ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Kanalga Telegram’da o‘tish
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Ko'proq ko'rsatish637
Obunachilar
-124 soatlar
-47 kunlar
-1230 kunlar
Postlar arxiv
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ጴጥሮስ_የተባለ_አባ_ብሶይ፦ እርሱም ከላይኛው ግብጽ አክሚም ከሚባል ከተማ ነው። በጐልማሳነቱም ጊዜ የክፉ ሥራዎችን የሚሠራ ሁኖ ነበር በመብላትና በመጠጣትም ይደሰት ነበር። እግዚአብሔርም የነፍሱን ድኅነት ሽፍ ጽኑ ደዌ አምጣበትና ለመሞት ተቃረበ። ነፍሱንም በተመሥጦ አውጥተው የሥቃይ ቦታዎችንም ጥልቅ የሆነች ጒድጓድንም አሳዩት። በዚያም ብሩህ ልብስ የለበሱ ሰዎች አሉ በእጆቻቸውም የሰው በድን ነበር አራት ክፍል አድርገው ለያዩትና "የሰውን ገንዘብ የሚሰርቀውን ሁሉ እንዲህ ያድርጉበታል" አሉት። ይህንንም ነገር በሰማ ጊዜ ጮኸ ከልቡም አዝኖ አለቀሰ ከዚህም በኋላ ነፍሱ ተመለሰች ዐይኖቹንም ወደ ሰማይ አቅንቶ "ጌታዬና ፈጣሪዬ ከዚህ ደዌ ከአዳንከኝ እኔ ስለ ኃጢአቴ ንስሐ በመግባት በፍጹም ልቡናዬ አመልክሃለሁ ከእንግዲህም ከቶ ለዘላለሙ የሴት ፊት አላይም" አለ።
❤ በዚያንም ጊዜ ከደዌው አዳነውና ተነሥቶ ብንዋይ ወደሚባል ገዳም ሔደ መንኰሳቱም ከፈተኑት በኋላ የምንኵስናን ልብስ አለበሱት በግብጽ አገር ሁሉ እስከሚሰማ ታላቅ ተጋድሎን በጾም፣ በጸሎት፣ በመስገድም ተጋደለ። ከሁሉ በላይም ከፍ ከፍ አለ ለመነኰሳትም ትምርት የሚሆኑ የሚጠቅሙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ አንድ ጊዜም እንጀራ ሳይቀምስ ውኃ ሳይጠጣ አንድ ወር ጾመ እንዲህም እየተጋደለ ሠላሳ ስምንት ዓመት ያህል ኖረ።
❤ መላዋንም ሌሊት በጸሎትና በስግደት በመትጋት ቁሞ ያድራል ሰዎች የሚሠሩት ሁሉ ጻድቅም ቢሆን ኃጢአተኛም ቢሆን በፊቱ ግልጥ ሆነ ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመና የካቲት 5 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ብሶይ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_አክርጵስ፦ ይህም አባት የእስክንድር አገር ሊቀ ጳጳሳት ዐሥረኛ ነው። እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጹሕ ቅዱስ ነው። በእስክንድርያ አገርም ቄስ ሁኖ የሚያገለግል ነበር ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኖስ በዐረፈ ጊዜ የእስክንድር አገር ሕዝቡና ኤጲስቆጶሳት መረጡት በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ጵጵስና ሾሙት።
❤ ከዚህም በኋላ እንደ ሐዋርያት መልካም ጒዞን ተጓዘ የእግዚአብሔርን ሃይማኖት ሕይወት የሆነ ሕጉንም እያስተማረ ቅዱሳት መጻሕፍትንም እያነበበላቸውና እያስተማራቸው መንጋዎቹን ይጠብቃቸው ነበር ሁል ጊዜም ይመለከታቸዋል አንድ የብር አላድን ወይም አንድ የወርቅ ዲናርን ጥሪት አላኖረም ከዕለት ምግቡ ከቁርና ከሐሩር ሥጋውን ከሚሸፍንበት ልብስ በቀር ምንም አላከማቸም።
❤ በዚህ ተጋድሎ ዐሥራ ሁለት ዓመት ኑሮ ጌታችንንም አገልግሎ የካቲት5 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አክርጵዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 5 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለብሶይ_ጴጥሮስሃ_ዘተሰምየ። ኵነኔ ሰራቂ በሕልሙ ሶበ ነጸረ ወርእየ። ኀዲጎ ዘትካት ምግባሮ እኩይየ። እንዘ ይፈዲ ብፅዓቶ በከመ ውእቱ ጸለየ። በመዋዕለ ጾሙ ኢጥዕመ ኅብስተ ወማየ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_5።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ብፁዓን እለ ተኀድገ ሎሙ ኃጢአቶሙ። ወእለ ኢሐሰበ ሎሙ ኵሎ ጌጋዮሙ። ብፁዕ ብእሲ ዘኢኈለቈ ሎቱ እግዚአብሔር ኃጢአቶ"። መዝ 31፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 14፥12-16 ፣ ይሁ 5፥15-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 1፥20-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 9፥10-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ አሞኒ የልደታቸው በዓልና የልጃቸው የአቡነ ዮሐኒ የመታሰቢያቸው በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፭ (5) ቀን።
❤ እንኳን አስቀድሞ ራሱን በኃጢአት አስገዝቶ ለነበረ ለጽኑዕ ተጋዳይ #ለአባ_ዕብሎይ ለዕረፍት በዓል፣ ለተጋዳይ ለሆነ #አባት_ጴጥሮስ_ለተባለው አስቀድሞ በድሎት ብቻ ይኖር ለነበረውና በኋላም ነፍሱ ተነጥቃ ሲኦልን አይቶ ከተመለሰ በኋላ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ሠላሳ ስምንት ዓመት ለኖረው #ለአባ_ብሶይ ለዕረፍት በዓል፣ መነሳንሱ የወርቅ ለሆነ ለጻድቅ #አባ_ኖብ ለዕረፍት በዓልና ለእስክድርያ አገር ዐሥረኛ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_አክርጵዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በአስቄጥስ ገዳም በሰማዕትነት ከሞቱ #ከአርባ_ዘጠኝ_መነኰሳት፣ ከሮሜ ሊቀ ጳጳሳት #ከአባ_አቡሊዲስ_ከቡላ_ከአሞኒ_ከዕብሎይ_እናት_ከአበያ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዕብሎይ፦ ይህይ የበጎች አርቢ ራሱን ለሰይጣን በማስገዛት ከኃጢአት ሥራ ምንም የቀረው የለም ያመነዝራል፣ ይሰርቃል፣ ይቀማል፣ ይድላል በዚህም የሰይጣንን ሥራ እየፈጸመ አርባ ዓመት ያህል ኖረ። በአንዲትም ዕለት ከቀኑ እኩሌታ ከበጎቹ ጋር በዱር ውስጥ ሳለ እነሆ የመውለጃዋ ጊዜ የደረሰ ያረገዘች ሴትን አየ ሰይጣንም በልቡ ክፉ ሐሳብን ጨመረ እንዲህም አለ "የተረፈችኝ ኃጢአት አንዲት አለች እርሷም ያረገዘች ሴት ሆዷን ሠንጥቄ በእናቱ ሆድ ሕፃኑ የማተኛበትን አይ ዘንድ ነው"። ያን ጊዜ ተወርውሮ ሔዶ በራስዋ ጠጒር ይዞ ከምድር ላይ ጣላት ሾተልም አንሥቶ ሆዷን ሠነጠቀ ሕፃኑንም በማሕፀኗ ውስጥ እንዴት ሁኖ እንደተኛ አየው እርሷም በጻዕር ተጨንቃ አስቀድማ ሞተች ሕፃኑ ግን በጻዕር እየተሠቃየ ብዙ ቆይቶ ሞተ።
❤ አባ ዕብሎይ (በግ አርቢው የሠራውን ይህን ታላቅ ኃጢአት ተመልክቶ ደነገጠ እጅግም አዘነ መራራ ልቅሶንም። በማልቀስ "ታላቅ ኃጢአትን ሠርቻለሁና ወዮልኝ" አለ። በጎቹ እንደተበተኑ ትቷቸው በእጁ የያዛትን መጠበቂያ በትሩን ብቻ ይዞ አስቄጥስ ገዳም እስከሚደርስ እያለቀሰ ተጓዘ፡፡ ወደ አረጋውያን መነኰሳት አልገባም ይልቁንም ዐሥር ምዕራፍ ያህል ርቆ ከበረሃው ውስጥ ገባ፡፡ ከዱር አራዊት ጋር በጫካ ያድራል እንጂ በቤት ውስጥም አያድርም ነበር፡፡ከአራዊት ጋር የሚኗር ሆነ እንጂ ከዕፅዋትም ፍሬ በየጥቂቱ ይመገብ ነበር። ከዕንባ እየጮኸ አላቋረጠም፡ "አቤቱ በደልኩ ክፉ ሥራንም ሠራሁ ይቅር በለኝ እኔ ኃጢአተኛ የሆንኩ ክፉ ባሪያ ነኝና አንተም ቸር አምላክ ይቅር ባይ አባት ነህና የማይበድል ባሪያ የማይምር ጌታ የለምና አቤቱ ይቅር በለኝ…" እያለ፡፡ እንዲህም እየተደለ አርባ ዓመት ኖረ፡፡ ከሌሊት ቁርና ከቀን ፀሐይ ሐሩርና የተነሣ ሥጋው ደርቆ ጠቆረ፡፡ከዚህም በኋላ እንዲህ የሚል ቃል ሰማ "ስለ ሴቲቱ ደም ጌታ ይቅር ብሎሃልና ጽና በርታ"፡፡ ይህንንም ያለው እንዳይታክትና ዳግመኛ ወደ በኃጢአት ውስጥ እንዳይወድቅ ነው፡፡ ይህንም በሰማ ጊዜ ከሦስት ቀን ብቻ በቀር ያቺን ዓመት እስከሚፈጽም መሪር ልቅሶ እያለቀሰ ተጋድሎውን ጨመረ የእግዚአብሔር መልአክ ከእርሱ ዐሥራ አምስት ምዕራፍ ያህል ርቆ ለሚገኝ ከቶ ሰውን ሳያይ በዚያች በርሀ ለሰባ ዓመት ዘግተው የኖረውን አንድ ገዳማዊ "አንተ ካለህበት ቦታ ወደ ውጭ ሂድና አንድ ሽማግሌ ታገኛለህ፣ ኃጢአቱን ካመነልህ አጽናናው፣ ኃጢአትህ ሁሉ ስለ ሕፃኑም መገደል ተሠርዮልሃል በለው" በማለት አዘዘው።
❤ በዚያም ጊዜ ያ ገዳማዊ ሒዶ አገኘው እርስበርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ። እርሱ ዕብሎይ ግን ያለማቋረጥ ያለቅስ ነበር ገዳማዊውም "የሠራኸውን ንገረኝ በምን ምክንያት ወደዚህ ወጣህ" አለው።እርሱም ሁሉንም ነገረው ያረገዘችውንም ሴት ሆድዋን እንደሠነጠቀ ነገው ገዳማዊውም "ኃጢአትህ ሁሉ ተሠርዮልሃል፣ አባቴ ሆይ ደስ ይበልህ ነገ የእግዚአብሔር መልአክ ወደ አንተ መጥቶ የክርስቶስን ሥጋና ደም ያቀብልሃል" አለው፡፡ የቀዳሚት ሰንበት ዕለትም በነጋ ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሁኖ የማያውቅ ጣፋጭ ሽታ ሸተተ ለአባ ዕብሎይ ገዳማዊውን "ከፍርሀት የተነሳ ነፍሴ ከሥጋዋ ልትለይ ደረሰች" አለው። ይህንንም ባለ ጊዜ በመነኰስ አምሳል መልአኩን አየው እርሱም ተቸገርኩ እግዚአብሔር አዳነኝ፡፡ ነፍሴ ሆይ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሽ። እግዚአብሔር ረዳትሽ ነውና። ነፍሴን ከሞት አድኗታልና። ዐይኖቼንም ከእንባ እግሮቼንም በዳጥ ከመሰናከል። በሕያዋን አገር እግዚአብሔር አገለግለው ዘንድ" እያለ ይዘምር ነበር። የበጎች ጠባቂ የነበረው አባ ዕብሎይም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ በምድር ላይ ወድቆ እንደ በድን ሆነ መልአኩም በሰው አምሳል እጁን ዘርግቶ አነሣው ልቡም ጸንቶ በመልአክ እጅ ከሰማይ የወረደለትን ሥጋውንና ደሙን ተቀበለ መልአኩም ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡
❤ አባ ዕብሎይም ቊርባኑን በተቀበለ ጊዜ ሰውነቱ ሁሉ እንደ በረድ ፀዓዳ እንደ ፋናም ብሩህ ሆኖ በዚያችም ዕለት ሁለቱም ደስ እያላቸው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እስከ ማታ ግን፡ የቀድሞ ጸሎቱን አላቋለጠም እንዲህም እያለ "እኔ ክፉ ባሪያ በየሰባቱ ሰባ ጊዜ በደልኩ ቸር ጌታ ይቅር በለኝ የማይበድል ባሪያ የማይምር ጌታ የለምና"። በዚያችም ዕለት እስከ ሌሊቱ እኩሌታ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አደሩ እርሷም እሑድ ናት። በዚያች ጊዜ ከፊተኛው የሚበልጥ የሽቱ መዓዛ ሸተተ ገዳማዊውም "ወንድሜ ዕብሎይ ና በውኃ ታጠብ ደስ ይበልህም በዚህች ሰዓት ከተቀበልከው መከራ ታርፋለህና" አለው፡፡በዚያንም ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለሁለቱም ቊርባኑን አቀበላቸው፡፡ አባ ዕብሎይም ዐረፈና መላእክት ነፍሱን ተሸክመው እስከ አርያም በረሩ፡፡
❤ ያ ገዳማዊ "እኔ ሽማግሌም ነኝ ሥጋውን መሸከም አልችልም የምቆፍርበትም የሌለኝ ምን አደርጋለሁ" ብሎ የሚያስብ ሆነ በዚያንም ጊዜ ሁለት፡ አንበሶች መጥተው ለሥጋ ሰገዱ መቃብራቸውን ቆፍረው ሥጋውን እንደ ሰው ተሸክመው ወስደው፡ ቀበሩት፡፡ገዳማዊውንም እጅ ነሱት እርሱም ባረካቸውና በሰላም ሄዱ፡፡ ከዚህም በኋላ ያ ገዳማዊ "የሚቀብረኝ አገኝ ይሆን" ብሎ አሰበ ወደርሱም እንዲህ የሚል ቃል መጣ "አትዘን ሥጋህን እኔ አስቀብራለሁ ያለ ሦስት ቀንም አልቀረህም ወደአንተም ሦስት ሰዎች እልካለሁ የበግ ጠባቂው የአባ ዕብሎይን ገድል ንገራቸው እነርሱም ለሌሎች ይንገሩ ከእግዚአብሔርም ምሕረት ተስፋ እንዳይቆርጡ በኃጢአት ለወደቁ አለኝታ ይሆን ዘንድ። በማግስቱም ሦስት ሰዎች መጡ እርሱም የበግ ጠባቂውን የአባ ዕብሎይን ተጋድሎ ነገራቸው እነርሱም እጅግ አድንቀው ጻፉት ከገዳማዊው ዘንድ ሦስት ቀን ተቀመጡ ከዚያም በኋላ ገዳማዊው ተነሥቶ ጸለየ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡ እነዚያም ሁለቱ አንበሶች መጡ መቃብርንም ቆፍረው እንደ፡ሰው ወስደው ቀበሩትና እነዚያ ሦስት ሰዎች ጋር ተጓዙ ወደ፡ አስቄጥስ ወደ አባ መቃርስ ገዳም እስከሚአደርሷቸው መርተው ወሰዱአቸው ሰዎችም የሆነውን ሁሉ ለመነኰሳት ነገሩአቸው፡፡ እነርሱ እጅግ አደነቁ የበግ አርቢው የአባ ዕብሎይ ገድል ጻፉ ሁል ጊዜም እሑድ እሑድ የሚያነቡት ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦የየካቲት 5 ስንክሳር።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፭ (5) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊያኑ_ጻድቃን_ለአቡነ_አሞኒ ለልደታቸው በዓልና ለልጃቸው #ለአቡነ_ዮሐኒም ለመታሰቢያቸው በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_አሞኒ፦ አባታችን የካቲት 5 ቀን አክሱም ውስጥ ሲወለዱ ሰይጣናት የወላጆታቸውን ቤት ከበው በማየታቸው እንደተወለዱ በእጃቸው ቢያመለክቱ በአንድ ጊዜ 60ሰይጣናት ተሸንፈው እንጢስ በነው ጠፍተዋል። አሞኒ ማለት አሸናፊ ማለት ነው። አባ አሞኒ የራስ ፀጉራቸው ልብስ መጎናጸፊያ ሆኖቸው የኖሩ ታላቅና ቀደምት አባት ናቸው። በደመና ተጭነው ኢየሩሳሌም ደብረ ዘይት ድረስ በመሄድ ከአባ ዕብሎይ ጋር ተገናኝተው ብዙ ምሥጢርን፡ አውርተዋል። አባ ዮሐኒንያ ሳደጉት አስተምረው ያሳደጓቸው አባ አሞኒ ናቸው፡፡ የእናቱን ጡት ፈጽሞ ጠብቶ የማያውቀውን የመንፈስ ቅዱስ ልጃቸውን አባ ዮሐኒን እሳቸው እያጫወቱት የታዘዘ አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው ቶራ (ሰሳ) እያጠባችው ነው ያደገው፡፡
❤ አባ አሞኒ ልጃቸው አባ ዮሐኒ አድጎ 12ዓመት ሲሆነው ከዚህም በኋላ ዲቁና ሊያሾሙትና አክሱም ጽዮን ወስደው ሊያስባርኩት ቤተ ካህናት ከተባለው ቦታ ይዘውት ሲሄዱ ልዩ ስሙ ሲሂታ ከሚባለው ቦታ ሲደርሱ ከወገባቸው በላይ እራቁታቸውን የሆኑ እንስራ የተሸከሙ ዐሥር ሴቶች አገኙ፡፡ አባ ዮሐኒም አባታቸውን "አባቴ እነዚህ ደረታቸው ላይ ቀንድ ያላቸው ጽጉራቸው የረዘመ ምንድናቸው? እንደእኛ የሆኑ መስህታን የሚባሉት እነዚህ ናቸውን?" አሏቸው፡፡ አባ አሞኒም"አይደሉም፡ልጄ፡ዝም፡ብለህ፡ሂድ" አሏቸው፡፡በኋላ ግን ትዝ ሲላቸው "በዱር እንስሳት ያሳደኩት ልጄ ወንድና ሴት ለይቶ ሲያውቅ በዚያው ሊሳሳት አይደልምን?" ብለው በማሰብ ዲቁናና ክህነቱ ይቅርበት ብለው ተመልሰው ወደ በዓታቸው ይዘውት ገቡ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ አበይዶ ወደ አባ አሞኒ መጣና እሳቸውን ከአባ ዮሐኒ ጋር እያገለገሏቸው ተቀመጡ፡፡ ዮሐኒ እየጻፈ አበይዶ የሚጻፍበትን ቆዳ እያዘጋጁ ሦስቱም በአንድነት በተጋድሎ መቀመጥ ጀመሩ፡፡
❤ አባ ዮሐኒ ሃያ ዓመት አባ አሞኒ ደግሞ አርባ ዓመት በሆናቸው ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለአባ አሞኒ ተገለጠላቸውና "አሞኒ ሆይ ከእንግዲህስ እግዚአብሔር ወደኔ ና ብሎሃል" አላቸው። እሳቸውም ልጆቻቸውን አባ ዮሐኒንና አባ አበይዶን ጠርተው "በሉ እንግዲህ እኔ ወደ እግዚአብሔር መሄዴ ነውና ጸልዩልኝ" አሏቸው፡፡ ከማረፋቸውም በፊት አባ ዮሐኒን ለብቻቸው ጠርተው "አንተ አባ ዮሐኒ ካሁን በፊት ሲሂታ ላይ ያየሃቸው ሴቶች ናቸው፣ አዳምንም ከገነት ያስወጡ ናቸው፡፡ ወደፊትም እንደ እነርሱ ያለ የደረሰብህ እንደሆነ ካለህበት ገደል ተወርውረህ ውደቅመ በባሕር ውስጥ ጥለቅ" ብለው ነግረዋቸው ዕለት ኅዳር 5 ቀን በሰላም ዐረፉና ወደ ጠራቸው እግዚአብሔር ሄዱ፡፡ ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፬ (4) ቀን።
❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው በአይሁድ እጅ በድንጋይ ተወግሮ ሰማዕትነት ለተቀበለው #ለሐዋርያው_ለከበረ_ቅዱስ_አጋቦስ ለዕረፍቱ በዓልና በምግባር ፍጹም ለሆነ ተጋድሎውም ለበዛ ለታላቁ አባት #ለአባ_ዘካርያስ_ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን፡፡ በተጨማሪ በዚች ቀን ከምትታሰበው፦ ስለ #ኢየሱስ_ክርስቶስ አምላክነትና #ስለሐዋርያው_ቅዱስ_አጋቦስ እውነተኛነት መስክራ #በሰማዕትነት_ከዐረፈችው_ሴት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_አጋቦስ፦ ይህም ቅዱስ ጌታችን ከመረጣቸውና የከበረች ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ፡ወደ ዓለም ከላካቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ ነው፡፡በጽርሐ ጽዮንም አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋር ስጦታውን ተቀብሏል፡፡ ከዚህም፡በኋላ፡እግዚአብሔር የትንቢትን ሀብት ሰጠው፡፡ ስለ እርሱ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንደተነገረ የቅዱስ ጳውሎስን መታጠቂያ አንሥቶ ራሱ እግሮቹን አሠረባትና "የዚህችን መታጠቂያ ባለቤት በኢየሩሳሌም አይሁድ እንዲህ ያስሩታል" ብሎ ትንቢትን ተናገረ፣ትነቢቱም ተፈጸመች፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ሕይወት በሆነ በወንጌልን ትህምርት ሊያስተምር ከሐዋርያት ወጣ፡፡ እያስተማረና ቀና የሆነ የእግዚአብሔርን መንገድ እየመራ ብዙ አገሮችም ዞረ ከአይሁድና ከዮናናውያንም ብዙዎችን የክብር ባለቤት ወደሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅን ሃይማኖት አስገባቸው፡፡ በከበረች በክርስትና ጥምቀትም አነፃቸው (አጠመቃቸው)፡፡ ቅናትን የተሞሉ አይሁድም ብቻውን በኢየሩሳሌም ድንገት ያዙትና ታላቅ ግርፋትን ገረፉት ከዚያም በአንገቱም ገመድ አስገብተው እስከ ከተማ ውጭ ጐትተው በዚያም ነፍሱን እስካለፈች ድረስ በድንጋይ ወገሩት፡፡ በዚያም ጊዜ ከሰማይ ብርሃን ወርዶ በሥጋው ላይ እንደምሰሶ ተተከለ ወደ ሰማይ ደርሶ አሕዛብ ሁሉ ወደርሱ ሲመለከቱ ነበር። እግዚአብሔርም የአንዲቱን አይሁዳዊት ሴት ልቡናዋን ገለጠላት፡፡ እርሷም በውስጥዋ ሽንገላ፣ ቅናትና ጠብ የሌለባት ናት የኦሪትንም ሕግ የምትጠብቅ መልካም ሴት ነበረች፡፡ እርሷም ይህንን ብርሃን አይታ "ይህ ሰው እውነተኛ የእግዚአብሔር ሰው ነው" አለች፡፡ ያን ጊዜም በላይዋ ብርሃን ወረደ፡፡ ከዚህም በኋላ ጮኻ "እኔ በቅዱስ አጋቦስ ፈጣሪ የእግዚአብሔር ልጅ በሆነ በጌታ ኢየሱስ የማምን ክርስቲያን ነኝ"። እግዚአብሔርንም ከፍ ከፍ እያደረገች እግዚአብሔርን ስታመሰግነው በደንጊያ ወግሩዋት ነፍሷንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠች፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛን በሐዋርያው በቅዱስ አጋቦስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዘካርያስ፦ እርሱንም ነፍሱ ከሥጋው በምትለይ ጊዜ አባ ሙሴ "ወንድሜ ሆይ! ምን ታያለህ?" አለው፡፡እርሱም "ለእኔስ ዝምታ ይሻለኛል" አለ ነፍሱም ስትወጣ አባ ኤስድሮስ ሰማይ ተከፍቶ አየ "ልጄ ዘካርያስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያት በር ተከፍቶልሃልና ደስ ይበልህ" አለው፡፡ በእንዲህ ያለ ሁኔታ ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አሜን። ምንጭ፦የየካቲት4 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአጋቦስ_እምአርድእተ_ክርስቶስ ዋሕድ። ከመ ወገርዎ በአዕባን ወቀተልዎ አይሁድ። ተተከለ ብርሃን በአምሳለ ዓምድ። መልዕልተ ሥጋሁ ቅድመ ጉቡአን በዓውድ። እስከ አይሁዳዊት ተመይጠት ወአምነት በወልድ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_4።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 12፥12-28-ፍ.ም፣ ያዕ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 21፥10፥10-15 የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው ቅዱስ አጋቦስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ሕዝብ መካከል ወጣ እያለቀሰ ጸለየ እንዲህም አለ "አቤቱ በጌትነትህ ክብር ፊት የረከሰች አፌን እንዴት እገልጣለሁ በኃጢአት ብዛት የጠቆረ ፊቴንስ እንዴት ቀና አደርጋለሁ ነገር ግን እንደ ይቅርታህ ገናናነት እንደ ቸርነትህም ብዛት ሕዝብህን ይቅር በል አንተ መሐሪና ይቅር ባይ ነህና" በዚያንም ጊዜ ብዙ ዝናም ወረደ እርሱም ጸሎቱንና ንስሓውን እግዚአብሔር እንደ ተቀበለው ኃጢአቱንም እንደ ተወለት አወቀ።
❤ ከዚህም በኋላ አስቀድሞ እንደሚሠራው ተግቶ መጸለዩንና መስገዱን አላጐደለም ነፍሱንም "ዳግመኛ በኃጢአት ውስጥ እንዳትወድቂ ተጠበቂ" በማለት ይገሥጻት ነበር ከዚህም በኋላ ዕድሜውን አድርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ያዕቆብ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት3 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለያዕቆብ_በደዌ_ኃጢኣት_ዘሐመ። ሶበ አመንከሮ ሰይጣን እንዘ ይነብር ገዳመ። እግዚአብሔር ምክሮ ውስተ ሕሊናሁ ዓቀመ። እምቀቢጸ ተስፋ ከመ ይነስሕ ዳግመ። እስከ በጸሎቱ አውረደ እምሰማይ ዝናመ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_3።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት። ወለአእይንትየኒ እምአንብዕ። ወለእገርየኒ እም ዳህፅ"። መዝ 55፥13። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 2፥1-17፣ ያዕ 4፥7-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥9-17። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 7፥12-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ እብሎይ የዕረፍት በዐልና የቅዱስ ኤፍሬም የሥጋ ፍልሰት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን ለባሕታውያን አለቃ #ኑሯቸውም_የመላእክት_ኑሮ_ለሚመስል ከትሩፋቱም የሃይማኖት ፍሬ ለተገኘ ቅዱሳን መላእክትም ክብራቸውን ለመሰከሩላቸው፤ በሌላ ቦታ ያሉ ሰዎችን በቃላቸው ብቻ ይፈውሱ ለነበሩ ለከበሩ አባት #ለአባ_ዕብሎይ ለዕረፍት በዓል፣ ተጋዳይ ለሆነ ለመነኰስ ሰይጣን በፈተና ጥሏቸው ለነበሩና በኋላም ምግብ ሳይበሉ ሳር ብቻ እየተመገቡ 30ዓመት ለኖሩት እግዚአብሔርም ይቅር ብሏቸው ስለእርሳቸው ብሎ በድርቅ ወቅት ዝናብ ላዘነበላቸው #ለአባ_ያዕቆብ ለዕረፍት በዓልና ለታላቁ አባት #ለሶርያዊ_ቅዱስ_ኤፍሬም_ለሥጋው_ፍልሰት በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ቀን #የሶርያዊ_ቅዱስ_ኤፍሬም_የሥጋው_ፍልሰት_ሆነ። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዕብሎይ፦በዕብሎይ ስም የተጠሩት ይኸኛው አባት "የባሕታዊያን አለቃ" የተባሉ ኑሯቸውም "የመላእክትን ይመስላል" የተባለላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ከስደቱ በተመለሰ ጊዜ ወደ ቂሳርያው ኤጲስቆጶስ አባ ባስልዮስ ዘንድ መጥቶ አንድ ላይ አድረው በግብፅ ገዳም ስለነበሩ ቅዱሳን እየተጨዋወቱና እያወዳደሩ ሲወያዩ አደሩ፡፡ በማግስቱም ቅዱስ አትናቴዎስ ታላቅ ራእይን አየ፡፡ይኸውም እስከ ሰማይ የምትደርስ ታላቅ ዛፍ ነበረች፣ ቅርንጫፎቿ እስከ ባሕር ደርሰዋል፡፡ ብዙ ሰዎችም ከቅርንጫፎቿ በታች ተጠልለዋል፡፡ በመካከሏም መሠዊያ ታቦት አለ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለአባ አትናቴዎስ ተገለጠላቸውና "ያየኸውን ራእይ ከአባ ባስልዮስ ጋር ተነጋገር ምሥጢሩን እኔ እገልጥልሃለሁ" አለው፡፡ መልአኩም ምሥጢሩን ለሁለቱ ቅዱሳን አባቶች ተረጎመላቸው፡፡ "ዛፏ በግብፅ አውራጃ የምትሠራ ገዳም ስትሆን ቅርንጫፎቿ መነኰሳት ናቸው፡፡ መሠዊያውም መላእክት የሚጎበኙት የእግዚአብሔር ማደሪያ ርኩሳን መናፍስትን የሚሽር የሐዋርያት አለቃ የጴጥሮስ አምሳል የሆነ አባ ዕብሎይ ነው"በማለት ገልጾላቸዋል፡፡
❤ አባ ዕብሎይ እጅግ ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ መልካቸው እየተለወጠ እንደሚነድ እሳት እየሆኑ ሰውነታቸው የሚያቃጥልበት ጊዜ አለ፡፡በቃላቸው ብቻ ለምጻሞችን ያነጹ ነበር፡፡ በእስክንድርያ የሚኖር አንድ የመቶ አለቃ የአባ ዕብሎይን ዜና ሰምቶ በረከታቸውን ይቀበል ዘንድ ወደ አባ ዕብሎይ እንዲልከው ሊቀ ጳጳሳቱን ቅዱስ አትናቴዎስን ለመነውና እርሱም ከሰባት መነኰሳት ጋር ላከው፡፡ የመቶ አለቃውም አባ ዕብሎይን ባገኛቸውና በተሳለማቸው ጊዜ ዕውር የነበረቸው አንድ ዐይኑ ወዲያው በራችለት፡፡ ዳግመኛም "ሚስቴ በለምጽ ደዌ ትጨነቃለችና እርሷም፡ በአስኬማህ የተማጸነች ናትና እኔ ያገኘሁትን ጸጋህን ለእርሷም ይድረሳት" እያለ ለመናቸው፡፡ አባ ዕብሎይም "በክብር ባለቤት በጌታችን ስም ፈውስ ይሁንላት" ብለው በተናገሩበት ቅጽበት የመቶ አለቃው ሚስት ባለችበት ሆና ከደዌዋ ተፈወሰች፡፡
❤ በአንዲትም ዕለት አቡነ ዕብሎይ ከመኰሳት መካከል ቁሞ "ቤተ ክርስቲያን የምሠራበትን ያስገነዝበው ዘንድ መድኃኒታችን ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ይመጣልና አንዱ ከእናንተ አይሒድ፡ከዚህ ይኑር እንጂ" አላቸው። ያን ጊዜም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከከበሩ ደቀ መዛሙሩቱና ከመላእክቶቹ ጋር መጣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃዋ የሚመሠረትበትንም አሳያቸው።
❤ እርሱም በበጎ ሥራ ሁሉ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ ፍቅርንም ያጸኑ ዘንድ ልጆቹን ይመክራቸው ነበር እየመከራቸውም ፊቱ ተለውጦ እንደ እግዚአብሔርን መልአክ ፊት ሆነ ሁለመናውም እንደሚነድ እሳት ሆነ እነርሱም ፈሩ። እርሱም "ልጆቼ አትፍሩ እነሆ እኔ እሰናበታችኋለሁ" አላቸው። ይህንንም ብሎ ነፍሱ ተመሠጠች በጎ መዓዛም ሸተተ ወዲያውኑ ዐይኑ ተገለጠና "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ርዳኝ ነፍሴንም ወዳንተ ተቀበል" አለ ይህንንም ብሎ የካቲት3 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ምንጭ፦ የየካቲት3 ስንክሳርና መዝገበ፡ቅዱሳን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ያዕቆብ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ ይህን ዓለም ትቶ መነኰሰና በአንዲት ዋሻ ውስጥ የሚኖር ሆነ ያለ ማቋረጥም በቀንና በሌሊት ሁል ጊዜ ይጾማል ይጸልያል በመስገድም ይተጋ ነበር ከበዓቱም ወጥቶ ወደ መንደር አይገባም የሴት ፊትም አያይም እንዲህም ሁኖ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ ዲያብሎስ ከሚከተሉት ክፉዎች ሰዎች ውስጥ ምክንያት ፈጥረው አንዲቷን አመንዝራ ሴት ወደርሱ እንድትገባ አደረጓት በገባችም ጊዜ የኃጢአትን ሥራ እያስታወሰች በፊቱ መጫወት ጀመረች ቅዱስ ያዕቆብም ገሠጻት በገሀነም እሳትም ዘላለም ሲቃጠሉ መኖርን አሳሰባት ደንግጣም ንስሐ ገባች እግዚአብሔርንም የምታገለግል ሆነች። ሰይጣንም መፈታተኑን አልተወውም ከአገር ታላላቆች በአንዱ ሰው በሴት ልጁ ላይ አደረ የሚጥላትና የሚያንከባልላት ሆነ ወደ አባ ያዕቆብም ይወስዳት ዘንድ እርሱም ሊያድናት እንደሚችል አሳበው አባቷም ወደ አባ ያዕቆብ አደረሳትና በላይዋ ይጸልይ ዘንድ ለመነው እርሱም በላይዋ ሲጸልይ ዳነች አባቷም ያ ሰይጣን እንዳይመለስባት ብሎ ከታናሽ ብላቴና ወንድሟ ጋር ከአባ ያዕቆብ ዘንድ ተዋት።
❤ ከዚህም በኋላ ከእርሷ ጋር በኃጢአት እስከ ጣለው ድረስ እርሷን በማሳሰብ በሌሊትም በቀንም በዝሙት ጦር ሰይጣን ተዋጋው በኃጢአትም በወደቀ ጊዜ ስለ ርሷ እንዳይገድሉት ፈርቶ ኃጢአቱ እንዳገለጥ ከወንድሟ ጋር ገደላት ሰይጣንም ደግሞ ቀቢጸ ተስፋ በልቡ አሳደረበት ወደ ዓለም ሊሔድ ከበዓቱ ወጣ። የኃጢአተኛውን ሞት የማይወድ መሐሪ ይቅር ባይ እግዚአብሔርም ጻድቅ የሆነ መነኰስ ወደርሱ ላከ በጐዳናም ሲጓዝ ተገናኘውና ሰላምታ ሰጠው እንዲህም ብሎ ጠየቀው "ወንድሜ ሆይ ምን ሁነሃል አዝነህ ተክዘህ አይሃለሁና የደአሰብህስ ምንድን ነው?"። እርሱም የሆነውን ሁሉ ከዚያች ብላቴና ጋር በኃጢአት እንደ ወደቀና ከወንድሟ ጋር እንደገደላት ነገረው። ያ ጻድቅ መነኰስም "አትፍራ ተስፋም አትቁረጥ እግዚአብሔር መሐሪ ይቅር ባይ ምሕረቱ የበዛ ነውና" አለው። ከዚህም በኋላ የጾም የጸሎት የስግደት ቀኖናን እንዲይዝ አዘዘው።
❤ እርሱም ተመልሶ ከአንድ ፍርኩታ ውስጥ ገባ በውስጡም ራሱን እሥረኛ አደረገ በታላቅ ድካምና በብዙ ችግርም ላይ ታገሠ በመጾም በመጸለይ አብዝቶ በመስገድም ሁልጊዜ ይተጋል ከምድር የሚበቅል ሣርንም የሚመገብ ሆነ አብዝቶ እያዘነ "እግዚአብሔር ይቀበለኝ ይሆን ብዙ በደሌንስ ይተውልኝ ይሆን" ይላል እንዲህም በመጸጸት እየተጋደለ ሠላሳ ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርም ንስሐውን እንደተቀበለለት ሊገልጥ ወዶ በአገር ውስጥ ረኃብን አመጣ ለዚያች አገር ኤጲስቆጶስም "በፍርኩታ ውስጥ ከሚኖር ከመነኰስ ያዕቆብ ጸሎት በቀር ይህ ረኃብ አያልፍም" አለው። በዚያንም ጊዜ ኤጲስቆጶሱ ከእርሱ ጋር ካህናቱንና የዚያችን አገር ሰዎች ይዞ ተነሣ ወደ ቅዱስ ያዕቆብም ደርሰው ስርሳቸው ይጸልይ ዘንድ ለመኑት እግዚአብሔር ይቅር እንዲላቸውና ዝናምንም እንዲአወርድላቸው አባ ያዕቆብም "እኔ እግዚአብሔርን በኃጢአቴ ያሳዘንሁት ኃጢአተኛና በደለኛ ሰው ነኝ" አላቸው። ኤጲስቆጶሱም ስለርሱ እግዚአብሔር ያለውን ነገረው።
❤ የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ በከሀዲው መርቅያኖስም ዘመን ወደ አገሮችም ሁሉ መልእክተኞችን ላከ ከእርሳቸውም ጋር አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የምትከፍል የረከሰች የሃይማኖቱ ደብዳቤ አለች። ከንጉሥ መልእክተኞች ሦስቱ ወደ ደብረ ዝጋግ በደረሱ ጊዜ ያንን ደብዳቤ ለአባ ለንጊኖስ ሰጡት በዚህ "ጽሑፍ እንድታምኑ በውስጡም እንድትፈርሙ ንጉሥ መርቅያኖስ አዝዞአል" አሉት። አባ ለንጊኖስም "ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ሳልማከር እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርም እናንተም ከእኔ ጋር ኑ" አላቸውና የቅዱሳን በድኖች ወደ አሉበት ዋሻ ውስጥ አስገባቸውና "የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን ወይም አታዙኝም የምሠራውንም ካልነገራችሁኝ ሕያው እግዚአብሔር ዐፅማቻችሁን ከዚህ ቦታ አወጣለሁ" አላቸው።
❤ ያን ጊዜ ሰዎች ሁሉም እየሰሙ ከአስከሬናቸው "የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል ከአስከሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ" የሚል ቃል ወጣ የንጉሥ መልክተኞችም ይህን ነገር ሰምተው እጅግ አደነቁ በላያቸውም ታላቅ ፍርሀት አደረባቸው ወደ ንጉሡም አልተመለሱም ራሳቸውን ተላጭተው መነኰሱ እንጂ እስከ ዐረፉም ድረስ ብዙ ዘመን እየተጋደሉ ኖሩ። የከበረ አባ ለንጊዮስ ያማረ ተጋድሎውን ጨርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት 2 ቀን በሰላም ዐረፈ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ለጊዮኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት 2 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለስሒት መኑ ይሌብዋ። እምኅቡዓትየ አንጽሐኒ። ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ"። መዝ 18፥12። የሚበበው ወንጌል ማቴ 5፥32-33።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አንተ አጽናዕካ ለባሕር በኃይልከ። ወአንተ ሰበርከ ርእሰ ከይሲ በውስተ ማይ። ወአንተ ቀጥቀጥከ ለአርእስቲሁ ለከይሲ"። መዝ 73፥13-14። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፊ 6፥10-19፣ ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 28፥1-7። የሚነበበው ወንጌል ማር 16፥14-ፍ.ም። የሚቀደሰው ወንጌል የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም የአቡነ ጳውሊ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "ዳግመኛም ይህ ስም ያልፋል ስማቸውም መነኰሳት ይባላሉ እነርሱም ብዙ ዘመናት ደስ ይላቸዋል እግዚአብሔርም ከቁጣው ቀን አስቀድሞ ከዚያ ያፈልሳቸዋል። ከእነርሱም በኋላ ሰምተው ለመምህሮቻቸው የማይታዘዙ ትውልድ ይነሣሉ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት በቀንና በሌሊት የማይተጉና የማይጸልዩ ናቸው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር ተቆጥቶ ይፈርዳል የማያስተውሉ ሕግ የሌላቸው አረማውያንም ተነሥተው ገዳማቱንና አድባራቱን ያጠፋሉ ብዙ ዘመናትም ምድረ በዳ ይሆናሉ የቅዱሳን መታሰቢያቸው አይጠፋም እግዚአብሔርም በሌሎች ሰዎች ልቡና ይቅርታውን ያሳድርባቸዋል እነርሱም ወደ ገዳማቱና ወደ አድባራቱ በመሔድ በውስጣቸው ዳግመኛ ይኖራሉ ሰይጣንም ወደ ገዳማት ሔዶ በመካከላቸው ጸብን ይዘራል እነርሱም የእግዚአብሔርን ፍቅር ገንዘብ በማድረግ ጨክነው አልታገሡባትምና ምንኵስናቸውን አስኬማቸውን ትተው ወደ ዓለም ይወርዳሉ "በትዕግሥታችሁ ነፍሳችሁን ገንዘብ ታደርጓታላችሁ" የሚለውን ጽሑፍ አላስተዋሉምና"።
❤ እንጦንዮስም "የከበርክ አባቴ ጳውሊ ሆይ ፊትህን አይ ዘንድ የታደልኩባት ሰዓት የተባረከች ናት" አለ። የከበረ አባ ጳውሊም "አሁን ወደ ማደሪያህ ሒድ ቈስጠንጢኖስ ለሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስ የሰጠውን ልብስ እርሱም አንተን ያለበሳትን ያቺን ከአንተ ጋር ይዘሃት ና ሥጋዬን በርሷ ትገንዝ ዘንድ" ብሎ ተናገረው የተሠወረውን በማወቁ እጅግ አደነቀ የተነበየለትንም ትንቢት ሁሉ አመነ። ዳግመኛም እንዲህ አለው "በሰው ሁሉ ላይ እንደተሠራ ከዓለም የምወጣበት ጊዜዬ ቀርቧልና ፈጥነህ ሒድና ተመለስ እርሱም ከአባ ጳውሊ ዘንድ ወጥቶ ወደ በዓቱ እስኪደርስ የሁለት ቀን ጎዳና ተጓዘ ያቺንም ልብስ ይዞ ተመለሰ በመንገድም እየተጓዘ ሳለ በአየር ውስጥ አባ ቡላን የመላእክትንም ማኅበር አየ "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን" ይሉ ነበር።
❤ ሁለተኛም "እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጠህ ሰላምታ ፍቅር አንድነት ይገባሃል የእግዚአብሔር ሰው አንተ ጳውሊ የተመሰገንክ ነህ እንግዲህስ በሰማያዊ መንግሥት ከመላእክት ጋር ደስ ይበልህ የጨለማውን ዓለም ትተህ የብርሃን ሀገርን አግኝተሃልና ወደ ዘላለማዊ ተድላ ደስታ ይወስዱሃልና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆንክ አንተ ገዳማዊ ጳውሎስ በትውልድህ የከበርክና የተመሰገንክ ነህ" እንዲህ እያሉ ተሠወሩ።
❤ የከበረ እንጦኒም "ይህች ወደ ሰማይ የሚያሳርጓት የአባቴ የጳውሊ ነፍስ ናት" አለ ወደ በዓቱም በገባ ጊዜ እንደ ሰገደ ሁኖ እጆቹም በመስቀል ምልክት ተዘርግተው አገኘው አንሥቶም ሸፈነው "አባቴ ሆይ በሰማያዊ ማደሪያህ ሁነህ አስበኝ" ብሎ በላዩ አለቀሰ።
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥቶ በዚያች ልብስ ሥጋውን ገነዘና በላዩ የቤተ ክርስቲያንን የጸሎት ሥርዓት ፈጸመ አደረሰም ከዚህም ቀጥሎ ከእርሱ ጋር የተማከርኩት ነገር የለም ምን ላድርግ ብሎ አሰበ በዚያንም ጊዜ አንበሶች መጡ እጅ ነሡትም ቀድሞ እንደሚያውቁትም ዘንበል ብለው የእግሩን ትቢያ ላሱ መቃብሩን በየት ቦታ እንቆፍርለት እንደሚሉ አመለከቱት እርሱም ምልክታቸውን አውቆ በቁመቱ ልክ ለክቶ ሰጣቸው አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ሁነው ቆፈሩ በአደረሱም ጊዜ "በቃችሁ" ብሎ አመለከታቸው እሊህ አንበሶችም ወጥተው ሰገዱለት። እርሱም ባረካቸውና ወደ ቦታቸው ሔዱ የከበረ እንጦኒ ወደ መቃብር አስገብቶ ዘጋው። ከሰኔል ቅጠልም የተሠራች ዐጽፉን ወሰደ የአባቱን ገንዘብ እንደሚወርስ ልጅ ነውና ወደ እስክንድርያም ሔደ፡፡ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም ገብቶ ከከበረ አባ ጳውሊ የሆነውን ሁሉ ነገረውና ያቺን ከሰኔል የተሠራች ዐጽፍ ሰጠው።
❤ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም የከበረ ጳውሊን ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ያቺንም ዐጽፍ ተቀብሎ በእርሱ ዘንድ አኖራት በየዓመቱም በከበረ በልደት በዓል በጥምቀትም በዓል በመድኃኒታችን ክርስቶስ ትንሣኤ በዓልም ሦስት ጊዜ ይለብሳት ነበር።
✝ ጌታችንም የቅዱስ ጳውሊን የልብሱን ክብር ሊገልጥ ወደደ በዚያችም ወቅት አንድ ወጣት ልጅ ሞተ አባ አትናቴዎስም ያቺን ልብስ በሞተው ላይ አኖራት ወዲያውኑ ተነሣ ይህንንም ያየ ኤጲስቆጶስ አባ ኤስድሮስ ምስክር ሆነ ይችም ተአምር በአገሮች ሁሉ ተሰማች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ በአባ ጳውሊ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ቶማስ_ያደረገው_ተአምር፦ ጌታችን ወደ አዘዘው ሊአስተምር በወጣ ጊዜ ከመንገድ ጥቂት ፈቀቅ አለ ድንገትም የሞተ ጐልማሳ አየ መልኩ እጅግ የሚያምር ነበር ሐዋርያውም "አቤቱ ይህን ጥፋት አይ ዘንድ ወደዚህ አመጣኸኝን ነገር ግን ፈቃድህ ይሁን" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ ስለሞተው ሰው ጸለየ ያን ጊዜ ታላቅ ከይሲ ከደንጊያዎች ውስጥ ወጥቶ በጅራቱ ምድሩን እየደበደበ መጣ "የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ እኔ ካንተ ጋር ምን አለኝ ሥራዬን ልትዘልፍ መጣህን" ብሎ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሐዋርያውም "አዎን ሥራህን ተናገር" አለው። ከሲውም እንዲህ አለ "በዚህ ቦታ አንጻር መልከ መልካም ሴት ነበረች እኔ የምወዳት ናት ይህም ጐልማሳ ሲሰማት አየሁት በሰንበት ቀንም ከርሷ ጋር አደረ ስለዚህም ነክሼ በመርዝ ገደልኩት" ሐዋርያውም "መርዝህን ከሱ ትወስድ ዘንድ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝዤሃለሁ" አለው። ሒዶም ከዚህ ከሞተው መርዙን መጠጠና ወሰደ ወዲያውኑ ተነፍቶ አበጠ ተሠንጥቆም ሞተ የሞተውም ሰው ድኖ ተነሣ። ስለዚች ምልክትም ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን አመኑ እርሱም ሃይማኖትን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው በአባታችን በቅዱስ ቶማስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የደብረ_ዝጋግ_ገዳም_አበ_ምኔት #አባ_ለንጊኖስ፦ ይህም ቅዱስ ከኪልቅያ አገር ነው በዚያም መነኰሰ መምህሩም ክርስቶስን የሚወድ ሰው ከሚሰጠውም ክብር የሚሸሽ ነበር። በዚያንም ጊዜ የገዳማቸው አበ ምኔት ዐረፈ ይህንንም ስሙ ሉክያኖስ የተባለ አረጋዊ መምህሩን አበ ምኔትነት ሊሾሙት መነኰሳቱ ወደዱ እርሱም ደቀ መዝሙሩን ለንጊኖስን ይዞ በጭልታ ከኪልቅያ ወጥቶ ወደ ሶርያ አገር ሔደ በአንዲት ቤተ ክርስቲያንም ግቢ በአንድነት ተቀመጡ በእጆቻቸውም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን ያደርግ ዘንድ ከንቱ ውዳሴና ክብር ሆነባቸው።
❤ አባ ለንጊኖስም በመምህሩ ምክር ወጥቶ ወደ ግብጽ አገር ሔደ ወደ ደብረ ዝጋግ ገዳምም በገባ ጊዜ በደስታ ተቀበሉትና ከእርሳቸው ጋራ ኖረ ከዚያም በኋላ አበ ምኔቱ ዐረፈ ተጋድሎውን ትሩፋቱንና ደግነቱን ስለ አወቁ በደብረ ዝጋግ ገዳም ላይ አባ ለንጊኖስን አበ ምኔት አድርገው ሾሙት። ከጥቂትም ወራት በኋላ መምህሩ አባ ሉክያኖስ መጣ የመርከቦችን ጣሪያዎች እየሠራ በእጆቻቸውም ከሚሠሩት እየተመገቡ በአንድ ልብ በመሆንም በአንድነት ኖሩ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ብዙዎች የሆነ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ከዚህም በኋላ አባ ሉክያኖስ ዐረፈ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን #ለመላእክት_ወገን_ለሆነ_ለገዳማውያን_ባሕታውያን (መናንያን) ሁሉ አለቃ ለሆነ ለከበረ ለታላቁ አባት #ለአባ_ጳውሊ ለዕረፍት በዓል፣ ለከበረ #ለሐዋርያው_ቅዱስ_ቶማስ አንድ ከይስ ነድፎ የገደለው ሰው ተምራትን በማድረግ ከሞት ላስነሳበትና ከይሲውን በመግደል ብዙዎችን አስተምሮ ላጠመቀበት፣ ከእስክንድርያ ውጭ ለደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት የቅዱሳን ዐፅም ቃል በቃል በማጋገር የሃይማኖት ነገር ለተረዳ ለከበረ አባት #ለአባ_ለንጊኖስ ለዕረፍት በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝ ❤ #ርዕሰ_ገዳማውያን_ባሕታውያን (መናንያን) #አባ_ጳውሊ፦ ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ አገር ጴጥሮስ የሚባል ወንድም አለው አባታቸውም የገንዘቡ ብዛት ሊቈጠር የማይቻል እጅግ ባለጸጋ ነበር በዐረፈም ጊዜ የኀዘናቸው ቀን ሲፈጸም ርስቱንና ገንዘቡን ሊካፈሉ ጀመሩ ጴጥሮስም ታላቁን ክፍል ወደራሱ በመውሰድ የሚያንሰውን ለጳውሊ የሚሰጠው ሆነ። ስለዚህም ጳውሊ አዘነና "ከአባቴ ርስት በትክክል ለምን አትሰጠኝም?" አለው እርሱም "አንተ ወጣት ስለሆንክ ታባክነዋለህ እስከ ምታድግ እኔ እጠብቅልሃለሁ" ብሎ መለሰለት።
❤ ስለዚህም ጳውሊ ተቆጣና እርስ በርሳቸው ተጣሉ ይፈርድላቸውም ዘንድ ወደ ዳኛ ሔዱ እነርሱም ወደ ዳኛ ሲሔዱ ሰዎች ተሸክመውት ወደ ሚቀብሩበት ሲወስዱት ብዙዎችም የተከተሉትን የሞተ ሰውን አገኙ ጳውሊም ከተከተሉት አንዱን ሰው "ዛሬ የሞተው ማን?" ነው ብሎ ጠየቀው። ያም ሰው እንዲህ ብሎ መለሰለት "ልጄ ሆይ ዕወቅ አስተውል ይህ የሞተ ሰው በወርቅ በብር እጅግ ባለጸጋ የሆነ ሁል ጊዜ ደስ የሚለው ነበር አሁንም እነሆ ይህን ሁሉ ትቶ ራቁቱን ወደ መቃብር ወደማይመለስበት መንገድ ይሔዳል በኃጢአት ማዕበል ውስጥ እያለ ሙቷልና። አሁንም ልጄ ሆይ ስለ ነፍሳችን ድኅነት ልንታገል ይገባናል እኛ መቼ እንደምንሞት አናውቅምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ውስጥ ገንዘብ ኑሮት ሥልጣንም ኑሮት ሳለ ይህን ሁሉ የተወ የተመሰገነ ነው እርሱ የቅዱሳን ሀገር በሆነች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ታላቅ ክብርን ይቀበላልና"።
❤ የከበረ ጳውሊም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ከልቡ አዘነ እንዲህም አለ "የዚህ የኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምኔ ነው ምን ይጠቅመኛል ከጥቂት ቀኖች በኋላ ትቼው ራቁቴን የምሔድ አይደለሁምን" አለ። ከዚህም በኋላ ወደ ወንድሙ ተመልሶ "ወንድሜ ሆይ ወደ ቤታችን እንመለስ ከእንግዲህ ስለ ገንዘብ ምንም ምን ከአንተ ጋር አልነጋገርም" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ከወንድሙ ሸሽቶ ከሀገሩ ወጣ ከመቃብር ቤት ውስጥም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት መንገዱን ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እየጸለየና እየማለደ ኖረ። ወንድሙ ጴጥሮስም በሀገር ውስጥ እየዞረ ሲፈልገው ሰነበተ ግን አላገኘውም ታላቅ ኃዘንንም አዘነ። የተመሰገነ ጳውሊ ግን ሦስት ቀኖች ያህል በዚያች መቃብር ቤት ሲኖር መብልና መጠጥን አላሰበም ፍርሀትና ድንጋፄም አልደረሰበትም አምላካዊ ኃይል ትጠብቀው ነበርና።
❤ በአራተኛዪቱም ዕለት እግዚአብሔር ወደርሱ መልአኩን ላከ ከዚያም ነጥቆ ወሰደው በምሥራቅ በኵል በምትገኝ በረሀ ውስጥ አኖረው በዚያም የውኃ ምንጭ አለ መልአኩም ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ የከበረ ጳውሊም አራዊት የሚኖሩበትን ጒድጓዶች አግኝቶ ወደ አንዲቱ ፍርኩታ ገባ ልብሱንም ሰኔል ሠርቶ ለበሰ። እንዲህም ብሎ ጸለየ "የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርኀራኄ ከሌለው ጠላት እጅ ጠብቀኝ አድነኝም ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ተጸናኝ ዘንድ ቸርነትህ ወደእኔ ትምጣ የትውልድ ሁሉ ንጉሥ ሆይ ኃይል ጌትነት ክብር ገንዘብህ ነውና ለዘላለሙ"።
❤ በዚያችም ዋሻ ውስጥ ሰማንያ ዓመት ኖረ ከሰውም ከቶ ማንንም አላየም ልብሱም ከሰኔል ቅጠል የተሠራ ነው እግዚአብሔር ወደ ማታ ሁል ጊዜ ወደርሱ ቁራን ይልክለታል ከርሱም ጋራ ግማሽ እንጀራ አለ ያንን ለከበረው ጳውሊ ይሰጠዋል።
❤ የክብር ባለቤት እግዚአብሔርም ቅድስናውንና ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደ ታለቅ አባት ወደ እንጦንዮስ ላከ ይህም እንጦንዮስ በበረሀ ውስጥ መኖርን የጀመረ እርሱ እንደሆነ በልቡ ያስብ ነበር መልአኩም እንዲህ አለው "እንጦንዮስ ሆይ ከአንተ የሁለት ቀን ጎዳና ርቆ በበረሀ ውስጥ ሰው አለ የዓለም ሰዎች ከሚረግጥባቸው የእግሩ ጫማዎች እንደ አንዲቱ ሊሆኑ የማይገባቸው ስለ ርሱም ጸሎት ዓለም ተጠብቆ የሚኖር ምድርም ፍሬዋን የምትሰጥ ጠል በምድር ላይ የሚወርድ በምድር በሚኖሩ ኃጢአተኞች ሁሉ ላይ ፀሐይ የሚወጣ የሰውም ፍጥረት በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ተጠብቆ የሚኖር"።
❤ አባ እንጦንዮስም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ተነሥቶ ወደ በረሀው መካከል ተጓዘ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ሁኖ ጎዳናውንም እንደሚጠርግለት አምኖ ሲጓዝ የሰውና የአራዊትን ፍለጋ አገኘ ያንንም ፍለጋ ተከትሎ ከቅዱስ ጳውሊ በዓት ደረሰ በሩንም አንኳኳ የከበረ አባ ጳውሊ ግን ከሰይጣን ሥራ እንደሆነ አስቦ ታላቅ ደንጊያ ወስዶ ከመዝጊያው ጀርባ አኖረ አባ እንጦንዮስም "ይሰጠኝ ዘንድ ፈለግሁ አገኝ ዘንድ ለመንኩ ይከፈትልኝም ዘንድ ቡሩን አንኳኳሁ" ብሎ አሰምቶ ተናገረ። በዚያንም ጊዜ ከፈተለትና ገባ እርስ በርሳቸውም በመንፈሳዊ ሰላምታ አጅ ተነሣሥተው በአንድነትም ጸልየው ተቀመጡ።
❤ አባ እንጦንዮስም "አባቴ ሆይ ስምህ ማነው?" አለው አባ ጳውሊም "አንተ ስሜን ካላወቅህ እስከዚች ቦታ ለምን ተጓዝክ" ብሎ መለሰለት በዚያችም ሰዓት እግዚአብሔር የእንጦንዮስን ልቡን ገለጠለትና "ገዳማዊ ጳውሎስን አየው ዘንድ ስለተገባኝ እኔ ብፁዕ ነኝ" አለ ከዚህም በኋላ እርስ በእርሳቸው የእግዚአብሔርን ልዕልናውን ቸርነቱን ይነጋገሩ ጀመር በመሸም ጊዜ ቍራ መጥቶ አንዲት ሙሉ እንጀራ ጣለለት አባ ጳውሊም አባ እንጦኒን "አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደሆንክ አሁን አወቅሁ እስከ ዛሬ ሰማንያ ዓመት በዚህ በረሀ ስኖር እግዚአብሔር ሁልጊዜ የሚልክልኝ ግማሽ እንጀራ ነበር እነሆ አሁን ምግብህን ላከልህ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥተው የማዕድ ጸሎት ጸለዩ በልተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት መላ ሌሊቱንም ሲጸልዩ አደሩ። ነግቶ ፀሐይ በወጣ ጊዜም እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ እንጦኒም "አባቴ ሆይ በዚህ ሁሉ ዘመን ሥጋውንና ደሙን ከወዴት ትቀበላለህ?" አለው የከበረ ጳውሊም "እግዚአብሔር መልአኩን ይልክልኛል በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ሰንበት በየሳምንቱ ከሥጋውና ከደሙ ያቀብለኛል በዘመኑም ሁሉ እንዲህ ያደርግልኛል" ብሎ መለሰለት።
❤ ከዚህም በኋላ አባ እንጦኒ አባ ጳውሊን "አባቴ ሆይ ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው። የከበረ ጳውሊም ወደ ሰማይ ተመለከተና ፈገግ አለ። ከዚህም በኋላ አዘነ ጩኾም አለቀሰ አባ እንጦንዮስም "ፈገግ ስትል በአየውህ ጊዜ ደስ አለኝ በአዘንክም ጊዜ አዘንኩ" አለው። የከበረ ጳውሊም እንዲህ ብሎ መለሰለት "እሊህ ተራሮችና በረሐዎች እግዚአብሔር ከሁሉ አገሮች መርጦ ለሚሰበስባቸው ንጹሐን ርግቦች ማደሪያዎች ይሆናሉ"።
+3
#ዜና_ዕረፍት
በደብራችን በግራር ደብረ አባይ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት የድጓ እና የመጽሐፍት መምህር ቃለጸድቅ (ወልደ ሐዋርያ ) በጋጠማቸው ድንገደተኛ አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል ።
በአባታችን እልፈተ ህይዎት ላዘኑ
ለቤተሰባቸው ፣ ለማህበረ ካህናት እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጸናናት እንመኛለን
የአባታችን በረከታቸው ይደርብን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለዘመ_አስተርዮ_የመጨረሻ_ሳምንት ለቅበላ #ለዕለተ_እሑድ_ሰንበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር_ዘቅበላ፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "#ወብዙኃን_ኖሎት_መጽኡ ወስዕኑ ከሢቶታ ለዕብን እምአፈ ዐዘቅት እስከ ይመጽእ #ያዕቆብ ዘክቡት ውስተ ሐቋሁ ዘሀሎ ይሠጐ እምሰብእ ከሠተ ወአስተየ መርዔቶ ወከማሁመ #መጽኡ_ብዙኃን_ነቢያት ወሰስዕኑ ከሢቶታ ለጠጥምቀት እስከ ይመጽእ #ዐቢይ_ኖላዊ እምሰማይ ከሠተ ወአጥመቀ ብዙኃነ አሕዛበ በውስቴታ መንክር ተአምሪሁ ለመድኀኒነ በከመ ወፅአት #በትር_እምሥርወ_ዕሤይ በአምሳለ #በትረ_ያዕቆብ በዘይርዒ አባግዒሁ #ይእቲኬ_ማርያም_ይእቲ ወበእንተ ዘይቤ ትወፅእ በትር ወየዐርግ ጽጌ ውእቱኬ ዋሕድ ውእቱ ውእቱኬ #ወልደ_አምላክ_ውእቱ። ትርጉም፦ #ብዙ_እረኞች መጡ ከጉድጓድ ውኃ ላይ የተገጠመው ድንጋይ ማንከባለልና በጎቻቸውን ውኃ ማጠጣት አልቻሉም #ያዕቆብ_ሲመጣ ግን ድንጋዩን ከጉድጓዱ ላይ አንሥቶ መንጋዎቹን አጠጣቸው፣ እንዲሁም #ብዙ_ነቢያት_ቢመጡም ከሰማይ የሚመጣው #ታላቅ_እረኛ_ክርስቶስ_እስኪመጣና_የጥምቀት ምሥጢር ከፍቶ ብዙ አሕዛብን በውኃ እስከያጠምቅ ድረስ የጥምቀትን ምሥጢር ሊገልጧት አልተቻላቸውም። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አግረረ ለነ አሕዛበ ወሕዝበ ታሕተ እገሪነ። ወኀረየነ ሎቱ ለርስቱ። ሥኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ"። መዝ 46፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 9፥1-17፣ 1ኛ ጴጥ 2፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥1-14። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 4፥1-28። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም ዕለተ ሰንበት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ ጻድቁ በሐይቅ ደሴት የተቀበሩ ቢሆንም ቀድሞ በሚያገለግሉበት በድፍን ምስራቅ ጎጃም ድርቅና ርኃብ ስለሆነ በደብረ ፅሞና ገዳም ይኖሩ የነበሩት አባ መቃርስ ዐፅማቸውን አፍልሰው በማምጣት በደብረ ዲማህ አጠገብ በስማቸው በተሰራው በደብረ ፅሞና ቤተ ክርስቲያን በክብር ሲያሳርፉት ወዲያው ዝናብ ጥሎ ድርቁም ጠፍቷል፡፡ ዐፅማቸውን ተሸክማ ያመጣችው በቅሎም ወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ሲኖዳ ለማይወልዱ መካኖች እጅግ ልዩ ቃልኪዳን ነው የተሰጣቸው፡፡ መቃብራቸውን እየዞሩ እምነታቸውን እየተቀቡ ገድላቸውን እየታሹ የማይወልዱ መካኖች የሉም፡፡ ከሩቅም ሆነው በስማቸው ተስለው እምነታቸውን ተቀብተው የሚወልዱ በጣም ብዙዎች ናቸው፣ እንኳንስ ሰው ይቅርና ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ወልዳለችና!።
❤ የጻድቁ ሌላኛው በስማቸው የተሰየመውና እጅግ ተአምረኛው ታቦታቸው ዛሬም አቡነ ሲኖዳ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከአ.አ 180 ኪ.ሜ ርቆ ከጣርማ በር አልፎ ሞላሌ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡ በሰሜን ሸዋ በሚገኘው በዚህ ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በዘመናችንም በጣም በርካታ ተአምራት ይደረጋሉ፡፡ ለጻድቁ የተሰጠችውን የስዕለት በግ ጅብ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሊበላ ሲል ቀንዱን ነክሶ ደርቆ ሞቶ ሲገኝ በጉ ግን ምንም አልሆነም፡፡ አቃቢቷም እንዲሁ ከትልቁ ተራራ ሥር በትልቅ ቅል ውኃ ቀድተው ሲመለሱ ገመዱ ተበጥሶ ቅሉ ከነውኃው ከትልቁ ገደል ገብቶ ድንጋይ ላይ ቢያርፍም ቅሉ ሳይሆን ድንጋዩ ነው የተሰበረው፡፡ የአካባቢው ነዋሪም "በጉ ጅብ ገደለ፣ ቅሉ ድንጋይ ሰበረ" እያሉ ጻድቁን ያወድሷቸዋል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ሲኖዳ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፩ (1) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮያዊያኑ_ጻድቅ ኤርትራ አገር የሚገኘው #ታላቁ_ገዳም_ደብረ_ጽጌ_ሰፍኣ ለመሰረቱት ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ደቀ መዝሙርቶቻቸው (ልጆቻቸውን) ከሰማይ ስንዴና ወርቅ በማዝነብ ውሃውን በመባረክ ወይን አድርገው ይመግባቸው ለነበሩ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_እንድርያስ_ዘደብረ_ጽጌ_ሰፍኣ ለዕረፍት በዓል፣ ለመካኖች ልዩ ቃል ኪዳን ለተሰጣቸው ለታላቁ አባት ለሰማዕቱ #ለአቡነ_ሲኖዳ ለፍልሠተ ዐፅማቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_እንድርያስ፦ የእናታቸው ስም ቅድስት ዓመተ መንፈስ ቅዱስ የአባታቸው ስም ቅዱስ ዘአማኑኤል ይባላል። የተወለዱትም ትግራ እንደርታ አካባቢ ነው። እናትና አባታቸው ልጅ ስሌላቸው ዘወትር ወደ እግዚአብሔር እየጸልዩ እናታቸውም "አንተ ደስ የሚያሰኝ ልጅ ካልሰጠኸኝ ማኅፀኔን ዝጋ" ይሉ ነበር። የእመቤታችንንም ዝክር በየወሩ ይዘክሩ ነበር። እመቤታችንም አንድ ቀን ተገልጻ "ደስ የሚያሰኝ ልጅ ትወልዳላችሁ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ቀን ነው" አለቻቸው። አባታችን ልክ ግንቦት አንድ ቀን ሲወለዱ በእናት በአባታቸው ቤት ብርሃን ወረደ። አርባ ቀን ሲሞላቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ሊያስነሷቸው ወሰዷቸው ሲጠመቁም አባታችን "በአብ ስም አምናለሁ በወልድ ስም አምናለሁ በመንፈስ ቅዱስ አምናለሁ" አሉ። ስመ ክርስትናቸውም መሐረነ እግዚእ ተባሉ።
❤ አቡነ እንድርያስ የስለት ልጅ ስለ ነበሩ 3ዓመት ሲሆናቸው ወደ ቤተ ክርስቲያም አስገባቸው። እርሷቸው ቀን ቀን እያገለገሉ እየተማሩ ሌሊት ሌሊት እየጸለዩ ይሆሩ ነበር እመቤታች በሌሊት ሲጸልዩ ተገልጻ በክንፍ ጋረደቻቸው። ከዚያም ዕድምያቸው ለጋብቻ ሲደርስ እናትና አባታቸው "እናጋባህ" አሏቸው እርሳቸው ግን "አልፈልግም" ብለው በሌሊት ተነስተው ወደ ደብረ ፀሎላ ገብተው በአባ ገብረ ክርስቶስ እጅ በ12ዓመታቸው መነኰሱ። የምንኲስና ስማቸውም አባ እንድርያስ ተባሉ። በዚያ ጊዜ ዲቁንና ክህነት የሚሰጥ ጳስስ በኢትዮጵያ ስላልነበረ አበምኔቱሙ አባ ገብረ ክርስቶስ "ዲቁንናንና ክህነት እንድትቀበል ወደ ግብጽ እንሒድ" አሏቸው። አባታችን "አይሆኑም" ሲሉ ጌታችን በሌሊት ተገልጾ "እንድርያስ ወዳጄ ለምን እቢ አልክ እኔ ምርጬሃለሁና" አላቸው አባታችን ጠዋት ተነስተው "ኑ እሒድ" አሏቸው። ከዚም ወደ ግብጽ ሒደው ዲቁንናንና ክህነት ተቀብለው ወደ ገዳማቸው ተመለሱ።
❤ አንድ ቀን አባታችን ሲቀድሱ ከምድር አንድ ሜትር ከፍ ብለው እርሳቸው የቆሙበት ቦታ ውሃ አፈለቀ። ይህን ያዩ መነኰሳት ለአበምኔቱ ለአባ ገብረ ክርስቶስ ነገራቸው አበምኔቱ መጥተው የፈለቀው ውሃ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ አቡነ እንድርያስ አስጠርተው "አንተ ከዛሬ ጀምሮ ከእኛ ጋር ለሥራ መውጣት የለብህ ስእኛ ጸልይን እንጂ" አሏቸው እርሳቸው አይሆኑም ብለው ከእዛ ገዳም ወጥው "ወደ ኢየሩሳሌም ሔጄ ጌታ የተጠመቀበትን ማየ ዮርዳኖስ አያለው" ብለው ከኢትዮጵያ ተነስተው ወደ ኤርትራ አዲ ሞገስ ወደሚባል አካባቢ ሲደርሱ አንድ ታምነ እግዚእ የሚባል ገበሬ "አባቴ የንስሐ አባት ሁኑኝ" አላቸው። አባታችን "በአገራችሁ ካህን የለም እንዴ?" አሉት እርሱም "አዋ የለም" አላቸው አባታችንም ሕዝቡ አስተምረው አጥምቀው ጉዞ ወደ ኢየሩሳሌም ጀመሩ። ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ሲደርሱ ጌታ ተገልጾ,"ይህን ቦታ ዳግማዊ ኢየሩሳሌም አድርጌልሀለው ውሃውም የዮርዳኖስ ውሃ ይሆንልሃል እና ከዚህ አትህድ" አላቸው።
❤ አባታችንን አቡነ እንድርያስ ተከትለው ወደዚህ ገዳም ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ተማሪዎች ወደ እሳቸው መጡ እነዚህ ልጆቻቸውን አመነኰሷቸው። ለእነዚህ ልጆቻቸው ቀድሞ በመንገድ ላይ አስተምረው ካጠመቁት ገበሬው ከታምነ በእግዚእ እንደ ሰው እየተላላከ እህል የፈጭልላቸው የሚያገለግላቸው ገብረ ኄር የሚባል አህያ ነበራቸው ሰይጣንም ቀንቶ ይህንን አህያ ብገለው ልጆቹ በርሃብ ምክንያት ይበተናሉ ብሎ አስቦ በአንበሳ አድሮ ገደለው። አንበሳው ደግሞ አቡነ እንድርያስ በአንድ መርገም ቃል ገደሉት። ልጆቻቸውም ምግብ ሲያጡ ጥለው ሊሆዱ ሲሉ አባታችን ትዕግስት ይኑራችሁ አላቸው። እነርሱም እንቢ ብለው ወደ ታምነ በእግዚእ ሆዱ። ታምነ በእግዚእ ባለቤቱን "ምግብ አዘጋጂላቸው" አላት እሷም "አቡነ እንድርያስ ሳይመጦ አላዘጋጅ" አለችው እነርሱም እቢ ስላለቻቸው ልጆቹም "እኛ የአባታችን ምክር ስልሰማን ነው የከለከለችን" ብለው ወደ ገዳማቸው ተመለሱ።
❤ አቡነ እድርያስም ልጆቹ ከተመለሱ በኋላ ውሃ የሞሉ እንስራዎች ነበሩና ቢባርኩት የወይን ጠጅ ሆነ። እንደ ገናም "እግዚአብሔር ዘላለም" ብለው ሲጸልዩ ከሰማይ አርያም ስንዴ ዘነበላቸው ያንን ለ14 ዓመታት ተመገብ ይህ ሲያልቅ ደግሞ ወርቅ አዘነቡላቸው ወርቁ በእህል እየለወጡ ተመገበሩ። አባታችን ልጆቻቸውን "እኔ ወደ እግዚአብሔር የምሄድበት ቀን ደርሷል" አሏቸው። ልጆቹም "አንተ ከሆድክ ማን ከሰማይ ስንዴና ወርቅ እያዘነበ ውሃው ወይን እያደረገ ይመግበናል" አሏቸው እሷቸው "እኔ ከሞትኩ በኋላ እናተም ከዐሥር ቀን በኋላ ወደ ትመጣላች እኔ ቦታ ላዘጋጅላችሁ ነው የምሆደው" ብለዋቸው በ126 ዓመታቸው የካቲት 1 ቀን ዐርፈዋል። ልጆቻቸውም እንዳሏቸው በአንድ ቀን በአረማውናን ሰማዕትነት በመቀበል የካቲት 10 ቀን ዐርፈዋል። ከአባታች ከአቡነ እንድርያስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከኤርትራ ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ገዳም የተገኘ ማስታወሻ።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ሲኖዳ፦ ሲኖዳ ማለት "ታማኝ" ማለት ነው፡፡ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ሲሆኑ የሸዋ ባላባት ልጅ ናቸው፡፡ በጎጃም ደብረ ዲማህ አጠገብ ደብረ ፅሞና በተባለው ቦታ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ያመልኩት የነበረውን ትልቅ ዘንዶ አቡነ ሲኖዳ በመስቀል ባርከው ከሁለት ሰንጥቀውታል፡፡ ሰዎቹንም አስተምረው አሳምነው አጥምቀው የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸዋል፡፡ ጻድቁ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓይነት ገድል አላቸው፡፡ ለዘንዶ ምግብ እንዲትሆን ግብር ሆና የተሰጠችውን ሴት ልጅ ከጫካ አግኝተው ዘንዶውን በመስቀላቸው አማትበው ገድለው ልጅቷን አድነዋታል፡፡
❤ በዘመናቸው ነግሦ የነበረው "ሕዝበ ናኝ" የተባለው ንጉሥ በሰዎች ወሬ "ንግሥናዬ ለሌላ ይሰጣል ትላለህሳ" በማለት ጻድቁን እጅና እግራቸውን አስሮ ካሠቃያቸው በኋላ እጃቸውን አስቆረጣቸው፡፡ ነገር ግን ለአቡነ ሲኖዳ እመ ብርሃን የብርሃን እጅ ተከለችላቸው፡፡ በጌቴሴማኒ ያለችው ሉቃስ የሳላትና ስርጉት የተባለችው የእመቤታችን ሥዕል በየጊዜው እየተገለጠች ታነጋግራቸው ነበር፡፡ ንጉሡ በስደትና በግዞት ብዙ እያሠቃያቸው ሳለ መልአክ መጥቶ ዕለተ ዕረፍታቸውን ነግሯቸው እሳቸውም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ጠርተው ከተሰናበቷቸው በኋላ ነው ንጉሡ በኅዳር 17 ቀን አንገታቸውን ያሰየፋቸው፡፡ ከአንገታቸው ውኃ፣ ደምና ወተት ፈሷል፡፡
