የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Kanalga Telegram’da o‘tish
4 648
Obunachilar
-23224 soatlar
-1 7917 kunlar
-3 26430 kunlar
Postlar arxiv
አሜሪካዊቷ ዲፕሎማት፤ የአፍሪካ ሃገራት ከስንዴ እና ማዳበሪያ ውጭ ከሩሲያ ምንም ነገር እንዳይገዙ አስጠንቅቀዋል
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ “የአፍሪካ ሃገራት እህልን ጨምሮ የሩሲያን የግብርና ምርቶች እና የአፈር ማዳበሪያን ሊገዙ ይችላሉ” ያሉ ሲሆን፤ ነገር ግን ነዳጅንና የነዳጅ ምርቶችን ሊገበያዩ እንደማይችሉ ገልጸዋል።
የሚገበያዩ ከሆነ በሩሲያ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን መጣስ እንደሚሆን ነው አምባሳደሯ የተናገሩት። በመሆኑም “ማዕቀቡን እንዳይጥሱ እናሳስባለን” ብለዋል ይህ ካልሆነ ተመሳሳይ እጣ ፋንታ ሊጠብቃቸው እንደሚችል በማስጠንቀቅ።
ss
የባህር ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪው አዲሱ የቻይና ድሮን
ድሮኑ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘር ይችላል
ቻይና በአይነቱ ለየት ያለ ባህር ስር እንደ ሰርጓጀ አየር ላይ ደግሞ ድሮን የሚሆን መሳሪያ እየሰራች መሆኑ ተሰምቷል።
የቻይና ተመራማሪዎች እየሰሩት ነው የተባለው አዲሱ ስተሊዝ ድሮን ታጣፊ ክንፍ የተገጠመለት ሲሆን፤ ከባህር ስር ወጥቶ ሲበር ክንፎቹ የሚዘረጉ ይሆናል።
የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አሁን ላይ ለናሙና የሚሆን አዲሱን ሰርጓጅ እና አየር ላይ በራሪ ድሮን በመስራት ሙከራ እያደረጉበት መሆኑም ታውቋል።
ሳውዝ ቻይና ሞኒተሪንግ ፖስት ጋዜጣ ባወጣው መረጃ፤ ድሮኑ አራት ተሸከርካሪ ሞተሮች የተገጠሙለት ሲሆን፤ ሁለቱ ከፊት ሁለቱ ደግሞ ከኋላ የተገጠሙ ናቸው።
ደሮኑ በባህር ስር በሚሆንበት ጊዜ ሁለቱ ክንፎቹን በማጠፍ የሚቀዝፍ ሲሆን፤ ይህም በጣም ዘመናዊ የሆነ የሰርጓጅ መርከብ ቅርጽ እንዲላበስ የሚያደርገው ነው።
ከባህር በመውጣት አየር ላይ በሚንሳፈፍበት ወቅት ደግሞ ክንፎቹን የሚዘረጋ ሲሆን፤ በሰዓት እስከ 120 ኪሎ ሜትር ድረስ መብረር የሚችል መሆኑንም የኒንጃንግ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታውቀዋል።
ድሮኑ በባህር ስር እንዲሁም በአየር ላይ ፈጣን እና የረጅም ርቀት ተልእኮዎችን በቀላሉ መከወን የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር አንግ ሂሶንግ ገልፀዋል።
አዲሱ ድሮን ከራዳር እይታ ውጪ እንዲሆን ታስቦ መሰራቱን የሚያነሱት የዘርፉ ባለሙያዎች፤ ትክክለኛ ጥቅሙ የአየር እና የባህር መከላከያዎችን በማምለጥ ድንገተኛ ጥቃት ለመሰንዘር መቻሉ እንደሆነም ተናግረዋል።
ድሮኑ መቼ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የቻይና ጦር ይታጠቀዋል በሚል ላይ እንዲሁም ድሮኑ ምን አይነት መሳሪያዎችን መታጠቅ ይችላል በሚለው ላይ የወጣ መረጃ የለም።
ቻይና በአንድ ቀን 16 አዳዲስ ሳተላይቶችን ወደ ጠፈር አመጠቀች
ቻይና በአንድ ቀን 16 ሳታላይቶን ወደ ጠፈር ማምጠቋን እና ሁሉም ሳተላይቶች ቦታቸውን መያዛቸውን አስታውቃለች።
ቻይና ዛሬ ማለዳ ላይ ካመጠቀቻቸው ሳተላይቶች መካከል ጂሊን 1 ጋዎፈን 03D09 እና ዩንያኦ 1 04-08 የተባሉ ሳተላይቶች እንደሚገኙበት የቻይና መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሳተላይቶቹ ለቅኝት አገልግሎት እና የአየር ንብረት ሁኔታ ምስልን ለማሰንሳት የሚያስችሉ መሆናቸውም ታውቋል።
የአል ዐይን ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም፡ https://t.me/alainamharic
ዩቲዩብ: https://bit.ly/AlAinAmharic
ድረገፅ: https://am.al-ain.com
ትዊተር: https://twitter.com/AlAinAmharic
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/AlAinAmharic
ኢንስታግራም: https://www.instagram.com/alainnewsamharic
#Breaking_News
ሰሜን-ኮሪያ ከሩሲያ ጎን የሚዋጉ 100,000 በጎ ፈቃደኞችን ማዘጋጀቷ ተነገረ
ሩሲያ በዩክሬን ለጀመረችው ዘመቻ ሰሜን ኮሪያ 100,000 በጎ ፍቃደኞችን ለማቅረብ ዝግጁ ማድረጓን ዘ ኒዮርክ ፖስት ዘግቧል።
"100,000 የሰሜን ኮሪያ በጎ ፈቃደኞች በግጭቱ ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የሚገልጹ ሪፖርቶች አሉ" ሲል የሩሲያ ወታደራዊ ተመራማሪ ኢጎር ኮሮቼንኮ በቻናል 1 ሩሲያ ላይ ተናግሯል ሲል ነው ኒውዮርክ ፖስት የዘገበው።
ኮሮቼንኮ የሰሜን ኮሪያን ወታደራዊ ኃይል "በፀረ-ባትሪ ጦርነት ያለውን የካበተ ልምድ" አወድሷል ሲል ጋዜጣው አስነብቧል።
አሜሪካ በርካታ ከፍተኛ ተንቀሳቃሽ የሮኬት ሲስተሞች (HIMARS) ለዩክሬይን መስጠቷን ተከትሎ የረዥም ርቀት እና ከፍተኛ ትክክለኛነት ያላቸው ሮኬቶች ለዩክሬን ትልቅ ለውጥ አምጥተዋል ያሉ ሲሆን አሁን ላይ የፀረ-ባትሪ ጦርነት ለሩሲያ ጦር የበለጠ ጠቀሜታ አለውም ተብሏል።
የጸረ-ባትሪ የጦርነት ስልት በራዳር ወይም COBRA በሚባለው መሣሪያ በመጠቀም ከ Howitzer, Mortar እና ሮኬት ማስወንጨፊያዎች የሚተኮሱትን መድፎች ትራጄክተሪ በማስላት በትክክል ከየቱጋ እየተተኮሱ እንዳሉ የሚሳይ ሲስተም ነው። የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በዚህ የጦርነት አይነት የተካኑ መሆናቸው ተገልጿል።
#ሠበር_ዜና_ኪም_ጆንግ_ዑን💪💪💪🎤
ሩሲያን አትንኩ ብሏል በቁጭት።
እኔ ፑቲን አይደለሁም አሜሪካ በሩሲያ ጦርነት ወይም በአለም ላይ እያደረሰች ያለውን ጣልቃገብነት ካለቆመች #እተኩሰዋለሁ💪💪💪💪🎤👉 ብለዋል አሜሪከን ወደአመድነት የሚቀይር ሀይፕርሶኒክ ሚሳዔሌን #እተኩሰዋለሁ😩 ብለዋል። ወየወልሽ አሜሪካ?
በተጨማሪም👇
#ሰሜን_ኮሪያ_ከሩሲያ ጎን የሚዋጉ 100,000 በጎ ፈቃደኞችን ማዘጋጀቷ ተዘገበ
ሩሲያ በዩክሬን ላይ የጀመረችውን ጦርነት እንድታሸንፍ ሰሜን ኮሪያ 100,000 "በጎ ፍቃደኛ" ወታደሮችን ለማቅረብ ዝግጁ ማድረጓን ዘ ኒዮርክ ፖስት ዘግቧል።
"100,000 የሰሜን ኮሪያ በጎ ፈቃደኞች በግጭቱ ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የሚገልጹ ሪፖርቶች አሉ" ሲል የሩሲያ ወታደራዊ ተመራማሪ ኢጎር ኮሮቼንኮ በቻናል 1 ሩሲያ ላይ ተናግሯል ሲል ነው ኒውዮርክ ፖስት የዘገበው።
ኮሮቼንኮ የሰሜን ኮሪያን ወታደራዊ ኃይል "በፀረ-ባትሪ ጦርነት ያለውን የካበተ ልምድ" አወድሷል ሲል ጋዜጣው አስነብቧል።
አሜሪካ በርካታ ከፍተኛ ተንቀሳቃሽ የሮኬት ሲስተሞች (HIMARS) ለዩክሬይን መስጠቷን ተከትሎ የረዥም ርቀት እና ከፍተኛ ትክክለኛነት ያላቸው ሮኬቶች ለዩክሬን ትልቅ ለውጥ አምጥተዋል ያሉ ሲሆን አሁን ላይ የፀረ-ባትሪ ጦርነት ለሩሲያ ጦር የበለጠ ጠቀሜታ አለውም ተብሏል።
የጸረ-ባትሪ የጦርነት ስልት በራዳር ወይም COBRA በሚባለው መሣሪያ በመጠቀም ከ Howitzer, Mortar እና ሮኬት ማስወንጨፊያዎች የሚተኮሱትን መድፎች ትራጄክተሪ በማስላት በትክክል ከየቱጋ እየተተኮሱ እንዳሉ የሚሳይ ሲስተም ነው። የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በዚህ የጦርነት አይነት የተካኑ መሆናቸው ተገልጿል።
በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በአሸባሪው ሸኔ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ባለቀይ ቦኔቶቹ ኮማንዶዎቻችን የአሸባሪውን አከርካሪ እያሽመደመዱ ይገኛሉ።
ክብርና ሞጎስ ለጀግኖቹ ባለቀይ ቦኔቶች🙏❤❤🇪🇹🇪🇹✅
በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ
በምስራቅ ወለጋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉን በቀጣናው የሚገኘው የክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ገለፁ።
በምስራቅ ወለጋ ዞን በጊዳ አያና፣ ኪረሙ፣ በኢበንቱ፣ በሀሮሊው እና በሊሙ ወረዳዎች ዙሪያና አካባቢው በአሸባሪው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ የተጠናከረ ወታደራዊ ዘመቻ እየተወሰደበት እንዳለ ተገልጿል።
በግዳጅ ቀጣና የሚገኘው የክፍለ ጦር ዋና አዛዥ እንዳሉት በአሸባሪው የሕወሓት ሳንባ በሚተነፍሰው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ላይ በተወሰደው የተጠናከረ ወታደራዊ ዘመቻ 49 የሸኔ ታጣቂ ቡድን አባላት ሲማረኩ፣ አምስቱ እርምጃ ተውስዶባቸዋል፤ 50 የሚሆኑት ጀሌዎች ደግሞ ለሽብር ቡድኑ መረጃ ሲያቀብሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በዚህ የተጠናከረ ወታደራዊ ዘመቻ አሸባሪው ሸኔ ከሕዝብና ከመንግሥት ተቋማት ዘርፎ ሲጠቀምባቸው የነበሩ 18 ሞተር ሳይክሎች፣ 44 ተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ 26 ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣ 25 በርሜል ነዳጅን ጨምሮ 74 ሺሕ 795 ብር መያዙን ተናግረዋል።
ዋና አዛዡ አክለውም ክፍለ ጦሩ በስፍራው ከመድረሱ በፊት የአሸባሪው ሸኔ ቡድን በአካባቢው ማኅበረሠብ ላይ ከፍተኛ የሆነ ስቃይና እንግልት ያደርስ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ግዙፉ የሩሲያ Tu-160 የጦር አውሮፕላን
እስከ 16 ሺህ ኪ.ግ ቦምቦችንና ክሩዝ ሚሳዔሎችን ታጥቆ ያለምንም ችግር መብረር ይችላል
ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በገጠመችው ጦርነት ከተጠቀመችባቸው የጦር አውሮፕላኖች ውስጥ “Tu-160” አንዱ እንደሆነ ይነገራል።
በጣም ግዙፍ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጦር አውሮፕላን በሶቪየት ህብረት ወቅት ማለትም በፈረንጆቹ 1981 ወደ አገልግሎት የገባ ሲሆን፤ በየጊዜው ማሻሻያ እየተደረገበት እስካሁን እያገለገል ይገኛል።
ሩሲያ አውሮፕላኑ ላይ በፈረንጆቹ 2008 አዳዲስ ማሻሻዎንብመ በማድረግ ይፋ ያደረገች ሲሆን፤ Tu-160R በሚል ስያሜ የአየር ኃይሏን ዳግም አስታጥቃለች።
ለመሆኑ ግዙፉ Tu-160 የጦር አውሮፕላንን ምን የተለየ ያደርገዋል?
የአወሮፕላ ቁመት 54.1 ሜትር ሲሆን፤ ክንፉ ርዝማኔም 35.6 ሜትር ይረዝማል፤ ክንፎቹ ላይ አራት ኩዜንትዞቭ NK-321 ቱርቦፋን ሞተሮች ተገጥመውለታል።
ክሩዝ ሚሳኤሎችን መታጠቅ የሚችል እና ኢላማውን በአግባ የሚመታ መሆኑም ተነግሯል።
ነሐሴ 3 ቀን 2014 ዓ.ም
የሆሩ ጉድሩ ዞን አስተዳደር በግዳጅ ቀጠናው ለሚገኙ የሠራዊት አባላት የእርድ በሬ ስጦታ አበረከተ።
ስጦታውን ያስረከቡት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ምሬሳ ፊጤ እንደገለፁት የሠራዊት አባላቱ ሰላም በማናጋት ዝርፊያና ግድያን በመፈጸም የአከባቢውን ህዝብ ሲያሰቃይ የነበረውን የአሸባሪው ሸኔን በማጥፋት ላደረጉት አስተዋፅኦ የተደረገ ትንሹ ስጦታ ነው።
ግዳጅ እየፈፀመ ያለው የክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ በበኩላቸው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው በዞኑ እና በአጎራባች ዞኖች ውስጥ በሚንቀሳቀሰው የአሻባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ሪፖርተር ታሪኩ ሻሜቦ
ፎቶግራፍ ሙልጌታ በቀለ
የሸኔው ም/አዛዥ ሙሃመድ አሜ በቁጥጥር ስር ውሏል
በቦረና ሞያሌ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ መሃመድ አሜ የተባለው የሸኔው ሁለተኛ ሰው ተይዟል‼️
የተያዘውም አብዱ ኡመር ሁሴን የሚል የሽፋን መታወቂያ ይዞ ወደ መሃል ሀገር ሊያቀና ሲል የታርጋ ቁጥሩ AA B37253 በሆነ መኪና ነበር።
ክትትሉ ፍተሻው ለዘላቂ ሰላማችን ሲባል ተጠናክሮ ይቀጥል‼️
አሜሪካ ለዩክሬን አንድ ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው አዲስ የጦር መሳሪያ ልታስጣጥቅ እንደሆነ ተገለጸ
አሜሪካ ለዩክሬን አንድ ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው አዲስ የጦር መሳሪያ ልታስጣጥቅ እንደሆነ ተገለጸ።
ከተጀመረ 165 ቀኑ ላይ የሚገኘው የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት እስካሁን መቋጫ አላገኘም።
ጦርነቱን በአሜሪካ አስተባባሪነት ምዕራባዊያን እና ሌሎች ሀገራት በተለያየ መንገድ በመሳተፍ ላይ ናቸው።
አሜሪካ በሩሲያ ላይ በተናጥል እና በቡድን በሺዎች የሚቆጠሩ ማዕቀቦችን ከመጣል ጀምሮ ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ድጋፍ በማድረግ ላይ ትገኛለች።
አሁን ደግሞ አንድ ቢሊዮን ዶናር ዋጋ ያላቸው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ለዩክሬን ልታስታጥቅ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።
የአሁኑ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ከዚህ በፊት ከተደረጉት ሁሉ ከፍተኛው ነው ተብሏል።
በአጠቃላይ ሩሲያ እና ዩክሬን ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ አሜሪካ ለዩክሬን የለገሰቻቸው የጦር መሳሪያ 8 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ እንዳላቸው ተገልጿል።
ይህ አዲሱ የጦር መሳሪያ ድጋፍ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ነገ እንደሚፈረም የሚጠበቅ ሲሆን፤ በጥንቃቄ ወደ ዩክሬን ይጓጓዛል ተብሏል።
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ በየዕለቱ እስከ 200 ወታደሮች በሩሲያ ጥቃት እየተገደሉባቸው እንደሆነ ገልጸው ምዕራባውያን የጦር መሳሪያ እንዲለግሱም ጥሪ አስተላልፈው ነበር።
የአሸባሪው ሸኔ የደቡብ ዞን ምክትል ሀላፊ በቁጥጥር ስር ዋለ
በአሸባሪው ሸኔ የደቡብ ዞን ምክትል ሀላፊ የሚል ሀላፊነት የተሰጠው ተጠርጣሪ በቤት መኪና ወደ መሀል ሀገር ሲጓዝ በቦረና ዞን ሞያሌ ወረዳ በቁጥጥር ስር መዋሉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ፡፡
ሩሲያ ቱርክ በሩብል ለመገበያየት ተስማሙ
ስብሰባው ፍሬያማ እንደነበር ፕሬዝደንት ኤርዶጋን ተናግረዋል የሩሲያ እና የቱርክ ፕሬዝደንቶች በትናንትናው እለት በሩሲያ ሶቺ ከተማ ተገናኝተው መክረዋል
ሩሲያ እና ቱርክ፤ በሩሲያው ገንዘብ ሩብልስ ለመገበያየት ተስማምተዋል፡፡
የሩሲያ እና ቱርክ መሪዎች በትናንትናው እለት በሩሲያዋ ሶቺ ከተማ ባደረጉት ውይይት የኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት መፈረማቸውን የሩሲያ አርቲ ሚዲያ ዘግቧል፡፡ ስምምነቱ መፈረሙን የገለጹት የቱርኩ ፕሬዝደንት ረሲፕ ተይፕ ኤርዶጋን ናቸው፡፡
ሩሲያ እና ዩክሬንን የማደራደር ሚያ ያላት ቱርክ ከሩሲያ ጋር በሩብልስ ለመገበያየት መስማማቷን ፕሬዘደንት ኤርዶጋን ተናግረዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አርብ ዕለት በቱርክ እና በሩሲያ ልዑካን መካከል የተካሄዱት ስብሰባዎች ፍሬያማ እንደነበሩ እና በሩሲያ በሚያደርጉት ጉብኝት በሶሪያ ስላለው ሁኔታ ከሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር እንደሚመክሩ ተናግረዋል።
ሩሲያ በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከጀመረች በኋላ ሩሲያ አሜሪካን ጨምሮ ከምእራባውያን ጋር ሁሉን አቀፍ ፍጥጫ ውስጥ ገብታለች፡፡
አሜሪካን ጨምሮ ምእራበውያን ሀገራት ሩሲያን ያዳክማል ያሉትን ማእቀብ ሁሉ በሩሲያ ላይ አዝንበዋል፤ ሩሲያ ማእቀቡን ለመመከት ምእራባውያን ሀገራት ጋዝ በሩብል እንዲገዙ አስገድዳለች፡፡
#ዝርዝር_ማብራሪያ
ኢትዮ ቴሌኮም ፦
• ቴሌብር መላ ፤
• ቴሌብር እንደኪሴ
• ቴሌብር ሳንዱቅ የተሰኙ የፋይናንሻል አገልግሎቶችን አስተዋውቋል።
ይህንን በሚመለከት ዝርዝር መረጃ አጠናቅረናል።
- " ቴሌብር መላ " አነስተኛ የብድር አገልግሎት ሲሆን ግለሰቦች እንዲሁም ነጋዴዎች እና ወኪሎች ያለየብድር ማስያዥያ ( Collateral ) ገንዘብ መበደር ያስችላቸዋል።
ምን ያህል መበደር እችላለሁ የአገልግሎት ክፍያውስ?
- " ቴሌብር እንደኪሴ " የክሬዲት ክፍያ/ኦቨርድራፍት ብድር አገልግሎት ሲሆን ገንዘብ በጎደሎት ጊዜ ሞልቶ ይከፍላል።
እንዴት መጠቀም እችላለሁ?
- " ቴሌብር ሳንዱቅ " የቁጠባ አገልግሎትን የሚሰጥ ሲሆን ከአንስተኛ ብር ጀምረው መቆጠብ ይችላሉ።
ወለዱ እንዴት ይሰላል ?
ያንብቡ : https://telegra.ph/telebirr-08-05
የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪ ሆቴል ውስጥ ሞተው ተገኙ.!!!
የታይዋን መከላከያ ሚኒሰቴር “ኦው ያንግ የታይዋን የሚሳዔል የማምረት አቅምን ለማሳደግ ሲሰሩ የነበሩ ከፍተኛ ባለሙያ ናቸው”ብሏል
የታይዋን የሚሳዔል ማምረቻ ከፍተኛ ተመራማሪና በወታደራዊ ባለቤትነት የተያዘው የናሽናል ቹንግ-ሻን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ምክትል ኃላፊ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ፤ ሆቴል ውስጥ ሞተው መገኘታቸው የታይዋን መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
እንደ የታይዋኑ ሴንትራል ኒውስ ኤጀንሲ ዘገባ ከሆነ ኦው ያንግ ሊ-ህሲንግ ሞተው የተገኙው በደቡባዊ ታይዋን በሚገኝ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡
‘አንድ ቻይና’ (ዋን ቻይና) ፖሊሲ፤ በሕጋዊው የቻይና መንግሥት ስር የምትዳደር ታይዋንን ያጠቃለለች አንዲት ሉዓላዊት ቻይና ብቻ መኖሯን የሚያረጋገጥ ፖሊሲ ነው።
አሜሪካንን ጨምሮ በርካታ ምዕራባውያን አገራት ይህን ‘የአንድ ቻይና’ ፖሊሲን አይገዳደሩም።
ይህ ፖሊሲ ከየት መጣ?
በቻይና የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት ተሸናፊ የነበረው የብሔርተኛው ቡድን ከዋናዋ የቻይና ግዛት ሸሽቶ በታይዋን ደሴት ላይ ከተመ።
በእርስ በእርስ ጦርነቱ ድል የተቀዳጀው ኮሚኒስት ፓርቲ 'ፒፕልስ ሪፓብሊክ ኦፍ ቻይናን' ማስተዳደር ሲጀምር፤ ተሸናፊው ቡድን ደግሞ ሸሽቶ የገባባትን ታይዋን መምራት ጀመረ።
ሁለቱም ቡድኖች መላዋን ቻይና የምንወክለው እኛ ነን ይሉ ነበር።
ቀደም ሲል ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው አገራት ለታይዋን እውቅና ይስጡ ነበር። ይሁን እንጂ የቻይና ምጣኔ ሃብት እና ተጽእኖ ፈጣሪነት እያየለ ሲመጣ ጀርባቸውን ለታይዋን ፊታቸውን ደግሞ ወደ ቻይና ማዞር ጀመሩ።
አሜሪካም ብትሆን ያደረገችው ይህንኑ ነው። አሜሪካ ለታይዋን እውቅና ሰጥታ ነበር። እአአ 1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከቻይና ጋር ያላት ግንኙነት እያደገ ሲመጣ በታይዋን መዲና የነበራትን ኤምባሲ ለመዝጋት ተገዳለች።
እአአ 1979 ላይ አሜሪካ በታይፒ የነበራትን ኤምባሲ ትዝጋ እንጁ፤ በዚያው ዓመት ታይዋን ሪሌሽን አክት የተሰኘ ከታይዋን ጋር ያላትን ግንኙነት የምትመራበትን ሕግ አውጥታ ነበር።
ይህም የአሜሪካን መሠሪነት ታይዋን ላይ ሁና ተቀናቃኙአን ቻይናን ለማዳከም በቻልለት ለመከፋፈል፣ለማፍረስ፣ልክ እንደ ሊቪያእና ሶሪያ ለመበታተን ነው፡፡
ይህ ሕግ አሜሪካ ታይዋን ራሷን እንድትከላከል የማገዝ ግዴታ አለባት የሚል አንቀጽን አካቷል። በዚህም መሠረት አሜሪካ የጦር መሳሪያዎችን ለታይዋን ትሸጣለች።
መሪዎቿም ከቻይና በተለየ ሁኔታ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጡ መሆናቸው ይነገራል።
ለዚህም አገራት ከታይዋን ጋር ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባይኖራቸውም፣ በንግድ እና በባህል ጽ/ቤቶች አማካይነት ይፋዊ ያልሆነ ግንኙነታቸውን እንዳስቀጠሉ ናቸው።
አሁን ላይ ለታይዋን እንደ አገር እውቅና የሚሰጡት ጥቂት አገራት ከመሆናቸውም በተጨማሪ፣ በተጽእኖ ፈጣሪነታቸው እዚህ ግቡ የሚባሉ አገራት አይደሉም።
ለታይዋን እውቅና ከሚሰጡ አገራት መካከል የመካከለኛው አሜሪካ አገራቱ ጓቲማላ፣ ሆንዱራስ፣ ኒካራጓ እና አፍሪካዊቷ ኢስቲዋኒ ይገኙበታል።
