uz
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Ko'proq ko'rsatish
636
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-47 kunlar
-1230 kunlar
Postlar arxiv
🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼           🌼 #መስከረም ፯ (7) ቀን። 🌼 እንኳን #ስለ_ተዋሕዶ_ሃይማኖት #በጉባኤ_ኬልቄዶን (ከለባት) #በ_451 ዓ.ም በንጉሥ መርቅያኖስና በሚስቱ በንግሥት ብርክልያ (በሊዮናውያን) #ጢሙን_ለተነጨና_ጥርሱንም ለተነቀለ  #ለእስክድርያ_ሃያ_አምስተኛ_ጳጳስ #ለታላቁ_ሊቅ_ለአቡነ_ዲዮስቆሮስ ለዕረፍት በዓል፣ ለገብላ ኤጴስቆጶስ ለከበረ አባት #ለአባ_ሳዊርያኖስ ለዕረፍት በዓል፣ ለከበሩ #ቅዱሳን_ሰማዕታት_ለአጋቶንና #ጴጥሮስ_ለዮሐንስና_ለአሞን_ለእናታቸው_ራፈቃ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦#ከቅዱስ_ፋሲለደስ ጋር በሰማዕትነት ከዐረፉ #ከሁለት_ሺህ_ሰዎች፣ ከጋንግራ ሰው #ዳሳ #ከአንጾኪያ_ኤጲስቆጶስ_ከናውላ፣ ከመነኵሴውም #ከአባ_ጴጥሮስ_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                           ✝ ✝ ✝ 🌼 #የእስክንድርያ_አገር_ሃያ_አምስተኛ_ሊቀ_ጳጳሳት #ሊቁ_አባ_ዲዮስቆሮስ፦ ስለ ቀናች ሃይማኖትም ታላቅ ተጋድሎን ከተጋደለ በኋላ ዕረፍቱ በተሰደደበት በደሴተ ጋግራ ሆነ። ይህም እንዲህ ነው ንጉሥ መርቅያኖስ ወደ ሰበሰበው ጉባኤ በጠሩት ጊዜ ሲደርስ ብዛታቸው ስድስት መቶ ሠላሳ ስድስት የሆነ ታላቅ ጉባኤን አየ። እንዲህም አለ "ይህ ታላቅ ጉባኤ እስቲሰበሰብ ድረስ በሃይማኖት ላይ የተገኘው ጉድለት ምንድን ነው"። "ይህ ጉባኤ የተሰበሰበው በንጉሥ ትእዛዝ ነው" አሉት። እንዲህም አላቸው "ይህ ጉባኤ ስለ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢሆን ኖሮ እኔ ተቀምጬ እግዚአብሔር በሰጠኝ በአንደበቴ እናገር ነበር ግን የዚህ ጉባኤ መሰብሰብ በንጉሥ ትእዛዝ ከሆነ የሰበሰበውን ጉባኤ ንጉሡ እንዳሻው ይምራ"። 🌼 ከዚህም በኋላ አንዱን ክርስቶስን ከተዋሕዶ በኋላ ሁለት ባሕርይ ሁለት ምክር የሚያደርግ የክህደት ቃል በውስጡ የተጻፈበትን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ልዮን የላከውን ደብዳቤ የከበረና የተመሰገነ ዲዮስቆሮስ ቀደደ። በመንፈስ ቅዱስ የሚናገር የከበረ ዲዮስቆሮስም በጉባኤው ፊት እንዲህ ብሎ አስረዳ "ሰው እንደመሆኑ ወደ ሠርግ ቤት የጠሩት ጌታችን ክርስቶስ አምላክ እንደመሆኑ ውኃውን ለውጦ ወይን ያደረገው ከሀሊ ስለሆነ ሰውነቱና መለኮቱ በሥራው ሁሉ የማይለይ አንድ ነው"። 🌼 ደግሞ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቄርሎስ ከተናገረው የአካላዊ ቃል ተዋሕዶ እንደ ነፍስና ሥጋ እንደ እሳትና ብረት ተዋሕዶ ነው ያለውን ቃል ምስክር አድርጎ በማምጣትም አስረዳ። "እሊህም የተለያዩ ሁለቱ ጠባዮች ስለ ተዋሕዷቸው አንድ ከሆኑ እንዲሁም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ አንድ መሲሕ አንድ ጌታ አንድ ባሕርይ አንድ ምክር ነው እንጂ ወደ ሁለት አይከፈልም" አላቸው። 🌼 ከዚያም ከተሰበሰበው ጉባኤ ውስጥ ማንም ሊከራከረው የደፈረ የለም ከውስጣቸውም የእግዚአብሔር ጠላት ስለሆነው ስለ ከሀዲው ንስጥሮስ በኤፌሶን ጉባኤ አስቀድሞ ተሰብስበው የነበሩ አሉ። ወደ ንጉሥ መርቅያኖስና ወደ ሚስቱ ንግሥት ብርክልያ "ከእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ከአባ ዲዮስቆሮስ በቀር ስለ ሃይማኖት ትእዛዛችሁን የሚቃወም የለም" ብለው ነገር ሠሩበት። 🌼 ቅዱስ ዲዮስቆሮስንም ወደ ንጉሥ አቀረቡት ከእርሱም ጋር ታላላቅ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት ከጉባኤው የሆኑ ነበሩ ከጥዋትም እስከማታ እርስበርሳቸው ሲከራከሩ ዋሉ። የከበረ ዲዮስቆሮስም የቀናች ሃይማኖቱን አልለወጠም ንጉሡና ንግሥቲቱ በእርሱ ተቆጥተው እንዲደበድቡት አዘዙ ስለዚህም ደበደቡት ጽሕሙን ነጩ ጥርሶቹንም ሰበሩ እንዲህም አደረጉበት። 🌼 ከዚህም በኋላ የተነጨውን ጽሕሙን ያወለቁትንም ጥሩሱን ሰብስቦ ወደ እስክንድርያ አገር ላካቸው "እነሆ የቀናች ሃይማኖት ፍሬ ይህ ነው" አላቸው። ለጉባኤውም የተሰበሰቡ ኤጲስቆጶሳት በዲዮስቆሮስ ላይ የደረሰውን መከራ በአዩ ጊዜ እጅግ ፈሩ በእርሱ የደረሰ በእነርሱ ላይ እንዳይደርስ ስለዚህም ከመናፍቁ ንጉሥ ከመርቅያኖስ ጋር ተስማሙ። 🌼 በሲኦል ውስጥ ይቆርጡት ዘንድ ባለው ምላሳቸውም "ለክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት" አሉት ብለው በንጉሡ መዝገብ ላይ በእጆቻቸው ጽፈው ፈረሙ። ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ተመልሶ ያን በውስጡ የጻፉበትን ደብዳቤ ያመጡለት ዘንድ ወደእሳቸው ላከ እነርሱም ላኩለት እነርሱ እንደጻፉ በውስጡ እርሱ የሚጽፍ መስሏቸዋልና። እርሱ ግን አባቶቻችን ሐዋርያት ከአስተማርዋት ከቀናች ሃይማኖት በኒቅያ የተሰበሰቡ ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ኤጲስቆጲሳት አባቶቻችን ከሠሩት ሕግ የሚወጣውን ሁሉ በደብዳቤው ግርጌ ጽፎ አወገዘ። 🌼 መናፍቁ ንጉሥም ተቆጥቶ ጋግራ ወደም ትባል ደሴት እንዲአግዙት አዘዘ ወደዚያም ወሰዱት። ከእርሱም ጋር የሀገረ ቃው ኤጲስቆጶስ አባ መቃርስ አብሮ ተሰደደ። ሌሎችም አራት መነኰሳት የሸሹ አሉ። እሊህም ስድስት መቶ ሠላሳ ስድስት ኤጲስቆጶሳት ተቀምጠው በኬልቄዶን ለራሳቸው መመሪያ የሚሆናቸውን ሥርዓት ሠሩ። 🌼 የከበረ ዲዮስቆሮስንም በአጋዙት ጊዜ ከዚያች አገር ኤጲስቆጶስ ጭንቅ የሆነ መከራ ደረሰበት ኤጲስቆጶስ ንስጥሮሳዊ ስለሆነ ታላቅ ጉስቁልናንም አጎሳቁለው በእጆቹ ላይ ድንቆች ታላላቅ ተአምራቶችን እግዚአብሔር እስከገለጠ ድረስ። የደሴቱም ሰዎች ሁሉ ሰገዱለት አከበሩት ከፍ ከፍም አደረጉት እግዚአብሔርም የመረጣቸውን በቦታው ሁሉ ያከብራቸዋልና። አባ ዲዮስቆሮስም አባ መቃርስን "አንተ በእስክንድርያ አገር የሰማዕትነት አክሊልን ትቀበል ዘንድ አለህ" አለው። ከዚህም በኋላ ከምእመናን ነጋዴዎች ጋር ወደ እስክንድርያ ላከው በእርሱ ላይ ትንቢት እንደተናገረ ገድሉን በዚያ ፈጸመ። 🌼 የከበረ አባት ዲዮስቅሮስ ግን መልካም ተጋድሎውን በፈጸመ ጊዜ ክብር ይግባውና እግዚአብሔርንም አገልግሎ ከዚች ኃላፊት ከሆነች ኑሮው ወጥቶ ሔደ የሃይማኖቱንም ዋጋ አክሊልን ተቀብሎ ወደ ዘላለም ዕረፍት ገባ ያረፈውም በዚያች በደሴተ ጋግራ ነው ሥጋውንም በዚያው አኖሩ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዲዮስቆሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                                                 

🌼 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼                🌼 #መስከረም ፯ (7) 🌼 እንኳን #ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም እናት #ለቅድስት_ሐና ለልደቷ_መታሰቢያ_በዓል፣ #ለመጥምቀ°መለኮት_ለቅዱስ_ዮሐንስ እናት #ለቅድስት_ኤልሳቤጥ_ለመታሰቢያዋ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ 🌼 #ቅድስት_ሐና፦ ይችም ቅድስት ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት። ለማጣትም ሦስት ልጆች አሉት የታላቂቱም ስሟ ማርያም ናት ሁለተኛዋም ስሟ ሶፍያ ሦስተኛዪቱም ስሟ ሐና ናት ታላቂቱ ማርያምም ለባል ተድራ አዋላጅ የሆነች ሰሎሜን ወለደቻት እርሷም መድኃኒታችንን ከወለደችበት ጊዜ ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ድንግል ማርያምን ያገለገለቻት ናት። ሶፍያም ለባል ተድራ ለመጥምቁ ዮሐንስ እናቱ የሆነች ቅድስት ኤልሳቤጥ ወለደቻት። 🌼 ይችንም ቅድስት ሐናን ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙ ኢያቆም ለሚባል አጋቧትና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት እሊህም ሰሎሜና ኤልሳቤጥ ለቅድስት ሐና የእኅትማማች ልጆች ናቸው። 🌼 የዚችንም የቅድስት ሐናን በሥውር የምትሠራውን ገድሏንና ትሩፋቷን እንዳናስታውሰው አናውቀውም ግን ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እናውቃለን እንረዳለን እርሷ አምላክን በሥጋ ለወለደችው ወላጅዋ ትሆን ዘንድ የተገባት ሁናለችና ከሴች ሁሉ የሚበልጥና የሚበዛ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ታላቅ ጸጋ ባልተገባት ነበር። 🌼 ይህችም ጻድቅት ሐና መካን በመሆንዋ ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር በጸሎት ትማልድ ነበር እግዚአብሔርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችና የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት። ስለዚህም ይህን ታላቅ ጸጋ ስለሰጣት የበዓሏን መታሰቢያ በደስታ ልናከብር ይገባል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በቅድስት ሐና በጸሎቷ የሚኝ በረከቷም ከእኛ ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 11 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ 🌼 #ቅድስት_ኤልሳቤጥ፦ ይህች ቅድስት ከኢየሩሳሌም የሆነች የእናቱዋ ስም ቅድስት ሶፍያ ነው። እርሷም ከሌዊ ነገድ ከአሮን ወገን ለሆነ ለማጣት ልጅ ናት በዝምድና አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የእናቷ እኅት ልጅ ናት። ማጣት ሦስት ልጆችን ወለዷልና የታላቂቱም ስም ማርያም ነው እርሷም ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ እመቤታችንን ያገለገለች ሰሎሜን ወለቻት፣ ሁለተኛዋም ሶፍያ ናት እርሷም የዚች ቅድስት ኤልሳቤጥ እናቷ ናት፣ የታናሺቱም ስም ሐና ነው። እርሷም የከበረች ድንግል እመቤታችንን ማርያምን ወለጀቻት። ሰሎሜ ኤልሳቤጥ እመቤታችን ማርያም የእኅትማማች ልጆች ናቸው። 🌼 ይችንም ቅድስት ኤልሳቤጥ ካህኑ ዘካርያስ አገባት የከበረ ወንጌልም ስለርሳቸው፡ ተናግሯልና እነርሱ ሁለቱም ያለ ነውር ያለ ነቀፋ በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው የሚኖሩ ዕውነተኞች ደጎች ሆኑ። ኤልሳቤጥም መካን ስለሆነች ወደ እግዚአብሔር የሚለምኑና የሚሚማልዱ ሆኑ አርጅተውም የመውለጃቸው ዘመን በአለፈ ጊዜ እግዚአብሔር መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ዘካርያስ ልኮ ጸሎታቸው ልመናቸው እንደ ተሰማ ስለ ዮሐንስ መወለድና ከእርሱ ስሚሆነው አስረዳው። 🌼 ከዚህም በኋላ ይቺ ቅድስት ኤልሳቤጥ መጥምቁ ዮሐንስን ፀንሳ ወለጀችው ከሰዎችም የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዶ እጅ ደስ አላት። ሕፃኑም በማሕፀኗ እያለ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሰላምታ በሰጠቻት ጊዜ እንዲ ብላ ጮኸች "ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽም ፍሬ ቡሩክ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድን ነኝ እነሆ እንዴት ነሽ ስትይኝ የሰላምታሽን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ልጁ በማሕፀኔ ውስጥ በደስታ ዘለለ (ሰገደ)"። 🌼 ከዚህም በኋላ ጌታችንን አየችው በአምላክነቱም አመነች የሚያምኑበትም በመዳናቸው ደስ አላት ዕድሜዋንም በፈጸመች ጊዜ በበረሀ ውስጥ ሳለች የካቲት16 ቀን በሰላም ዐረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኤልሳቤጥ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 16 ስንክሳር።

🌼 "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼                           ✝ ✝ ✝ 🌼 "#ሰላም_ለኢሳይያስ_ነቢይ_ወልደ_አሞጽ ዘፈጸመ ገድሎ በሞሠርተ ዕፅ ደራሲ ትንቢተ እምነቢያት ልዑላተ"። ትርጉም፦ በዕንጨት መጋዝ ተተርትሮ ገድሉን የፈጸመ ለኾነ፤ ከታላላቆች (ከዐበይት) ነቢያት ይልቅ ትንቢትን ለጻፈ #ለነቢዩ_ለቅዱስ_ኢሳይያስ_ሰላምታ ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።        

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼           🌼 #መስከረም ፮ (6) ቀን። 🌼 እንኳን #ከዐበይት_ነቢያት_አንዱ_ለሆነው ለታላቁ ነቢይ #ለአሞጽ_ልጅ_ለቅዱስ_ኢሳይያስ_ለዕረፍት በዓልና በከሀዲ ንጉሥ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበለች #ቅድስት_ሰብልትንያ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን ። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከመነኰስ_ያዕቆብ፣ ከኤጲስቆጶስ #ከአናቲሞስ_ከባስሊስና_ከአሮጦስ_ከውርዋና፣ #ከሳውልስ_ከሰማዕቱ_ከሰውላስም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                    ✝ ✝ ✝ 🌼 #የአሞጽ_ልጅ_ታላቁ_ነቢዩ_ቅዱስ_ኢሳይያስ፦ ይህም ነቢይ ለይሁዳ በነገሡ በአምስቱ ነገሥታት ዘመን አስተማረ ትንቢትም ተናገረ እሊህም አዝያን ኢዮአታም አካዝ ሕዝቅያስና ምናሴ ናቸው። 🌼 በአካዝ ዘመንም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ። "እነሆ ስለዚህ እግዚአብሔር ምልክትን ይሰጣችኋል። እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች። ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ አንድ ሆነ ማለት ነው"። እርሱም በኃጢአታቸው ከሚመጣባቸው ፍዳ ወገኖቹን የሚያድናቸው ወደ ሃይማኖቱም የሚአስገባቸው እንደሆነ የእስራኤልንም ልጆች መሥዋዕታቸውንና ክህነታቸውን እንደሚሽር ከሐዲስ ወገኖችም የሚያመሰግኑት ካህናትን እንደሚሾም ተናገረ። 🌼 የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬምም ኢየሩሳሌምን ከቦ የስድብ ቃልን በክብር ባለቤት በእግዚአብሔር ላይ በተናገረ ጊዜ የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬምን ያጠፋው ዘንድ እግዚአብሔር እንዳለው ለሕዝቅያስ ትንቢትን ተናገረ። በዚያች ሌሊትም እግዚአብሔር የላከው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደ ሠናክሬም ሰፈር መጥቶ ከፋርስ ሠራዊት መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ አርበኞችን ገደለ። የለኪሶ ሰዎች ሲነጋ በተነሡ ጊዜ የሞቱትን ሰዎች ሬሳ ሁሉ አዩ ። 🌼 ሕዝቅያስም ታሞ ለሞት በተቃረበ ጊዜ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ወደርሱ መጥቶ "እግዚአብሔር ትሞታለህ እንጂ አትድንም ብሏልና ቤትህን አዘጋጅ" አለው። ሕዝቅያስም ፊቱን ወደ ግድግዳው መልሶ ወደ እግዚአብሔር ለመነ ፈጽሞ ጽኑ ልቅሶንም አለቀሰ። ይህን ከነገረው በኋላ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ነቢዩ ወደ ኢሳይያስ መጣ "ሒደህ ለሕዝቅያስ "የአባትህ የዳዊት ፈጣሪ እግዚአብሔር ጸሎትህን ሰማሁ ዕንባህንም አየሁ። እነሆ በዘመንህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት ጨመርኩልህ" አለ በለው"። 🌼 ዳግመኛም ስለ እስራኤል መማረክና ከምርኮ ስለ መመለሳቸው ትንቢት ተናገረ የፈሳሽ ውኃን ምንጭ በማፍሰስ በእጆቹ ላይ እግዚአብሔር ምልክትን ገለጠ። ክብር ይግባውና ስለ መድኃኒታችን ክርስቶስ መከራ ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ። "እርሱም በመከራው ጊዜ ነገርን አልተናገረም እንደ በግ ይታረድ ዘንድ መጣ በግ በሚሸልተው ሰው ፊት እንደ ማይናገር እንዲሁ በመከራው ጊዜ አልተናገረም"። 🌼 ከዚህም በኋላ ደግሞ በሕዝቅያስ ልጅ በንጉሥ ምናሴ ላይ ትንቢት ተናገር ጣዖትን ስለማቆሙና ስለማምለኩ ገሠጸው። ስለዚህም ንጉሥ ምናሴ ተቆጥቶ በዕንጨት መሰንጠቂያ መጋዝ በራሱና በእግሮቹ መካከል ሠነጠቀው ምስክርነቱንም በዚህ መስከረም 6 ቀን ፈጸመ ። 🌼 ትንቢት እየተናገረ የኖረበትም ዘመን ሰብዓ ዓመት ከዚያም በላይ ይሆናል ። እርሱም ያስተማረው ክብር ይግባውና ጌታችን ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በዘጠኝ መቶ ዐሥራ ሦስት ዓመት ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ 🌼 #ሰማዕቷ_ቅድስት_ሰብልትንያ፦ ይችንም ቅድስት ዕድሜዋ ዘጠኝ ዓመት ሲሆን ከሀድያን ያዙዋት እጆቿንና እግሮቿንም አሥረው ከሚነድ እሳት ውስጥ ጣሏት የክብር ንጉሥ በሆነ በእግዚአብሔርም ኃይል ከእሳት ዳነች። 🌼 ውኃን በተጠማች ጊዜ እግዚአብሔርን ለምናው ውኃን አፈለቀላትና ጠጣች ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንንም አመሰገነችው። ከዚህም በኋላ ነፍሷን በእግዚአብሔር እጅ አደራ ሰጥታ ራሷን ከእሳት ውስጥ ወረወረች ምስክርነቷንም ፈጸመች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ሰብልትንያ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመስከረም 6 ስንክሳር።                         ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ቃለ እግዚአብሔር ያድለቀልቆ ለገዳም። ወያድለቀልቆ እግዚአብሔር ለሐቅለ ቃዴስ። ቃለ እግዚአብሔር ያጸንዖሙ ለኃየላት። መዝ 28፥8-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 3፥1-7።                          ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወገሠጸ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥25_ፍ.ም፣ 2ኛ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 28፥25-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥36-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼           🌼  #መስከረም ፮ (6) ቀን። 🌼 እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ዐፅማቸው #ከዋልድባ_አብረንታንት_ወደ ደብረ_ዓባይ ለፈለሰበት ቀን መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።                                                       ✝ ✝ ✝ 🌼 #የአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_የሥጋ_ፍልሰት፦ ከዋልድባ አብረንታንት ወደ ደብረ ዓባይ፤ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ ትውልዳቸው ከካህናቱ ወገን አክሱም ነው አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ። ለመምህር ሰጥተዋቸው ሲማሩ አድገው በኋላም ወላጆቻቸው በሞት ሲለዩአቸው ደብረ በንኰል ገዳም ገብተው ሥርዓተ ምንኩስናን ከአበው እያጠኑ ለትልቁም ለትንሹም በትሕትና እየታዘዙ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየሰበሩ በትኅርምት በጽሞና በጸሎት ይኖሩ ነበር። 🌼 ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ጾር ቢመጣባቸው ከማሕበረ መነኰሳቱ ተለይተው በተባሕትዎ ለመኖር ሽተው ወጥተው ሲሔዱ ተከዜ ደረሱ። ወንዙ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትምህርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉ ሳይበላሽ ተሻግረዋል። ዋልድባ ሲደርሱ ጌታ እዚህ ተቀመጥ ስላላቸው ገዳም መሥርተው ሥርዓተ ምንኩስናን እያስተማሩ ተቀመጡ። ዛሬ በዋልድባ የሚያመሰግኑበት ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡ እሳቸው ናቸው። ይህንን እየጸለዩ ሲሔዱ ክንድ ከስንዝር መሬት ለቀው ይታዩ ነበር። 🌼 አንድ ቀንም ይህንን ጸሎት ደግመው ውኃውን ቢባርኩት ኅብስተ ሕይወት ሆነላቸው ከነደቀ መዛሙርቶቻቸው ተመግበውታል። እመቤታችንም የፍቅር መግለጫ ዕጣን፣ ወርቅ፣ እንቁ ሰጥታቸዋለች። "ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ የደገመውን አንተ ከገባህበት መካነ ሕይወት አስገባዋለሁ" ብላ ቃልኪዳን ሰጥታቸዋለች። ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታን በስብሐተ መላእክት ተገልጦ "በስምህ የተማጸነውን በጎ የሰራውን፣ ዜና ገድልህን የጻፈውን፣ ያስጻፈውን፣ ያነበበ፣ የተማረ፣ ያስተማረ፣ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ምሬልሃለሁ። በዚህ ቦታ በዋልድባ የሚሰበሰቡ ልጆችህን ከእዳ ከፍዳ እሰውርልሃለሁ" አላቸው። እንኪያስ ቦታዋን ባርክልኝ ብለው እንደ መሶብ አንስተው አስባርከዋታል ጌታችንም "እህል አይብቀልብሽ ኃጢአት አይሻገርብሽ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባላት ለገዳመ ዋሊ። አባታችን አቡነ ሳሙኤል በበዓታቸው ውስጥ ጸንተው ሲኖሩ ታህሣሥ 12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዛሬ መስከረም 6 ግን ፍልሰተ አጽማቸው የተከናወነበት ዕለት ነው። ከአባታቸው ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።

የሚያሠቃየው የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር በደብሩ ነበር፡፡ አቡነ መልክአ ክርስቶስም በጸሎቱ ክፉ ጠላትን ድል አደረገለት፡፡ "ልጄ አይዞህ አትፍራ ጽና" ይለው ያበረታው ነበር፡፡ 🌼 ከዚኽም በኋላ በጎንደር ዙሪያ ብዙ መነኰሳት ሰማዕት በሚሆኑበት ዘመን ማኅደረ ክርስቶስ ለአባታችን በራእይ ያየውን ነገረው፤ "አንተ ሰማዕት ለመሆን ሒድ፣ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ግን አይሔድም፣ ብዙ ሥራ ከፊቱ አለ፣ ብዙዎችን ወደ መንግስተ ሰማያት ይጠራልና" ተብያለው በማለት የተነገረውን መልእክት አስረዳው፡፡ አባታችንም "የነብያትን መንገድ ያቀና ሰማዕታትን በፈተና ሁሉ ያጸና አምላክ መንገድህን ያቅናልህ ያስፈጸምህ" ብሎ ልጁን መረቀውና ሰማዕትነት ወደሚቀበልበት ቦታ ሰደደው፡፡ ማኅደረ ክርስቶስም ወደ ንጉሥ ወታደሮች ዘንድ ቀርቦ ስለ ሃይማኖቱ መስክሮ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ አንገቱንም በሰይፍ ከቆረጡት በኋላ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ራስ የሰማዕቱ ማኅደረ ክርስቶስ ራስ መዝሙረ ዳዊት መኃልየ ሰሎሞን ውዳሴ ማርያም ዘመረች፡፡ 🌼 የአቡነ መልክአ ክርስቶስ የዕረፍቱ ቀን በደረሰ ጊዜ በጽኑ ደዌ ታመመ፡፡ ከመረጣቸው ጋር ቃልኪዳን ያደረገ መድኀኔዓለም ለአቡነ መልክአ ክርስቶስም እንዲሁ አደረገ፡፡ "…ድካምህን ተቀብያለሁ፣ በእጅህ የመነኰሱ፣ በመስቀልህ የተባረኩ፣ ከሩቅ አንተን ብለው ደጅህ የመጡ፣ በስምህ መታሰቢያህን የሚያደርጉትን ሁሉ የልባቸውን በጎ መሻት እፈጽምላቸዋለሁ፤ በደላቸውን ሳልመለከት ጸጋ በረከትን እሰጣቸዋለሁ፤ የወዳጆችህን ትውልድ እስከ 15 ትውልድ እምርልሃለሁ" ብሎ ቃልኪዳን ከገባላቸው በኋላ መስከረም 5 ቀን በዕለተ ቀዳሚት በ86 ዓመታቸው ነፍሳቸው ከሥጋው ተለየች። 🌼 ከመቃብራቸውም ላይ ሕሙማን የሚፈወሱበት ድንቅ ድንቅ ተኣምራትን የሚያድርግ ጠበል ፈለቀ፡፡ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ለአገልግሎት ሲጓዙ በመንገድ ላይ ከሞተ 900 ዓመት የሞላውን ሰው ዐፅም አግኝነተው ወደ እግዚአብሔር ጸልየው በመስቀላቸው ባርከው ከሞት አስነሥተውታል፣ ከሞት የተነሣውም ሰው ኢአማኒ ስለነበር ጻድቁ አጥምቀው ለክርስቶስ መንግሥት አብቅተውታል፡፡ 🌼 ጻድቁ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ ነው፡- ለጻድቁ እንደ ሰው እየተላላከ ከበሸሎ ወንዝ ውኃ እየቀዳ ወደ ገዳማቸው የሚያመጣላቸው አንድ በቅሎ ነበራቸው፡፡ በቅሎውም ሰው ሳይጭነው ባዶ እንስራ ወደ ወንዙ ወስዶ በተአምር ውኃው በእንስራ ሲሞላለት ሳያጋድል ይዞ ሩቅ መንገድ ተጉዞ ከአባታችን ገዳም ይደርሳል፡፡ ነገር ግን በአንደኛም ቀን ይህንን አገልጋይ በቅሏቸውን ጅብ በላባቸው፡፡ 🌼 አቡነ መልክአ ክርስቶስም በበቅሏቸው ፈንታ ጅቡን 7 ዓመት ውኃ አስቀድተውታል፡፡ ቅዱሳኑ አቡነ መልክአ ክርስቶስ እና አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በአንድ ዘመን አብረው የኖሩ ሲሆን ኹለቱ ቅዱሳን የቅርብ ወዳጆችም ነበሩ፡፡ ገድላቸው እንደሚናገረው አቡነ መልክአ ክርስቶስ ከግራኝ አህመድ የ15 ዓመት ጥፋት በኋላ የቅዱስ ያሬድን የቅዳሴ ዜማ ትምህርት ጠብቆ ለትውልድ በማበርከት እጅግ የጎላ ድርሻ አላቸው። 🌼 አቡነ መልክአ ክርስቶስ ዐቢይ ጾም ሲገባ ብዙ ጊዜ ብቻውን ሱባኤ ይይዛል፡፡ በዐቢይ ጾም ወቅት ከዕለታት በአንደኛው ቀን በግሸቅ ማርያም ሳለ ክፉ ጠላት በከባድ ረኀብ ፈተነው፡፡ አባታችንም በዚህ አዝኖ ሲጨነቅ ክብርት እመቤታችን ተገጻለት "ሰላም ለአንተ ይሁን ወዳጄ መልክአ ክርስቶስ" አለችው፤ ዳግመኛም "ስለምን ትተክዛለህ? አይዞህ ጽና…" ብላ በልጇ ቸርነት ሰማያዊ ኅብስት መገበችው፡፡ አባታችንም ይህን ምሥጢር ለልጁ ለአባ ሚካኤል ከነገረው በኋላ "እስከምሞት ድረስ ይህን ለማንም አትንገር፣ በኋላ ግን እንደፈቃድህ" አለው፡፡ ቅዱሳን ከውዳሴ ከንቱ ለመሸሽ ሲሉ በሕይወት እያሉ በጎ ሥራቸውን መደበቅ ልማዳቸው ነው፡፡ ከአቡነ መልክአ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ የድባ አቡነ ሙሴ ገዳም ገጽ የተወሰደ።

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።  🌼           🌼 #መስከረም ፭ (5) ቀን። 🌼 እንኳን #ለኢትዮጵያው_ጻድቅ የሚያገለግላቸውን #በቅሎ_ጅብ_ቢበላባቸው በበቅሏቸውቸው ፋንታ #ጅቡን_ለሰባት_ዓመት_ውሃ_እየቀዳ_እንዲያገለግላቸው_ላደረጉት_ለታላቁ_አባት_ለአቡነ_መልክአ_ክርስቶስ_ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።                              ✝ ✝ ✝ 🌼 #አቡነ_መልክአ_ክርስቶስ፦ የእህ ጻድቅ አባታቸ ጣዕመ ክርስቶስ እናታቸው አውጋንያ ይባላሉ፡፡ እነርሱም ልጅ አልነበራቸውምና የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ዘወትር ወደ እግዚአብሔር ይማጸኑ ነበር ነገር ግን "የተባረከ ፍሬ የማትሰጠን ከሆነ ልጅ አትስጠን" እያሉም ይጸልዩ ነበር፡፡ ጣዕመ ክርስቶስና አውጋንያ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፣ ሕጉን ዘወትር የሚጠብቁ፣ ለተቸገሩ የሚራሩ ናቸው፡፡ የተራቡትን በመመገብ የታረዙትን በማልበስ የበረቱ በመሆናቸው ዘወትር ከቤታቸው ድኆች አይጠፉም ነበር፡፡ 🌼 የቅዱሳኑን ልመና የተቀበለ አምላክ የእነርሱንም ልመናቸውን ሰምቶ የተባረከ ልጅ አቡነ መልክአ ክርስቶስን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በምድረ ኢትዮጵያ ሳርካ በሚባል ቦታ ሰኔ 26 ተፀንሶ መጋቢት 27 ቀን ተወለደ፡፡ዕድሜውም ለትምህርት ደርሶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲማር ከዕለታት በአንድ ቀን ከሕፃናት ጋር ሲጫወት እመቤታችን ተገልጻለት "ልጄ ከእንግዲህ አንተ የምትጫወተው ከቅዱሳን መላእክት፣ ከጻድቃንና ከሰማዕታት ጋር ይሁን" አለችው፡፡ እርሱም ዘወትር ጸሎትን መጸለይ ጀመረ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ስለገለጠለት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ወድያው አጠናቀቀ፡፡ 🌼 ከዚኽም በኋላ አቡነ መልክአ ክርስቶስ ገና በለጋ ዕድሜው ስለ ጌታችን መስክሮ ሰማዕት ይሆን ዘንድ በመመኘት በዘመኑ ሰማዕታት ሰማዕትነትን ከሚቀበሉባቸው ቦታዎች ቢሔድም ሰማዕትነት ለእርሱ አልተፈቀደለትም ነበር፡፡ ወደ ወግዳ እና ምድረ ሰርማት የሚባሉ ቦታዎች ቢሔድም የተመኘውን ሳያገኝ ቀረ፣ በዚኽም ጊዜ ቃል ከሰማይ ወደ እርሱ መጣና "ወዳጄ መልክአ ክርስቶስ ሆይ! ሰማዕትነት ክፍልህ አይደለም ይልቁንም እንደ አብርሃም የብዙሃን አባት የሕፃናትና የደካሞች መጠጊያ ትሆናለህ" አለው፡፡ 🌼 ከዚኽም በኋላ ጻድቁ በመንዝ፣ በጎንደር፣ በመቄት፣ በዳውንት፣ በላስታ፣ በዋድላና በሌሎቹም ቦታዎች ተዘዋውሮ የከበረች ወንጌልን በመስበክ ድዉያንን በመፈወስ ብዙ አገልግሏል፡፡ መንዝ ሪቅ በሚባል ቦታ አቅም የሌላቸውን በዕድሜም የገፉትን እናቶችንና አባቶችን ውኃ በመቅዳት ምግብ በማብሰል ዕንጨት በመሸከም አገለገላቸው፡፡ እንግዶች ሲመጡ እግራቸውን አጥቦ ያሳርፋቸዋል፡፡ ሥራዎችን በሚሠራ ጊዜም ከአንደበቱ ጸሎት አይቋረጥም ነበር፡፡ በእንዲህ ያለ ምግባር ዐሥር ዓመት ካገለገለ በኋላ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደቀ መዝሙር ከሆነው ከአቡነ አኖሬዎስ ቤተ ክርስትያን ደብረ ጽጋጃ አባ ጴጥሮስ በተባለ መምህር እጅ መነኰሰ፡፡ 🌼 አባ ጴጥሮስም አቡነ መልክአ ክርስቶስን ካመነኰሰው በኋላ ወደ ቀደመ ቦታው ሔዶ በዚያ ያሉትን በክህነቱ እንዲያገለግላቸው እንዲያመነኵሳቸው መስቀል ሰጥቶ ሸኘው፡፡ እርሱም ተጨማሪ 12 ዓመት አገልግሏቸው በአጠቃላይ 22 ዓመት ሲሞላው የእግዚአብሔር ጸጋ የበዛላት ወለተ ጽዮን ስታርፍ ፍትሐት አድርሶ ከቀበራት በኋላ ወደ ሌላ ቦታ በመሔድ የእግዚአብሔር መልአክ እየመራው ዳውንት ደረሰ፡፡ በዳውንት አጽፍት ሚካኤል ዘጠኝ ዓመት አገልግሎ ብዙዎችን አመነኰሰ፡፡ ከዚያም ወደ ሌላ ቦታ እንዲሔድ እግዚአብሔር ነግሮት ለሔድ ጉዞ ሲጀምር ድንጋዮች ዕፅዋቶች ከነበሩበት ተነሥተው ይከተሉት ጀመር፣ እርሱ ግን በሥልጣኑ በቦታቸው እንዲወሰኑ አዘዛቸው፡፡ ወደ ዋድላ በመሔድ በሰለልኩላ በየጭራ በሐዲስ አምባ እና በደብረ ዳሪት አቡነ አሮን ተመላልሶ ወንጌልን ሰበከ ድዉያንን ፈወሰ ብዙዎችንም አመነኰሰ፡፡ 🌼 ከዚኽም በኋላ ዐብይ ጾምን ወደ ጎንደር ሔዶ ሱባኤውን በዚያ ከቆየ በኋላ ወደ ሰለልኩላ ተመለሰ፡፡ የቅድስት ድንግል ማርያምና የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት አብሮ ይዞ ስለነበር ሀገሩ እንዲባረክ በሰላልኩላ የቅዱስ ሚካኤልን ቤተ ክርስትያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አስገብቶ አከበረ፡፡ ዛሬም ድረስ በዋድላ ሰለልኩላ ሚካኤል በሰለልኩላ ቅዳሴ መገኛነቱ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል፡፡ አባታችንም ጥቂት ጊዜ በሰለልኩላ ሚካኤል እንደቆየ እመቤታችን "…ይህ ስፍራህ አይደለምና ወደ ደብረ አብ ደብረ ወልድ ደብረ መንፈስ ቅዱስ ሒድ" አለችው፡፡ በተነገረው ቦታም ተወስነው የሚጸልዩ ሦስት ደገኛ መነኰሳት አባቶች "በቶሎ ወደዚህ ና ፣በዚህ አንተ የብዙዎች አባት ትሆናለህ" ብለው ወደ አቡነ መልክአ ክርስቶስ መልእክት ላኩበት፡፡ 🌼 አባታችንም ከዳውንት ወደ ግሸቅ መሔጃ መንገዱ ላይ መንኳክ ማርያም ደርሶ አደረ፤ ጸሎት አድርሶ ቦታዋን ቢባርካት ጠበል ፈለቀ፤ የገዳም ሥርዓትንም ሠራላት፡፡ ዛሬም ድረስ አባታችን ያፈለቀው ጠበል ብዙ ተኣምራት እያደረገ ምስክር ሆኖ በቦታው ላይ አለ፡፡አቡነ መልክአ ክርስቶስ የእመቤታችንን ታቦት ይዞ በሽሎ የሚባል ወንዝ ሲደርስ እንደ ሱራፌል ቀንና ሌሊት ሳያስታጉሉ የሚያመሰግኑ ሥዉራን ቅዱሳን በደብሩ እንዳሉ አስተዋለ፡፡ እመቤታችን እየመራችው በደብሩ አናት አድርሳው "ይህ ቦታህ ይሁን፣ ስሙም ግሸቅ ይባል፣ ታቦቴንም በቀኝህ አኑር" አለችው፡፡ዳግመኛም "ልጄ ገዳመ አስቄጥስን፣ ገዳመ ሲሐትን እንደባረከ ይህን ገዳምህንም ይባርክልህ፤ ማህበረ መቃርስ ወማኅበረ ጳኩሚስ፣ ማኅበረ ሖር ወአባ አብሎ፣ ደብረ ኮኖብዮስ እና ሌሎችንም እንድባረከ ይባርክልህ፤ ከአንተ የሚወለዱ አንዱስ እንኳን አይጠፋም፤ በገዳምህ የተቀበረ አይጠፋም" አለችው። 🌼 አባታችንም ገዳሙን ግሸቅ ካደረገ በኋላ ገዳማዊ አንድነቱ እየጠነከረ በመምጣቱ በደብሩ ዙሪያ የነበሩ ክፉዎች "ቦታችንን ሊቀሙን ነው" ብለው በማሰብ ክፋትን ማድረግ ጀመሩ፡፡ በድንግልና ራሳቸውን ጠብቀው ከዓለም የተለዩ ደናግል መነኰሳት ሴቶቹን በማየት እንዲፈተኑ ተንኮል አስበው መነኰሳት አባቶች ውኃ ከሚቀዱበት ማይ ዘአጋም ከተባለ ምንጭ ሴቶች ልጆቻቸውን መላክ ጀመሩ፡፡ መነኰሳቱም በዚህ አዝነው ውኃ ሳይቀዱ በመመለስ ለአቡነ መልክአ ክርስቶስ የሆነውን ሲነሩት "ልጆቼ ይህን ቦታ እመቤታችን ነች የሰጠችኝ፣ "አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ የፈቀዱልህ ቦታህ ነው፣ ለአንተና ለልጆችህ ለዘለዓለም ማደርያ ርስትህ ይሁን፣ ወገን የሌላቸው ታማሚዎች ስምህን በመዘከር ከመከራ ይዳኑ" ብላ ተናግራ ሰጥታኛለች፤ እግዚአብሔር ለኛ ካለው ያድርገው ለእነርሱ ካለው ይሁን" ብሎ ሱባኤ ይዞ እናትና ልጅን ለመነ፡፡ የአካባቢው ሰዎችም እግዚአብሔርን አሳዝነዋልና ከእነርሱ ውስጥ ብዙዎች በሕማም በደዌ ተመቱ፤ ብዙ ሰው መሞት ሲጀምር ቀሪዎቹ ከገዳሙ ክልል ሸሽተው ወጡ፡፡ 🌼 በዚህም ጊዜ የአቡነ መልክአ ክርስቶስ ዝና በመላው ኢትዮጵያ ደረሰ፡፡ ዳግመኛም አባታችን "…የኤርትራን ባሕር ከፍለህ ሕዝብህን ያሻገርኽ፣ እንዳይርባቸው በበረሓ መና ያወረድኽ፣ እንዳይጠሙ ከዓለት ውኃ ያፈለቅኽ አምላክ ሆይ! ዛሬም አንተ ነኽና ውኃ አፍልቅልኝ" ብሎ ቢማጸን በግሸቅ ተራራ ላይ ውኃ ፈለቀለት፡፡ በገዳሙ የነበሩ ሁሉ ከእርሷ ተጠምቀው ጠጥተው ተፈወሱ፡፡ የጎንደሩ ንጉሥ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሙያተኞችን ልኮ በግንብ አሰራት፡፡ የአጼ ኢያሱ ልጅ ልዑል ሰገድ ተክለ ሃይማኖትም ውኃ የሚቀዱበት በቅሎ ሰጥቷቸዋል፡፡ ማኅደረ ክርስቶስ የሚባል ክፉ ጠላት በብዙ ፈተና

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼           🌼  #መስከረም ፭ (5) ቀን። 🌼 እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ታላቁን አስገራሚውን ጣራዊ ክፍት ሆኖ ዝናብ የማይገባው ቤተ መቅደስ ለአነጹ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አሮን_ዘመቄት (መንክራዊ) ለዕረፍት በዓል፣ ጥርሳቸው እያበራ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይሰጥ ለነበሩት #ለአቡነ_ገብረ_ኢየሱስ_ዘጎንደር ለልደት በዓልና እግዚአብሔር ለሚወድ ሃይማኖቱ ለቀና #ለኢትዮጵያዊው_ንጉሥ_ለአፄ_ልብነ_ድንግል ለዕረፍት በዓልና  በሰላም አደረሰን።                            ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 #አቡነ_አሮን_ዘመቄት (መንክራዊ)፡- የመቄቱ አቡነ አሮን ወላጅ አባታቸው የላስታው ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ናቸው፡፡ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የላስታ ነገሥታት የዘር ሐረጋቸው ከንጉሥ ሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ "የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት" ወይም "የላስታ መንግሥት" በመባል ይታወቃል፡፡ የንጉሥ ሰሎሞን ዘር የሆነው መራ ክርስቶስ 3 ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም ጠንጠውድም፣ ግርማ ስዩምና ዣን ስዩም ናቸው፡፡ 🌼 ጠንጠውድም ገብረ መስቀልን ወለደ፣ ገብረ መስቀልም አቡነ አሮንን ወለደ፣ ግርማ ስዩም ይምርሐነ ክርስቶስን ወለደ፣ ዣን ስዩም ደግሞ ገብረ ማርያምንና ላሊበላን ወለደ፡፡ ገብረ ማርያምም ነዓኲቶ ለአብን ወለደ፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ (ዘፍ14፡18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሕዝብንም በቅድስናና በንጽሕና አገልግለው አልፈዋል፡፡ 🌼 አቡነ አሮን ግን ገና በ7 ዓመታቸው ነው ዓለምን ፍጹም ንቀው በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እጅ የመነኰሱት፡፡ በ16 ዓመታቸውም ዋልድባ ገዳም ገብተዋል፡፡ ነሐሴ 5 ቀን ገና ሲወለዱ ሙት አስነሥተዋል፡፡ በሀገራችን እየተዘዋወሩ ወንጌልን ሲሰብኩ የሸዋው ንጉሥ አንኮበር ድረስ ጠርቷቸው ሲሔዱ አዋሽ ወንዝ ሞልቶባቸው አገኙት፡፡ ሲሻገሩም ዳዊታቸውን ወስደባቸው፡፡ "ልጆቼን አመነኰስክብኝ" በሚል ሰበብ ንጉሡ 7 ዓመት በግዞት አስሮ አስቀመጣቸው፡፡ ነገር ግን ከ7 ዓመት በኋላ አቡነ አሮን ተመልሰው በአዋሽ ወንዝ ሲመጡ መልአክ መጣና "መቋሚያህን ወደ ወንዙ ላክ" አላቸው። መቋሚያቸውንም ቢልኩ ከ7 ዓመት በፊት ወደ ወንዙ ገብቶባቸው የነበረውን ዳዊታቸውን ይዘው አወጡ፡፡ ዳዊቱም በውኃው አልራሰም ነበር፣ ይልቁንም አቧራውን አራግፈው ፈጣሪያቸውን አመስግነው ዳዊታቸውን ይዘው ሄደዋል፡፡ ያ ዳዊታቸው ዛሬም ድረስ በጋይንት አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ይገኛል፡፡ 🌼 ሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ ውስጥ የሚገኘው እጅግ አስደናቂ ገዳማቸው ፍልፍል ዋሻ ሲሆን ጣራው ክፍት ነው፣ ክፍት በሆነው ጣራ በኩል ፀሐይ ሲገባ ስለሚያቃጥል ጥላ ይይዛሉ ነገር ግን የጻድቁ ግዝት ስላለበት ዝናብ ወደ መቅደሱ ፈጽሞ አይገባም፡፡ እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ አቡነ አሮን በዋድላ ሜዳ አልፈው ሲሄዱ አንችም ሜዳ ላይ እንደ ኢያሱ ፀሐይን በቃላቸው ገዝተው አቁመዋታል፡፡ ከታች ጋይንት ተነሥተው መንገድ ሲሄዱ በሰንበት ቀን በሬ ጠምዶ ሲያርስ የነበረን ገበሬ "ለምን በሰንበት ታርሳለህ?" ቢሉት "ምቀኛ መነኵሴ" ብሎ በጅራፉ ቢገርፋቸው በሬዎቹ ግን ፈጽሞ አልንቀሳቀስ ብለው ቆመዋል፡፡ በዚህ የተናደደው ገበሬም አቡነ አሮንን መሬት ላይ ጥሎ ገረፋቸው፡፡ እሳቸውም ተነሥተው ሲሄዱ ዛፎች ተነቅለው እየተከተሏቸው፣ ቃልም አውጥተው በሰው አንደበት አመስግነዋቸዋል፡፡ ከአቡነ አሮን መንክራዊ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!።                             ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 #አቡነ_ገብረ_ኢየሱስ_ዘጎንደር፦ የትውልድ አገራቸው ጎንደር ፎገራ ሲሆን መስከረም 5 ቀን ተወለዱ። ጻድቁ የሚታወቁት አንድ ትልቅ ግብር አላቸው። እርሱም ጥርሳቸው እያበራ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይሰጥ ነበር። መነኰሳቱ በጥርሳቸው ብርሃን ብቻ አገልግሎት ያካሄዱ ነበር። ጻድቁ ሲያርፉም ጥርሳቸው የ6 ሰዓት መንገድ ተሂዶ ሲያበራ ታይቷል። በጻድቁ ስም የተጠሩ ገዳማት በትግራይና ሽሬና በጎንደር ይገኛል። ዕረፍታቸው መጋቢት5 ነው። ከአባታችን ገብረ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።                           ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 በዚችም ቀን እግዚአብሔርን የሚወድ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ #የኢትዮጵያ_ንጉሥ_ልብነ_ድንግል ዐረፈ። የንጉሥ የአፄ ልብነ ድንግል በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመስከረም 5 ስንክሳር።

🌼 ቅዱስ ዮሐንስ በተለያዩ ስሞች ይጠራል፡፡ በሕይወቱና በኑሮው ሁሉ ጌታችንን ለመምሰል ይጥር ነበርና ጌታችንም እጅግ ይወደው ስለነበር "ፍቁረ እግዚእ" ተባለ፡፡ የታላቁ ያዕቆብ ታናሽ ወንድም ስለሆነና አባቱም ዘብድዮስ ስለሚባል "ዮሐንስ ወልደ ዘብድዮስ" ተባለ፡፡ ለጌታችን ባለው ቅናትና ከወንድሙ ጋር ሆነው ባሳዩት የኃይል ሥራ እንዲሁም የጌታችንን አምላክነት በመግለጡ "ወልደ ነጎድጓድ" ተብሏል፡፡ ነገረ መለኮትን ከሌሎቹ በበለጠ ሁኔታ አስፍቶና አምልቶ በማስተማሩ "ነባቤ መለኮት ወይም ታኦሎጎስ" ተብሏል፡፡ ኃላፊውንና መጻዒውን ጊዜ በራእዩ ስለገለጠ "አቡቀለምሲስ" ተባለ፣ ይህም በግሪክኛ ባለራእይ ማለት ነው፡፡ የጌታችንን መከራ መስቀሉን እያስታወሰ 70 ዘመን ሙሉ እያለቀሰ ስለኖረና ፊቱም በሀዘን ስለተቋጠረ "ቁጽረ ገጽ" ተብሏል፡፡ ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያስትፈን። በጸሎቱ ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።                                                                               ✝ ✝ ✝ 🌼 #የእስክንድርያ_ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_መቃርስ፦ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ከቍጥራቸው ውስጥ ነው። ይህም አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል የተጠመደ ሆነ የምንኲስናንም ልብስ ሊለብስ ወዶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጣ። በዚያም በመጀመሪያው አባት በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መነኰሰ በምንኲስና ያለውንም ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። 🌼 ይህምእርሱም ሁልጊዜ መጻሕፍትን የሚያነብና ትርጓሜያቸውንም የሚያስረዳ ሁኗልና በትሩፋት ስራ ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ ቅስና ተሾመ። ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልም በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳቱ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔዱ። ከእርሳቸውም ጋር ሃይማኖታቸው የቀና ብዙዎች አዋቂዎች ካህናት ነበሩ በአስቄጥስ ገዳም ከሚኖሩ ከታላላቅ መነኰሳትም ጋራ ስብሰባ አድርገው ለዚች ለከበረች ሹመት ስለሚገባው ሰው እየመረመሩ ብዙ ቀኖች ተቀመጡ። 🌼 ከዚህም በኋላ የተሻለና ለዚች ለከበረች ሹመት የሚገባ ይህን አባ መቃርስን አግኝተው ሊቀ ጵጵስና ሊሾሙት ሁሉም በአንድ ምክር ተስማው። ስለ ትሩፋቱና ስለ ተጋድሎው በአስቄጥስ ገዳም የሚኖሩ ብዙ መነኰሳት ምስክሮች ሁነዋልና ይዘውትም ሊሔዱ ያለ ፍቃዱ ይዘው አሰሩት እርሱ ግን እንዲህ እያለ ይጮህ ነበር። "እኔ ለዚች ለከበረች ሹመት የማልገባ ነኝ እናቴ ሁለት ባሎችን አግብታ ስለነበር" ይህንንም ያለው እንዲተዉት እንጂ እናቱ ግን በአንድ ባል ብቻ የኖረች ሌላ የማታውቅ ንጽሕት እንደሆነች ስለርሷ ብዙዎች ምስክሮች ሁነዋልና። ስለዚህ እርሱ  የተናገረውን ምክንያት አልተቀበሉትም። 🌼 ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ከዚያም ወደ ምስር አውጥተው በመዓልቃ በሚገኘው አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሹመቱ ደብዳቤ በዮናኒ በቅብጥ በአረብ ቋንቋ ተነበበች። 🌼 ከዚህም በኋላ በሹመቱ ወራት በጎ ስራ ትሩፋትን ተጋድሎውን አብዝቶ የሚሰራ ሆነ ። ሁል ጊዜም ለህዝቡ እግዚአብሔርን እንዲፈሩ ያስተምራቸዋል ስለ ነፍሳቸውም ድኀነት ይገሥጻቸው ነበር። 🌼 በሹመቱ ወራትም ከራሱ ከሚገባው ከግብሩ ለቤተ ክርስቲያን ይሰጣል ለድኆችና ለችግረኞችም ይመጸውታል እንጂ ከቤተ ክርስቲያን ገንዘብ ምንም ምን አልወሰደም። በሹመቱም ሃያ ሰባት ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ደስ አሰኝቶ በሰላም በፍቅር ሳለ ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ መቃርስ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመስከረም 4 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ 🌼 "#ሰላም_ለመቃርስ_በእስክንድርያ_ዘተአምነ። መርዔተ ክርስቶስ ይርዓይ መሲሐውያነ። ለእለ ኀረይዎ ሕዝብ ዘይሰመዩ ኄራነ። ጸሊዖ ሢመተ እንዘ ውእቱ ኢኮነ። ወልደ ዳግሚት ብእሲት ይቤሎሙ አነ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመስከረም_4።     

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼           🌼  #መስከረም ፬ (4) ቀን። 🌼 እንኳን #ለሐዋርያው_ለወንጌላዊው ለወልደ ነጎድጓድ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ለልደት_በዓል፣ #ለነዌ_ልጅ_ለቅዱስ_ኢያሱ ለመታሰቢያ በዓሉና ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ለአባ_መቃርስ_ዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #በአንጾኪያ_በሰማዕትነት_ከዐረፉ_ከ_2መቶ_ሰዎች ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                          ✝️ ✝️ ✝️ 🌼 #ቅዱስ_ዮሐንስ_ወንጌላዊ፡- ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌልን ለመስበክ ዕጣ የደረሰው እስያ ስለነበር ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን አስከትሎ ሄደ፡፡ ይኽችውም ኤፌሶን በጥንቱ በታናሽ እስያ በዛሬው የቱርክ ግዛት ውስጥ ከተማ ናት፡፡ ዛሬ ኢያዞሎክ ተብላ የጥንት ታሪኳ ጠፍቷል፡፡ አስቀድሞ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን ሰብኮባታል፡፡ ደቀ መዝሙሩን ቅዱስ ጢሞቴዎስንም በከተማዋ ላይ ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ እርሱም በግፍ እስከተገደለበት ጊዜ ድረስ ቅዱስ ዮሐንስን እየረዳው በከተማዋ ብዙ አገልግሏል፡፡ በኋላ ግን በግፍ ገድለውታል፡፡ 🌼 ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ኤፌሶን ለመሄድ በመርከብ ሲሳፈር መርከቡ በማዕበል ተሰበረ፡፡ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን ማዕበሉ ወደ አንዲት ደሴት አደረሰው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን በመርከቡ ስባሪ ተንጠልጥሎ በባሕሩ ማዕበል መካከል 40 ቀንና 40 ሌሊት ከኖረ በኋላ ማዕበሉ ተፍቶ አብሮኮሮስ ካለበት ደሴት አደረሰውና ተያይዘው ኤፌሶን ከተማ ገቡ። የከተማይቱም ሰዎች እጅግ ክፉዎች ስለነበሩ መጀመሪያ ላይ ቅዱስ ወንጌልን መስበክ አልቻሉም ነበር፡፡ እነርሱም እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ስላወቀ ቅዱስ ዮሐንስ ገና ዕጣው ሲደርሰው በሀዘን አልቅሶ ነበር፡፡ አሁንም ከተማው በገቡ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ምክንያት በመፍጠር ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤቷ እሳት አንዳጅ ሆኖ አብሮኮሮስም ዕቃ አጣቢ ሆነው ተቀጠሩ፡፡ የቀጠረቻቸው ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ጀመር፡፡ ባሮቿ እንደሆኑ ተስማምተው ስለጻፉላት ትደበድባቸውም ነበር፡፡ እነርሱም በታላቅ ጉስቁልና ውስጥ እየኖሩ እያለ በአንዲት ዕለት የአገረ ገዥው ልጅ ለመታጠብ ወደ ውሽባው ቤት ገባ፡፡ በውሽባ ቤቱም የሰይጣን ኃይል ስለነበረበት የመኰንኑን ልጅ አንቆ ገደለው፡፡ የአገሪቱም ሰዎች ሁሉ ለሞተው የመኰንን ልጅ ሊያለቅሱ ሲሰበሰቡ ቅዱስ ዮሐንስም አብሮ ቆሞ ሲመለከት ሮምና መጥታ "በጌታዬ ልጅ ሞት ልትደሰት መጣህን" እያለች ረገመችው፡፡ እርሱም "አይዞሽ አትዘኚ" አላትና ወደ ሞተው ልጅ ቀርቦ በመስቀል ምልክት ካማተበበት በኋላ በፊቱ እፍ አለበት፡፡ የሞተውም ልጅ ድኖ ተነሣ፡፡ የሀገሪቱም ሰዎች እጅግ ደነገጡ፡፡ ሮምናም ደንግጣ "እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን" ብላ ጠየቀችው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም "በፍጹም እኔ አምላክ አይደለሁም፣ እኔ የእርሱ አገልጋዩና ሐዋርያው ነኝ እንጂ" አላት፡፡ ሮምናም ስለበደለቻቸው በደል ሁሉ መሪር ዕንባን እያለቀሰች ይቅር እንዲሏት ለመነቻቸው፡፡ እነርሱም አረጋጉዋት፡፡ ከሕዝቡም ውስጥ ብዙዎቹ በጌታችን አመኑ፡፡ 🌼 ቅዱስ ዮሐንስም ሌሎች ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ ወንጌልን እየሰበከ ከጣዖት አገልጋዮች በቀር ሁሉንም አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ አገልጋዮችን ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ከሾመላቸው በኋላ ወደ ሌሎች አቅራቢያ አገሮች ሄደ፡፡ በመጨረሻም በከሃዲውና በጨካኙ በድምጥያኖስ ዘመን በጣዖት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ ቀረበ፡፡ በፈላ ውኃ ካሠቃዩት በኋለ በፍጥሞ ደሴት አጋዙት፡፡ በዚያም ሳለ ራእዩን ተመልክቶ ጻፈው፡፡ ድምጥያኖስም ከተገደለ በኋላ ከግዞቱ ተመልሶ ሦስቱን መልእክታቱንና ቅዱስ ወንጌሉን ጽፏል፡፡ 🌼 ጌታችንም አስቀድሞ ሞትን እንደማይቀምስ ለዮሐንስ ቃል ገብቶለት ነበርና (ዮሐ 21፡22) ጥር 4 ቀን እንደ ኤልያስና ሄኖክ ሞትን እንዳያይ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስዶታል፡፡ ጌታችን ለዮሐንስ ያልነገረው እርሱም ያላስተማረው ምሥጢር የለም፡፡ ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር "በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ..." ብሎ የጌታችን ነገር ተመራምሮ ለመድረስ ሲል በመሀል መልአኩን በዮርዳኖስ ባሕር ላይ ሲሄድ አገኘው፡፡ መልአኩም የዮርዳኖስን ባሕር በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ ውጭ ሲያፈስ ተመለከተው፡፡ ዮሐንስም ተገርሞ "ምን ማድረግህ ነው" አለው፡፡ መልአኩም "የዮርዳኖስን ባሕር ቀድቼ እየደፋሁ ልጨርሰው ነው" ሲለው ዮሐንስም መልሶ "ታዲያ በእንቁላል ስባሪ ነውን?" አለው፡፡ መልአኩም "አዎን" አለው፡፡ ዮሐንስም "በከንቱ ደከምክ" አለው፡፡ ይህን ጊዜ መልአኩም መልሶ "አንተስ እንጂ ደግሞ የአምላክን መገኘት፣ አኗኗሩንም ተመራምረህ በጥበብ ለማግኘት ብለህ "በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ.." ብለህ ጀምረህ የለምን? አንተ ጌታን ተመራምረህ ካገኘህና ከደረስክበት እኔም የዮርዳኖስን ወንዝ በዚህ እንቁላል ቅርፊት ቀድቼ እጨርሰዋለሁ" አለው፡፡ ዮሐንስም ይህን ጊዜ ደንግጦ ዝቅ ብሎ "ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ…" ብሎ ሀሳቡን ለወጠና ሌላ ታሪክ ቀጠለ፡፡ 🌼 ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ክርስቲያኖችን ሁሉ ወክሎ እመቤታችንን በአደራ የተቀበለ እርሱም ለእመቤታችን በአደራ የተሰጠ ሲሆን እመቤታችንን ከወሰዳት በኋላ ለ15 ዓመት እየተንከባከበ ጠብቋታል፡፡ እናቱም በሕፃንነቱ ስለሞተች እመቤታችን ናት እየተንከባከበች ያሳደገችው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመልኩም ከጌታችን ጋር ይመሳሰል ነበር፡፡ 🌼 ቅዱስ ዮሐንስ ሥዕል የመሳል ተሰጥኦም ነበረው፡፡ ጌታችን በተሰቀለበት ዘመን የነበረው ጢባርዮስ ቄሳር ልጁ በሽተኛ ነበር፡፡ የጌታችንን የማዳን ሥራ እየሰማ እነ ጲላጦስም ስለጌታችን የሚጽፉለትን ይሰማ ስለነበር ልጁን ከጌታችን መቃብር ላይ እንዲያኖሩለት ላከው፡፡ ልጁም ፈጥኖ ተፈወሰለት፡፡ ጢባርዮስ ቄሳርም በልጁ መዳን ምክንያት የጌታችንን ውለታ ማስቀመጥ ፈልጎ የጌታችንን ሥዕሉን የሚሥልለትን ሲያጠያይቅ ቅዱስ ዮሐንስን አገናኙት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ጌታችንን ልክ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለ አድርጎ በመሣል ለጢባርዮስ ቄሳር ሰጠው፡፡ ሲሥለውም በመጀመሪያ ጌታችንን ልክ እንደተሰቀለ አድርጎ ራቁቱን ነበር የሳለው፡፡ ዮሐንስ የሳለው የጌታችን ሥዕልም አፍ አውጥቶ "በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሩሳሌም ራቁቴን ሰቀሉኝ፣ አሁን ደግሞ አንተ ድጋሚ በሮም ራቁቴን ትሰቅለኝን?" ብሎ ተናገረው፡፡ ዮሐንስም እጅግ ደንግጦ "እንዴት አድርጌ ልሳልህ?" ብሎ የሳለውን ሥዕል ቢጠይቀው ሥዕሉም "ከለሜዳ አልብሰህ ሳለኝ" አለው፡፡ ዮሐንስም እንዳለው ከለሜዳ አልብሶ ከሳለው በኋላ ሥዕሉን ትኩር ብሎ ተመልክቶ ቢስመው ከንፈሩ አንድ ቀን ተኩል ያህል ተጣብቆ ቆይቷል፡፡ ዛሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የምትጠቀምባቸውን የጌታችንን ስነ ስቅለት የሚያሳዩ ሥዕሎች መገኛቸው ይህ ወንጌላዊው ዮሐንስ የሳለው ሥዕል ነው፡፡

🌼 "በስመ አብ ወወልደ  ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌼            🌼 #መስከረም ፬ (4) ቀን። 🌼 እንኳን #ከግብጽ_ለኢትዮጵያ_ሊቀ_ጳጳስ ተሾመው ለመጡ በመላው ዓለም እና በኢትዮጵያ ብዙ የዋሻ እና የሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን ላነጹ #ለብፁዓዊ_አቡነ_ሙሴ ዘድባ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ 🌼 #ብፁዕ_አቡነ_ሙሴ_ዘድባ፦ በአባታቸው የእቤታችን ጠባቂ የአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የልጅ ልጅ ሲሆኑ፤ በእናቸው በኩል ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር በቃና ዘገሊላ ሰርግ የተገኘችበት የዶኪማስ የልጅ ልጅ ናቸው። የአባታቸው ስም ቅዱስ ዮስጦስ ሲባል፤ የእናታቸው ስም ቅድስት ጵስርስቅላ (ሶልያና፡ማርያም) ይባላል። 🌼 በሊቀ መላእክት በቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት ታኅሣሥ 8 ቀን ተወለዱ። በዚህች ቀን ከእናታቸው እቅፍ በመውረድ "ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን፤ ከጨለማ ወደ ብርርሃን ላወጣኸኝ" ብለው ፈጣርያቸውን አመስግነዋል። በ40 ኛው ቀን የጌታ ሐዋርያት ቅዱሳን ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ፊሊጶስና እንድርያስ ሆነው ጥር 18 ክርስትናን አቡነ ሙሴን አነሱዎቸው። 🌼 በ3 ዓመታቸው ወላጆቻቸው ለቤተ ክርስቲያን ሰጧቸው። ቅዱስ ፋኑኤልና ቅዱስ ዮናኤል ሕብስት ሰማያዊ እያመጡ ይመግቧቸው ነበር። ከዚህ በኋላ መምህራቸው ዝክረ ጻድቅ ብሉያትንና ሐዲሳትን አስተማራቸው። በወንጌላዊው በቅዱስ ማርቆስ እጅ ዲቁና ተሾሙ። እመቤታችን ማርያምም ለብፁዓዊ ሙሴ ልፋፈ ጽድቅ፣ ሰኔ ጎልጎታን፣ ባርቶስና ራዕየ ማርያምን ሰታቸዋለች። ወገባቸውን ከጠጉር በተሰራ መታጠቂያ ይታጠቁ ነበር። አቡነ ዘበሰማያትም በጀመሩ ጊዜ ሰባቱ ሰማያት ተከፍተውላቸው ከአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ ጀምሮ ሁሉንም ቅዱሳን በግልጥ ያያሉ። ሲሰግዱ እንባቸው ደረታቸውና እግራቸውን እያራሰ በመሬት ይፈሳል። በዓለም ብዙ የዋሻ ቤተ ክርስቲን አንጸዋል። 🌼 የህንፃ ሥራ ከመደመራቸው በፊት 40 ቀን ይጾማሉ። ሁለቱ መላእክት ቅዱስ ፍርክኤልና ቅዱስ ፍናኤል እየረዷቸው መቅደስን ያንጻሉ። የዋሻ ቤተ መቅደስ ሥራ ጎን ለጎን መስቀልና ሌሎች ንዋየ ቅዱሳት ይሠራሉ። የሚሠሯቸው መቅደሶች ከፊሉ የሚታዩ ምዕመናን የሚገለገሉባቸው ሲሆን የቀሩት የማይታዩ ስውራን የሚገለገሉበት ነው። አቡነ ሙሴ ጵጵስና የተሾሙት በ 12ቱ ሐዋርያት በአንድነት ነው። ዘመናቸውን ሁሉ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በመሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስን መንበር አጥነዋል። በድንግልናቸው በንጽሕናቸው የከበሩ 12 ክንፍ የተጎናጸፉ ናቸው። ጥቂቶች ለማየት የታደሉትን ብሔረ ብፁዓን ሄደው አይተዋል። 🌼 አቡነ ሙሴ በግብፅና በእስራኤል መካከል ሲካር በሚባል ቦታ ካገለገሉ በኋላ ጣዖታትን ለማሳፈር ወደ መቄዶንያ ሄደው ጣዖት አምላኪውን ንጉሥ ገሰጹት። ንጉሥ ተቆጥቶ አጥንታቸው እስኪሰበር ድረስ በብረት አስደብድቦ በብረት አልጋ ላይ አስተኝቶ እሳት አነደደባቸው። ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ግን ዳሰው ፈወሷቸው። በማግስቱ ወደ ፍርድ አደባባይ ቢወስዷቸው ምንም እንዳልሆኑ ንጉሡ በማየቱ በንዴት ሰውነታቸውን በሰይፍ አስቆራረጠ። ከሰውነታቸው ደም፣ ውሃ፣ ወተትና መዓር ወጣ። ጌታችንም አድኗቸው "በስምህ የተማፀነውን መልካም ነገር አደርግታለሁ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባላቸው። 🌼 በግብጽ አንስጣስዮስ ቴዎዶስዮስ ተብለው ሢነግሡ መላእክት የአባቱ የዳዊት መንግሥት ቅባት ቀቧቸው፤ የመንግሥት ልብስ አለበሷቸው፤ የመንግሥት ሥርዓት ሁሉ ሰጧቸው። የጣዖታትን ቤት አፍርሱ "ቤተ ክርስቲያንን ሥሩ" በማለት ኅዳር 12 ቀን አዋጅ ነጋሪን ላኩ። ጌታችን በግብፅ ተሶዶ ሳለ ለአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ የተናገረው ትንቢት ተፈፀመ "ከልጅህ የሚወለድ በግብፅ ያሉትን ጣዖቶች አፍርሶ ሃይማኖትን ያጸናል" ብሎ ነበር። እዲሁም ቅድስት አርሴማ ሳትወለድ በስሟ የተሰየመውን ታቦት በግብፅ ያገኙና ያከበሩ ናቸው (ገድለ አርሴማ 7ኛ ተአምር)። 🌼 በግብፅ ደብረ ምጥማቅ ማርያም በመጀመሪያ ሰርተው የቀደሱት አቡነ ሙሴ ናቸው። በተጨማሪ ብዙ የሕንጻ ቤተ ክርስቲያንና የዋሻ ቤተ ክርስቲያን አንጸዋል። እንደ ቅዱሳን ብዙ ድንቅ ተአምር አድርገዋል። ለምሳሌ አውሬ ገድሏቸው ተጠራቅሞ የነበረ አፅም ላይ ጸልየው አራት ሺህ የሞቱ ሰዎችን ከሞት አስነስዋል። 40 ዓመት በንግሥና ከቆዩ በኋላ ከብዙ ተከታዮቻቸው ጋር ወደ አስቄጥስ ገዳም ለምነና ስጓዙ በበረሃው ተርበው ለወደቁት ወደ እግዚአብሔር ሲጸልዩ መና ወርዶላቸው መግበዋል አስቄጥስ ገዳም ሲደርሶ አቡነ መቃርስ ነበሩ የተቀበሏቸው፡፡ 🌼 በአስቄጥስ በአቡነ እንጦንስ ስም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ከፈፀሙ በኋላ አቡነ እንጦንስንና አቡነ መቃርስ በምንኵስና ልብስ፣ በመላእክት አስኬማ፣ በቅንዓት፣ በቀሚስና በቆብዕ ላይ ለ40 ቀን ጸልየው ጥር 22 ቀንተክለ ማርያም ብለው ሰይመው አመነኰሷቸው። በዚያውም አቡነ መቃርስ ከበታቻቸው ሾሙ። በአስቄጥስ ብዙ ተከታዮቻቸውን አመንኵሰው ቀድሞ ወደ፡ሠሯቸው ቤተ መቅደሶች ይልኳቸው ነበር። የቀሩት ደግሞ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ አብረዋቸው መጥተዋል። 🌼 የኢትዮጵያ የመጀመርያው ጳጳስ አቡነ ሰላማ በማረፋቸው ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ ጳጳስ እንዲልኩላቸው ከእጅ መንሻ ጋር ወደ ግብፅ ላኩ። አቡነ አትናቴዎስ ፈቃደ እግዚአብሔር ጠይቀው አቡነ ሙሴ ከአስቄጥስ ገዳም ለኢትዮጵያውያን አባት እዲሆኑ አቡነ ሚናስ ብለው ሾሙ። ከሦስት ሺህ ልጆቻቸው ጋር ሆነው ብዙ ቅርስ ይዘው አባታችን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ሕዝቡ በደስታ ተቀበሏቸው። ብዙ መጽሐፍትን ከአረብኛ ወደ ግእዝ ቋንቋ ተርጉመው ጽፈዋል። ይጽፉበት የነበረው ብዕር አድሮ በማግስቱ ለምልሞ አብቦ ይገኛል። ቀለም ይበጠብጡበት የነበረው የቀንድ ዋንጫም ከመሬት ተጣብቆ ያገኙት ነበር። በእጃቸው ሲያላቅቁት ከመሬት ጠበል ይፈልቃል፣ በጠበሉም ህሙማንን ፈውሰውበታል። 🌼 በኢትዮጵያ 5መቶ የዋሻ ቤተ ክስቲያን ያነጹ ሲሆን በአጠቃላይ በመላው ዓለም ከ10 ሺህ በላይ ቤተ ክርስቲያ ሰርተዋል፣ አንጸዋል (መለከት መጽሔት 2007 ዓ.ም)። በእንቁና በእብነ በረድ ከሠራቸው ቤተ ክርስቲያኖች መካከል በአራራት ደብር (ከምድር ጥፋት በኋላ የኖኅ መርከብ መጀመርያ ያረፈችበት) በጻድቁ ኖኅ ስም፣ አብርሃም ሥላሴን በድንኳኑ ባስተናገደበት ስፍራ በቅድስት ሥላሴ ስም፣ በሕንድ (በሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ መቃብር ቦታ) በቅዱስ ቶማስ ስም፣ በአርማንያና በፋርስ (በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስጋውን ባሳረፉበት ቦታ) በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም። 🌼 በኢትዮጵያ በአቡነ ሙሴ ከታነጹት ቤተ ክርስቲያ ውስጥ የተወሰኑት፦ 1.የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ገዳም (ባለ ሰባት መቅደስ ፎቅ)፣ የረፍታቸው ቦታ፣ በትረ ሙሴያቸውና የእጅ መስቀላቸው ያለበት (ሰሜን ወሎ ዳውንት) 2.አእማድ ቅድስት ሥላሴ ገዳም (መቄት) እንደ አቡነ አሮን መንክራዊ ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማይገባው፣ 🌼 በመጨረሻ ብፁዕ አቡነ ሙሴ በቤተ ሚናስ ቤተመቅደስ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ ገዳም መሰከረም 4 በዕለተ እሁድ ዐረፋ። ወርሃዊ በዓላቸው ወር በገባ በ4 ነው። በተለይ ጋብቻን የሚቀድሱ፣ ክህነት የሚባርኩ፣ መናንያንን የሚያጸኑ አረጋዊን አባት ናቸው። ከአባታችን ከብፁዕ አቡነ ሙሴ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትንና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ የድባ መቅደሰ ማርያም አቡነ ሙሴ አንድነት ያሳተመው መጽሔት ላይ የተወሰደ።