ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Kanalga Telegram’da o‘tish
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Ko'proq ko'rsatish637
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-1230 kunlar
Postlar arxiv
❤ የደማስቆውም ገዥ የተጻፈለት እውነት መስሎት የቅዱስ ዮሐንስ ቀኝ እጁን ቆረጠው፡፡ አባ ዮሐንስም የተቆረጠች እጅን ይዞ ወደ የብርሃን እናቱ ወደሆነች ወደ እመቤታችን ሥዕል ሄዶ በብዙ ዕንባ እንዲህ ብሎ ለመናት፡- "እመቤቴ ሆይ! ለሥዕልሽ መስገድ እንደሚገባ በተጣላሁ ጊዜ ነው ይህ የእጄ መቆረጥ የደረሰብኝ፣ አሁንም ሁሉ ይቻልሻልና በቸርነትሽ ፈውሽኝ" ብሎ ከለመናት በኋላ ወዲያው ከባድ እንቅልፍ ጣለው፡፡ በእንቅልፉም ሳለ እመቤታችን ተገለጸችለትና እጁን እንደቀደሞው አድርጋ መለሰችለት፡፡ እርሱም በነቃ ጊዜ እጁ ድና ስላገኛት እጅግ ተደስቶ እመቤታችንን አመሰገናት፡፡
❤ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳም ሄዶ መነኰሰ፡፡ መምህሩ የሆኑት አንድ አረጋዊ አባትም "ዮሐንስ ሆይ አፍአዊት ከሆነች ትምህርትህ ምንም ምን አታድርግ ግን ዝምታን ተማር" አሉት፡፡ ዮሐንስም የመነኮሳቱን የመጸዳጃ ቤታቸውን እያጸዳና በሁሉ ነገር እያገለገላቸው በተጋድሎ ኖረ፡፡ መምህሩም አርምሞውን ፈትቶ ካገኙት ይቀጡት ነበር፡፡ እመቤታችንም አንድ ቀን ለመምህሩ ተገለጠችላቸውና ዮሐንስ ድርሳናትን እንዲደርስ ይፈቅድለት ዘንድ አዘዘችው፡፡ ዮሐንስም ከዚህ በኋላ ብዙ ድርሳናትን ደረሰ፡፡ ስለ ቀናች አንዲት ሃይማኖትና ስለተሣሉ ቅዱሳት ሥዕላት ብዙ የደከመው አባት አባ ዮሐንስ የእርጅና ዘመኑን ጨርሶ በዚህች ዕለት ታኅሣሥ8 በሰላም ዐረፏል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ በቅዱስ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ያሬክላ፦ ይህም አባት ለእስክድርያ ለአገር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሦስተኛ ቊጥር ነው። የዚህም ቅዱስ አባት ወላጆቹ አስቀድሞ አረማውያን ነበሩ በወለዱትም ጊዜ የአረማውያንን ትምህርት መጻሕፍቶቻቸውንም ሁሉ አስተማሩት።
❤ ከዚህም በኋላ አምነው ተጠመቁ ይህን ልጃቸውንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት የሐዋርያትንም መጻሕፍት አጠና ሊቀ ጳጳሳት ድሜጥሮስም ዲቁና ሾመው ከዚህም በኋላ በእስክንድርያ አገር ቤተ ክርስቲያን ቅስና ሾመው መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። ሥራውንም ፈጸመ የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ ጠንቅቆ አወቀ።
❤ አባት ድሜጥሮስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት መርጠው በእስክድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በቀናች ሃይማኖት አጽንቶ ጠበቀ ከአረማውያንም ብዙዎችን ክብር ይግባውና ክርስቶን ወደ ማመን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ለቅዱስ ዲዮናስዮም ለምእመናን እንዲፈርድ ሥልጣን ሰጠው እርሱ ግን ዓላውያንን ወደ ቀናች ሃይማኖት እስከሚመልሳቸው ድረስ ያስተምራቸውና ይገሥጻቸው ነበር። በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ሦስት ዓመት ኑሮ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ያሬክላ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ8 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላክ አማልክት በጽዮን"። መዝ83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥1-17።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ኀብአኒ ውስተ ጽላሎቱ በዕለተ ምንዳቤየ። ወሠወረኒ በምኅባአ ጽላሎቱ። ወዲበ ኰኵሕ አልዐለኒ"። መዝ 26፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 12፥1-8፣ 1ኛ ጴጥ 3፥8-15 የሐዋ ሥራ 21፥1-8። የሚነበበው ወንጌለሰ ሜቴ 11፥16-20። የሚቀደሰው ቅዳሴ የያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ተክለ አልፋ የዕረፍት በዓል፣ የአቡነ እስትፋሰ ክርስቶስና የአቡነ ኪሮስ የልደት በዓልና የነቢያት (ገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችን ይሁንልን።
❤ ቃልኪዳንም ስለተቀበለበት በገዳሙ ውስጥ ርሀብ፣ ቸነፈርና መቅሰፍት ፈጽሞ አይገባም፡፡ "መምሕረ ንስሓ" በመባል የሚታወቁት አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን ወንጌልን በማስተማር፣ አስደናቂ ተአምራትን በማድረግ ድውያንን እየፈወሱ በብዙ ድካም ከተጋደሉ በኋላ ከጌታችን ቃልኪዳን ተቀብለው ታኅሣሥ 8 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ሳሙኤል ጸሎት ይማረን በከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ኤሲና_እኅቱ_ቅድስት_ቴክላ፡- እነዚህም ቅዱሳን ለእስሙናይን በስተምራብ ካለው አውራጃ ብጺር ከሚባል መንደር የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ አባታቸው ኤልያስ እናታቸው ማርያም ይባላሉ፡፡ ኤሲም ዕድሜው እንደደረሰ ወላጆቹ ሊያጋቡት ሲሉ እርሱ ግን እምቢ አለ፡፡ ኤሲ እግዚአብሔርን እጅግ የሚፈራ ብዙ ሀብት የነበረው እጅግ ባለጸጋም ነበር፡፡ እጅግ የበዙ በጎች ስለነበሩት ጸጉራቸውን እየሸጠ ድኆችንና ጦም አዳሪዎችን ይረዳል፡፡ ዕድሜውም 20 በሆነ ጊዜ አባቱና እናቱ ሞቱ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ አረመኔው ዲዮቅልጥያኖስም በዚያ ዘመን ነግሦ የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ማፍሰስ ጀመረ፡፡
❤ አባ ኤሲም በእስክንድርያ አገር ጳውሎስ ከሚባለው ባልንጀራው ጋር የታሰሩትን ሰማዕታት እየጎበኟቸው ያገለግሏቸው ነበር፡፡ ሰማዕታቱም ለአባ ኤሲና ለጳውሎስ "እናንተም እንጂ ደግሞ ሰማዕት ትሆኑ ዘንድ አላችሁ" እያሉ ትንቢት ይነግሯቸው ነበር፡፡ በዚያም ወራት የንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ባለሟል የነበረውን የኅርማኖስን ልጅ ታላቁን ሰማዕት ቅዱስ ፊቅጦርን ወደ እስክንድርያ በግዞት እያሠቀዩ አመጡት፡፡ ኤሲና ጳውሎስም የቅዱስ ፊቅጦርን ጽናት አይተው መንፈሳዊ ቅናት ቀኑ፡፡ ኤሲም ወደ መኮንኑ ቀርቦ የጌታችንን ክብር መሰከረ፡፡ መኮንኑም ኤሲን ይዞ ማሠቃየት ጀመረ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ኤሲን በብረት አለንጋ ብዙ ግርፋትን ገረፉት፡፡ ህዋሳቱንም በሾተሎች ሰነጣጠቁ፡፡ በሥጋውም የችቦ መብራቶችን እያደረጉ አቃጠሉት፡፡ ዳግመኛም በሰንሰለት አሥረው በሚነድ እቶን እሳት ውስጥ ጨመሩት፡፡ ነገር ግን ወደ ጌታችን በጸለየ ጊዜ ጌታችን መልአኩን ቅዱስ ሱርያልን ላከለት፡፡ መልአኩም ለኤሲ "ጻድቅ ሰው ሆይ ሰላምታ ለአንተ ይገባሃል" አለውና እሳቱን አጠፋለት፡፡ እጁንም ይዞ ከጉደጓዱ አወጣው፡፡ አባ ኤሲም ወደ መኰንኑ ዘንድ ሄዶ "ከሃዲ ንጉሥ ሆይ አንተ ጣዖታቶችህ እፈሩ አምላኬ አድኖኛል" አለው፡፡ ሕዝቡም አባ ኤሲን ሕያው ሆኖ ባዩት ጊዜ እጅግ ተደንቀው "እኛም በአባ ኤሲ አምላክ አምነናል" ብለው መስክረው ብዙዎች ሰማዕት ሆኑ፡፡ አባ ኤሲንም አሠሩት፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ለእኅቱ ለቅድስት ቴክላ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላትና ወደ ወንድሟ እንድትሄድ ነገራት፡፡ እርሷም ከእንዴና ከተማ ተነሥታ ወደ ባሕር ዳርቻ በደረሰች ጊዜ መንፈሳዊት መርከብን አገኘች፡፡ እመቤታችንና አክስቷ አልሳቤጥም በውስጧ አሉ፡፡ ቅድስት ቴክላም "እመቤቶቼ ሆይ! የደረሰባችሁ ምንድነው/አዝናችሁ አያችኋለሁና" አለቻቸው፡፡ ቅድስት ኤልሳቤጥም "በእርጅናዬ ወራት የወለድኩት አንድ ልጅ ነበረኝ፣ ወስደው አረዱብኝ" አለቻት፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያምም "ለእኔም አንድ ልጅ ነበረኝ፣ እርሱንም ወስደው ሰቅለው ገደሉብኝ" አላቻት፡፡ ቅድስት ቴክላም ይህንን በሰማች ጊዜ እጅግ አዝና "እመቤቶቹ ሆይ! በእውነት ጽኑ የሆነ ሀዘን አግኝቷችኋል" አለቻቸው፡፡ ይህንና የመሳሰለውንም ነገር እየተነጋገሩ ወንድሟ አባ ኤሲ ካለበት አደረሷት፡፡ የተገለጡላት ግን እነማን እንደሆኑ አላወቀችም፡፡
❤ አባ ኤሲም እኅቱን ቴክላን ባያት ጊዜ ደስ አለው፡፡ አብረው ስለጌታችን ክብር ይሞቱ ዘንድ ተስማሙ፡፡ ሌሊት በሆንም ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሱርያል አባ ኤሲን ነጥቶ ወደ ሰማይ ወሰደውና ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን አሳየው፡፡ የጻድቃንንና የሰማዕታትን መኖሪያቸውን የራሱንም መኖሪያውን አሳየው፡፡ መልአኩ "በሰማዕታት ስም የሚዘክሩ የዓለም ሰዎች ቢኖሩ በዕለተ ሞታቸው ቀን የዘከሯቸው ቅዱሳን አማልደው በዚህ የብርሃን ድንኳን አዳራሽ ውስጥ ለዘለዓለም በክብር ያኖሯቸዋል" እያለ እያንዳንዱን የቅዱሳንን የብርሃን ድንኳን ያለውን የቅዱሳንን መኖሪያ አሳየው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱሳን ሁሉ መጥተው አባ ኤሲን ሰላምታ ሰጡት፡፡
❤ መልአኩም አባ ኤሲን ሰማዕትነቱን እንዲፈጽም ከነገረው በኋላ ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም መልሶ አምጥቶ እሥር ቤቱ ውስጥ አስቀመጠውና ተመልሶ ዐረገ፡፡ በነጋም ጊዜ መኮንኑ አባ ኤሲንና እኅቱን ቅድስት ቴክላን ከእሥር ቤት አውጥተው ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃዩአቸው፡፡ በተሸከርካሪዎች መሣሪያ፣ በብረት ቃጠሎ፣ በችንካሮች በመቸንከር የራሳቸውንም ቆዳ በመግፈፍ ብዙ አሠቃዩአቸው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ከሕመማቸው ሁሉ ፈወሳቸው፡፡ መኮንኑም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ወደላይኛው ግብጽ ይወስዳቸውና ያሠቃያቸው ዘንድ ለእንዴናው አገር መኮንን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ 8 ቀን ያህል እንደተጓዙም መርከቧ ቆመች፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ የአባ ኤሲንና የቅድስት ቴክላን ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ እነርሱም በዚህ ደስ ተሰኝተው ጸሎታቸውን ከፈጸሙ በኋላ አንገታቸውን አሳልፈው ለሰያፊዎቻቸው ሰጧቸውና በየተራ ቆረጧቸው፡፡ ሰማዕትነታቸውንም በዚሁ ፈጽመው የክብርን አክሊል ተቀዳጁ፡፡ እግዚአብሔርም ስንሑፍ ከሚባል አገር ስሙ ኦሪ የሚባለውን ቄስ የቅዱሳንን ሥጋቸውን እንዲያነሣ አዘዘው፡፡ እርሱም መጥቶ በክብር ወስዶ የመከራው ዘመን እስኪያልፍ በንጹሕ ቦታ አኖራቸው፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ከእነርሱም ጋር አብረው ተሰይፈው የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ ቅዱሳን 477 ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዮሐንስ_ዘሀገረ_ደማስቆ፡- ይኽም ቅዱስ ከደማስቆ ከከበርቴዎቿና ከታላላቆቿ ወገን ከሆነው መንሱር ከሚባለው ሰው የተወለደ በጥበብና በፈሪሃ እግዚአብሔር ያደገ ነው፡፡ የቀርሊ ፈላስፋ ከሆነው ቁልፋህ ከሚባል መነኩሴ ቁልዝማቂ መምህሩ ዘንድ የፍልስፍና ትምህርትን ተማረ፡፡ ትምህርቱንም ሲጨርስ ቁልዝማዊ መምህሩን ተሰናብቶ ወደ ከበረ ሊቅ ሳበ ሰማዕት ገዳም ሄደ፡፡ አባቱም በሞተ ጊዜ ለአገረ ገዥው ጸሐፊ ሆነ፡፡
❤ በዚያም ወራት የከሃዲው ልዩን ልጅ ቆስጠንጢኖስ ተነሥቶ በአምላክ ፈቃድ ስለተሣሉ ቅዱሳት ሥዕላት ጸብ በማንሣት አብያተ ክርስቲያናትን የሚያውክ ሆነ፡፡ ይህም አባ ዮሐንስ የቤተ ክርስቲያን ሹመት ሳይኖረው በቀናች ሃይማኖት እያጸናቸው በአምላክ ፈቃድ ለተሣሉ ሥዕላት ስግደት እንደሚገባ ምስክር ከቅዱሳት መጻሕፍት እያመጣ የሚጽፍ ሆነና ወደ ምእመናን ሁሉ የሚልክ ሆነ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም ይህንን በሰማ ጊዜ ጥርሱን እያፋጨ በዮሐንስ ብዕር አምሳል የሚጽፍ ጸሐፊ ፈልጎ አመጣና ዮሐንስ እንደጻፈው አድርጎ እንዲህ ብሎ ጻፈ፡- "ከአንተ ዘንድ ያለው ዮሐንስ ከአንተ ጋር ተዋግቼ አገርህን እማርክ ዘንድ ይህን ደብዳቤ ጽፎ ላከልኝ" ብሎ በወንጀል ለደማስቆው ገዥ ላከለት፡፡
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፰ (8) ቀን
❤ እንኳን #መልአከ_እግዚአብሔር_እስከ_ማማለድ ስልጣን ለተሰጠው #ለደብረ_ቀልሞን_ለአባ_ሳሙኤል ለዕረፍት በዓል፣ የከበሩ ሴቶች #ለቅድስት_በርባራና_ለቅድስት_ዮልያና ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለእስሙናይን በስተምዕራብ ካለ አውራጃ ብጺር ከሚባል መንደር ለሆኑ #ለቅዱሳን_ለአባ_ኤሲና ለእኅቱ #ቅድስት_ቴክላ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓላቸው፣ ለእስክንድር አገር ዐሥራ ሦስተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ያሬክላና ለተመሰገነ #ለአባ_ዮሐንስ_ዘአገረ_ደማስቆ ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የከበሩ_ሴቶች_ቅዱሳን_በርባራና_ዮልያና፦ ይችም ቅድስት በርባራ በከሀዲው መክስምያኖስ ዘመን ታላቅ መስፍን ለሆነ ሰው ልጁ ናት ስሙም ዲዮስቆሮስ ነው እርሱም ለልጁ ለበርባራ ማንም እንዳያያት ታላቅ ጽኑ የሆነ ሕንፃ አሠራ ከዚህም ዳግመኛ መታጠቢያ የውሽባ ቤት በግንብ ሠራ የሚከፈቱ ሁለት መስኮቶችንም በውስጡ እንዲሠሩ አዘዘ። ቅድስት በርባራም ሁለቱን መስኮቶች በአየች ጊዜ ሦስት መስኮትን እንዲሠሩ ሐናፂዎችን አዘዘቻቸው ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝ የሆነ የመስቀሉን ምልክት በውኃ መታጠቢያው ላይ አሠራች።
❤ አባቷም ወደዚህ ሕንፃ በገባ ጊዜ ይህን ልጁ ያሠራችውን አይቶ አናፂዎችን ጠየቀ እነርሱም "ይህን እንድንሠራ ልጅህ አዘዘችን" አሉት እርሷንም ጠርቶ "ለምን እንዲህ አደረግሽ" አላት። እርሷም "አባቴ ሆይ አስተውል ልዩ ሦስት በሆነ በሥላሴ ስም ሥራ ሁሉ ይፈጸማልና ስለዚህ ሦስተኛ መስኮት አሠራሁ ይህም መስቀል ዓለሙ ሁሉ በእርሱ በዳነበት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አምሳል ነው አንተም አባቴ ሆይ ከስሕተትህ ተመለስህ የፈጠረህን አምላክ አምልከው" አለችው። አባቷም ከእርሷ ይህን በሰማ ጊዜ ሰይፋን መዝዞ በኋላዋ ሮጠ እርሷም ሸሸች በፊቷም የነበረች ዐለት ተሠንጥቃ በውስጧ ገብታ ሠወረቻት።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ አባቷ ተመለሰች እርሱም እንዲአሠቀሠያት ለሌላ መኰንን አሳልፎ ሰጣት እርሱም ታላቅ ሥቃይን አሠቃያት በዚያም ዮልያና የምትባል ሴት ነበረች ቅድስት በርበሠራንም አየቻትና የምታጽናናትና የምታረጋጋት ሆነች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅድስት በርባራ ተገለጸላትና አረጋጋት።
❤ ከዚህም በኋላ አባቷ በሰይፍ ራሷን እንዲቆርጡ የባልንጀራዋ የዮልያና ራስ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ። በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እሳት ወርዶ አባቷንና ጓደኛው የሆነ መኰንን መርትያኖስን አቃጠላቸው ያም በውሽባ ቤት ውስጠሰ በመስቀል ምልክት ያሠራቸው መታጠቢያ ለታመመ ሁሉ ከእርሱ በታጠበ ጊዜ የሚያድን በውስጡ ታላቅ ፈውስ ያለበት ሆነ።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱሳን ሰማዕታትን ሥጋቸውን ወስደው ከከተማ ውጭ ባለች ቤተ ክርስቲያን ስሟ ገላልያ በሚባል ቦታ አኖሩአቸው ይህ ሥጋቸውም በቅዱሳን ሰማዕታት በአቡቂርና በዮሐንስ በምስር አገር በአለ ቤተ ክርስቲያናቸው እስከ ዛሬ አለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳት ሰማዕታት በርባራና ዮልያና ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
❤ አባቷም ወደዚህ ሕንፃ በገባ ጊዜ ይህን ልጁ ያሠራችውን አይቶ አናፂዎችን ጠየቀ እነርሱም "ይህን እንድንሠራ ልጅህ አዘዘችን" አሉት እርሷንም ጠርቶ "ለምን እንዲህ አደረግሽ" አላት። እርሷም "አባቴ ሆይ አስተውል ልዩ ሦስት በሆነ በሥላሴ ስም ሥራ ሁሉ ይፈጸማልና ስለዚህ ሦስተኛ መስኮት አሠራሁ ይህም መስቀል ዓለሙ ሁሉ በእርሱ በዳነበት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አምሳል ነወሰ አንተም አባቴ ሆይ ከስሕተትህ ተመለስህ የፈጠረህን አምላክ አምልከው" አለችው። አባቷም ከእርሷ ይህን በሰማ ጊዜ ሰይፋን መዝዞ በኋላዋ ሮጠ እርሷም ሸሸች በፊቷም የነበረች ዐለት ተሠንጥቃ በውስጧ ገብታ ሠወረቻት።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘደብረ_ቀልሞን፡- የትውልድ ሀገራቸው ደቡባዊ ግብፅ ሲሆን በ14 ዓመታቸው ነው አስቄጥስ ገዳም ገብተው የመነኮሱት፡፡ በመነኰሱበት ዕለትም መልአክ ከጎናቸው ቆሞ ታይቷል፡፡ ታላቁ አባት አባ አጋቶን ካረፉ በኋላ ገዳመ አስቄጥስን ያስተዳደሩት አቡነ ሳሙኤል ናቸው፡፡ በዓለም ታሪክ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁለት በተከፈለችበትና "የውሾች ጉባኤ" በተባለው በ451 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ላይ የእነ ልዮን የክህደት ቃለ ጉባኤ ለአቡነ ሳሙኤል ተልኮላቸው ነበር፡፡ እሳቸውም ቃለ ጉባኤውን ተቀብለው መነኰሳቱን ሰብስበው እያሳዩአቸው በእሳት አቃጥለውታል፡፡ በዚህም ጊዜ በገዳሙ ለ14 ቀን ያህል ቀስተ ደመናና ብርሃን ወርዶ ታይቷል፡፡ ልዮንም ይህንን ሲሰማ ለንጉሡ በመንገር አቡነ ሳሙኤልን ሊያስገድላቸው ሲል እመቤታችን ለአቡነ ሳሙኤል ተልጻላቸው ወደ ደብረ ቀልሞን እንዲሄዱ ነገረቻቸው፡፡ እሳቸውም ተነስተው ደብረ ቀልሞን ገቡ፡፡ በገዳሙ በአበምኔትነት ተሹመው ማገልገል ጀመሩ፡፡
❤ አቡነ ሳሙኤል በዚሁ ዘደብረ ቀልሞን ገዳም የእግዚአብሔርን መልአክ አማልደው መልአኩን ምሕረት ያሰጡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መልአኩ የታዘዘውን ባለመፈጸሙ ኃይሉን አጥቶ በምድር ወድቆ ቀርቶ ነበር፡፡ ሁለት ልጆች በገዳሙ ውስጥ ሆነው በቅዳሴ ጊዜ ሲሮጡና ሲዘፍኑ መልአኩ ሁለቱንም ልጆች በሞት እንዲቀስፋቸው ተላከ፡፡ ከልጆቹም አንደኛው መልኩ እጅግ የተዋበ ድምፁም ያማረ ስለነበር መልአኩ አሳዝኖት "አንተንስ የፈጠረህ ይቅሰፍህ?" ብሎ ተወውና በማዳላት ሌላኛውን መልኩም ድምፁም የማያምረውን ልጅ ብቻ ቀስፎ ሊያርግ ሲል ኃይሉን ተነጥቆ በመሬት ላይ ወደቆ ቀረ፡፡ ሄዶም ከቤተልሔሙ በራፍ ላይ ወደቀ፡፡ በቀጣዩ ቀን ዲያቆኑ ለተልእኮ ሲሄድ እዚያ ወድቆ ቢያየው እጅግ ደንግጦ "ሰማያዊ ነህ ወይስ ምድራዊ? ከዚህስ ምን ትሠራለህ?" አለው፡፡ መልአኩም "በአፈጣጠሬስ ሰማያዊ ነበርኩ ነገር ግን ምግባሬ ምድራዊ አድርጎኛል" አለው፡፡ መልአኩም በመቀጠል "እባክህ ሄደህ አባ ሳሙኤልን ከበዓቱ ጥራልኝ" አለው፡፡ ዲያቆኑም አቡነ ሳሙኤልን ጠርቶለት አቡነ ሳሙኤል መጡና በሐዘን ውስጥ ሆነው "ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ?" አሉት፡፡ መልአኩም "አማልደኝ" አላቸው፡፡
❤ አቡነ ሳሙኤልም በእመቤታችን ሥዕል ሥር ሄደው እመቤታችንን እያለቀሱ በመጸለይ ተማጸኗት፡፡ እመቤታችንም ተገለጠችላቸውና "ሕዝቡን ሁሉ ሰብስበህ 41 እግዚኦታና 41 በእንተ ማርያም አድርሰህ ክንፍና ክንፉን ይዘህ ተንስዕ በስሙ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ወበስማ ለእግዝእትነ ማርያም ብለህ አንሳው" አለቻቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤልም እመቤታችን እንደነገረቻቸው አደረጉለትና መልአኩ ኃይሉ ተመለሰለት፡፡ ወዲያውም በማዳላት ሳይቀስፈው የቀረውን ልጅ ቀስፎ ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ያም መልአክ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከደብረ ቀልሞን ገዳም በረድኤት ተለይቶ አያውቅም፡፡
ማርቆስ እጅ ዲቁና ተሾሙ።
❤ እመቤታችን ማርያምም ለብፁዓዊ ሙሴ ልፋፈ ጽድቅ፣ ሰኔ ጎልጎታን፣ ባርቶስና ራዕየ ማርያምን ሰታቸዋለች። ወገባቸውን ከጠጉር በተሰራ መታጠቂያ ይታጠቁ ነበር። አቡነ ዘበሰማያትም በጀመሩ ጊዜ ሰባቱ ሰማያት ተከፍተውላቸው ከአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ጀምሮ ሁሉንም ቅዱሳን በግልጥ ያያሉ። ሲሰግዱ እንባቸው ደረታቸውና እግራቸውን እያራሰ በመሬት ይፈሳል። በዓለም ብዙ የዋሻ ቤተ ክርስቲን አንጸዋል። የሕንፃ ሥራ ከመደመራቸው በፊት 40ቀን ይጾማሉ። ሁለቱ መላእክት ቅዱስ ፍርክኤልና ቅዱስ ፍናኤል እየረዷቸው መቅደስን ያንጻሉ። የዋሻ ቤተ መቅደስ ስራ ጎን ለጎን መስቀልና ሌሎች ንዋየ ቅዱሳት ይሰራሉ። የሚሰሯቸው መቅደሶች ከፊሉ የሚታዩ ምዕመናን የሚገለገሉባቸው ሲሆን የቀሩት የማይታዩ ስውራን የሚገለገሉበት ነው።
❤ አቡነ ሙሴ ጵጵስና የተሾሙት በ12ቱ ሐዋርያት በአንድነት ነው። ዘመናቸውን ሁሉ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በመሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስን መንበር አጥነዋል። በድንግልናቸው በንጽሕናቸው የከበሩ 12ክንፍ የተጎናጸፉ ናቸው። ጥቂቶች ለማየት የታደሉትን ብሔረ ብፁዓን ሄደው አይተዋል።
❤ አቡነ ሙሴ በግብፅና በእስራኤል መካከል ሲካር በሚባል ቦታ ካገለገሉ በኋላ ጣዖታትን ለማሳፈር ወደ መቄዶንያ ሄደው ጣዖት አምላኪውን ንጉሥ ገሰጹት። ንጉሥ ተቆጥቶ አጥንታቸው እስኪሰበር ድረስ በብረት አስደብድቦ በብረት አልጋ ላይ አስተኝቶ እሳት አነደደባቸው። ቅዱስ ሚካኤልና ገብርኤል ግን ዳሰው ፈወሷቸው። በማግስቱ ወደ ፍርድ አደባባይ ቢወስዷቸው ምንም እንዳልሆኑ ንጉሡ በማየቱ በንዴት ሰውነታቸውን በሰይፍ አስቆራረጠ። ከሰውነታቸው ደም፣ ውሃ፣ ወተትና መዓር ወጣ። ጌታችንም አድኗቸው በስምህ የተማፀነውን መልካም ነገር አደርግታለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገባላቸው።
❤ በግብፅ አንስጣስዮስ ቴዎዶስዮስ ተብለው ሲነግሱ መላእክት የአባቱ የዳዊት መንግሥት ቅባት ቀቧቸው፤ የመንግሥት ልብስ አለበሷቸው፤ የመንግሥት ሥርዓትን ሁሉ ሰጧቸው። የጣዖታትን ቤት አፍርሱ ቤተ ክርስቲያንን ሥሩ በማለት ኅዳር12 አዋጅ ነጋሪን ላኩ። ጌታችን በግብፅ ተሶዶ ሳለ ለአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የተናገረው ትንቢት ተፈፀመ "ከልጅህ የሚወለድ በግብፅ ያሉትን ጣዖቶች አፍርሶ ሃይማኖትን ያጸናል" ብሎ ነበር። እዲሁም ቅድስት አርሴማ ሳትወለድ በስሟ የተሰየመውን ታቦት በግብፅ ያገኙና ያከበሩ ናቸው (ገድለ አርሴማ 7ኛ ተዓምር)።
❤ በግብፅ ደብረ ምጥማቅ ማርያም በመጀመሪያ ሰርተው የቀደሱት አቡነ ሙሴ ናቸው። በተጨማሪ ብዙ የህንጻ ቤተ ክረስቲያንና የዋሻ ቤተ ክረስቲያን አንጸዋል። እንደ ቅዱሳን ብዙ ድንቅ ተዓምር አድርገዋል። ለምሳሌ አውሬ ገድሏቸው ተጠራቅሞ የነበረ አፅም ላይ ጸልየው አራት ሺህ የሞቱ ሰዎችን ከሞት አስነስዋል። 40ዓመት በንግሥና ከቆዩ በኋላ ከብዙ ተከታዮቻቸው ጋር ወደ አስቄጥስ ገዳም በደመና ስጓዙ በበረሃው ተርበው ለወደቁት ወደ እግዚአብሔር ሲጸልዩ መና ወርዶላቸው መግበዋል አስቄጥስ ገዳም ሲደርሶ አቡነ መቃርስ ነበሩ የተቀበሏቸው፡፡ አቡነ ሙሴ በአስቄጥስ በአቡነ እንጦንስ ስም የመጀመርያውን ቤተ ክርስቲያን ሰርተው ከፈፀሙ በኋላ አቡነ እንጦንስንና አቡነ መቃርስ በምንኵስና ልብስ፣ በመላእክት አስኬማ፣ በቅንዓት፣ በቀሚስና በቆብዕ ላይ ለ40ቀን ጸልየው ጥር22 ተክለማርያም ብለው ሰይመው አመነኰሷቸው። በዚያውም አቡነ መቃርስ ከበታቻቸው ብፁዓዊ ሙሴን ሾሙ። በአስቄጥስ ብዙ ተከታዮቻቸውን አመንኵሰው ቀድሞ ወደ ሰሯቸው ቤተ መቅደሶች ይልኳቸው ነበር። የቀሩት ደግሞ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አብረዋቸው መጥተዋል።
❤ የኢትዮጵያ የመጀመርያው ጳጳስ አቡነ ሰላማ በማረፋቸው ሁለቱ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ ጳጳስ እንዲልኩላቸው ከእጅ መንሻ ጋር ወደ ግብፅ ላኩ። አቡነ አትናቴዎስ ፈቃደ እግዚአብሔር ጠይቀው አቡነ ሙሴ ከአስቄጥስ ገዳም ለኢትዮጵያውያን አባት እዲሆኑ አቡነ ሚናስ ብለው ሾሙ። ከሦስት ሺህ ልጆቻቸው ጋር ሆነው ብዙ ቅርስ ይዘው አባታችን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ሕዝቡ በደስታ ተቀበሏቸው። ብዙ መጽሐፍትን ከአረብኛ ወደ ግእዝ ቋንቋ ተርጉመው ጽፈዋል። ይጽፉበት የነበረው ብዕር አድሮ በማግስቱ ለምልሞ አብቦ ይገኛል። ቀለም ይበጠብጡበት የነበረው የቀንድ ዋንጫም ከመሬት ተጣብቆ ያገኙት ነበር። በእጃቸው ሲያላቅቁት ከመሬት ጠበል ይፈልቃል፣ በጠበሉም ህሙማንን ፈውሰውበታል።
❤ በኢትዮጵያ አምስት መቶ የዋሻ ቤተ ክስቲያን ያነጹ ሲሆን በአጠቃላይ በመላው ዓለም ከዐሥር ሺህ በላይ ቤተ ክርስቲያ ሰርተዋል፣ አንጸዋል (መለከት መጽሔት 2007 ዓ.ም)። በእንቁና በእብነ በረድ ከሰራቸው ቤተ ክርስቲያኖች መካከል በአራራት ደብር (ከምድር ጥፋት በኋላ የኖኅ መርከብ መጀመርያ ያረፈችበት) በጻድቁ ኖኅ ስም፣ አብርሃም ሥላሴን በድንኳኑ ባስተናገደበት ስፍራ በቅድስት ሥላሴ ስም፣ በሕንድ (በሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ መቃብር ቦታ) በቅዱስ ቶማስ ስም፣ በአርማንያና በፋርስ (በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋውን ባሳረፉበት ቦታ) በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም።
❤ በኢትዮጵያ በአቡነ ሙሴ ከታነጹት ቤተ ክርስቲያ ውስጥ የተወሰኑት፦
1.የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም (ባለ ሰባት መቅደስ ፎቅ)፣ የረፍታቸው ቦታ፣ በትረ ሙሴያቸውና የእጅ መስቀላቸው ያለበት (ሰሜን ወሎ ዳውንት)
2.ደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ላይ በምሥራቅ በኩል ስውር ቤተ መቅደስ (ድርሳነ፡ራጉኤል)
3.አእማድ ቅድስት ሥላሴ ገዳም (መቄት) እንደ አቡነ አሮን መንክራዊ ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማይገባው፣
❤ በመጨረሻ ብጹዕ አቡነ ሙሴ በቤተ ሚናስ ቤተ መቅደስ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ ገዳም መሰከረም 4 በዕለተ እሁድ አረፋ። ወርሃዊ በዓላቸው ወር በገባ በ4 ነው። በተለይ ጋብቻን ሚቀድሱ፣ ክህነት የሚባርኩ፣ መናንያንን የሚያጸኑ አረጋዊን አባት ናቸው። ከአባታች አቡነ ሙሴ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም ያሳተመው መጽሔት።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፰ (8) ቀን
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያኑ_ጻድቃን ለደብረ ድማሕ(ዲማ) ገዳም አበምኔት በፊትም በኋላም የሚያዩ ለሆኑ #ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_ለተክለ_አልፋ ለዕረፍት በዓል፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ማልኝ ብለው በአባይ ወንዝ ውስጥ ለዘጠኝ ዓመት ለጸለዩ #ለአቡነ_እስትፋሰ_ክርስቶስ_ለልደት በዓል፣ በክርስቶስ ለሚታመን የሰማዕታትንና የጻድቃንን በየዕረፍታቸው ቀን ለእያንዳንዳቸው ርኁባንን በማጥገብ የተራቆቱትን በማልበስ መታሰቢያቸውን ለሚያደርግ ለነበረ #ለቅዱስ_ገብረ_ማርያምና፣ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ኪሮስና ከግብጽ ለኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ተሾመው ለመጡ በኢትዮጵያ ብዙ የዋሻ ቤተ ክርስቲያንን ላነጹ #ለብጹዓዊ_ለአቡነ_ሙሴ_ዘድባ ለልደታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ስለ_አቡነ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ_ልደት፦ (የተወለዱበት) ቦታ ዳውንት ፀወን ዓባይ ይባላል። በአካባቢውም በገዳሙ አንፃር በሰሜን በኩል የእናታቸው አገር ደብረ ድባ የቄርሎስ ቦታ ይባላል የአባታቸውም አገር የእግዚአብሔር አብ ደብር አጠገብ ዳውንት ወይም ደብረ አስጋጅ ይባላል።
❤ አባታቸው ስም ቅዱስ መልአከ ምክሩ ሲሆን የእናታቸው ስም ቅድስት ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ደጋጎች እግዚአብሔር እንዳዘው በሕጉ ጸንተው ተስማምተው የሚኖሩ መልካም ሥራን በመሥራት እንደ ዘካርያስና እንደ ኤልሳቤጥ እውተኞች ነበሩ። እነርሱም ሁለት ደጋጎች ልጆች አሏቸው፤ የተባረከ መልካም ፍሬ በመጾምና በመጸለይ እግዚአብሔር የሚያገለግል በጸሎቱ ሰውን የሚጠቅም በጻድቃንም ዘንድ የተመረጠ ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ዘወትር ወደ እግዚአብሔር እና ወደ ድንግል ማርያም ይለምኑ ነበር እግዚአብሔር በዓይነ ምሕረት ተመለከታቸው ልመናቸውንም ሰምቶ አባታች አቡነ እስትንፋስ ክርስቶስ ሚያዝያ 8 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ8 ቀን ተወለዱ፤ በተወለዱበትም ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ጣዕም ባለው አንደበትም አመሰገኑ ዘጠኝ ጊዜም ሕፃናትን ለሚያናግሩ ገዢ ለሚሆኑ ለሥላሴ፣ ለእመቤታችንና ለመስቀሉ ሰገዱ፡፡
❤ የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን አወቁ። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ እስትፋሰ ክርስቶስ።
✝ ✝ ✝
❤ #ስለ_አቡነ_ኪሮስ_ልደት፦ በሮም አገር እግዚአብሔርን የሚፈራ ስሙ ዮናኒ የሚባል አንድ ሰው ነበር። በአባቱ ዙፋን ተቀምጠ ድንቅ ሥራንም ሠራ አባቱ ከሠራው ሥራም ምንም አላጐደለም ስድሳ ዓመት ኖረ ስሙ አብያ የሚባል ልጅም ወለደ በክብርም ዐረፈ።
❤ አብያም በአባቱ ዙፋን ነገሠ አባቱ ከሠራው መልካም ሥራ አንድም ስንኳን አላጐደለም። የሚስቱም ስሟ ሜናሴር ይባል ነበር ሠላሳ ዓመትም መካን ሆና ኖረች። ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ ሜናሴርም ፀነሰች ሁለት ልጆችም ወለደች ታላቁን ቴዎዶስዮስ ታናሹን ዲላሶር አለችው። በመልካም አስተዳደግ አሳደጓቸው ከዚህ በኋላ አባታቸው አብያ በክብር ዐረፈ።
❤ ቴዎዶስዮስም በአባቱ በአብያ ዙፋን ነገሠ። ከሦስት ዓመት በኋላ ዲላሶር ቴዎዶስዮስን "ከአባቴ ገንዘብ ድርሻዬን ስጠኝ" አለው። ቴዎዶስዮስም "ወንድሜ ሆይ የእኔ የሆነው ሁሉ የአንተ ነው የአንተም የእኔ ነውና ከእኔ በታች የፈቀድከውን የሚከለክልህ ማነው?" አለው። "ልጅ ስለሆንክ ግን ፈጽሜ ከፍዬ አልሰጥህም" አለው በዚህም ምክንያት እርስበርሳቸው ተጣሉ። ዲላሶርም በሌሊት ተነስቶ ተሸሽጐ ወጥቶ አድርስ ወደ ሚባል ተራራ ሄደ። በዚያም ትንሽ ዋሻ አግኝቶ እስከ ዐሥር ቀን በውስጧ ተቀመጠ። መንፈስ ቅዱስም "ኪሮስ ሆይ ብሎ ጠርቶ ለብዙዎች አባት ትሆናለህ በቃልህም እንክርዳድ ኃጢአት ይነቀላል ጽድቅ ስንዴ ያፈራል። አሁንም ከዚህ ተነስተህ ወደ ፊትህ የአንድ ቀን ጐዳና ሒድ። በዚያም ባሕታዊ መነኵሴ ታገኛለህ ከእርሱም የምንኵስናን ልብስ ትለብሳለህ" አለው። ይህን ብሎት ከእርሱ ተሰወረ። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ኪሮስ።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ተክለ_አልፋ_ዘደብረ_ድማህ (ዲማ) ፡- ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ አልፋ ልደታቸውም ዕረፍታቸውም ታኅሣሥ 8 ነው፡፡ "ተክለ አልፋ" ማለት ለዘለዓለም የሚኖር ድንቅ ሥራ ማለት ነው፡፡ ጻድቁ ቀደምትና ዓበይት ከተባሉት ከ72 ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በደብረ ድማህ አበምኔትነት ተመርጠው ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ የሴቶችን ማኅፀን የምታበላሸውንና መካን የምታደርገውን "እመ ሙላድ" የተባለችውን ዛር አቡነ ተክለ አልፋ በመቋሚያቸው እንደ አውሬ አባረው አጥፍተዋታል፡፡ እርሷም እንደ ሰው ትልካ ሄዳ ማኅፀን የምታጠፋ ነበረች፡፡
❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ተክለ አልፋ ሹመትን አልፈልግም ብለው በጸሎት ብቻ ተወስነው የኖሩ በዲማ ትልቅ ክብር ታላቅ አባት ናቸው፡፡ በተወለዱበት ዕለት ታኅሣሥ 8 ቀን ሲያርፉ ማረፋቸውን መቁዋሚያቸው ናት በሰው አንደበት "አባታችን ዐረፉ" ብላ ለመነኮሳቱ የተናገረችው፡፡ ጻድቁ የጠቀበሩት በተሾሙበትና ለ35 ዓመታት ባገለገሉበት በዚያው በዲማህ (ዲማ) ነው፡፡ ከአባታችን ከአቡነ ተክለ አልፋ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕቱ_አባ_ገብረ_ማርያም፡- ይህም ቅዱስ የሰማዕታትንና የጻድቃንን በየዕረፍታቸው ቀን ለእያንዳንዳቸው ርኁባንን በማጥገብ የተራቆቱትን በማልበስ መታሰቢያቸውን የሚያደርግ ነው፡፡ እንዲህም ባለ ሥራ ላይ እያለ ይን ጊዜ እስላሞች ወደ ሸዋ አገር መጡ፡፡ እርሱም ያማሩ የክህነት ልብሶቹን ለብሶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ጸሎትን ጸለየ ሲጸልይም እስላሞች ወደርሱ መጥተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ አባት በቅዱስ ገብረ ማርያም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 8 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #ብፁዕ_አቡነ_ሙሴ_ዘድባ፦ በአባታቸው የእቤታችን ጠባቂ የአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የልጅ ልጅ ሲሆኑ፤ በእናቸው በኩል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር በቃና ዘገሊላ ሰርግ የተገኘችበት የዶኪማስ የልጅ ልጅ ናቸው። የአባታቸው ስም ቅዱስ ዮስጦስ ሲባል፤ የእናታቸው ስም ቅድስት ጵስርስቅላ (ሶልያና ማርያም) ይባላል።
❤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት ታኅሣሥ 8 ቀን ተወለዱ። በዚህች ቀን ከእናታቸው እቅፍ በመውረድ "ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን፤ ከጨለማ ወደ ብርርሃን ላወጣኸኝ" ብለው ፈጣርያቸውን አመስግነዋል። በ40ኛው ቀን የጌታ ሐዋርያት ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ፊሊጶስና እንድርያስ ሆነው ጥር 17 ቀን ክርስትናን አቡነ ሙሴን አነሱዎቸው። በ3 ዓመታቸው ወላጆቻቸው ለቤተ ከክርስቲያን ሰጧቸው። ቅዱስ ፋኑኤልና ቅዱስ ዮናኤል ሕብስት ሰማያዊ እያመጡ ይመግቧቸው ነበር። ከዚህ በኋላ መምህራቸው ዝክረ ጻድቅ ብሉያትንና ሐዲሳትን አስተማራቸው። በወንጌላዊው በቅዱስ
ከዚህም በኋላ ወደ ዱር ሔዱ።
❤ ይህም አባ ማቴዎስ የዜናው መሰማት በቦታ ሁሉ እስከመላ ድረስ ተአምራትን እያደረገ ኖረ በየአይነቱ በሆነ ደዌ የተያዙትን ያመጡለታል። እርሱም በላዩ በአደረች በእግዚአብሔር ኃይል ይፈውሳችዋል።
❤ ከተአምራቶቹንም አንዱን በአንዲት ቀንም ጋጌን ያደረበት ዲዳ ሰውን ወደ እርሱ አመጡ ቅዱን ማቴዎስን በአየው ጊዜ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሰውየውም ከምድር ላይ ጣለው ቅዱሱም በዘይት ላይ ጸለየ በመስቀል ምልክትም አማትቦ ቀባው በዚያንም ጊዜ ድኖ አዕምሮው ተመለሰ የሚሰማና የሚናገርም ሆነ ደስ ብሎትም ወደ ቤቱ ሆደ። ጨዋዎችም በመጡ ጊዜ ማዕድ ያቀርብላደውና በሰላም በፍቅር ያሰናብታቸዋል እነርሱም ለበረከት እያሉ ጥቂት ቁራሽ ወደ ቤታቸው ይመስዳሉ በበሽተኞችም ላይ በአደረጉ ጊዜ ወዲያውኑ ድነው እግዚአብሔር ያመሰግኑታል።
❤ ሁለተኛ ተአምር በአንዲትም ዕለት ደምግባቷም ያማረ ጋጌንም ያደረባትም ብላቴና ወደ እርሱ አመጡ እርሷ ብዙ ጊዜ ልብሷን ትቀዳለች ወደ እርሷም መቅረብ የሚችል የለም ወላጆቿም በታላቅ ኃዘን ውስጥ ይኖራሉ ቅዱስ አባ ማቴዎስም በላይዋ ጸለየና ክብር ይግባውና ኢየሱስ ክርቶስም ዘይቱን ቀብቶ አዳናት።
❤ ሦስተኛ ተአምር በአንዲት ዕለት እጅግ በከፋችና ታላቅ በሆነች ኃጢአት ላይ የወደቀች ኃጢያተኛ ሴት ወደ እርሱ አመጡ እርሷ ጸንሳ የመውለጀዋ ጊዜ የደረሰ ነው በቀንና በሌሊትም በምጥ ሕማም ትሰቃይ ነበር አባ ማቴዎስም "ልጄ ሆይ ኃጢአትሽን እመኚ በእግዚአብሔር ፊት አትዋሺ" አላት እርሷም እንዲህ አለችዉ "እኔ ከሁለት ወንድማማቾች ጋር እነርሱ ሳያውቁ ሳመነዝር ኖርኩ በጸነስኩም ጊዜ ሕጻኑን በመርዝ አውጥቼ ለውሾች ሰጠሁት" አባ ማቴዎስም በሰማ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ በዚያንም ጊዜ ለሌሎች መቀጣጫ ትሆን ዘንድ ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻት።
❤ የዚህም አባት ተአምራቶቹ ብዙ ናቸው ተነግሮ አያልቅም በአንዲትም ቀን በበረሀ ውስጥ ሲጓዝ ጅብ ልብሶቹን በጥርሶቿ ይዛ ሳበችውና በሠንጣቃ ገደል ውስጥ የወደቁ ልጆቿን አሳየችው በአወጣላትም ጊዜ ሰገደችለት እግሮቹንም ላሰች።
❤ ከዚህም በኋላ ዕረፍቱ ሲቀርብ በታኅሣሥ ሦስት ቀን ወደ ሠርግ እንደሚጠራው ራእይን አየ ይኸውም የቅዱሳን አባቶች የአባ እንጦንስ የአባ መቃርስ የአባ ጳኲሚስ የአባ ቴዎድሮስ የአባ ሙሴ ጸሊም የአባ ሲኖዳ የአንድነት ተድላ ደስታ ወዳለበት ነው። እነርሱም በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ከእኛ ጋር ትኖር ዘንድ ወደእኛ መምጣትህ መልካም ነው" አሉት ብዙ አትክልቶችና ዙፋኖች ወዳሉት ታላቅ አዳራሽም ደጅ አደረሱት ማቴዎስ ይገባ ዘንድ የአዳራሹን ደጆች ክፈቱ የሚልንም ቃል ሰማ ከዚህም በኋላ በታኅሣሥ ሰባት ቀን ዐረፈ ሦስት አክሊላትንም ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 7 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ሌሊተ ተዛዋዕኩ ምስለ ልብየ ወአንቃሕክዋ ለነፍስየ። ቦኑ ለዓለም ይገድፍ እግዚአብሔር። ወኢይደግምኑ እንከ ተሣህሎ"። መዝ 76፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 6፥10-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥10-15 እና የሐዋ ሥራ 16፥16-25። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 15፥20-24 ወይም ማር 16፥15-ፍ.ም የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፯ (7) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት_አራዊቶች_ጋር_ይኖር ለነበረ ጅቦች ሳይቀር ይሰግዱለት ለነበረ ለታወቀች እስዋን ለተባለች ገዳም አበምኔት ለሆነ ለሚጋደል #ለቅዱስ_አባት_አባ_ማቴዎስ_ለዕረፍት_በዓልና በአባ መቃርስ ገዳም በደብረ ሲሐት ለሚኖር #ለአባ_ዳንኤል_ለዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦#ከብፅዕት_ዲዮጥርስ ከመታሰቢያዋ ረድኤትና እግዚአብሔር አምላክ በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዳንኤል፦ ይህም አባት በአባ መቃርስ ገዳም በደብረ ሲሐት የሚኖር ነው። አባ ዳንኤልም ስሟን እንጣልዮስ አሰኝታ የነበረች ንግሥት በጥሪቃን የገነዛት ነው እርሷም ከሞቷ በኋላ እንጂ ሴት እንደሆች አልታወቀችም ነበር።
❤ በአንዲት ቀንም ወደ እስክንድርያ አገር ከረድኡ ጋር ሲጓዝ ስሙ ምህርካ የሚባል እብድ አገኘ ብዙ እብዶችም ይከተሉታል ለአገሩ ሰዎችም በእውነት ያበደ ይመስላቸው ነበር አባ ዳንኤልም እጁን ይዞ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ወስዶ ትሩፋቱን ተጋድሎውን ነገረው እንዲነግራቸውም በአማሉት ጊዜ ከዝሙት ጦር ለመሸሽ ራሱን እብድ እንዳስመሰለ ነገራቸው ሰምተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት።
❤ በአንዲትም ዕለት ወደ አንዲት አገር ደረሰ በዚያም አውሎጊስ የሚባል ለድኆች የሚራራ እንግዳም የሚቀበል ደንጊያ በመውቀር የሚኖር ሰው አገኘ እርሱንም ተቀብሎ በደስታ አሳደረው መልካም ሥራውንም በአየ ጊዜ ድኆችን የሚረዳበት ገንዘብን ለአውሎጊስ ይሰጠው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ስለርሱ ለመነ ጌታችንም በሕፃን አምሳል ተገለጠለትና "ገንዘብ ባገኘ ጊዜ ጣባዩን እንዳይለውጥ አንተ ትዋሰዋለህን?" አለው አባ ዳንኤልም "አዎን እዋስዋለሁ" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ አውሎጊስ በድስት የመላ ወርቅን አግኝቶ ያንን ይዞ ወደ ንጉሥ ሔዶ የጭፍራ አለቃ ሆኖ ተሾመ ጠባዩንም ለወጠ። ጠባዩንም እንደለወጠ አባ ዳንኤል ሰምቶ ልመክረውና ሊገሥጸው ሔደ የአውሎጊስ ወታደሮች ለሞት እስኪደርስ ድረስ ደበደቡት በዚያም እያዘነ ሳለ ያ ሕፃን ታየው አባ ዳንኤልንም "ለምን በሌላ ሰው ነገር ገባህ" ብሎ እንዲሰቅሉት አዘዘ። ከዚህም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መጥታ ለሕፃኑ ሰገደች እግሮቹንም እየሳመች ስለ አባ ዳንኤል ለምና ከስቅላት አዳነችው።
❤ ከዚህም በኋላ ሌላ ንጉሥ በነገሠ ጊዜ አውሎጊስ ሊገለው ፈለገው ያን ጊዜ አውሎጊስ ሸሸ ወደ አገሩም ደርሶ ወደ ቀድሞ ሥራው ተመለሰ። በአንዲት ቀንም በሌሊት በበረሃ በጨረቃ ብርሃን ሲጓዝ በተራራ ላይ ተቀምጣ ሴት አገኘ ጠጉሯም ሥጋዋን ሁሉ ሸፍኖአል እየተጋደለች ሠላሳ ስምንት ዓመት የኖረች ናተ ምጢርዋንም ሁሉ ነግራው ከዚህ በኋላ ዐረፈች።
❤ ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን የሊዮን ደብዳቤ ሰውዎች አምጥው በሕዝብ ፊት አነበቧት አባ ዳንኤልም ዘሎ ቀደዳትና "የኬልቄዶን ሃይማኖት የተወገዘ ነው" አለ ወታደሮችም አይተው ደብድቡት ከገዳሙም አሳደዱት።
❤ በአንዲት ቀንም አባ ዳንኤል ከደናግል ገዳም ደርሶ ደጁን አንኳኳ አባ ዳንኤልም እንደሆነ አውቀው ከፈቱለትና በደስታ ተቀበሉ። ከእነርሱም አንዲቷ እራሷን እብድ አስመስላ በደጅ የምትተኛ አለች ስለ እርሷም እመ ምኔቷን ጠየቃት እርሷም "እብድ ናት" አለችው። እርሱም መስተጋድል ቅድስት ሴት እንጂ እብድ እንዳልሆነች ነገራት። እብድ የተባለችውም በሌሊትም ተነሥታ "የከበራችሁ እህቶቼ ስለ አሳዛንኳችሁ ይቅል በሉኝ" ብላ ጽፋ ያንን ትታ ታጣች ደናግሎም እጅግ አዘኑ ተጸጸቱም።
❤ በውስጡ ብዙ ደናግል የሚኖሩበት ገዳም ነበር መዝጊያውም የጸና ነው። ገንዘባቸውን ይበረብሩ ዘንድ ሰይጣን ወንበዴዎችን በላያቸው አስነሣ የወንበዴዎችም አለቃ በመራቀቅ በራሱ ላይ ቆብ አድርጎ በአባ ዳንኤል ለብሶ ደጃፋቸውን ሔዶ በማንኳኳት "አባ ዳንኤል ነኝ" አለ አይተውም ከፈቱለት በደስታም ተቀበሉት እግሩንም አጠቡትና ስለ በረከት የእግሮቹንም እጣቢ በየፊታቸው እረጩ ከውስጣቸው አንዲት ዕውር ነበረች ውኃው ሲነካት አይኖቿ በሩላት ደናግሉም "አንተ አባ ዳንኤል ንዑድ ክቡሩ ነህ" አሉት የሽፍቶች አለቃ አይቶ ተጸጸተም ከአባ ዳንኤል ዘንድ መንኲሶ የሚጋደል ሆነ።
❤ ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ነገረው ጥቂት ጊዜም ታመመ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየና ታኅሣሥ 7 ቀን በሰላም ዐረፈ። እግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዳንኤል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ማቴዎስ፦ ይህም አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ በፈሪሃ እግዚአብሔር ጸንቶ ያደነገ ነው ከገዳማት በአንዱ መንኲሶ በጾም በጸሎት የሚጋደል ሆነ በገዳሙም ውስጥ ለራሱ መኖርያ ሠራ ደቀ መዛሙርቱ አባ ሰራብዮንና አባ ኅድራ ሥራውንና ተጋድሎውን ተአምራቱን እንደተናገሩቱ መረብን በመሥራት ሽያጩ ለድኆች ይመጸውታል።
❤ እነርሱም እንዲህ ብለው ተናገሩ በአንዲት ዕለትም ከማደሪውም በውጪ ተቀምጦ ሳለ በማደሪያውም አንዱ ከሌላው ጋር እንዲነጋገር ሆኖ ቃልን ሰማን በገባንም ጊዜ ከእርሱ በቀር ያገኘነው የለም። "አባታችን ሆይ በውጪ ሳለን ከአንተ ጋር ሰው እንዲነጋገር ድምጽ ሰምተን ነበር በገባን ጊዜ ከአንተ በቀር ያገኘነው የለም" አልነው። በብዙ ትሕትና እንዲህ አለን "ልጆቼ ሆይ የምትጠብቀኝን የሞት ፃዕርና ስቃዮችን ለነፍሴ በማሳሰብ የኃጢያቴን ብዛ አስቤ ከራሴ ጋር ተነጋገሩኩ። ለድኃ ማቴዎስ ወዮለት ንጽሕናን ቅድናን በለበሱ መላእክት የጻድቃንና የሰማዕታት ጉባኤ አንድነት በአለበት በልዑል እግዚአብሔር ፊት ራቁቱን ያቆሙታልና እንዲህ አድርገው የኃጥኣንን ሥቃይ የጻድቃንን መልካም ዋጋ ለልጆቹ አስተማራቸው።
❤ ቅዱስ ማቴዎስ በሠራት ገዳም ውስጥ ጸሎትን ተጋድሎን አገልግሎትን በማድረግ ጸንቶ ኖረ ገዳሙም በአባ ጳኲሚስ ስም አከበረ እርሷም የታወቀች ሰሌን ያለባት ተራራ ነች። ርኩሳት የሆኑ ረቂቅ ሰይጣናት በቀንና በሌሊት የሚያስፈራሩት ሆኑ በየአይነቱ በተለያዩ መልክ ፊት ለፊት እያያቸው እርሱ በፊቱ ይሮጣሉ በኋላ ይከተሉታል እርሱ አይፈራቸውም እጆቹን ዘርግቱ በመስቀል ምልክት ሲያማትብ በዚያን ጊዜ በንፋስ ፊት እንዳለ ጢስ ይበተናሉ።
❤ በአንዲት ዕለትም ጥቂት እንጀራና ውኃ በመንቀል ከገዳሙ ውስጥ ይዞ በበረሃ ውስጥ ወደአለች ዋሻው እንዲሆዱና እርሱ በማግሥቱ እስኪመጣ በዚያ እንዲጠብቀው ረድኡን ሰራብዮንን አዘዘው። ሰራብዮንም ወደ ዋሻው ሲደርስ ሁሉት አራዊት በውስጡ ተኝቶ አገኘ በርቶ በሩን ዘግቶ ከዐለት ቋጥኝ ድንጋይ ወጣ። ከዚህም በኋላ አባ ዳንኤል የዳዊትን መዝሙር እያነበበ መጣ ረድኡንም አይቶ ፈገግ ብሎ ሳቀ "ሰራብዮን ሆይ እኔ ወደ አንተ እስክመጣ ለምን ወደ ዋሻው ውስጥ ለምን አልገባህም" አለው። እርሱም ረድኡ "ሁለት ታላላቅ አውሬዎች ተኝተው ስላገኘው እነርሱን ፈርቼ አልገባሁም" አለው። ንጹሕ ነፍስ ያለው የዋህ የሆነ የተመሰገነ "ልጄ እመነኝ እኔ ከእነርሱ ጋር ስኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሆነኝ ያሳደግኋቸው እኔ ነኝ ይህንንም እንጀራና ውኃ እንድታመጣ ያዘዝኩህ ለእነርሱ ነው" አለው። ከዚህም በኋላ በሩን በከፈተ ጊዜ እነዚያ አውሬዎች ወደ እርሱም ወጥተው ቅዱስ አባት ማቴዎስን እግሮቹን ላሱ ባልጆሮቹም ሆነውት በታላቅ መለማመጥ ተገዙለት ያንንም ውኃ በገዳው ላይ አፈሰሰላቸው ጠጡ እንጀራውንም በሉ
❤ በዚህም ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱ ተነሥቶ ፈጥኖ ሔደ ያንንም ሰው አግኝቶ ያዘው "የክርስቲያን ወገኞች እዘንላቸው ራራላቸው አምላክ የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደተ ገለጸችለትና እርሱን እንዳመለከተችሁ ነገረው" እርሱ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱን ሰግዶ "አባቴ ሆይ እኔ ኃጥያተኛ በደለኛ ነኝና ይቅርታ አድርግልኝ ይህን የምትለኝን ላደርገው የማልችል ነኝ ነገር ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎት በእናንተ በከበረች ጸሎትህ የክርስቲያ ወገኖችእንድትረዳችሁ ይሁን። እኔንም ለማን እንዳትገልጠኝ እለምንሃለሁ እኔ የዚህ ዓለም ክብር መሸከም አልችልምና ነገር ግን የምልህን አድርግ አንተም ንጉሡ ይነሣልኝ የሚልህ ተራራ ትይዩ ካህናቶችና ከሕዝቡ ጋር ቁም ወንጌሎችን፣ መስቀሎችን፣ ማዕጠንቶችን፣ የሰም መብራቶችን ያዙ ንጉሡም ከነሠራዊቱ በአንዲት ዳርቻ ይቁም እኔም ማንም እንዳውቀኝ ከሕዝቡ ጋር ተደባልቄ በፊትህ እቆማለሁ አርባ አንድ ጊዜ ኪራላይሶን እያላችሁ በመጮህ ወደ እግዚአብሔር ማልዱ ይኸውም አቤቱ ክርስቶስ ማረን ራራል ይቅር በለን ማለት ነው። ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ዝም እንዲሉ እዘዛቸው እኔም ያንጊዜ ስሰግድ አንተም ስገድ እንዲህም ሦስት ጊዜ አድርገህ በዚህ ተራራ አንጻር ማሕያዊ መስቀል ምልክት በየስግደትህ አማትብ" አለው።
❤ ሊቀ ጳጳሳቱ ይህ ሰምቶ ለወገኖቹ በማሰማት አስገነዘባቸው በዚህም ተራራ በሌላ ገጽ ከሠራዊቱ ጋር ወጥቶ እንዲቆም ለንጉሡ ነገረው ሊቀ ጳጳሳቱ እንደነገራቸው ሁሉም ወጥተው ቆሙ ከዚህ በኋላ ሊጸልዩ ጀመሩ አርባ አንድ ጊዜ አቤቱ ክርስቶስ ማረን አሉ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ሦስት ጊዜ ሰገደ ሲነሳም ወደዚያ ተራራ አማተበ በዚያ ጊዜ ተራራ ከቦታው ተነቅሎ በአየር ላይ ተንሳፈፈ ሊቀ ጳጳሳቱ ሕዝቡ ሲሰግዱ ያ ተራራ ወደ ቦታው ይወርዳል ከሰገዱበትም ሲነሱ ከቦታው ተነቅሎ ወደ አየር ወጥቶ ይንሳፈፍል እንዲህም ሦስት ጊዜ አደረገ ሕዝሙ ሁሉ ይህ ድንቅ ሥራ አይተው አደነቁ ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት ሊቀ ጳጳሳቱ አባ አብርሃምንም ፈሩት ንጉሡሙ ወደ ርሱ አስቀርቦ ታላቅ ክብር አከበረው እንህም አለው "የምትሻው ለምነኝ ከእኔ ተመኝ ምን ምንም አልከለክልህም" ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱ ግድ ለምነኝ በለው ጊዜ "አብያተ ክርስቲያን ልሠራ እሻለሁ ይልቁን የሰማዕቱን ቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን በምስር አገር ልሰራ እሻለሁ" አለው። እንደወደደውም ይሰራ ዘንድ አዘዘለት ከቤተ መንግሥቱም ብዙ ገንዘብን አቀረበለት ሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምም "በምድር ላይ እግዚአብሔር እድሜህን ያርዝም መንግሥትህ ያጽና እኔ ገንዘብ አልሻም" አለው። ይህንንም በአለው ጊዜ ንጉሥ አደነቀ የዚህን ዓለም ገንዘብ መናቁን እጅግ ወደደው።
❤ ከዚህም በኋላ የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ሥራዋ እስኪፈጸም ሌሎችም በግቡጽ አገር የተሰሩ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያኖች እስቲሠሩ ንጉሡ በፈረስ ተቀምጦ ከሠራቱ ጋር በመሆን ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር አብሮ ለሥራ ይሰለፍ ነበር የሚቃወሙ ክፉዎች ሰዎች የተሠራውንም ያፈርሱ ዘንድ የሚሹ ስለነበር ስለዚህ ንጉሥ አጽንቶ አስጠበቀ። ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ እግዚአብሔርም አገልግሎ በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ስድስት ዓመት ከስድስት ወር ከኖረ በኋላ በዚች ቀን ታኅሣሥ6 ዐረፈ። በዚህም አባት በገድሉ መጽሐፍ ያ ስለ ዕቊባቶቹ ያወገዘው ጸሐፊ በመርዝ ገደለው የሚል አለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ አብርሃም ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 6 ሰንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለከ_ለአብርሃም_ነጋዲ። ወሊቀ ጳጳሳት ዓዲ። ሶበ ዐጸወ ቅድሜከ በግዝፈተ ልብ አባዲ። ሰምዖ ቃለ ግዘት እምልሳንከ ነዳዲ። መድረከ ኆኅቱ ተሠጥቀ ለብእሲ ከሀዲ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የታኅሣሥ_6።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ይኄይስ ሕጻጥ ዘበጽድቅ። እምብዙኅ ብዕለ ኃጥአን። እስመ ይትቀጥቀጥ ኃይሎሙ ለኃጥአን"። መዝ36፥16-17። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥34-ፍ.ም።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወእለመኒ ፈለሱ አድባር ውስተ ልበ ባሕር። ደምፀ ወተሐምጉ ማያቲሆሙ። ወአድለቅለቁ አድባር እምኃይሉ"። መዝ 45፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥12-21፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-9 እና የሐዋ ሥራ 5፥1-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 17፥14-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት አርሴማ በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፮ (6) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት ተራራ ላፈለሰ ለእስክንድርያው ስልሳ ሁለተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአቡነ_አብርሃም_ሶርያዊ_ለዕረፍት_በዓል፣ ከእርሱ ጋር ተራራን አብሮ ላፈለሰው #ለቅዱስ_ስምዖን_ጫማ_ሰፊ ለመታሰቢያ በዓሉ፣ #ለታላቋ_ሰማዕት_ለቅድስት_አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ ለከበረችበትና ለሥጋዋ ፍልሰት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ ከእርሷ ጋር ለተገደሉ #ሃያ_ሰባት_ደናግል_ለሥጋቸው_ፍልሰት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቀሲስ ሰማዕት #ከቅዱስ_እንጣልዮስ፣ ከቅዱሳን አረሚ ከነበረ #ከኤልያስ_ከበጥልስ_ከሱርፍት_ከማርያ፣ #ከሚካኤል_ከይልሰውል_ከተለሜዎስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #በዚችም_ቀን_የድንግሊቱ_ቅድስት_አርሴማ ቤተ ክርስቲያኗ #የከበረችበትና_የሥጋዋ_ፍልሰት የሆነበት ከእርሷ ጋር የተገደሉ #የሃያ_ሰባት_ደናግልም የሥጋቸው ፍልሰት የሆነበት ነው። ይችንም ቅድስት አርሴማኔ ንጉሥ ድርጣድስ "ይህን ታላቅ ክብር ካለው ከእኛ ጋር መኖርን እምቢ ያልሽ ልብ የለሽምን" አላት እርሷም "በሰማያት ያለው ይበልጣል እጅግም ይሻላል" አለችው ወደ ጐን ወስደው ልብሷን ገፈው አንገቷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የደናግሉንም ሁሉ አንገት እንዲቆርጡ አዘዘና ተቆረጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አርሴማና በደናግሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_አብርሃም_ሶርያዊ፦ ይህም አባት ከምሥራቅ አገር የክርስቲያ ወገን ነው እርሱም ብዙ ገንዘብ ያለው ነጋዴ ነበር እየነገደም ብዙ ጊዜ ወደ ምስር አገር ደረሰ ከዚህም በኋላ በውስጧ የሚኖር ሆነ ከእርሱም ለድኆችና ለችግረኞች ርኅራኄ ማድረግና ብዙ ትሩፋቶች ተገለጡ። የደግነቱና የትሩፋቱ የአዋቂነቱም ዜና በተሰማ ጊዜ አባቶች ኤጲስቆጶሳት የአገር ታላላቆችና ምሁራኖች በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተስማሙ።
❤ በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ከዚህም በኋላ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጥቶ የሊቀ ጵጵስናውን ሥራ መሥራት ጀመረ። በሹመቱም ወራት ክፉ ልማድን ሁሉ አስወግደ ኤጲስቆጶሳቱንም ሰዎች ዕቁባቶቻቸውን እንዲተው አወገዛቸው ውግዘቱንም በሰሙ ጊዜ ሁሉም ፈርተው ክፋ ልማዳቸውን ተው ወደርሱም መጥተው ከእግሮቹ በታች ወድቀው በደላቸውን ያስተሰርይላቸው ዘንድ ለመኑት።
❤ የንጉሥ ጸሐፊ ከሆነ ከአንድ ሰው በቀር ቃሉን ያስተሐቅር ዘንድ የደፈረ ማንም የለም። ይህም ልዑል እግዚአብሔርን ስለ ማይፈራ የዚህን የቅዱስ አባት ግዝትን አላሰፈራም ይህ አባት ግን ስለ ራሱ ድኅነት ብዙ ጊዜ ለመነው ከክፋቱ ተመልሶ ከመቅሠፍት ይድንም ዘንድ ገሠጸው መከረውም ሰውዬው ግን አልሰማውም። ይህም አባት ማስተማሩንና መገሠጹን ስልችቶ አልተወውም ለሌሎች ዕንቅፋት እንዳይሆን ስለዚህ ወደዚያ ሰው ቤት ሔደ የሊቀ ጳጳሳቱንም መምጣት በሰማ ጊዜ ደጁን ዘጋ ይህ አባትም ደጁን እያንኳኳ ሁለት ሰዓት ያህል ቆመ ከዚህም በኋላ "የዚህ ሰው ደሙ በራሱ ላይ ነው እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ" ብሎ የእግሩን ትቢያ አራግፎ ተመለሰ። ወዲያውኑ ከዚህ ሰው ላይ ምልክትን ጌታችን ገለጸ ከደንጊያ የተሠራ የቤቱ መድረክ ከሁለት ተከፈለ ይህ ፈጽሞ ድንቅ ነውና ከዚህ አባት ግዝት የተነሣ ጠንካራው ዐለት ተሠነጠቀ ለመለም የነበረ የሰውየው ልብ ግን ከዐለት ጠነከረ።
❤ ዳግመኛም ድንቅ ምልክትን እግዚአብሔር በዚህ ሰው ላይ አደረገ ከድኆች ሁሉ እጅግ የባሰ ድኃ ሁኖአልና ከሹመቱም በጒስቊልናው ሻሩት ከገንዘቡም አንዲት መሐልቅ እንኳ አልቀረለትም ደግሞም ሥጋውን ጭንቅ በሆነ ደዌ ቀሠፈው እጆቹና እግሮቹም ተቆራርጠው በክፉ አሟሟት ሞተ ለሁሉም መቀጣጫ ሆነ ብዙዎች ከኃጢአተኞች ውስጥ ንስሐ ገቡ።
❤ በዚህም አባት ዘመን ለምስር ንጉሥ የጭራ አለቃ የሆነ አንድ ሰው ነበር እርሱም ወደ እስልምና ሕግ የገባ አይሁዳዊ ነው ለዚህም የጭፍራ አለቃ አይሁዳዊ የሆነ ወጃጅ ነበረው ወደ ንጉሡም አብሮት እየገባ ከንጉሥ ጋር ይነጋገራል ከጭፍራው አለቃው ጋር ወዳጅ ስለሆነ በንጉሥ ባለሟልነት በአገኘ ጊዜ ንጉሡን እንዲህ አለው "ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ሊቀ ጳጳሳትን እንድታስመጣውና በፊትህ እንድከራከረው ተመኛቻለሁ" ንጉሡም ይህን አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምን አስመጣው ከእርሱም ጋር የመቅፋዕ ልጅ የእስሙናይም ኤጲስቆጶስ አባ ሳዊሮስ ነበር ይህ አይሁዳዊ ከእርሳቸው ጋር በተከራከረ ጊዜ ረትተው አሳፈሩት ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱንና ከእርሱር ጋር ያሉት ታላቅ ክብርን አከበራቸው። በፍቅር በሰላምም ወደ ቤተቻው አሰናበታቸው።
❤ የጭፍራ አለቃና ወደጃጁ አይሁዳዊው አፈሩ ሊቀ ጳጳሳቱን የክርስትያን ወገኖችንም የሚወድቁበትን የሚፈልጉ ሆኑ በአንዲት ቀንም የጭፍራ አለቃ ወደ ንጉሥ ገቡቶ "ጌታዬ ንጉሥ የማስረዳህ አለ እሊህ ክርስቲያኖች ሃይማኖት የላቸውም እኮን ወንጌላቸው የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል ሃይማኖት ካላችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደዚያ ሄድ ብትሉት ይሆዳል የሚሳናችሁ የለም" ይላልና አለው። ንጉሡም ይህ በሰማ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሳት አባ አብርሃምን ልኮ አስመጣውና "ወንጌላችሁ የሰናፍጭ ቅጣት ታህል ሃይማኖት ካላችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደዚያ ሒድ ብትሉት ይሆዳል ይላል ስለዚህ ነገር ምን ትላላችሁ" አለው። ሊቀ ጳጳሳቱም "እውነት ነው የከበረ ወንጌል ይላል" አለው። ንጉሡም መልሶ እንዲህ አለው "እነሆ ይህ ሃይማኖት ያላችሁ እናንተ የብዙ ብዙ ናችሁ ከእናንተ ውስጥ ይህ ምልክት የሚገልጽ አንድ ሰው ልታመጣል እሻለሁ አለዛም ለክርስቲያን ወገኖች ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህና ይህ ምልክት ትገልጥ ዘንድ ይገባሃል" አለው። ሊቀ ጳጳሳቱ ሰምቶ ደነገጠ እጅግም ፈራ ንጉሡንም "እስከ ሦስት ቀን ታገሰኝ" አለው። ንጉሡም ይሁንልህ አለው።
❤ ሊቀ ጳጳሳቱም ከንጉሡ ወቶ በአቅራቢያው የሚገኙት ኤጲስቆሳቱን፣ ካህናቱን፣ መነኰሳቱን ሁሉ ሰበሰባቸው በምስር አገር በመሐልቃ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በእሊህ በሦስት ቀኖች እየጾሙና እየጸለዩ የእመቤታችን ሥዕል ፊት ቆመው ወደ እግዚአብሔር ሲማልዱ ቆዩ። በሦስተኛው ቀን በሌሊት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሊቀ ጳጳሳቱ በብሩህ ገጽ ተገልጣ እንዲህ አለችው " በፊቴ ያፈሰስከውን እንባ ተቀብያለሁ ስለ አንተ ልጄን ለምኘዋለሁና አትፍራ አሁንም የብረት አፈር በአለበት ሜዳ ወደ ገበያ በሚወስደው ጎዳና ተነስተህ ሂድ አንድ አይና የሆነ የውኃ እንስራ የተሸከመ ሰው ታገኛለህ ይህ ምልክት እርሱ ያደርግልሃልና እርሱ ያዘው የዚህ ሰው ስሙ ጫማ ሰፊ ስምዖን ይባላል እርሱም ስለምወደው ልጄ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝ ዓይኑን አውልቆ ጥሏልና"።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጽያዊው_ጻድቅ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዜና_ማርቆስ_ለዕረፍታቸው ዓመታዊ ክብረ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ስለ_አባታችን_አቡነ_ዜና_ማርቆስ_ዕረፍት፦ በታኅሣሥ ወር በሦስተኛው ዕለት ዐርብ ጥዋት ይኸውም እመቤታችን ቅድስት ድግንል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበትና የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል በዓል በሆነበት ቀን። ያን ጊዜ ለነግህ ጸሎት እጆቹን ዘረጋ፤ በመንግሥት የተካከሉ፥ አንድ አምላክ የሆኑ፥ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ታላቅ ጻድቅ ወደሆነ አባታችን ዜና ማርቆስ ወረዱ፥ በሰማያት የሚኖሩ ሠራዊቶቻቸውም ሁሉ መልካም ጣፋጭ መዓዛም ሸተተ፤ ይህም መዓዛው ታላቁ የዠማ ወንዝ እስከ ምሁር አውራጃ ድረስ አርባ ቀን ያህል ኖረ። በዚህም ሰማያዊ ሽቱ መዓዛ ከጣዕሙ ኃይል የተነሣ የሞት ፃዕር ሳያገኛት መልአከ ሞትም ሳያስደነግጠመት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች።
❤ ሰውን የሚወድ የጻድቃን ሞገሳቸው፣ የመነኰሳት ተስፋቸው፥ የሰማዕታት አክሊላቸው የሆነ ቸር አምላካችን እግዚአብሔር በእጆቹ ውስጥ ተቀበላት አቅፎም ንጹሕ ቅዱስ በሆነ አፉ ሳማት። ነፍሱም አክሊል ተቀዳጅታ በሰማይ ወደአለች ብርሃናዊት አዳራሽ ከጌታችን፣ ከቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጋር ዐረገች።
❤ ያን ጊዜም ንጹሕ ክብር የሆነ ሥጋውን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይቀብሩ ዘንድ መነኰሳት ልጆቹ ተሰበሰቡ ያን ጊዜም፦ "የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ ጣዕም ባለው ታላቅ ድምፅ ሲዘምሩ የልዑል እግዚአብሔር መላእክትን ሰሙአቸው። ዳግመኛም "በዘይት ሃይማኖቱ ለኢትዮጵያ ያበራላት የዚህ የዜና ማርቆስ በዓል በደስታ እናክብር። አሁንም የዘይት ዛፍ ሃይማኖት የተባለ የዜና ማርቆስን በዓል በታላቅ ክብር እግዚአብሔርን እያመሰገን ዛሬ እናክብ" አሉ። እዲህም የሚሉ ነበሩ፦ "ጻድቅ ሰው እንደ ዘንባባ ያፈራል በደጋ እንዳለ ዝግባም ይዛል" ሌሎችም እንዲህ የሚሉ ነበሩ፦ "በዓለም ሳለ በገድል፣ በትሩፋት የደከሙ በፈጣሪያችን እግዚአብሔር ፊቴ ለዘለዓለሙ ሕያው ሁኖ ይኖራል ጥፋትን አያይምና"።
❤ ዳግመኛ እንዲህ የሚሉ ነበሩ፦ "በጽዮን ደብረ ብሥራት ዘር ያለው ዜና ማርቆስ ብፁዕ ነው። ይህቺም ዳግሚት ደብረ ዘይት የተባለች የዜና ማርቆስ ገዳም የከበረች ደብረ ብሥራት ናት"። የአባታችን ዜና ማርቆስ መነኰሳት ልጆቹ ይህን የመላእክት ምስጋና በሰሙ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው፤ እነርሱም እግዚአብሔር አመሰገኑት፤ የገድሉንም መጽሐፍ ሁሉ ጻፉ። ይህንም የመላእክት ምስጋና ከሚዘምሩበት መጽሐፋቸው ውስጥ ጻፉቱ። በዚህም የመላእክት ምስጋና በመንፈሳዊ አባታችን ዜና ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውሰረጥ ሲዘምሩ ኖሩ።
❤ ደቀ መዛሙርቱም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል በአገኘባት በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአነጻት በደብረ ብሥራት ቤተ ክርስቲያን በስተቀኝ በኩል በታላቅ ክብር ሥጋውን አስቀመጡ። ደሙን በማፍሰስ በእውነት ሰማዕት የሆነ፣ በትዕግሥቱ ጻድቅ የሆነ፣ ለኢትዮጵያ አገር ብርሃን በሆነ ሃይማኖቱና ትምህርቱ ያበራ፤ አራቱን ወንጌላት ዙሮ ያስተማረ ታላቅ ሐዋርያ የሆነ፣ ሙሴ የጸፈውን ዐሠርቱ ቃላተ ኦሪትን የሚያሰተምር ነቢይና ካህን የሆነ፣ በሚያመለክተው ትንቢቱ ከእግዚአብሔር ዘንድ በጎ ነገር የሚመጣለት፣ በአደረበት መንፈስ ቅዱስ ራእይን የሚያይ፣ በሹመቱ ወራት ሃይማኖት ጽናትና የበጎ ሥራ መስፋፋት የተደረገበት ታላቅ ሊቀ ካህናት የሆነ፤ የአባታችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ የምስጋና ቃል ይህ ነው። ከአባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ምዕራፍ 33።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ማኅሌቱ_ምስባክ፦ "እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ። ወእሁብ ብጽዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ። ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ"። መዝ65፥13-14። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-17።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ። ርስዒ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ። እስመ ፈተወ ንጉሥ ስነኪ"። መዝ 44፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 9፥1-11፣ 2ኛ ዮሐ 1፥5-8 እና የሐዋ ሥራ 1፥12-15። የሚነበበው ወንጌልን ሉቃ 1፥39-57። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የበዓታ ለማርያም በዓል፤ የቅዱስ ፋኑኤል በዓል፣ የአቡነ ዜና ማርቆስ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን #አምላክን_ለወለደች_ለእናታች_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_በሦስት_ዓመቷ_ወደ_ቤተ_መቅደስ_ለገባችበት (ለበዓታ ለማርያም) በዓል፣ ለሊቀ መላእክት #ለቅዱስ_ፋኑኤል_እመቤታችንን_ሰማያዊ_መናና_መጠጥን_ለመገበበትና_ላጠጣበት ዓመታዊ ክብረ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የእመቤታችን_ወደ_ቤተ_መቅደስ_መግባት፦ እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝ ሆነች። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች "የሰጠህኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርገዋለሁ"።
❤ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻች ጊዜ በንጽሕና ሲያሳድጉ ሦስት ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ሐና ባሏን ኢያቄምን "ወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር ብፅዓት አድርገን እንስጥ ልጃችን ቤተ እግዚአብሔር ልታገለግል እንጂ በዚህ ዓለም እኛን ልታገለግ እንዳልተሳልን አስብ" አለችው። ኢያቄብም ይህን ነገር ከሚስቱ ከሐና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ለመንገድ የሚሆነውን ስንቅና ለቤተ እግዚአብሔር የሚሆነውንም መባዓ ሁሉ አዘጋጀ ቤተ ሰቦቻቸውንና ወዳጆቻቸውን ዘመዶቻቸውንም ሁሉ ጠሩ ልጃቸው ይዘው ሄደው ወደ ቤተ መቅደስ አገቧት።
❤ ካህናቱና በቤተ መቅደስም ያሉ ሁሉ በሰሙ ጊዜ እነሱን ለመቀበል ወጥተው መንፈሳዊ ሰላምታ ሰጡቸው ኢያቄምንና ሚስቱ ሐናን ልጃቸውን ማርያምንም አመሰገንዋቸው በአንብሮተ እድ ፈጽመው ባረኳቸው "እግዚአብሔር ኀዘናችሁን በዕውነት ተቀብሏችኋል የተመረጠች በምትሆን በዚች ልጅም ደስ አሰኝቷችኋል" አሏቸው።
❤ በዚህም ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ስለ ምግቧ ነገር ቢያዝልኝ ብሎ በማሰብ ደወል አስደወለና ሕዝቡ ሁሉ እንዲሰበሰብ አደረገ። በዚያም ጊዜ ሕዝቡ በተሰበሰበበት አደባባይ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል ሰማያዊ ኅብስት ሰማያዊ ጽዋ ይዞ በአየር ላይ ረቦ ታየ። ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም "ዛሬስ የእስራኤል አምላክ ክብሬን በዚህ ሕዝብ መካከል ሊገልጽልኝ ፈቅዷል" በማለት ኅብስቱንና ጽዋውን ሊቀበል ተነሣ። መልአኩ ግን ወደ ላይ ሰቀቀበት መጠቀበት። ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም ሐናን ጠርቶ "ለእናንተ ለእግዶቹ የወረደ ክብር ይሆናልና ሕፃኗን ይዘሽ ከዚህ እኛ ካለንበት ቦታ ፈቀቅ ወይም እልፍ ብለሽ ተቀመጭ" አላት ሐናም ልጅዋን ይዛ ፈቀቅ ብላ ተቀመጠች። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ፋኑኤል ግን ከሐና እና ከልጅዋ ራስ በላይ ረቦ ቆየ እንጂ አልወረደም።
❤ ዳመኛም ዘካርያስ ሐናን "የእግዚአብሔር ምስጢር አይመረመርምና ልጅቷን ከዚያው ትተሻት ተመልሰሽ ነይ" አላት። ሐናም ብላቴናቱን በዚያው ትታት ወደ እነሱ ተመልሳ መጣች በዚያን ጊዜ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል ወርዶ ክንፎቹን አጎናጽፏት ከመሬት ወደላይ የሰው ቁመት ያህል ከፍ ብሎ ኅብስቱን መግቧት ጽዋውን አጠጥቷት ወደ ሰማይ ዐረገ።
❤ ከዚህም በኋላ ዘካርያስና የአይሁድ ሊቃውንትም የምገሰቧ ነገር ከተያዘልንስ ከሰው ጋራ ምን ያጋፋታል ቦታዋ ወይም መኖሪያዋ በቤተ መቅደስ ይሁን እንጂ ብለው ዙፋን ዘርግተው ስጋጃውን አንጥፈው ምስጋና የባሕርዩ የሆነ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በታላቅ ክብር ወደ ቤተ መቅደስ አገቧት በብላቴናይቱ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል ተገልጿልና።
❤ በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ። ከሴቶች ሁሉ የተመረጠች ይቺ ናት በቤተ መቅደስም በመኖር ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲፈጸምላት እርሷ ለእግዚአብሔር የተሰጠች የስለት ልጅ ናትና ለሚጠብቃት ይሰጧት ዘንድ ካህናት እርስበርሳቸው ተማከሩ በሴቶች ላይ የሚደርስ በርሷ ላይም ይደርስባታል ብለው ስለፈሩ በቤተ መቅደስ ውስጥ ይተዋት ዘንድ ለእርሱ ትክክል መስሎ አልታያቸውም ስለዚህም ሊጠብቃት ለሚገባው በእርሷ ላይ እጮኛ ሊአኖሩ ወደዱ።
❤ ከዚህም አስቀድሞ ሊቀ ካህናት ዘካርያስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ልጄ ማርያም ሆይ አንቺ እንዳደግሽና ለካለ መጠን እንደደረስሽ ዕወቂ ልትታጪ ትወጃለሽን እግዚአብሔርን የሚፈራ መልካም የሆነ የተባረከ ጐልማሳ እንፈልግልሽን ወይም በሕይወትሽ ዘመን ሁሉ በቤተ መቅደስ ተቀምጠሽ እግዚአብሔርን ልታገለግዪው የምትሺ ከሆነ በሴቶች ላይ የሚደርሰው በሚደርስብሽ ወራት ወደ ቤተ መቅደስ ደጅ ከመግባት ትጠበቂ ዘንድ በኦሪቱ የተጻፈውን የርግማን ሥርዓት በአንቺ ላይ እንሠራለን" አላት። ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም "እነሆ እኔ የእግዚአብሔር አገልጋዩ በፊታችሁ ነኝ አባትና እናትም የሉኝም ስሙ ቡሩክ ምስጉን ከሆነ ከእግዚአብሔር በታች በእናትና አባት ፈንታ እናንት ናችሁና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንደምታውቁ አድርጉ" ብላ መለሰች።
❤ ካህናቱና ማኅበሩም ሁሉ ዘካርያስን "ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ስለዚች ብላቴና ማርያም ወደ እግዚአብሔር ጸልይ" አሉት። ዘካርያስም ገብቶ ሲጸልይ በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና እንዲህ አለው "ዘካርያስ ሆይ ወጥተህ ከዳዊት ወገን ሚስቶቻቸው የሞቱባቸውን ሁሉ ወንዶች ሰብስብ የየአንዳንዱንም በትር ከስሙ ጋር ውሰድ ወደ ቤተ መቅደስም በምሽት አግብተህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይበት በነጋ ጊዜም በትሮቻቸውን አውጣ እግዚአብሔርም በበትሩ ላይ ምልክት ለገለጠልህ ለዚያ ሰው ማርያምን ተቀብሎ ሊጠብቃት ይገባዋል"። ካህኑ ዘካርያስም ወጥቶ አንድነት ለተሰበሰቡ ሕዝቡ የእግዚአብሔር መልአክ የነገረውን ነገራቸው በዚያንም ጊዜ ከዳዊት ወገን ጐልማሳም ቢሆን ሽማግሌም ቢሆን ሚስቱ የሞተችበት ሁሉ በኢየሩሳሌም ወደአለ ቤተ መቅደስ ይሒድ እያለ ዓዋጅን ዙረው የሚናገሩ በእስራኤል አገር ሁሉ ላከ።
❤ ከዳዊት ወገን የሆነ ጠራቢው ዮሴፍም በሰማ ጊዜ በትሩን ይዞ ከናዝሬት ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ካህኑ ዘካርያስም የሁሉንም በትሮች ተቀብሎ ስማቸውን በላያቸው ጻፈ ቊጥራቸውም አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ሆነ ዘካርያስም በትሮችን ወደ ቤተ መቅደስ አስገብቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ እንዲሁም ሰዎች ሁሉ ከቤተ መቅደስ ውጭ ቁመው ይጸልዩ ነበር ዘካርያስም ጸሎቱን በፈጸመ ጊዜ ለየአንዳንዱ በትራቸውን አውጥቶ ሰጠ ጠራቢው ዮሴፍም በትሩን ሊቀበል በቀረበ ጊዜ ከእርሷ ነጭ ርግብ የመሰለች ተገለጠች እየበረረችም ሒዳ በጠራቢው ዮሴፍ ራስ ላይ ተቀመጠች ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ አይተው እጅግ አደነቁ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔር አመሰገኑት።
❤ ዘካርያስ ዮሴፍን "ዮሴፍ ሆይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እንደ ተናገረ ድንግል ማርያምን ወደ ቤትህ ወስደህ ጠብቃት" አለው። ዮሴፍም ቅድስት ድንግል ማርያምን ከካህናት እጅ ተቀበላት በእርሱም ዘንድ ኖረች። ከዚህም በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ስለ እግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ሁኖ ስለመወለዱ በዮሴፍ ቤት አበሠራት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን በማርያም በአማላጅነቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ ተአምረ ማርያም ተአምር 15ና የታኅሣሥ 3 ስንክሳር።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ታኅሣሥ ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን #ለሠለስቱ_ደቂቅ_ለአናንያ_ለአዛርያና_ለሚሳኤል #እግዚአብሔር_ኃይል_ላደረገላቸው ለመታሰቢያ በዓላቸው፣ #ለቅዱስ_አውክያኖስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከላይኛው ግብጽ ከሚኖሩ ሰዎች ወገን ለሆነ #ለቅዱስ_አባት_ለአባ_ሖር ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_ፋሲለደስ አገልጋዮቹና ዘመዶቹ ከሆኑ #ከሰባት_ሺህ_ሠላሳ_ሦስት_ከሆኑ_ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው፣ #ከአብላፍታን፣ ከዐረብ ወገን ከሆነ #ከሰማዕት_አንበስና_ከመነኰስ_ናትናኤል ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሠለስቱ_ደቂቅ፦ በዚች ቀን ናቡከደነፆር ከአባታቸው ጋር ለማረካቸው ሦስቱ ለሆኑ ለይሁዳ ንጉሥ ለኢዮአቄም ልጆች እግዚአብሔር ኃልን አደረገላቸው። እሊህም አናንያ አዛርያ ሚሳኤል ናቸው በቤቱም ውስጥ አሳድጎ በባቢሎን አገሮች ውስጥ ሾማቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ናቡከደነፆር የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉትን ሁሉ በዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ እሊህ ቅዱሳን ግን መስገድን እምቢ አሉ በወነጀሏቸውም ጊዜ ከቀድሞው ሰባት እጅ ወደ አነደዱት የእሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሯአቸው ዘንድ ንጉሥ አዘዘ። በእሳቱ መካከል ረጅም ጸሎትን ጸለዩ የእግዚአብሔር መልአክም ቅዱስ ገብኤልም ወርዶ እንደ ቀዘቀዘ ነፋስ አደረገው።
❤ ንጉሥ ናቡከደነፆርም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ አደነቀ ለእግዚአብሔርም በመገዛት ሰገደ እነርሱንም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ አወጣቸው እጅግም አከበራቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ቅዱሳን በሠለስቱ ደቂቅ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_አውክያኖስ፦ እርሱም ሃይማኖቱን ጠብቆ ሰዎች አባለ ዘሩን እስከ ቆረጡት ድረስ ተጋድሎውን የፈጸመ ነው እግዚአብሔርም አመሰገነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውክያኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሖር፦ ይህም አባት ደግነት ያለው መነኰስ በመሆን ጽኑዕ ገድልን ተጋደለ በአምልኮቱና በተጋድሎው ከቅዱሳን ሁሉ ተለይቶ በብዙዎች ላይ ከፍ ከፍ አለ ለብቻ መኖርን ስለወደደ ወደ በረሀ ወጥቶ በገድል ተጠምዶ ብዙ ዘመናት ኖረ። የበጎ ሥራ ጠላት የሆነ ሰይጣንም ቀንቶበት በግልጥ ታየውና "በበረሀ ውስጥ ግን አንተ ድል ትነሣናለህ በዚህ ሰው የለምና ጽኑ ኃይለኛ ከሆንክ ወደ እስክንድርያ ከተማ ና" ብሎ ተናገረው።
❤ አባ ሖርም ይህን በሰማ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ኃይል ተማምኖ ወደ እስክንድርያ ከተማ ሒዶ ለእሥረኞችና ለችግረኞች ደካሞች ውኃ የሚቀዳ ሆነ በአንዲት ዕለት ሦስት ፈረሶች በከተማው ውስጥ እየዘለሉ ሲያልፉ አንዱ ፈረስ አንዱን ሕፃን ረገጠውና ወዲያውኑ ሞተ ሰይጣንም በሰዎች ልብ አደረና "ይህን ሕፃን ያለዚህ አረጋዊ መነኵሴ የገደለው የለም" ብለው አሰቡ አባ ሖርም መጣና ሕፃኑን አንሥቶ ታቀፈው በልቡም በመጸለይ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር ማለደ በመስቀል ምልክትም በላዩ አማተበ የሕፃኑም ነፍስ ተመለሰች ድኖም ተነሣ ለአባቱም ሰጠው ወደ ከተማ ውጭ ሸሽቶ በመሔድ ወደ በዓቱ ገባ ፈልገውም አላገኙትም ጽድቅንና ትሩፋትንም በመሥራት ብዙ ዘመናት በገድል ተጠምዶ ኖረ።
❤ የሚሞትበት ጊዜ ሲቀርብ ብዙዎች ቅዱሳንን ሲጠሩት አያቸው እጅግም ደስ አለው ልጆቹንም ሰብስቦ በምንኵስና ሥርዓት ጸንተው ትሩፋትን እንዲሠሩ አዘዛቸው ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እርሱ እንደሚሔድ ነገራቸው እርሱም እጅግ አዘኑ ጥቂት ቀንም ታሞ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት በአባ ሖር ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ2 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለሖር_በምንሀብ_ፍቱን። እስከ ተለዓለ ጥቀ ላዕለ ብዙኃን። ሶበ ተንሥኡ ላዕሌሁ በምክረ ጸላኢ ሰይጣን። ከመ ኢቀተሎ እስከ አእመሩ አብዳን። በኃይለ ጸሎቱ አንሥኦ ለምውት ሕፃን"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የታኅሣሥ_2።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ። ወእነግር ኲሎ ስብሐቲከ። እትፌሣሕ ወእትሐሠይ ብከ"። መዝ9፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 6፥35-39።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አኅለፍከነ ማእከለ እሳት ወማይ። ወአውጻእከነ ውስተ ዕረፍት። እበውእ ቤተከ ምስለ መባእየ"። መዝ 65፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥9-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 19፥10-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
