uz
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Kanalga Telegram’da o‘tish

Addis abeba Ethiopia

Ko'proq ko'rsatish
5 204
Obunachilar
-11024 soatlar
-1 9137 kunlar
-2 77030 kunlar
Postlar arxiv
ግብፅ ግዙፍ የተባለ የወታደራዊ ትርዒት በዛሬው እለት እያሳየች ነዉ ግብፅ በዛሬዉ እለት ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ አል ሲሲ በተገኙበት ግዙፍ የጦር ትርዒት በማሳየት ላይ ትገኛለች። ፕሬዚዳንቱ ፤ የስል
+4
ግብፅ ግዙፍ የተባለ የወታደራዊ ትርዒት በዛሬው እለት እያሳየች ነዉ ግብፅ በዛሬዉ እለት ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ አል ሲሲ በተገኙበት ግዙፍ የጦር ትርዒት በማሳየት ላይ ትገኛለች። ፕሬዚዳንቱ ፤ የስልጣን ቅዠቶች በመረጃ ላይ ያልተመሰረቱ ውሳኔዎችን እንድትወስኑ ሊገፋፋችሁ አይገባም ሲሉም ለተቃዋሚዎቻቸዉ ጠንከር ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል። ከባድ መሳሪያዎችን በማሰለፍ በመከናወን ላይ ባለዉ የጦር ትርዒት ፤ ሜጀር ጀነራል ሸሪፍ አል አራኢሺ ሰራዊታቸዉ በተመደበበት ቦታ ሁሉ አገራቸውን ለመከላከል ሙሉ በሙሉ መዘጋጀቱን እና ከፍተኛውን የውጊያ ዝግጁነት ደረጃ ማሳካት መቻሉን መናገራቸውን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከዴይሊ ኒዉስ ኢጅብት ዘገባ ተመልክቷል። የጦር መኮንኑ ፤ማንም  ሰው የሀገራቸዉን ጥቅምና አቅም አደጋ ላይ መጣል እንደማይችል ገልፀው ፤ የግብፅ እጣ ፈንታ በሁከትና በችግር በተሞላ ክልል ውስጥ መኖር ነው ብለዋል። ሜጀር ጀነራሉ ባለፉት ጥቂት አመታት የግብፅ ጦርን በማደራጀት ፣ በማሰልጠን እና በማስታጠቅ ረገድ የነበረውን የጥራት ለውጥ ጥንካሬ እና ቅልጥፍናን ያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል ብሏል ዘገባዉ። የግብፅ ወታደራዊ ትርዒት አላማዉ በዘገባዉ ላይ ባይጠቀስም አንድም ለሀገር ዉስጥ ተቃዋሚዎች መልዕክት ለማስተላለፍ ሌላም ከእስራኤል ጋር ሊከሰትት ለሚችል ጦርነት ያላትን ዝግጁነት ለማሳየት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ረቡዕ ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም "ውትድርና ህይወቴ ነው " ኢትዮጵያዊያን በሀገራችው ሰማይ ስር የመጣን ጠላት በማሽመድመድ ካስመዘገቡት ደማቅ ታሪክ ፊት ለፊት ትልቁን ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ ናቸው፡፡  ለሀገራቸው በዋሉት ውለታ ከሚተረክላቸው ቀዳሚ ባለ ታሪኮች ቀድመው ይጠቀሳሉ፡፡ ሙሉ ህይወታቸውን ለሀገራቸው የሰጡ ናቸው፡፡ ጀግና ተዋጊ፣ የበቁ የጦር መሪ፣ የተሳካላቸው የጦር አዛዥ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በበርካታ የጦር ሜዳ ውጊያዎች ተሳትፈው የሀገርን ሉዓላዊነት፣ የህዝብን ነፃነት ያስከበረ ደማቅ ድል አስመዝግበዋል፡፡ ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም ፡፡  ጄኔራል መኮንኑ በ1934 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም እዚያው እምድብር ከተማ ተምረው በ1948 ዓመተ ምህረትም አጠናቀዋል፡፡ ከ1949-1952 ዓ.ም ድረስ አምቦ የእርሻ ልማት ትምህርት ቤት ተምረዋል፡፡ በመቀጠልም የምርጥ መኮንኖች ማፍሪያ በነበረው በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ሀረር) የጦር አካዳሚ  በመግባት ለ3 ዓመታት ያህል የወታደራዊ ሳይንስና የአካዳሚ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ ጥቅምት 4 ቀን 1956 ዓ.ም ከሀረር የጦር አካዳሚ ከተመረቁ በኋላ የአየር ወለድ ስልጠናም ለ6 ወራት ያህል ወስደው በምስራቅ ዕዝ 3ኛ ክፍለ ጦር 25ኛ ሻለቃ ልዩ ስሙ ኦጋንዳን /ደጋሃብር/ በተባለ ቦታ ላይ በመቶ አዛዥነት ተመድበው ሰርተዋል፡፡ ከ6 ወራት የኦጋደን ደጋሀቡር ቆይታ በኋላ ደሬድዋ ላይ ለ2 ዓመታት ያህልም የስፔሻል ፎርስ አሰልጣኝ በመሆን ሰርተዋል፡፡ በ1960 ዓ.ም የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ የትምህርትና  ስልጠና ሃላፊ ሆነውም አገልግለዋል፡፡ በ1967 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ መደረጉን ተከትሎ ገነት ጦር ትምህርት ቤት በእግረኛ አስተማሪነት ተመድበው ሰርተዋል፡፡ በመቀጠልም የኢትጽያን አየር ወለድ ሀይል በሻምበል አዛዥነት መምራት ችለዋል፡፡ በወቅቱ የክበር ዘበኛ ክፍለ ጦርና የ3 ብርጌድ አካል የነበረች የ15ኛ ሻለቃ የጦር ከፍል የሳህላ አወራጃ የናቅፋ ከተማን ፀጥታ እስከበረችና ከጠላት ጋር እየተፋለመች ነበር፡፡ ነገሮች እየተካረሩ ሲሄዱም ሻለቃዋን የሚያጠናክር ኃይል መላክ እንዳለበት በመንግስት ታምኖ አየር ወለድም በፓራሹት ወርዶ ድጋፍ እንዲያደርግ ተወሰነ፡፡ በወቅቱ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማርያም የአየር ወለድ አዛዥ ነበሩ፡፡ የአየር ወለድ አባላቱም አምነውበት ሀለፊነቱን ተቀበልው ከመንደፍራ ወደ አስመራ ከዚያም ወደ ናቅፋ የግዳጅ ቀጠና በረራ አደረጉ፡፡ በቦታው እንደደረሱም የተቀናጀ ስኬታማ ውጊያ አድርገው የሻለቃዋን ማሽግ ተረክበው ለ6 ወራት ያህልም በምግብ፣ በመጠጥ፣ በልብስ፣ በጥይት በህክምና እጥረት መፈተናችውን ያስታውሳሉ፡፡ በመጨረሻም ከነበረው መንግስት ከአቅሜ በላይ ስለሆነ ራስህ ወስን የሚል ትዕዛዝ ደረሳቸው፡፡ ይህ ሲባልም ለጠላት እጅ መስጠት፣ ራስን ማጥፋት ወይም ሰብሮ መውጣት ከሚሉ 3 ነገሮች አንዱን መምረጥ ግድ ይላል፡፡    ጀግና ታሪክ ይሰራል እንጂ ታሪክ አያበላሽም፡፡ ስለጉዳዩ ውይይት ካደረጉ በኋላም የእጅ በእጅ የጨበጣ ውጊያን ምርጫቸው አድርገው ጠላትን ደምስሰው መውጣታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ከ3ቀናት የ60 ኪሎ ሜትር ጉዞ በኋላ ከወገን ጦር ጋር ሲገናኙም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ለፈፀሙት ጀብዱ ማበረታቻ ይሆን ዘንድም ሻለቃ ማዕረግ በለበሱ ከጥቂት ወራት በኋላ የሌተናል ኮሎኔል የማዕረግ ዕድገት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ሀዋሳ ላይ ተቋቁሞ የነበረውን የፓራ ኮማንዶ ብርጌድ አደራጅተው አሰልጥነዋል፡፡ በወቅቱ የብረጌድ አንድቀ ክፍል በነበረው ጦርነት ክፍላቸውን ይዘው የተሠጣቸውን ግዳጅ በብቃት ተወጥተዋል፡፡ በ1970 ዓ.ም  ከምስራቁ የሀገራችን ክፍል ወደ ሰሜን በመመለስ የግብረ ሃይል አዛዥ በመሆን ሰርተዋል፡፡  በኤርትራ ምድር ጥይት በጮኸበት ቦታ ሁሉ ያልተሳተፉበት ውጊያ የለም፡፡ ለዚህም መስከረም 3 ቀን 1972 ዓ.ም ወደር የሌለው የኢትዮጽያ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜድይ ተሸላሚ ለመሆን በቅተዋል፡፡ ዘንድሮ በሀገራችን 116ኛው የሠራዊት ቀን ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ይከበራል፡፡ የሠራዊት ቀን ማክበር ደግሞ ለሀገር ብለው ለተሰውም ሆነ በህይወት ላሉት እውቅና መስጠት ነው፡፡ ሀገራችንም በዚሁ አግባብ ማክበሯ ተገቢ ነው፡፡ ለሀገር መከላከያ ሠራዊታችን አሁንም ቅርበት አላቸው፡፡ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ሁኔታ በሰራዊቱ ላይ የደረሰው ጉዳት ጉዳታቸው ሆኖ አሟቸዋል፡፡ በጋሸና በአፋርና በጣርማ በር ግንባሮች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ አበረታተዋል፡፡ የውትድርና ህይወት በጣም ከባድ ህይወት ነው፡፡ የህይወት መስዋዕትነትን ይጠይቃል፡፡ ሰው ሆኖ የማይሞት የለም፡፡ መለየት ያለበት የት ሆነህ መሞትን ትመርጣለህ የሚለው ነው፡፡ በውትድርና ህይወት ውስጥ መሞት ታሪክ ነው፡፡ እንደመኖር ይቆጠራል፡፡ ለሀገርና ለህዝብ ደግሞ ህይወትን መስጠት መታደል ነው፡፡ ህይወትህን ከፍለህ ህይወት ትሰጥበታለህ፡፡ የሀገር ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፣ ህዝቦች ከቦታ ቦታ በነፃነት ተንቀሳቅሰው መኖር እንዲችሉ ወታደሩ ድንበር ላይ ይቆማል፡፡ ወታደር በወታደራዊ ንድፈ ሀሳብ አእምሮው የጎለበተ መሆን አለበት፡፡ ከብረት የጠነከረ የአካል ብቃትና ስነ-ስረዓት ሊኖረው ይገባል፡፡ ለችግሮች እጂ የሚሰጥ ሳይሆን ችግርን የሚረታ መሆን አለበት፡፡ የዘመናዊነት መነሻው ስህተትን አውቆ ለማስተካከል ጥረት ማድረግ ስለሆነ አሁን እየተወሰደ ያለው ሠራዊቱን የማዘመን ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡ ጠንካራ ሠራዊት ለመፍጠር ስልጠና ወሳኝ ነው፡፡ በማሰልጠኛዎች ላይ ሊሰራ ይገባል፡፡ የሠራዊት ፈጣሪ ሞተሮች አሰልጣኞች ናቸው፡፡ አሰልጣኞችም መስለው ሳይሆን ሆነው ቆመው ሳይሆን ሰርተው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ያኔ ሰራዊታችን ብቃትና ድስፕሊንን ከህዝባዊነት ጋር አጣምሮ ይዟል፡፡ የተሻለና ዘመናዊም ይሆናል፡፡ ስለሆነም ለእናት ሀገሩና ለአለም ሰላም ከፍተኛ ዋጋ እከፈለ ነው፡፡ ሀገራችን በሰላም ማስከበር ግዳጅ በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ዝናና ክብር አላት፡፡ ሰራዊቱም ከፍተኛ ፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሚናዎችን መጫዎት ችሏል፡፡ የጀኔራል መኮንኑ ድንቅ የህይወት ተሞክሮም አሁን ላለው የሰራዊት አመራርና አባላት የሞራል ስንቅ ነውና በዚሁ ልክ ለሀገራችን ልንሰራ ይገባናል፡፡ " በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ማክሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም 116ኛውን የሠራዊት ቀን አስመልክቶ በበጎ ስራቸው ከሰራዊቱ ጎን ለተሠለፉ የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም ተካሂዷል። የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ዛሬ የመከላከያ ሰራዊት የክብር አባልነትን ሽልማት ያገኛችሁ ግለሠቦች ተቋሙ ሳያውቃችሁ በርቱ ጠንክሩ ሳይላችሁ ከሰራዊቱ ጎን በመቆማችሁ እና የሠራዊቱን መልካም ስነ ምግባርና ዝና ከጠላት መንጋጋ ፈልቅቃችሁ ስላወጣችሁ የተበረከተላችሁ ሽልማት ነው ብለዋል። ተሸላሚ በጎ ሰዎች ያለባቸውን ጫና ሁሉ በመቋቋም ከብሔርና ከወገንተኝነት በፀዳ መልኩ ሰራዊቱን እና ሀገርን በሙያቸው ከመጥፎ ድርጊት እየተከላከሉ የመጡ በመሆናቸው ክብር ይገባቸዋል ሲሉም አክለዋል። በቀጣይም ለሀገር እና ለሠራዊታችን ክብር በሙያቸው ያገለገሉትን እውቅና እየሠጠን እንቀጥላለን ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀገርን እና ሰራዊቱን ለማፍረስ ተልዕኮ ይዞ የሚንቀሳቀስ ሀይልን ደግሞ ከኢትዮጵያ በላይ ማንም የለምና ልንታገላቸው ይገባል ብለዋል። የመከላከያ ሰራዊት የክብር አባልነት ሽልማት ከተሰጣቸው ውስጥ ናትናኤል መኮንን፣ ሲሳይ አጌና፣ አርአያ ተስፋ ማርያም፣ ስዩም ተሾመ፣  ቴዎድሮስ አለማየሁ እና ሰለሞን ኃይለ እየሱስ እንዲሁም ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች፣ መምህራን እና ጋዜጠኞች ይገኙበታል። አስተያየታቸውን የሰጡ የዕለቱ ተሸላሚዎች ሽልማቱ ከፍተኛ ደስታን የፈጠረላቸው መሆኑን በመግለፅ በቀጣይም እየሞተ ለሚያኖረን ሰራዊት የሚመጥነው ባይሆንም በሙያችን ከዚህ በፊት እንደምናደርገው የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል። " በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ማክሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም የሁለቱ ሀገራት ኢታማዦር ሹሞች ከኢትዮጵያ አየር ሃይል ጋር በጋራ የመሥራት ፍላጎት ኦንዳላቸው ገለፁ። በ116ኛው የሰራዊት ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ከውጭ ሀገር ከመጡት እንግዶች መካከል የደቡብ አፍሪካ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም  ጄኔራል ሮዲዛኒን ማፕዋኒያንና የታንዛኒያ ሪፓብሊክ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ጃኮብ ጆን ማኩኑዳ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ጉብኝት አድርገዋል። ለኢታማዦር ሹሞች የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አቀባበል አድርገውላቸዋል ። በዕለቱም የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ተቋማዊ ሪፎርም በማድረግ አለም ከደረሰበት የአቭዬሽን ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ መምጣቱን እና በዚህም ተጨባጭ ድሎች መመዝገባቸውን ገልፀውላቸዋል። አየር ሃይል አሁን ላይ ከራሱም አልፎ ለአከባቢው ብሎም ለቀጠናው ጭምር እየሰራ መሆኑን የገለፁት  አዛዡ በቀጣይነት ከመላው አፍሪካዊያን ወንድሞቹ ጋር በአቭዬሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ የልምድና እውቀት ሽግግር  ለማድረግ እንዲሁም በሁሉም መስክ ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል። የደቡብ አፍሪካ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሮዱዝኒ ማፕዋኒያን በአፍሪካ የአቭዬሽ እንዱስትሪ ደማቅ ታሪክ ባለው የአትዮጵያ አየር ኃይል ጉብኝት በማድረጋቸው ትልቅ ኩራት እንደተሠማቸው ገልፀው ወደፊት በጋራ ጉዳዮች ከተቋሙ ጋር ለመስራት ጉብኝቱ ትልቅ አጋጣሚ የፈጠረላቸው መሆኑንም ተናግረዋል። የታኒዛኒያ ሪፐብሊክ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ እታማዦር ሹም ጃኮብ ጆን ማኩንዳ በአፍሪካ የአቭዬሽን እንዱስትሪ ዘርፍ  ታላቅ ስምና ዝና ያለው የኢትዮጽያ አየር ኃይል አሁን ይበልጥ እየዘመነ መምጣቱን መታዘባቸውን እና ይህም ለሌሎች አፍሪካዊያን እንደመልካም ምሳሌ የሚጠቀስ ተግባር ነው ብለዋል። አያይዘውም የታኒዛኒያ አየር ኃይል ከኢትዮጵያ አየር ኃይል የእውቀት ሽግግር ዙሪያ ከሀገራቸው ሰልጣኞችን በመላክ የጋራ ትብብሩን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልፀዋል።  በዕለቱ በሁለቱ ሀገራት ተወካዮች አማካኝነት ለኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዡ ስጦታ ተበርክቷል። " በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ማክሰኞ ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ 116ኛ የሠራዊት ቀን አከባበርን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። ከዚህ ቀደም በነበረው ስርዓት ሠራዊት እንደ አዲስ የተደራጀበት በሚል ምክንያት የሠራዊት ቀን ይከበር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በተደረገው ሪፎርም መሠረት ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጦር ሚኒስትር  በሠየመችበት ቀን ላይ ቀኑን ለማክበር መቻሉን በመግለጫቸው አስረድተዋል። በዚህ መሠረትም ሰራዊታችን  ከዛ ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ በተፈተነችበት ሁኔታ ሁሉ በፈተና እየተሻገረ የመጣ ሀይል ስለሆነ የሠራዊቱ ቀን በዛ ቀን ሊከበር እንደቻለ በመግለጫቸው አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ ትልቅ ሰራዊት የነበራት ጠላቶቿ በተነሱባት ጊዜ ሁሉ ከህዝቡ ጋር በመሆን ተልዕኮውን፣ ሀገሩን እና ህዝቡን እየጠበቀ የመጣና ረጅም እድሜ ያስቆጠረ ሰራዊት ያላት ሀገር መሆኗን ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ ገልፀዋል። ጄኔራል አበባው የበዓሉ ዋና አላማ ለዘመናት ሀገራቸውን ከጠላት ለመፋለም መስዋዕት የሆኑ ጀግኖችን የምናከብርበትና ቃላቸውን በመጠበቅና ለቀጣዩ ትውልድ ለማሻገር ቃለ መሀላ የምንፈፅምበት፣ ባሳለፍነው አመት የነበሩ ጥንካሬዎችን እና ድክመቶችን በማየት ለቀጣይ ግዳጆቻችን ዝግጁ የምንሆንበት፣እንደ ተቋም የተሠጠንን ሀገርን እና ህዝብ የመጠበቅ ሀላፊነት አጠናክረን የምንቀጥልበት እንዲሁም በሀገራችን በምንም አይነት መልኩ ትንኮሳ ሊቃጡ የሚችሉ ሀይሎች ካሉ አይቻልም የምንልበት  በዓል ነውም ብለዋል። ኢትዮጵያ ጦር የምታዘጋጀው በዋናነት ህዝቦቿን ለመጠበቅ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ በዓሉ ህዝባችን ሀገራችንን በመጠበቁ በኩል ከጎናችን በመሆን ሚናውን እንዲጫወት መልዕክት የምናስተላልፍበት ዕለትም ነው ሲሉ አክለዋል። በዓሉ በተለያዩ ዝግጅቶች በተቋም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል ያሉት ጄኔራል አበባው የፊታችን ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከህዝቡ ጋር በጋራ በማክበር የበዓሉ ፍፃሜ እንደሚሆን አስታውቀዋል። "በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት"