የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Kanalga Telegram’da o‘tish
4 770
Obunachilar
-23224 soatlar
-1 7917 kunlar
-3 26430 kunlar
Postlar arxiv
🇪🇹 ይህ ነው ምኞቴ እኔ በህይወቴ 🇪🇹
🇪🇹 ለውድቷ ሃገሬ ለኢትዮጵያ እናቴ 🇪🇹
🇪🇹 ክብር ለመከላከያ ሰራዊታችን 🇪🇹
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ሰበር መረጃ‼️
የ WFPን መረጃ ያረጋገጠ መግለጫ UN ሰጥቷል። ለእርዳታ የገቡ 12 ነዳጅ የያዙ ቦቴዎችን ዛሬ ከመቀሌ በሽብርተኛው ህወሃት ታጣቂዎች ተዘርፈዋል።
#Update
ተመድ በመቐለ ነዳጅ መዘረፉን ገለፀ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ፤ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ዛሬ ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ጥዋት በትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን መዘረፉን ገልፀዋል።
ዱጃሪች ፤ ዛሬ ማለዳ ላይ የትግራይ ኃይሎች መቐለ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በኃይል በመግባት 12 የነዳጅ ታንከር ተሽከርካሪዎችን 570,000 ሊትር ነዳጅ መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
በቦታው የነበረው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ቡድን ዘረፋውን ለመከላከል ጥረት ቢያደርግም እንዳልተሳካለት ተናግረዋል።
የተዘረፈው ነዳጅ ለሰብዓዊ ድጋፍ ፣ ምግብ፣ ማዳበሪያና ሌሎች አስቸኳይ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የሚውል ነበር ያሉት ዱጃሪች " ነዳጁ በመዘረፉ በመላው ሰሜን ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመድረስ የሚሰራው የሰብዓዊው ድጋፍ ስራ ላይ ተፅኖ ይኖረዋል " ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰብዓዊ ስራ ሊውል የነበረው ነዳጅ ላይ የተፈፀመውን ዝርፊ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ
ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ከነሃሴ 16/2014 ዓ/ም ጀምሮ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር በመሆን በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ፒ ኤች ዲ) ተሾመዋል፡፡
ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከኔትወርክ ኢንጂነር ባለሙያነት ጀምሮ እስከ ዲቪዥን ሃላፊነት ለ14 አመታት ያክል ተቋሙን አገልግለዋል፡፡ በ2014 ዓ/ም ተቋሙን ከለቀቁ በኋላም በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሚኒስትር ቴክኖሎጂ አማካሪ ሆነው ለአንድ አመት ሰርተዋል።
ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ከአንድ አመት ቆይታ በኋላ ወደ ኢመደአ በመመለስ ከነሃሴ 16/2014 ዓ/ም ጀምሮ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሾመዋል ፡፡
ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ከማይክሮ ሊንክ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በኮምፒዩተር ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ሲሆን የማስተርስ ዲግሪያቸው ደግሞ ዩናይትድ ኪንግደም ከሚገኘው ሮበርት ጎርደን ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን እና ኔትወርክ ሴኪዩሪቲ አግኝተዋል፡፡
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አመራርና አባላትም ለወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ መልካም የሥራ ጊዜን ይመኛሉ፡፡
✍️ ስለ ጦርነት ወቅት መረጃ አሰጣጥ
በመኩሪያ መካሻ ~ ከአአዩ
1. በጦርነት ወቅት የመረጃ አሰጣጥ ጥብቅ ቁጥጥርን ይሻል።ወታደራዊ የግንባር መረጃዎች ይፋ መደረግ ያለባቸው በመከላከያ ቃል አቀባይ ብቻ ነው።
2.ሀገራዊ አጠቃላይ መረጃዎች በመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ብቻ ይሰጡ።ከዚህ በፊት እንደታየው የወረዳ ኮሙኒኬሽንና የከተማ ሹም የሚሰጠው መግለጫ መኖር የለበትም።
3. ሀገር አቀፍ የዘማች ጋዜጠኞችን ቡድን በማደራጀት የዕዝ ጠገጉን የጠበቀ መረጃ ማሰራጨት።ጋዜጠኞቹ ከመከላከያ ጋር ተዳብለው(embedded) እንዲሰሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸት።
4.በየሚዲያው የወታደራዊና ደህንነት ጉዳዩችን የሚከታተል የአርታኢያን ቡድን መሰየም።
5.በመንግስት ኮሙኒኬሽን በኩል ሀቅ አጣሪ፣የስነልቡና ጦርነቱን የሚመራ( ግብረ ሃይል(Ninja) በማቋቋም ሃሰተኛ ወሬዎችን፣የተዛቡና የተበከሉ መረጃዎችን በማጣራት አምካኝ ሥራ መሥራት።
የትግራይ ማህበረሰብ የወደፊት ሁኔታው ያስፈራኛል!
የትግራይ ክልል ፖለቲካ ሁኔታ በኤሊቶችና በጀሌዎቻቸው የሚዘወር ነው።
ይህ የትግራይ ህዝብ እጅግ አናሳ በመሆኑ ምክኒያት አብዛኛው የሀገራችን ክፍል በውስጡ ባፈራቸው ተንከሲስ ሽብርተኞች ጦስ የተነሳ ተጎጂ ሆነው ኖሮዋል።
ለምሳሌ ባለፉት አመታት ከአማራ ህዝብ አብራክ ውስጥ የወጡ ሙህራንን የትህነግ አፈ_ቀላጤዎች የሴራ ክንውን በፈጸሙት ተግባር ንጹሀኑ እና አብዛኛው የአማራ ህዝብ ነፍጠኛ የሚል ታርጋ ተሰጥቶት በየቦታው ለሞት ለስደት ለስቃይ ተዳርጓል ይህ ሁሉ መከራ በአማራ ህዝብ ላይ የደረሰው የህውሃት መሪዎች በጊዜያቸው በሰሩት ግፍ ነው።
ንጹሀን የትግራይ ተወላጆችም በየቦታው ሲገላቱ ሲገደሉ ሲፈናቀሉ ነበር ይህም የሆነው የትግራይ ኤሊቶች በማንአለኝበነት በፈጸሙት ግፍ የተነሳ ነው።
ዘሬስ የትግራይ ህዝብ አንገቱን አዞሮ ማየት ያለበት ጉዳይ ካልሆነ በቀር አሁናዊ የትግራይ ህዝብ ከየት ወደ የት እየሂደ ነው!! ለወደፊቱስ እጣፈንታቸውን በእጃቸው እያለ ለምን በራሳቸው ጊዜ ኢትዮጵያ የጠላቻቸውን ግለሰቦችን አቅፎ ይቀጥል ይሆን??! የወደፊት እጣ-ፈንታው ምን ይሆን??!!
ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም
የትግራይ ጉዳይ መፍትሔ ሊያገኝ የሚችለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ ነው - ዶክተር አብርሃም በላይ
የትግራይ ጉዳይ ዘላቂ መፍትሔ ሊያገኝ የሚችለው በመነጋገር፣ በመወያየት እና በሰላማዊ መንገድ ብቻ ነው ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብረሃም በላይ ለትግራይ ወጣቶች የሰላም ጥሪ አቀረቡ።
ዶክተር አብርሃም በላይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ የፌደራል መንግስት ለሰላም ያሳየውን ዝግጁነትና ያቀረበው ጥሪ አሸባሪው ህወሓት ወደ ጎን በመተው፣ የትግራይ ህዝብ ተስፋ ያደረገበትና በጉጉት ሲጠብቀው የቆየውን የሰላም አማራጭ በመተው ዛሬ ጦርነት መጀመሩን ገልጸዋል፡፡
ሰበር መረጃ!!
ለህወሃት የጦር መሳሪያ ጭኖ የኢትዮጵያ የአየር ክልል ጥሶ የገባ አውሮፕላን መምታቱን አየር ኃይሉ አስታወቀ
የኢትዮጵያን መዳከም የሚፈልጉና ለዚሁም ለዘመናት የሚንቀሳቀሱ ህወሃትን በመደገፍ ላይ የሚገኙ ታሪካዊ ጠላቶች ንብረት እንደሆነ የሚታመን አውሮፕላን ለሽብር ቡድኑ የጦር መሳሪያ ጭኖ በሱዳን አልፎ የአየር ክልላችንን ጥሶ ሲገባ በጀግናው አየር ሃይል ተመትቶ ወድቋል::
ሠራዊቱ የሀገሩን ሉዓላዊነት ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ዝግጁ መሆኑም ተገልጿል።
በሀገር መከላከያ ሠራዊት የመከላከያ ህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊ ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ላለፉት በርካታ ወራት ከፍኛ ወታደራዊ ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው አሸባሪው ህወሃት ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ ኃይሉን ለውጊያ ሲያስጠጋ ነበር።
በየጊዜውም ተኩስ እየከፈተ የሀገር መከላከያን ሲተነኩስ መቆየቱንም ነው ያነሱት።
ቡድኑ መንግስት የዘረጋውን የሰላም አማራጭ ከቁብ ሳይቆጥርና የሰላም ሂደቱ ቴክኒካሊ ፈርሷል ብሎ መግለጫ ባወጣ ማግስት ትናንት ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ሌሊት 11 ሰዓት ላይ በቆቦ ግራና ቀኝ ባሉ አካባቢዎች፣ በዞብል ተራራ፣ በቢሶበርና በወትወት ውጊያ መክፈቱን ገልጸዋል። በዚህም የተኩስ አቁም ስምምነቱን ማፍረሱን ጠቅሰው፤ የሽብር ቡድኑ እየላከ ያለው ጀሌ በሀገር መከላከያ ሠራዊትና በጸጥታ ሃይልች እየተለበለበ ነው ብለዋል።
ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም
የትግራይ ህዝብ ችግሮችን ለመፍታት ሰላማዊ አማራጭ ዛሬም፤ ነገም ብቸኛዉ መፍትሄ ነዉ!
መንግስት ተገዶ የገባበትን የሰሜኑን ጦርነት በሰላም ለመቋጨት ያስችላሉ ያላቸውን እርምጃዎች ሲወስድ መቆየቱ ይታወቃል። የሽብር ቡድኑ ህወሃት ከወረራቸው የአማራና የአፋር አብዛኞቹ አካባቢዎች ተገፍቶ እንዲወጣ ከተደረገ በኋላ መንግስት፤
• ሙሉ የሰራዊትና ሎጂስቲክስ አቅም እያለው ወደ ትግራይ ክልል ከመግባት መቆጠቡ
• የተሳለጠና ያልተቋረጠ የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል እንዲገባ የተናጠል ተኩስ አቁም ማድረጉና ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ
• ለሰላም በር ይከፍታል በሚል እስረኞችን መፍታቱ
• የሰላም አማራጭንም አሟጦ ለመጠቀም እንዲቻል የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴን በይፋ ወደ ስራ አስገብቶ ግልጽ አቅጣጫንም ማስቀመጡ
• አስፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ ቁሳቁሶች ወደ ትግራይ እንዲጓጓዝ ማድረጉ
• በአሸባሪዉ ቡድን የወደሙ አገልግሎት መስጫዎችን በመጠገን በሶስተኛ ወገን በኩል ስራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሆኖም አሸባሪው ቡድን ከውጪ ደጋፊዎቹ ጋር በመሆን ጦርነቱን የመቀጠል ከፍተኛ ፍላጎትን ሲያንጸባርቅ ቆይቷል፡፡ ከበባውን እንሰብራለን፣ መተማመኛችን ክንዳችን ነው፣ የትግራይ መሬቶች ተወረዋል፣ እናስለቅቃለን፣ ወዘተ በሚል ፉከራ ታጅበው ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ ትንኮሳዎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። በምዕራብ በኩል በተደጋጋሚ ሞክረው ሽንፈትን እየተከናነቡ ተመልሰዋል። በደቡብ ትግራይ በኩልም ተደጋገሚ ሙከራ ቢያደርጉም መንግስት ሙከራቸውን እያከሸፈ ዋናው መፍትሔ የሰላም መንገዱ ነው በሚል ጉዳዩ እንዳይባባስ አድርጓል።
ሆኖም ከመንግስት በኩል የቀረቡለትን በርካታ የሰላም አማራጮች ሁሉ ወደጎን በመተው የሽብር ቡድኑ ህወሃት ታጣቂ ቡድን ሰሞኑን ሲፈጽም የሰነበተዉን ትንኮሳ ገፍቶበት ዛሬ ንጋት ላይ በምስራቅ ግንባር በቢሶበር፣ በዞብል እና በተኩለሽ አቅጣጫዎች ከለሊቱ 11 ሰአት ጀምሮ ጥቃት ፈጽሟል። በወሰደዉ እርምጃም ተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል፡፡ የፈጸመው ጥቃትም ሆነ እሱን ተከትሎ ያወጣው መግለጫ አሰቀድሞ ለትንኮሳው ሲዘጋጅ እንደነበር ግልጽ ማሳያ ነው።
ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችንና መላው የጸጥታ ሃይላችን ከሽብር ቡድኑ የተሰነዘረውን ጥቃት በተቀናጀ መልኩ በድል እየመከቱት ይገኛሉ። የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ከአሸባሪው ቡድን ለመጠበቅም በወትሮ ዝግጁነት ሁሉም የጸጥታ ሃይላችን በተጠንቀቅ ቆሟል።
ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል እንደሚባለው ቀድሞም በተካኑበት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ስራ ራሳቸዉ ተንኩሰዉ ራሳቸዉ እየጮሁ ይገኛሉ፡፡
ለሰላም እጁን የዘረጋዉን መንግስት በሃሰት በመወንጀል “ድርድሩ አስቀድሞ ከሽፏል” በሚል ለተለያዩ ወገኖች ጦርነቱ እንደማይቀር ሲያደርጉ የነበረዉን ቅስቀሳ በማጠናከር የትግራይን ወጣት ዳግም ሊማግዱት በይፋ አዉጀው ወደ ጦርነት እየተንደረደሩ ነዉ፡፡
ሰሞኑን አለም አቀፍ አጫፋሪዎቻቸው ካሸለቡበት ብቅ ብቅ ማለታቸውም የጦርነት ዝግጅቱን በፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የማጀብ አካል መሆኑ ግልፅ ሆኗል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የትግራይን ወጣት ለማስጨረስ ሕወሓት የሚያደርገውን የጦርነት ጉሰማ እንዲያቆም ጠንካራ ግፊት ማድረግ ይኖርበታል፡፡
በሃገር ውስጥም ሆነ በመላው አለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ከዚህ የጥፋት ሃይል የሚሰነዘረውን ጥቃት ለመመከትና ኢትዮጵያን የመበተን ግልጽ አላማ የያዘውን ይህንን የሽብር ቡድን የጥፋት ሙከራ ለማምከን በጋራ እንድንቆም መንግስት ጥሪውን ያቀርባል።
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ መፍትሄ ማግኘት የሚችለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በመገንዘብ ዛሬም ነገም የሰላም አማራጭ የመጀመሪያ መፍትሔ እንደሆነ መንግሥት ፅኑ እምነት አለዉ፡፡
ሆኖም አሸባሪዉ የሕወሓት ቡድን በትንኮሳው ከገፋበት፤ መንግስት ሀገር የማዳን ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታ ስላለበት እንዲሁም የሽብር ቡድኑ ወደደም ጠላም ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ ለማድረግ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳል፡፡
ይህንን ለማስፈፀም ደግሞ መንግስትና መላው የፀጥታ ሃይላችን ከነሙሉ ብቃትና ቁመናቸዉ በተጠንቀቅ ላይ ናቸው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በራያ በኩል እጃቸውን በፍቃደኝነት እየሰጡ ያሉ ምርኮኞች ከአንድ ቤት አንድ ሰው ግዴታ ነው:: ይቅርታ አማርኛ በደንብ አልችልም ተገደን ነው ይህን ያዘዘው ደብረጺዮን ነው::
የመከላከያ ሚኒስቴር እና የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠቃል ።
የአጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮኋል እንደተባለው የሆነው የአሸባሪው የህወሓት ጉዳይ የመግለጫው አካል ነው።
መግለጫው ከሰዓታት በኋላ ይሰጣል።
የህወሓት ወያኔ ጋዜጠኛ ነው። ጦርነት እንደተከፈተብን በሁሉም የሚዲያ አማራጮች አጀንዳ እናድርገው ነው የሚለው።
ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም
በኢሊባቦር ዞን ለዘረፋ የገባው አሸባሪው ሸኔ በጥምር ፀጥታ ሀይሉ መመታቱ ተገለፀ።
በኢሊባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ ዱጳ ከተማን ለማውደምና ለመዝረፍ አልሞ የመጣው የአሸባሪው ሸኔ ቡድን መመታቱን በስፍራው የሚገኘው የክ/ጦር ዋና አዛዥ ተናገረዋል።
የዘራፊው ስብስብ ቡድን ሠላምና ፀጥታ በመንሣት አካባቢውን የሽብር ቀጠና ለማድረግ እና የህብረተሠቡን የተረጋጋ ኑሮ ለማወክ አቅዶ ቢመጣም ከክ/ጦሩ ጋር የተጣመረው የፀጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ቁርጠኝነት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አካባቢውን ከስጋት ነፃ ማድረግ መቻሉን ዋና አዛዡ ገልፀዋል።
ዋና አዛዡ አክለውም የአካባቢው የፀጥታ ኃይል እና ማህበረሰቡ ያደረገውን ተጋድሎ በማመስገን ለቀጣይም ጠንክረው ለአካባቢያቸው ሠላም ከፀጥታ አካላቱ ጋር ተባብረው እንዲሠሩ መልዕክት አስተላልፈው የአሸባሪውን ሸኔ ስብስብ በገባበት ገብተን ለመደምሰስ ቀን ከሌት እንሠራለን ብለዋል።
ክፍለ ጦሩ እግር በእግር ተከታትሎ ከመታው የሸኔ ዘራፊ ቡድን ከህብረተሠቡ የዘረፋቸውን ኮምፒውተሮች፣ ሞተር ሣይክሎችን ጨምሮ የሽብር ቡድኑን የሚመሩት ናስር ኢብራሂም ፣ገመቹ ኢተፋ እና ገመቹ ወላኔ መማረካቸውን የክፍለ ጦሩ አዛዥ ገልፀዋል።
አጋሜዎቹ ርዕሰ መዲና አዲግራት ከተማ ዛሬ ወያኔን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል። ጦርነት በቃን ብለዋል አዲግራቶች🙏🇪🇹🇪🇹🙏
✍️ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
አጋሜዎቹ ርዕሰ መዲና አዲግራት ከተማ ዛሬ ወያኔን በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል። ጦርነት በቃን ብለዋል አዲግራቶች🙏🇪🇹🇪🇹🙏
የአሜሪካ ነገር
በመጨረሻም አሜሪካ ዜጎቿ ዩክሬንን ለቀው እንዲወጡ አስጠነቀቀች‼️
በኪቭ ያለው የአሜሪካ ኢምባሲ አሜሪካዊያን በአስቸኳይ ዩክሬንን ለቀው እንዲወጡ አሳስቧል።
ኢምባሲው ማስጠንቀቂያውን ያወጣው ሩሲያ በዩክሬን መሰረተ ልማቶች ላይ አዲስ ጥቃት ልትሰነዝር እንደምትችል ስጋት ስላለው እንደሆነ አስታውቋል።
በመሆኑም በዩክሬን ያሉ አሜሪካዊያን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ተጠቅመው በየብስ እና በአየር ትራንስፖርት እንዲጓዙም ኢምባሲው አሳስቧል።
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 181ኛ ቀኑ ላይ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት ተሰደዋል።
Via አል ዐይን
#ስትሞት ማንም ሰው #እንዳይረሳህ ከፈለክ
ከሁሉም ሰው #ተበድረህ ሙት ።
ሮበርት ሙጋቤ
"የሠራዊቱን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ባልተረጋገጡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የማራገብ አሉታዊ ሙከራዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ እናሳስባለን" -የመከላከያ ሚኒስቴር
የሠራዊቱን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ባልተረጋገጡ፣ ባልተገቡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የመዘገብ ወይም የማራገብ አሉታዊ ሙከራዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ የመከላከያ ሚኒስቴር አሳሳበ።
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ የህዝቡ ድጋፍ እና ተሳትፎ ጠንካራ መሆን፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን በፅናት ያምናል ብሏል ነው ያለው፡፡
የመከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የሠራዊታችንን ወቅታዊ ሁኔታ፣ ባልተረጋገጡ፣ ባልተገቡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የመዘገብ ወይም የማራገብ አሉታዊ ሙከራዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ በጥብቅ ስለ ማሳሰብ የተሰጠ መግለጫ:-
የህዝባችን ድጋፍ እና ተሳትፎ ጠንካራ መሆን፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን በፅናት ያምናል፡፡
የህዝባችን ድጋፍ እና ተሳትፎ ጠንካራ መሆን፤ መከላከያ ሰራዊት የሀገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት ወሳኝ መሆኑን በፅናት ያምናል፡፡ በህዝባችን እና በሰራዊታችን የተገነባው መተማመንና መደጋገፍ በፅኑ መሰረት ላይ የቆመ በመሆኑ፣ ፈተናዎች በጋራ እያለፍን የሃገራችንን አንድነትና ሉዓላዊነት አስከብረን ቆይተናል፡፡ ወደፊትም ጠላቶቻችን የሚደግሱልንን ሴራ እና ወጥመድ አውቀን በማክሸፍ ለዕኩይ ዓላማቸው የማንበገር መሆናችንን በተግባር እያሳየን እንቀጥላለን፡፡ ይህ የጋራ ታሪካችንና ተስፋችን አይቀሬ ቢሆንም ለድላችን የምንከፍለው ዋጋ እንዲቀንስ ግን ጠንካራ ስራ ያስፈልገናል፡፡
ጠላቶቻችን ከሰሞኑ ግልፅ አደጋ ለመፍጠር አስበው በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ሰርጎ የገባው አልሸባብ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኃይሉ መደምሰሱ ይታወቃል፡፡ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍልም አሸባሪው የህወሃት ቡድን የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል፡፡ በተለይ የአሸባሪው ህወሓት አፈ ቀላጤዎች ሰሞነኛ ሰበካቸው የሰራዊታችን ስም ማጥፋት ስራዬ ብለው ተያይዘውተዋል፡፡ ተቀባይነት የሌላቸውን ሰበቦች በመደርደር መከላከያ ሰራዊታችንን በመወንጀል ዘመቻ መሰማራታቸው የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡
ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ጭምር እየለፈፉ ያሉት፤ "…የሰላም ድርድሩ ቴክኒካል ፈርሷል…፣ …መከላከያ ኃይሉን እያስጠጋ ነው…፣ …መከላከያ በከባድ መሳሪያ እየደበደበን ነው…፣ …ከላይ እስከታች የዕዝ ሰንሰለቱን ጠብቆ እየተፈፀመ ያለ ጥቃት ነው…" ወዘተ በማለት የቅድመ ግጭት ጩኸታቸውን በስሙልኝ ፕሮፖጋንዳቸው እያስተጋቡት ይገኛሉ፡፡
የሃገራችን ሚዲያዎች፣ የጠላትን ሴራ እና አጀንዳ በውል ተገንዝበው የሚሞግቱ የመኖራቸውን ያህል፣ አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ዘገባዎችና መረጃዎች ይህንኑ አፍራሽ ውንጀላ ባልተገባም መልኩ እየተቀባበሉት መሆኑን አስተውለናል፡፡
ያለበቂ መረጃ የጠላትን እንቅስቃሴ መዘገብ በራሱ የህዝባችንን የዕለት ከዕለት ኑሮ ያውካል። ጠላት በዚህ ገባ፣ በዚህ ወጣ ፤ የወገን ሠራዊት በዚህ ገባ፣ በዚህ ወጣ የሚለው ወሬ በፍፁም ዜና እና የዜና ትንታኔ ሊሆን አይችልም። ጦርነቱን እንዲዘግቡ ፍቃድ ከተሰጣቸው ውጭ በሀገር ህልውና ላይ የተቃጣን ጦርነት የሚያክል ነገር በማህበራዊ ሚዲያ ገቢ ማስገኛነት ተቆጥሮ ምንም የተረጋገጠ መረጃ ሳይኖር ወሬውን ማናፈስ የህዝባችንን መረጋጋት የሚነሳ ጉዳይ ነው ፤ የፀጥታ ሃይሎችን ተግባርንም ያውካል።
የሠራዊታችን ወቅታዊ ሁኔታ እና እንቅስቃሴ አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ ለህዝባችን ይፋ ስናደርግ እንደነበረው ወደፊትም በዚሁ አግባብ የሚከናወን ተግባር ሆኖ ሳለ፤ ሰራዊታችን ማንኛውንም ጥቃት ለመመከት በፅናትና በጥንቃቄ፤ ተዘጋጅቶ በተጠንቀቅ በቆመበት በአሁኑ ወቅት ጠላት ባሰናዳው ፕሮፖጋንዳ ወጥመድ የተጠለፉ አሉታዊ መረጃዎች በማስተጋባት እና በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች የሰራዊታችንን እንቅስቃሴ በማሰራጨት ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት እንዳሉም አይተናል፡፡ ይህ ድርጊት በሰራዊታችን የግዳጅ አፈፃፀም ላይ ምንም አወንታዊ ተፅኖ ሊኖረው አይችልም።
በመሆኑም ይህን አሉታዊ ተግባር በማወቅም ሆነ ባለማወቅም የተዛባ፣ ተገቢና የማይመለከታቸውን ዘገባ የሚዘግቡ የማህበራዊ ሚዲያ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
ይህንን ተግባር በግዴለሽነት ወይም በማንአለብኝነት የሚቀጥሉና የማይታረሙ ካሉ መከላከያ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ ከመሆኑም በላይ የሰራዊቱን ምስጢር በመንዛት፣ የጠላትን አጀንዳ በማራገብ የሃገር ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥሉትን እንደ አስፈላጊነቱ የወንጀል ክስ በመመስረት ተጠያቂ ለማድረግ እንደምንገደድ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
