cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Muslim ሙስሊም

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
801
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-17 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

#ልዩ_ልዩ_አጀንዳዎችና_ጣፋጭ_መልዕክቶች #ክፍል_2 #ሐዲሥ 370 / 1081 ረቢዕ ኢብኑ ሒራሽ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከአቡ መስዑድ አል አንሷሪ ጋር ወደ ሁዘይፈት ቢን አል የማን ሔድኩ። "አቡ መስዑድ ሆይ! ከአላህ መልዕክተኛ ስለ ደጃል የሰማሃውን ንገረኝ።" አሉት። እንዲህ ሲል አጫወታቸው፦ "ደጃል በእጁ ውሃና እሳት ይዞ ይነሳል። ለሰዎች ውሃ መስሎ የሚታያቸው ነገር የሚያቃጥል እሳት ሲሆን፣ እሳት መስሎ የሚታያቸው ደግሞ ቀዝቃዛና ጣፋጭ ውሃ ነው። ከእናንተ መካከል እርሱን ያገኘው እሳት መስሎ ከሚታየው ላይ ይውደቅ። ምክንያቱም እርሱ ጣፋጭና ተስማሚ ነውና።" አቡ መስዑድም፦ "እኔም ይህን ሰምቻለሁ" አሉ። (ቡኻሪና ሙስሊም) Umma Life https://ummalife.com/MuslimEthio ቴሌግራም/ telegram/ https://t.me/ethiomuslim_1
Hammasini ko'rsatish...
MuslimEthio

Photo unavailableShow in Telegram
አይነናስ ምንድነው_⎹ ቁርዓናዊ ሕክምና⎹ ኡስታዝ ዓብዱልዓዚዝ ሙሀመድ⎹ #ዛውያቲቪ.mp3
Hammasini ko'rsatish...
አይነናስ_ምንድነው_⎹_ቁርዓናዊ_ሕክምና⎹_ኡስታዝ_ዓብዱልዓዚዝ_ሙሀመድ⎹_#ዛውያቲቪ.mp37.71 MB
#ልዩ_ልዩ_አጀንዳዎችና_ጣፋጭ_መልዕክቶች #ክፍል_1 #ሐዲሥ 370 / 1080 ነዋስ ኢብኑ ሰምዓን እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋ፤፦ የአላህ መልዕክተኛ አንድ ቀን ጠዋት ድምጻቸውን ከፍና ዝቅ እያደረጉ ከተምር ዛፎች መሐል (ከአጠገባችን) ያለ መስሎ እስኪሰማን ስለ ደጃል ተረኩ። ተመልሰን በሔድን ጊዜ ይህን ስሜታችንን ተረዱ። "ምን ሆናችሁ?" አሉን። "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጠዋት ስለ ደጃል አውስተውልን ነበር። ድምጽዎትን ከፍና ዝቅ እያደረጉ ሲናገሩ ከተምር ዛፎች መሐል (ከአጠገባችን) ያለ ያህል ተሰማን።" አልናቸው። እንዲህ አሉን፦ "ይበልጥ የምፈራላችሁ ደጃልን ሳይሆን ሌሎች ነገሮችን ነው። እኔ በሕይወት እያለሁ ከመጣ እናንተን ወክዬ ራሴው እሟገተዋለሁ። እኔ ከእናንተ በሌለሁበት ዘመን ከመጣ ግን እያንዳንዱ ሰው ስለ ራሱ ይሟገታል። አላህ እያንዳንዱን ሙስሊም ስለኔ ሆኖ ይጠብቀዋል። ደጃል ፀጉሩ የተቋጠረ ወጣት ነው። ዓይኑ ወጣ ወጣ ያለ ነው። ዐብዱልዑዝዛ ኢብኑ ቀጠን በተባለው ሰው እመስለዋለሁ (እርሱን ይመስላል)። ከመካከላችሁ እርሱን ያገኘ የአል ከህፍ ምዕራፍ መግቢያዎችን ይቅራበት። በሻምና በዒራቅ መካከል ባለ ቦታ ላይ ነው የሚመጣው። በስተቀኝም በስተግራም ብክለትን ያስፋፋል። የአላህ ባሮች ሆይ! ጽኑ።" እኛም፦ "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ምድር ላይ ምን ያህል ጊዜ ይቆያል?" አልናቸው። "አርባ ቀናት ይቆያል። አንድ ቀን እንደ አንድ ዓመት፣ አንድ ቀን እንደ አንድ ወርና አንድ ቀን ደግሞ እንደ አንድ ሳምንት። ቀሪዎቹ ቀናት የተለመዱ ዓይነት ቀኖች ይሆናሉ" አሉ። "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በዚያ እንደ ዓመት በሚሆነው ቀን የአንድ ቀን ሶላት ይበቃናልን?" አልናቸው። "አይበቃችሁም፣ ግና ጊዜውን እየገመታችሁ ስገዱ" አሉን። "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ምድር ላይ ምን ያህል ይፈጥናል?" አልናቸው። "አፈጣጠኑ ነፋስ እንደተከተለው ዝናብ ነው። ከሰዎች ዘንድ ይመጣና ጥሪ ያደርግላቸዋል። በርሱ ያምናሉ። ይቀበሉታልም። ሰማይን ያዝዛትና ታዘንባለች። ምድርም ታበቅላለች። እንስሳዎቻቸው ጋቶቻቸው ሞልተውና ጠግበው ይመለሳሉ። ከሌሎች ሰዎች ዘንድ ይሔድና ጥሪ ያደርግላቸዋል። ንግግሩን ሳይቀበሉት ይቀራሉ። እርሱም ጥሏቸው ይሔዳል። ወዲያውም ድርቅ ይመታቸዋል። ከእጃቸው ላይ የምቀር ሃብት አይኖራቸውም። በሞተች ምድር አጠገብ ያልፍና 'ድልብሽን አውጭ' ሲል ያዝዛታል። ድልቧን እንደንብ አውራ ታግተለትልለታለች። አንድን ወጣት ይጠራውና በሰይፍ በመምታት ከሁለት ይበጥሰዋል። ከዚያም ይጠራዋል። ፊቱ በሳቅ ተሞልቶ ጥሪውን በመቀበል ይመጣል።በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለ አላህ የመርየምን ልጅ አልመሲሒን ያስነሳዋል። በደማስቆ በስተምስራቅ በኩል ከአንድ ነጭ ሚናራዎች ላይ ሁለት ያማሩ አልባሳት ተጎናጽፎና መዳፎቹን ከመላእክት ክንፍ ላይ አሳርፎ ይወርዳል። አንገቱን ሲደፋ ውሃ ከርሱ ይንጠባጠባል። ቀና ሲያደርገውም ልክ እንደ ሉል ሆኖ እየተንኳለለ ይወርዳል። ትንፋሹን ያሸተተ ከሐዲ ሁሉ ወዲያውም ይሞታል። ትንፋሹ ዓይኑ እስከሚያየው ክልል ድረስ ይደርሳል። ዒሳ ደጃልን ያሳድደዋል። "ሉድ" ከተባለው በር ላይ ያገኘውና ይገድለዋል። ከዚያም የመርየም ልጅ ዒሳ አላህ ከደጃል ፈተና ከጠበቃቸው ሰዎች ዘንድ ይመጣል። ፊታቸውንም ያብሳል። ጀነት ውስጥ ያላቸውን ደረጃም ይነግራቸዋል። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ አላህ እንዲህ የሚል መልዕክት ያስተላልፍለታል። አንድም ሰው ሊዋጋቸው የማይደፍር ባሮቼን አውጥቻለሁና የኔን አገልጋዮች ወደ ጡር ጋራ ይዘሐቸው ዝለቅ።" አላህ የእጁጅና መእጁጅ (ጎግ ማንጉግ) የተባሉ ፍጡራንን ያስነሳል። ከየከፍታ ቦታው ይወርዳሉ። የመጀመሪያው በጠበሪይያህ ሐይቅ አጠገብ ያልፋል። ከውስጡ ያለውን ውሃም ምጥጥ አድርጎ ይጠጣል። የመጨረሻዎቹ በሐይቁ አጠገብ ሲያልፉ፦ "ከዚህ ቦታ ላይ ውሃ ነበረበት" በማለት (እንደታሪክ) እስኪያስቡት ድረስ ውሃው ይደርቃል። የአላህ ነቢይ ዒሳ እና ባልንጀሮቻቸው ይከበባሉ። ያንዬ ለነርሱ የአንድ በሬ ራስ ዛሬ ለናንተ መቶ ዲናር ከሚኖረው የበለጠ ዋጋ ይኖረዋል። ዒሳና ባልንጀሮቹ አላህን ይማጸናሉ። አላህም አንገቶቻቸውን የምነድፉ ትሎች (ተባዮችን) ይልክባቸዋል። ሁሉም እንደ አንድ ሰው ይሞታሉ።ከዚያም የአላህ ነቢይ አሥር ባልንጀሮቻቸው ወደ መሬት ይወርዳሉ። ስፍራው ሁሉ ስንዝር ቦታ ሳይቀር በነርሱ ጥንብና መጥፎ ሽታ ተሞልቶ ያገኙታል። የአላህ ነቢይ ዒሳ እና አሥር ባልንጀሮቻቸው አላህን ይማጸናሉ። አላህም የግመል አንገት የመሰሉ በራሪዎችን ይልካል። እነዚህ በራሪዎች ሬሳዎቻቸውን እያነሱ አላህ ከሻው ቦታ ላይ ይጥሉታል። ከዚያም አላህ ዝናብ ይልካል። ይህ ዝናብ አንድም ቤት ሳይቀር ሁሉንም ያደርሳል። ምድርንም ልክ እንደ መስታወት እስክትጸዳ ድረስ ያነጣል። ከዚያም ምድር፦ "አትክልቶችሽን አብቅይ። በረከትሽንም መልሺ" ትባላለች። በዚህ ጊዜ ሁሉም ሮማን ይመገባሉ። በቆዳዋም ይጠለላሉ። ወተቱም ይበረክታል። የምትታለብ ግመል ለብዙ ሰዎች የሚበቃ ወተት ትሰጣለች። የምትታለብ ላም ለአንድ ጎሣ የሚበቃ ወተት ትሰጣለች። የምትትታለብ ፍየል ለአንድ ነገድ የሚበቃ ወተት ትሰጣለች። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ አላህ በጎ ነፋስ ያስነሳል። ከብብታቸውም ሥርም ታጠቃቸዋለች። የአማኞቹን ነፍስም ታወጣለች። ልክ እንደ አህያ በአደባባይ ወሲብ የሚፈጽሙ እኩይ ሰዎች ብቻ ይቀራሉ። በነርሱ ላይ ትንሳኤ ትቆማለች (ትከሰታለች)።" (ሙስሊም) Umma Life https://ummalife.com/MuslimEthio ቴሌግራም/ telegram/ https://t.me/ethiomuslim_1
Hammasini ko'rsatish...
MuslimEthio

Photo unavailableShow in Telegram
#እርም_የሆነ_ነገር_የፈጸመ_ሰው_ማለትና_ማድረግ_ያለበት አላህ እንዲህ ብሏል፦ "ከሰይጣንም ጉትጎታ ቢያገኝህ (ከመልካም ጠባይም ቢመልስህ) በአላህ ተጠበቅ፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡" (ፈሲለት፡ 36) "እነዚያ የተጠነቀቁት ከሰይጣን የኾነ ዘዋሪ በነካቸው ጊዜ (ጌታቸውን) ይገነዘባሉ፡፡ ወዲያውም እነሱ ተመልካቾች ይኾናሉ፡፡" (አል አዕራፍ፡ 201) "ለእነዚያም መጥፎ ሥራን በሠሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኀጢአቶቻቸው ምሕረትን የሚለምኑ ለኾኑት ከአላህ ሌላ ኀጢአቶችን የሚምር ማነው? (አንድም የለም)፡፡ (በስሕተት) በሠሩትም ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑ የማይዘወትሩ ለኾኑት (ተደግሳለች)፡፡ እነዚያ ምንዳቸው ከጌታቸው ምሕረትና በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ በሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶችም ናቸው፡፡ የሠሪዎችም ምንዳ (ገነት) ምንኛ አማረች!፡፡" (አል ዒምራን 135-136) "... ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ (በመመለስ) ተጸጸቱ፡፡" (አንኑር፡ 31) #ሐዲሥ 369 / 1807 አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፦ "በላትና በዑዝዛ የማለ፣ 'ላ ኢላሀ ኢልለልላህ' ይበል። 'ና ቁማር እንጫወት' በማለት ባልንጀራውን የጋበዘ ምጽዋት ይስጥ።" (ቡኻሪና ሙስሊም) ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች 1/ በጣዖት ወይም ከአላህ ውጭ በሌላ አካል መማል የከፋ ጥፋት ነው። 2/ ይህን ጥፋት የፈጸመ ሰው፦ "ከአላህ ሌላ አምላክ የለም" በማለት ጥፋቱን ያካክስ። እምነቱንም ያድስ። 3/ መቆመር ይቅርና ለቁማር ሰውን መጋበዝ እንኳ የከበደ ወንጀል ነው። ማካካሻና ተውባ ያስፈልገዋል። 4/ ሳናስበውና ሳናንዛዛ መግለጽ መቻል ተወዳጅ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዱዓዎች ይህን ባሕሪ የተላበሱ ነበሩ። Umma Life https://ummalife.com/MuslimEthio ቴሌግራም/ telegram/ https://t.me/ethiomuslim_1
Hammasini ko'rsatish...
MuslimEthio

👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
#አንድ_ቀን_ከነ_ሌሊቱ #በዝምታ_ማሳለፍ_ስለመከልከሉ #ሐዲሥ 366 / 1800 ዐሊይ እንዲህ ብለዋል፣ ከነቢዩ የሚከተሉትን ምክሮች በአእምሮዬ ይዣለሁ፦ "ለአካለ መጠን ከደረሱ በኋላ የቲምነት የለም። አንድ ቀን ከነሌሊቱ በዝምታ ማሳለፍም አግባብ አይደለም።" (አቡ ዳውድ) አል ኸጧቢይ ይህን ሐዲሥ ሲያብራሩት እንዳሉት፥ በቅድመ ኢስላም የጃሂሊያ ዘመን ዝምታ የአምልኮ አካል ተደርጎ ይወሰድ ነበር። ኢስላም ውስጥ ከዚህ ድርጊት ተከለከሉ። አላህን እንዲያወሱና ደጋግ ጨዋታዎችን እንዲጨዋወቱ ታዘዙ። #ሐዲሥ 366 / 1801 ቀይስ ኢብኑ ሐዚም እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፣ አቡበክር ሲዲቅ ከአሕመስ እንስቶች ከአንዷ ዘንድ ገቡ። ስሟ ዘይነብ ይባላል። የማትናገር ሆና አገኟት። "የማትናገሪው ለምንድን ነው ?" ሲሉ ጠየቁ። "ዝምታ ተስላለች" አሏቸው። "ተናገሪ፣ ይህ ድርጊት አይፈቀድም፣ የድንቁርና ዘመን ተግባር ነው" አሏት። መናገር ጀመረች። (ቡኻሪ) ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች 1/ የቲም ማለት አባቱ የሞተበት ሕጻን ሲሆን፣ ለአካለ መጠን ከደረሰ በኋላ ግን የቲም የመባሉ ነገር ያበቃል። ከዚህ ስያሜ ጋር የተያያዙ ሸሪዓው ድንጋጌዎችም በልጁ ላይ ተፈጻሚነታቸው ይቋረጣል። 2/ በዝምታ አላህን ማምለክ የቅድመ ኢስላም የድንቁርና ዘመን የአምልኮ ዓይነት እንጅ የኢስላም አካል አይደለም። ስለዚህ በጎ ነገርን መናገር ይመረጣል። ክፉ ነገርን መናገር ግን ሐራም ተደርጓል። ስለዚህም ክፉ ከመናገር ዝምታ፣ ከዝምታ ደግሞ በጎ ነገር መናገር ይመረጣል። 3/ ላይናገር የተሳለ ሰው ስለቱን የመሙላት ግዴታ የለበትም። ምክንያቱም ስለቱ የሸሪዓውን ትእዛዝ የጣሰ ነውና። Umma Life https://ummalife.com/MuslimEthio ቴሌግራም/ telegram/ https://t.me/ethiomuslim_1
Hammasini ko'rsatish...
MuslimEthio

Photo unavailableShow in Telegram
#ወንድ_ልጅ_በቢጫ_ቀለም_የተነከረን_ልብስ_መልበሱ_ክልክል_መሆኑ #ሐዲሥ 365 / 1798 አነስ እንዳስተላለፉት ወንድ ልጅ በቢጫ ቀለም የተነከረ ልብስ እንዳይለብስ ነቢዩ ከልክለዋል። (ቡኻሪና ሙስሊም) #ሐዲሥ 365 / 1799 ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር ኢብኑ አል ዓስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ "ነቢዩ ሁለት ቢጫ ቀለሞች የተቀለሙ ልብሶችን ከኔ ላይ አዩብኝ። "ይህን እንድትለብስ ያዘዘችህ እናትህ ናትን ?" አሉኝ። "ልጠባቸውን ?" አልኳቸው። "አቃጥላቸው" አሉኝ። በሌላ ዘገባ "እነዚህ የከሐዲያን ልብሶች ስለሆኑ አትልበሳቸው" አሉኝ። (ሙስሊም) ከሐዲሦቹ የምንማራቸው ቁምነገሮች 1/ በቢጫ ቀለም የተነከረን ልብስ መልበስ ለወንዶች ተከልክሏል። እቀባውን በተመለከተ ዑለሞች የተለያዩ አስተያየት ሰጥተዋል። ከፊሎቹ ሐራምነትን ያመለክታል ሲሉ ሌሎች ደግሞ የተጠላ መሆኑን ከማመልከት አያልፍም ብለዋል። 2/ የእቀባው ዓላማ በቀለም የተሽቆጠቆጡ አልባሳት ይበልጡኑ ለሴቶች መዋቢያነት የሚውሉ በመሆናቸው ወንድ ልጅ እንዲህ ዓይነቱ ዝንባሌ እንዳይኖረው ለመከላከል ነው። 3/ በተጨማሪም ከሐዲያን የሚያዘወትረዋቸውን በአንዳንድ ቦታዎችም የሃይማኖት አባቶቻቸው የተለዩ አልባሳት ሆነው ስለሚያገለገሉ ነው። 4/ የእቀባው ትርጉም ሐራምነትም ይሁን መጠላት፥ ወንድ ልጅ ከእንዲህ ዓይነት አልባሳት መራቁ ይመረጣል። 5/ ሙስሊም በአለባበሱ፣ በአመጋገቡና በጠቅላላ ሕይወቱ ከሌሎች ሕዝቦች የተለየ እንዲሆን ነቢዩ የነበራቸውን ጽኑ ፍላጎት ይህ ሐዲሥ ያሳያል። Umma Life https://ummalife.com/MuslimEthio ቴሌግራም/ telegram/ https://t.me/ethiomuslim_1
Hammasini ko'rsatish...
MuslimEthio

Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.