኔራል ሰዓረ መኮንን ቤተሰቦችና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ሐውልቱ በአዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ አካባቢ በስማቸው በተሰየመ ፓርክ ውስጥ ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱ ተገልጿል። የቀድሞ የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን አገር ወዳድ የኢትዮጵያ ልጅ እንደነበሩ ተወስቷል። ጄኔራል ሰዓረ ከግንቦት 2010 ዓ.ም ሕይወታቸው እስካለፈበት ሰኔ 15/2011 ዓ.ም ድረስ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም በመሆን ኢትዮጵያን በታላቅ ታማኝነትና ቅንነት አገልግለዋል።

ኢድ ሙባረክ ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። በዓሉ የሰላም የጤና የፍቅር የአንድነት ያድርግልን። የዒድ አልፈጥር በዓል በድምቀ
+2
ኢድ ሙባረክ ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። በዓሉ የሰላም የጤና የፍቅር የአንድነት ያድርግልን። የዒድ አልፈጥር በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። የ2015 ዓ.ም የዒድ አልፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት እየተከበረ ነው። 1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በመላው ኢትዮጵያ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው እየተከበረ የሚገኘው። የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የመተዛዘን እና የመረዳዳት እንዲሆን የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፏል። በታላቁ የረመዷን ወር መጨረሻ የሚከበረውን የዒድ አልፈጥር በዓልን በሰላምና በመተሳሰብ እንዲሁም የተቸገሩ ወገኖችን በማገዝ ማሳለፍ እንደሚገባም ጥሪ አቅርቧል።

👉 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ-አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ እያልን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡ ❤❤ ኢድ ሙባረክ! ❤❤
👉 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ-አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ እያልን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡ ❤❤ ኢድ ሙባረክ! ❤❤

👉 የመንግሥት ማስጠንቀቂያ‼ ~"በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል‼"-ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ "በኢትዮጵያ እና በሱዳን ወንድ
👉 የመንግሥት ማስጠንቀቂያ‼ ~"በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል‼"-ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ "በኢትዮጵያ እና በሱዳን ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሠሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል‼" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አሳሰቡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ጉዳዩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ እና የሱዳን ሕዝቦች ብዙ ፈተናዎችን እየተጋፈጡ በሚገኙበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፤ የሐሰት ውንጀላዎችን በማሰራጨት የፖለቲካ ዓላማቸውን ለማሳካት የሚጥሩ ወገኖች እንዳሉ ጠቁመዋል። እነዚህ አካላት "ኢትዮጵያ በሱዳን ድንበር አካባቢ ወታደሮቿን አስጠግታለች" የሚል የሐሰት መረጃ እያሰራጩ መሆኑንም ነው ያነሱት፡፡ ይህን የወንድማማች ሀገራትን ግንኙነት የሚያሻክር የሐሰት ውንጀላም ኢትዮጵያ በጽኑ እንደምታወግዘው አስገንዝበዋል፡፡ በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ያለው ጉዳይም በውይይት እንደሚፈታ እምነታቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሚያዚያ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ለሰላም ስምምነቱ ስኬት-የሁሉም ወገን ቁርጠኝነት በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት የቆየውን ጦርነት በድርድር ለመፍታት በፌዴራል መንግስትና በሕወሃት መካከል በደቡብ አፍሪካና ናይሮቢ የሰላም ስምምነትና ማስፈፀሚያ ሰነዶች መፈረማቸው ይታወሳል፡፡ ይህ ርምጃ በዋነኝነት ጦርነት በተካሄደበት አከባቢ ያሉ ነዋሪዎችንና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ሕዝብ በእጅጉ ያስደሰተ ቢሆንም የስምምነቱን ዘላቂነት በጥርጣሬ የሚመለከቱ ወገኖች ቁጥር ግን ቀላል የሚባል አይደለም፣ በዚህ ላይ በአንዳንድ ወገኖችና ሚዲያዎች የሚቀርቡ አሉታዊ ዘገባዎች የሕዝቡን ጥርጣሬ ይበልጥ አሳድገውታል፡፡ ‹‹ ዕውን የሰላም ስምምነቱ በአንዳንድ ወገኖች እንደሚባለው ተስፋ ቢስ ነው ወይንስ የሚጨበጡና ተስፋ ሰጪ እርምጃዎች እየታዩበት ነው? በሠላም ስምምነቱ መሠረት እስካሁን ምን ምን ተግባራት ተከናወኑ? የስምምነቱን ተፈፃሚነት የሚያመለክቱ ምን ተጨባጭ እውነታዎች አሉ? በአንዳንድ ወገኖች እንደሚወራው ሕወሐት የሰላም ስምምነቱ ዕውን እንዳይሆን የማደናቀፍ ተግባር እየፈፀመ ነው ወይንስ ለስኬታማነቱ እየሰራ ነው? በሚሉት ጥያቄዎችና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ መከታ መፅሄት ከክቡር የኢፌዲሪ ጦር ሐይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጋር ቃለ ምልልስ አካሒዷል፡፡ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ሂደቱን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ የሚከተለውን ብለዋል ፦ "የሰላም ሒደቱን አስመልክቶ አንዱ መነሳት ያለበት ጉዳይ ወደ ሰላም የመጡት ሁለቱም ወገኖች የነበራቸው መንፈስ ምን ይመስላል? የሚለው ነው ይሕ መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ይሕንን አስመልክቶ ብዙ ውዥንብር አለ:"ስምምነቱ የተፈረመው ለጊዜ መግዣ እንጂ ከልብ ተግባራዊ ሊደረግ ታስቦ አይደለም፤ የሕወሐት ሐይሎች ምሽግ በመቆፈርና ተዋጊዎቻቸውን በማሰልጠን ለአራተኛ ዙር ጦርነት እየተዘጋጁ ነው" የሚል ውዥንብር በስፋት የሚያሰራጩ ወገኖች አሉ::÷ እነዚህ የተሳሳቱ መረጃዎች ከተጨባጭ ሁኔታው ጋር  ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸውና  ሕዝብን ዕምነት ለማሳጣት ታልሞ የሚነዙ የሀሰተኛ ኘሮፓጋንዳዎች ናቸው ። ወሬዎቹ ስምምነቱን ከማይፈልጉና፣ ከጦርነቱ ከሚያተርፉ  ሐይሎች የሚመነጩ ናቸው። ኢትዮጵያ ሳትፈልግና ተገዳ የገባችበት ጦርነት ተቋርጦ ሰላም እንዲሰፍን በኢፌዴሪ መንግስት በኩል ከመጀመሪያው ጀምሮ ከፍተኛ ፍላጎት፣ ተነሳሽነትና  ቁርጠኝነት ነበር:፣ ዘግይተውም ቢሆን የሕወሐት አመራሮችም ጦርነቱን በድርድር ማቆም አማራጭ የሌለው ርምጃ መሆኑን ተገንዝበው ወደ ሰላም መጥተዋል፡፡ በአንዳንድ ምክንያቶች መዘግየቶች ቢታዩም ሁለቱም ወገኖች ለስምምነቱ ተፈፃሚነት እየሰሩ ናቸው፤የሐገራችንን ሰላም በዘለቄታው በማረጋገጥ የወደሙትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተቋማትን መልሰን በመገንባት የሕዝቡን ሕይወት የመለወጥ ጉዳይ ሁሉም ወገኖች ሊረባረቡበት የሚገባው የሕልውና ጉዳይ ነው፡፡ በመጀመሪያ በደቡብ አፍሪካ፣ ቀጥሎ በኬኒያ ናይሮቢ በተደረጉ ስምምነቶችና የማስፈፀሚያ ሰነዶች መሰረት በሁለቱም በኩል ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተገብቷል። ፌዴራል መንግስት ሰብዓዊ እርዳታ፣ ባንክ፣ ስልክ፣ መብራት እና የመሣሠሉ አገልግሎቶች እንዲመለሱ አድርጓል። ሠራዊቱን ከውጊያ አላቋል። ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን እና የሀገር ሽማግሌዎችን ወደ መቀሌ በመላክ መተማመን እንዲፈጠር ብዙ ርቀት ተጉዟል። በህወሐት በኩልም  በጎ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ። ሠራዊቱን ወደ ካምኘ አስገብቷል። ከባድ መሣሪያዎችን ለመንግስት ማስረከብ ጀምሯል። ስምምነቱ በሚፈለገው ልክ ተግባራዊ እንዲሆንና ተቀባይነት እንዲያገኝ ህዝቡን አወያይቶ መግባባት ላይ ደርሷል። የሠላሙ አስፈላጊነት በእጅጉ የታመነበት በመሆኑ ለስኬታማነቱ ከልብ የሚሠሩ የህወሐት አመራሮች አሉ።  በርግጥ ከጉዳዩ ክብደት አንፃር አሁንም የሚቀሩና ጊዜ የሚፈልጉ በርካታ ስራዎች መኖራቸው እሙን ነው። ስምምነቱ ምህረትን የሚያካትት በመሆኑ የተከሰሱ ሰዎችን ክስ ማንሳትና የመሳሰሉትም ቀጣይ ተግባራት ውስጥ የሚካተቱ ናቸው፡፡  የቀሩ ትጥቆችን የማስፈታቱ ሂደትም የሚቀጥል ይሆናል። የህወሀትን ተዋጊ ሀይል ወደ ካምፕ ማስገባት ፣ትጥቅ ማስፈታትና  ከህዝቡ ጋር እንዲቀላቀሉ የተሀድሶ ስልጠና መስጠት DDR /disarmed dimoblized and rehablitate/ የስምምነቱ አካል ናቸው። ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተተግብሯል ማለት የሚቻለውም እነዚህ ስራዎች ከተከናወኑ በኋላ ነው። እስካሁን ህወሀት ተዋጊ ሀይሉን  ወደ ካምፕ በማስገባቱ  የመጀመሪያው ስራ ተተግብሯል። ትጥቅ ማስፈታትና የተሀድሶ ስልጠናዎቹ  ደግሞ የሚቀጥሉ ናቸው ። በአጠቃላይ የሰላም  ስምምነቱ አተገባበሩ በፌዴራል መንግስቱም ሆነ በሕወሃት በኩል በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ይገኛል ማለት በሚቻልበት ደረጃ ላይ ነው ያለው። ይሁንና በአንዳንድ መገናኛ ብዙሀን በተለይም በማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚነዙ አፍራሽ አሉባልታዎች አሉ። አሁን ላይ ህዝቡም ሆነ አመራሩ ጦርነትን አይፈልጉም። ጉዳቱንም በሚገባ ተረድተውታል። ይሁንና በዜጎች መካካል አንድነት እንዳይኖር፣ ልዩነት እንዲፈጠር፣ ኢትዮጵያ እንድትዳከም የሚሠሩ የውጭ ጠላቶቻችንና የውስጥ ባንዳዎች የሰላም ስምምነቱ ስኬታማ እንዲሆን አይፈልጉም  ለሆዳቸው የተገዙ ባንዳዎችን እኩይ ድርጊትና የቀጣሪዎቻቸውን ፍላጎት በመረዳት በጋራ መመከት የህልውና ጉዳይ መሆኑ መታወቅ አለበት። ለሠላም ሲባል የሚተገበሩ በርካታ ጉዳዮች ይኖራሉ። በመንግስት እና ህውሐት መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት ጦርነቱን የሚያባብሱ ተግባራት ይቅሩ ብለናል። ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ አካሄድ መከተል ግድ ስለሚል ፉከራ፣ ሽለላና የአሸናፊነት መፈክር ማንፀባረቅ አይፈለግም። ከቆምንበት መጀመር እንደሚያስፈልግ ሁለታችንም ተግባብተናል። የሠላም ስምምነቱን በተፈራረሙት ሐይሎች በኩል  ነገሮችን የማባባስና ሠላምን የሚያደፍረስ ፍላጎት የለም። በዚህም ሆነ በዚያ በኩል ቁጥሩ አነስተኛ ቢሆንም ሠላም የማይፈልግ ሐይል መኖሩ ግን እየታየ ነው። የኢትዮጵያን ጠላቶች ማድመጥ አያስፈልግም። ባንዳም ቢሆን በታሪካችን ጠፍቶ አያውቅም። ሌላው ቀርቶ በታላቁ የጥቁር ህዝቦች ድል የአድዋ ጦርነት ወቅት እንኳ በሺህዎች የሚቆጠሩ ባንዳዎች ነበሩ። ‹‹ግጭት ተፈጥሯዊ ነው። በተለያዩ ወቅቶች በተለያዩ ምክንያቶችና በተለያዩ አካላት ሊከሰት ይችላል። አለመግባባትን በሠላም መፍታት የሰው ህይወት መጥፋትንና የንብረት ውድመትን ለማስቀረት ሲባል ለሠላም መረታት ሐላፊነት የሚሠማቸው አመራሮች ተግባር ነው። በመሆኑም ለሠላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መሆን እየተሠራ ሲሆን የእስካሁኑ ጉዞም ውጤታማ ነበር ማለት ይቻላል›› ብለዋል ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡ በጦር ሐይሎች ጠቅላይ መምሪያ በየሦስት ወሩ የሚታተመው መከታ መፅሔት ቁጥር 1 ህትም ላይ  የተወሰደ 👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneCommand YouTube https://youtu.be/hhcmZ_R7MQE

👉 ስለሀገር የመኖር ፅናት~እንደ ወታደር‼️🙏🙏🙏 ሀገርን መውደድ ስለ ሀገር መሞገት ከማንኛውም ዜጋ የሚጠበቅ በጎ እሳቤ ነው። ነገር ግን ሀገርን መውደድና ስለሀገር መኖር ለየቅል የሚሆኑበት እውነታዎችም አሉ።    በስመ - ሀገር ወዳድነት ህጸጽ ብቻ እያነፈነፉ፣ የተፈጠሩ ችግሮችን ከሚገባው በላይ እየለጠጡና ከመጠን በላይ እያገዘፉ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ሲያላዝኑ መዋል የሚያስገኘው ጠብ የሚል ነገር የለም።     ይህ ሲባል በሚከሰቱ ችግሮች ሁሉ ዝም ይባል፣ አንዳችም የግል አስተያየት አይሰጥ ለማለት ተፈልጎ እንዳልሆነ ልብ ይባል።      ሀገር ትውልድ እስከቀጠለ ድረስ እንደየዘመን ሁነቱ ችግሮች አሉ። ነበሩ። ይኖራሉም። ምክንያቱም ፍጹም ትክክል የሆነ ነገር ከሰው የሚጠብቅ ካለ የራሱን ሰዋዊ እውነታ የዘነጋ ነው ቢባል ስህተት አይሆንም።     ከፀሐይ በታች ዓለምን በማያቋርጥ ምርምርና ጥናት እየታገዘ በአስገራሚ ፈጠራዎች የሚያስደምም ግኝት እውን እያደረገ የሰው ልጅ ህይወትና ኑሮን ለእስከዛሬው ዓለማዊ ዕውነት ያበቃው የሰው ልጅ ዕውቀት በብዙ ስህተቶች ባለፈ ጉዞ የተገኘ ትሩፋት መሆኑን ማጤን ግድ ይላል።     በተለይ...በተለይ እንደኛዋ ኢትዮጵያችን ዓይነት በየዘመናት አንጓ እየተፈጠሩ በመጡ የታሪክ፣ የፖለቲካና መልከ - ብዙ ስብራቶች እያነከሰች ዛሬ ላይ የደረሰች ሀገር ላይ በጥቂት ዓመታት ሆይ ሆይታ ሁሉም ነገር በምናስበው ልክ ትክክል እንዲሆን መጠበቅ የዋህነት ነው የሚሆነው።    "እና ምን? " የሚል ጥያቄ አጭሮብን ይሆን ይሆናል። ምላሹ ከተባለ እንደኔ "ሀገርን ከመውደድ እና ስለ ሀገር ከመሞገት ባሻገር፤ ስለሀገር የመኖር ጽናት ይኑረን።" ነው።   " እንደ ማን?" ከተባለ ደግሞ "እንደ ወታደር" እላችኋለሁ።     የሀገሬ የሀገራችሁ ወታደር አሁን ላይ ከየትኛውም ፖለቲካዊ ሆነ ሌሎች ውግንና ነጻ ሆኖ፤"ከራስ በፊት ለሀገርና ህዝብ" በሚል መርህ ሁለንተናውን በሙያዊ ዲሲፕሊን ለሀገሩ ፍቅር አውሎ በሳምንት ሰባት ዕለታት በቀንም ሃያአራት ሰዓታት ያለ ዕረፍት እየሰራ ይገኛል።ሲሰራም እስከሚደክመው ሳይሆን እስከሚሞት ድረስ።     በነገራችን ላይ የውትድርና ሙያ በራሱ በስብዕናና ዜግነታዊ ዕምነት ላይ የበዙ በረከቶችን ለግሶ፣ በችግሮች ማላዘንን ሳይሆን፤የመፍትሄ አካልነትን፣ በስሜት ከመንተክተክ ይልቅ ስክንነትን፣ ከሆይ ሆይታ ይልቅ አስተዋይነትን፣በትንሽ ነገር ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ ጽናትን የሚያላብስ የሞያዎች ሁሉ በኩርና ክቡር ነው።     የውትድርና ህይወት በማያቋርጥ የዕውቀት ዑደት ውስጥ ዕለት በዕለት ማለፍም ነው።በዘላቂ ሳይንሳዊ ተጨባጭ ዕውቀትና ጥበባዊ አመራር እየተገነባ የሚራመድ ተቋም አባል የመሆንን ወርቃማ ዕድል የሚያጎናፅፍም ነውና፤አያልቄ ገጸ - በረከት የሚገኝበትም ነው።     ለዚያም ነው  ወታደር በጠባብ ደረቱ በምትገኝ ልቡ ውስጥ ታላቋንና ግዙፏን ኢትዮጵያ ይዟት ለጸና ሰላሟ ሲያካልላት የሚኖረው።     በሀገሩ ምንም ቢፈጠር ምን፤ መፍትሄ እንደሚኖር ተስፋ አድርጎ ብቻ ሳይሆን አምኖም ጭምር ስለሰላም ይሰራል።በመስዋዕትነት ታጅቦ።     ታዲያ ስለድካሙና ቃላት ሊገልጹት አቅም በሚያንሳቸው ብርቱ ልፋትና ድካሙ ምትክ ክፍያ አይሻም።ክፍያው የሀገሩ መጽናት መከበርና የታላቅነት ጉዞ መቀጠል ነው።     እናም ወታደር ሀገሩን ከመውደድ ተሻግሮ ስለሀገር ይኖራል። በታመነና ከእውነተኛ ልባዊ ፍቅሩ በመነጨ ኢትዮጵያዊ እምነት።     ይህንን ጽኑ እምነት አይተን፣ ሀገራዊ ችግሮችን ለግላዊ ጥቅም የሚያውሉ ቀላማጅ ዩቱዩበሮች 'እውን የሀገር ተቆርቋሪ ናቸውን?' ብለን ራሳችንን እንጠይቅ።     አንድ ነገር ግን ማለት ግድ ይላል። ሁሉም ዜጋ ባለው ሙያ፣ ዕውቀት፣ ገንዘብና ጉልበት እንደ ወታደሩ ሁሉ፤ ፖለቲካውን ለፖለቲከኞች ትቶ፤ የበኩሉን ዜግነታዊ አበርክቶ ለሀገር በመኖር መርህ ቢወጣ ምን ውጤት እንደሚገኝ ለመገመት አይከብድም።    እንዲህ ያሉ ዜጎች የሉም ማለት ሳይሆን እልፍ አዕላፍ ቢሆኑ አስባችሁታል? ክብር ስለሀገሩ በፅናት ለሚኖረው ወታደር‼️

#ሱዳን " ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን " በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል። በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካር
+1
#ሱዳን " ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን " በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል። በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካርቱም ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስልክ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ እዚህ ኢትዮጵያ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት ልከዋል። በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸው እንደተጨነቁ የገለፁት እንዚሁ የአባላት ፤ ማንን መጠየቅ እንዳለብን ግራ ገብቶናል ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አካል ምላሽ ሊሰጠን ይገባል ብለዋል። ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሁለተኛ ቤት በሆነችው ሱዳን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለስራ እና በቋሚነት ለኖሮ እንደሚገኙ ይታወቃል። የሰሞኑ የሱዳን ውጊያ ደግሞ እዛ ያሉትን ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሉ ቤተሰቦችንም ጭምር ጭንቀት ውስጥ ጥሏል። ከትላንት በስቲያ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አሳውቋል። ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር ባይገልፅም ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል። መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻልም ገልጿል።

#ሰበር ሱዳን ኢትዮጵያ ድንበሯን እንድትዘጋላት ጠየቀች። ሾልኮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው የሱዳን መንግስት ለኢትዮጵያ ያቀረበው ጥያቄ የፈጥኖ ደራሽ ታጣቂዎች በድንበር በኩል ወደ ጎረቤት ሃገራት
#ሰበር ሱዳን ኢትዮጵያ ድንበሯን እንድትዘጋላት ጠየቀች። ሾልኮ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው የሱዳን መንግስት ለኢትዮጵያ ያቀረበው ጥያቄ የፈጥኖ ደራሽ ታጣቂዎች በድንበር በኩል ወደ ጎረቤት ሃገራት ሾልከው ሊያመልጡ ይችላሉ ከሚለው ስጋት የመነጨ ነው ተብሏል። በሱዳን መንግስት ሰራዊትና በፈጥኖ ደራሽ የሃገሪቱ ሃይል መካከል የተከፈተው ግጭት ሳምንት ሊሞላው ነው። በዚህ ሂደት ኢትዮጵያ የሱዳን ህዝብ ወደ ሰላም እንዲመለስ ለማድረግና ልዩነቶችም በንግግር እንዲፈቱ ድጋፍ እንደምታደርግ በይፋ ማስታወቋ ይታወሳል። አንዳንድ ሃገራት በሱዳን ግጭት ጣልቃ በመግባት የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር እየሞከሩ መሆኑን ደግሞ ሁለቱም የሱዳን ተፋላሚዎች ሲከሱ እንደነበር ይታወሳል። ወታደሮቻቸውን መሃል ሱዳን ውስጥ አስፍረው የተገኙት  ሃገራት ደግሞ የራሳቸውን ግልፅ የጣልቃ ገብነት ሴራ ለመሸፈን ኢትዮጵያንም ወደ እኩይ ሴራቸው ስበው ለመክተትና ስሟን ለማጠልሸት የበሬ ወለደ ወሬያቸውን መንዛት ጀምረዋል።

ሱዳን 200 የሚደርሱ የግብጽ ወታደሮችን ማስወጣቷን አሳወቀ የግብጽ ወታደሮች ለጋራ ወታደራዊ ልምምድ ተልእኮ በሱዳን ነበሩ ተብሏል። የግብጽ ጦር ወታደሮቹ ሱዳንን ለቀው እንደወጡ እስካሁን አላሳወቀም።  ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ያንብቡ፤ https://am.al-ain.com/article/egyptian-troops-evacuated-from-sudan