uz
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Ko'proq ko'rsatish
637
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-1230 kunlar
Postlar arxiv
❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ጥር ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን #ለቅዱስ_እግዚአብሔር ስለ ልጅ ወልድ በዮርዳኖስ ለመሰከረበትና ቃና ዘገሊላን አሰመልክቶ መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ #372 ዓመት አንቀላፍተው ለተነሱ #ለሰባቱ_ደቂቅ ስማቸው #ለቅዱሳን_ለአርሰሌዳስ_ለዱአሚዶስ_ለአውጋንዮስ፣ #ለድሜጥሮስ_ለብርጥስ_ለእስጢፋኖስና_ለኪራኮስ ዕረፍትና ለአባ ነካሮ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ ሰላምና በጤነሠ አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦#ለቃሮስና_ለሰሚኖስ_ለመታሰቢያቸው  እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን።                                                                                      ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰባቱ_ደቂቅ፦ እነዚህም  ስማቸው አርሰሌዳስ፣ ዱአሚዶስ፣ አውጋንዮስ፣ ድሜጥሮስ፣ ብርጥስ፣ እስጢፋኖስና ኪራኮስ ናቸው። እሊህ ቅዱሳን ሃይማኖታቸው ለቀና ለታላላቅ የአገር ሰዎች ልጆቻቸው ናቸው እነርሱም ክርስቲያኖች እንደሆኑ በከሀዲ ንጉሥ ዳኬዎስ ዘንድ ሰዎች ነገር ሠሩባቸው ወደርሱም አስቀርቦ ለጣዖት እንዲሰግዱ ግድ አላቸው እምቢ ባሉትም ጊዜ ከልባቸው ጋር ይመክሩ ዘንድ ቀጠሮ ሰጣቸውና እርሱ ወደ ተግባሩ ሔደ። ❤ እሊህ የተባረኩ ሰባቱ ደቂቅም ወደ ቤታቸው ሔዱና ገንዘባቸውን ለድኆችና ለምስኪኖች በተኑ የቀረውንም ለስንቃቸው ይዘው ሔዱ ከከተማውም በስተ ምሥራቅ በዋሻ ውስጥ ተሠውሩ ብልና አስተዋይ የሆነ ወጣት ዱአሚዶስ ወደ ከተማ ሒዶ ምግባቸውን በመግዛት የሚያገለግላቸው ሆነ የሰማውንም ነገር ይነግራቸዋል። ንጉሥ ዳኬዎስም ከሔደበት በተመለሰ ጊዜ እሊህን ሰባት ልጆች ፈለጋቸው በዋሻ ውስጥ ተሸሽገው እንዳሉ በነገሩት ጊዜ የዋሻውን አፍ በደንጊያ እንዲደፍኑ አዘዘ የእነዚህንም ቅዱሳን ነፍሳቸውን በተኙ ጊዜ ጌታችን ወሰደ። ሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመትም እንዲአንቀላፉ አደረጋቸው ከንጉሥ አሽከሮችም ስማቸው ቴዎድሮስና መቅዶስዮስ የተባሉ ሁለት የእርሳስ ሠሌዳዎች ወስደው የእሊህን የሰባት ደቂቅን ዜናቸውንና የዘመኑን ቊጥር ጽፈው ቀርጸው ከዋሻው አፍ አኖሩት። ❤ ከዚህም በኋላ ዳኬዎስ ሞተ እስከደጉ ንጉሥ እስከ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ብዙ ነገሥታት ነገሡ በዚህም ደግ ንጉሥ ዘመን ትንሣኤ ሙታን የለም የማሉ ከሀድያን ሰዎች ተነሡ እሊህም ሰባቱ ደቂቅ የሚነቁበት ጊዜ ሲቀርብ ለበጎቹ ማደሪያ ሊአሠራ ሽቶ ደንጊያ እየፈለገ የዋሻውን አፍ አንድ መኰንን ከፈተው። እሊህ ቅዱሳንም በሦስት መቶ ሰባ ሁለት ዓመት በነቁ ጊዜ ምግባቸውን ይገዛ ዘንድ ዱአሚዶስን ላኩት የአገር ሰዎችም የዳኬዎስ ስም የተጻፈበትን ዲናር በእጁ ውስጥ በአዩ ጊዜ የተሸሸገ የወርቅ ሣጥን ያገኘ መስሎአቸዋልና ይዘው ወደዳኞቹና ኤጲስቆጶሳት አቀረቡት በመረመሩትም ጊዜ እነርሱ ሰባት ልጆች እንደሆኑ ነገራቸው። በሔዱም ጊዜ ፊታቸው እንደ ፀሐይ ሲበራ አገኙአቸው ኤጲስቆጶሱም የዕርሳስ ሠሌዳ አየ አንሥቶም በላዩ የተጻፈውን ዜናቸውንና የዘመኑን ቊጥር አነበበ በዳኬዎስ ዘመን እንዳንቀላፉ ሕዝቡ ሰምተው እጅግ አደነቁ። እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ላኩ እርሱ መጥቶ እጅ ነሣቸው ከእርሳቸውም ተባረከ ከሠራዊቱ ጋር ከተነጋገሩም በኋላ ሁሉንም ባረኳቸውና በምድር ላይ ተኙ ነፍሳቸውንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ በዚያቺም ዋሻ ውስጥ ቀበሩአቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የእሊህም  ቅዱሳን በረከት ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ነካሮ፦ ይህም ቅዱስ ሰው ሳያውቀው በሥውር የሚጋደል ሆነ እርሱም ከምንጣፉ በታች እሾህ ይጐዘጒዛል ጤና አግኝቶ እንዳይተኛ ነው በቀንና በሌሊትም ለጸሎት ይተጋ ነበር። ከትሑትነቱም የተነሣ የበር ጠባቂ አደረጉት። በዚያም ገዳም በመንፈስ ቅዱስ የተሠወሩ ነገሮችን የሚያይ ባሕታዊ መነኰስ አለ በአንዲትም ሌሊት በሕልሙ በከፍታ ቦታ ላይ ቁሞ አየ ከበታቹም ፍሬው በየዓይነቱ የሆነ አትክልት አለ ወንዞችም ከበውታል አባ ነካሮም በመካከላቸው ሁኖ በወዲያና በወዲህ ያጠጣቸው ነበር። ያ መነኰስም "ወንድሜ ነካሮ ሆይ ይህ አትክልት የማን ነው" አለው አባ ነካሮም "እኔ የተከልኳት ናት" ብሎ መለሰለት መነኰሴውም "ከፍሬዋ ትሰጠኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው አባ ነካሮም ሦስት የሮማን ፍሬ ቆርጦ ሰጠው በልሱም ቋጠረው። ❤ በነቃም ጊዜ እነዚያን የሮማንፍሬዎች አገኛቸው ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሔደ ከበር ቁሞ አገኘውና "ወንድሜ ነካሮ ሆይ በዚች ሌሊት አይተኸኛልን" አለው እርሱም "አዎን አይቼሃለሁ ሦስት የሮማን ፍሬዎችን ሰጥቼህ የለምን" አለው። በዚያንም ጊዜ ያ መነኵሴ ወደ ገዳሙ ሔዶ የሆነውን ሁሉ ለአበምኔቱና ለመነኰሳቱ ነገራቸው እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አሳያቸው መነኰሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሣ አደነቁ ያን ጊዜም የበጋ ወራት ነበርና የሮማንም ጊዜው አልበረምና። ❤ በዝቅተኛ ማዕረግ ላይ ስለአደረጉት መነኰሳቱ አዘኑ በከፍተኛም ማዕረግ ሊያደርጉት ሽተው ወደርሱ በሔዱ አጡት ታላቅ ኀዘንንም አዘኑ ከዚህም በኋላ በዚች ዕለት እንዳረፈ። መጻተኞች ነገሩአቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ነካሮ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 13 ስንክሳር።                                                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መኑ አምላክ ዐቢይ ከመ አምላክነ። አንተ እግዚአብሔር ባሕቲትከ ዘትገብር መክረ። አርአይኮሙ ለሕዝብከ ኃይለከ"። መዝ 76፥13-14። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 4፥43-46።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ነጽረኒ ወስምዐኒ እግዚኦ አምላኪየ። አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢይኑማ ለመዊት። ወከመ ኢይበሉኒ ጸላእትየ ሞዕናሁ"። መዝ 12፥3። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ10-1-14፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10-22፣ የሐዋ ሥራ 2፥22-33። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 2፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ወይም የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ እግዚአብሔር አብ በዓልና የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።              

❤ ከዚያም ወደ በርሃ ሄደ ከብዙ ተጋድሎ የተነሳ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከ ደረቀ ድረስ ቅጠላቅጠል እየበላ ኖረ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ ፈወሰው። አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና በጸሎት በመጋደል በክረምት ዝናብ እየወረደበት ራቁቱን ቁሞ ያድራል በበጋም በቀን የፀሐይ ትኩሳት በሌሊትም ቊር ሰማያዊ ሀብት እስከተሰጠው ድረስ መላዕክትም ወደርሱ መጥተው ሰማያዊ ኅብስትን ሰማያዊ መጠጥን ይመግቡት ነበር የተሰወሩ ራእዮችን ያውቅ ዘንድ ተገባው ሦስት ድርሰቶችንም ደረሰ አንዱ በበረሀ ስለሚኖሩ ሁለተኛው በአንድነት ስለሚኖር መነኰሳት ሦስትኛው ስለካህናት ነው። ❤ በአንዲት ዕለትም ስሙ ቡላ የሚባል ገዳማዊ ወደርሱ መጥቶ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ ብላም እንዲህ አለው "ወንድሜ ወቅሪስ ሆይ! ብቻህን አትሁን ጥቂት ወንድሞችን ካንተ ጋር አኑር እንጂ ያረጋጉህ ዘንድ ከሰይጣንም ጦርነት እንድትድን" እንዲሁም አደረገ። ❤ ከዕለታትም በአንዱ ሃይማኖትን በለወጡ በአርዮስ በንስጥሮስና በማኒ አምሳል ሆነው ሦስት ሰይጣናት ወደርሱ መጥተው በሃይማኖታቸው ተከራከሩት እርሱም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትና ሃይማኖታቸው በቀናች አባቶች ትምህርት ረታቸውና አሳፈራቸው። ብዙዎችም የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን የሚሠራ ሆነ በአንዲትም ዕለት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሄደ ጊዜ ተዘግታ አገኛት መነኰሳቱም መክፈቻ ፈልገው አላገኙም በላይዋም በአማተበ ጊዜ በሩ ተከፈተለት "አባትህ ሞተ ብለው" በነገሩት ጊዜ "ዋሽታችኋል አባቴስ የማይሞት ሰማያዊ ነው" አለ ተብሎ ስለርሱ የሚነገርለት ወቅሪስ ይህ ነው ዜናውም በገድሉ መጻሐፍና የአባቶች ዜና በተጻፈበት መጻሐፍ አለ። ❤ ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ጥር 11 ሄደ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ባሕርኒ ርእየት ወጐየት። ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ። አድባር አንፈርዐፁ ከመ ሐራጊት። መዝ113፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ማቴ3፥13-ፍ.ም።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ርእዩከ ማያት እግዝኦ። ርእዩከ ማያት ወፈርሁ። ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምፀ ማያቲሆሙ"። መዝ 76፥16። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 3፥4-8፣ 1ኛ 5፥5-13 እና የሐዋ ሥራ 10፥34-39። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 3፥21-38። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ጥምቀቱ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።            

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ጥር ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለብርሃነ_ጥምቀቱ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን ከሆነ #ከከበረ_ቅዱስ_እንጣልዮስ በሰማዕትነት ከዐረፈ፣ #ከከበሩ_አዮስጦስና_ከፋይዮስ ዕረፍት፣ ከከበረ ተጋዳይ #ከአባ_ወቅሪስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ከአጥማቂው_ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘንድ_በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ። ይችም ዕለት በዮናኒ ቋንቋ ኤጲፋንያ ትባላለች ትርጓሜውም መለኮት የተገለጠበት ማለት ነው ልዩ የሆነች የሦስትነቱ ምሥጢር ገልጦባታልና አብ ከሰማይ ሁኖ የምወደው በርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት እያለ ሲመሰክር ወልድም በዮርዳኖስ ወንዝ ቁሞ ሳለ መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል በወልድ ራስ ላይ ሲቀመጥ ይህ አጥማቂው ዮሐንስ እንደመሰከረ። እንዳህ ሲል "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠምቆ ከውኃ በወጣ ጊዜ ወዲያኑ ሰማይ ተከፈተ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በጌታችን ራስ ላይ ተቀምጠ ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ "ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ነው እርሱንም ስሙት"። ❤ በዚች ዕለት ጌታችን ራሱን ገልጦአልና ከዚህ በፊት ሠላሳ ዓመት ያህል ራሱን አልገለጠም ነበር ግን በዚች ዕለት ለእስራኤል ልጆች ራሱን ገለጠ እነሆ "የእግዚአብሔር በግ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ" ብሎ መጥምቁ ዮሐንስ እንደገለጠው የከበረ ወንጌል ምስክር ሆነ። "እኔ አላውቅውም ነበር ነገር ግን እስራኤል ያውቁት ዘንድ በውኃ ላጠምቅ ስለዚህ መጣሁ" አለ። ❤ በዚህም በዓል የእግዚአብሔር ልጅ የክርስቶስ የጌትነቱ ክብር ተገልጧል እርሱም የዓለሙን ሁሉ ኃጢአት ለማስወገድ የሚሠዋ የእግዚአብሔር አማናዊ በግ ነው። ስለዚህም ይህ በዓል በክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ዘንድ የከበረና ከፍ ከፍ ያለ ሆነ በርሱም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ በአበረው ውኃ ይነጹበታል የተቀበሉትንም ንጹሕና ጠብቀው ቢኖሩ በውስጡ የኃጢአታቸውን ሥርየት ያገኛሉ። ❤ ስለዚህም ከክፉ ነገር ሁሉ ተጠብቀን የፈጠሪያችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የቸርነቱን ብዛት ልመናመሰግን ይገባናል እርሱ ስለ እኛ ሰው ሁኖ ከኃጢአታችን አድኖናልና። ለእርሱም ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ቅዱስ_እንጣልዮስ_ሰማዕት፦ ይህም ቅዱስ ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ ነው። አስቀድሞ በሮም አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ሆኖ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። ❤ የክብር ባለቤት ክርስቶስን ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በካደው ጊዜ ይህ ቅዱስ ሰማያዊ መንግሥትን መረጠ የዚህ የኃላፊውንም ዓለም ክብር ንቆ ተወ መጥቶም በከሀዲው ንጉሥ ፊት በመቆም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ረገመ ንጉሡም ስለ ድፍረቱ ደነገጠ። ከፋርስ ሰዎችም ከታላላቆቹ ወገን እንደሆነ በአወቀ ጊዜ በሽንገላ በጎ ነገርን ተናገረው ምናልባት ከጌታ ክርስቶስ ሃይማኖት ልቡን መመለስ ቢችል ብሎ ለሠራዊት አለቃ ለኅርማኖስ ሰጠው። ኅርማኖስም ጌታ ክርስቶስን ከማምለክ ሐሳቡን ሊአስለውጠው ባልተቻለው ጊዜ ወደ ንጉሡ መለሰው እርሱም በየራሱ በሆነ ሥቃይ አሰቃየው። ❤ ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ ያጸናውና ያረጋጋው ነበር በብዙ በተለያዩ ሥቃዮችም እየተሠቃየ ለረጅም ጊዜ ኖረ ብዙ ጊዜም ሰቅለውታልና ከዚያም አርደው ቆዳውን ገፈፉት ምላሱንም ቆረጡት ለነጣቂዎች አውሬዎችም ጣሉት በጨለማ ቤትም ዘጉት ሶስት ጊዜም ነፍሱን አሳለፈ እግዚአብሔርም አስነሣው ። ❤ ዲዮቅልጥያኖስም ማሠቃየቱን በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታትን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የእስክንድርያ_ አገር ሊቀ ጳጳሳት_አባ_ዮሐንስ፦ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አራተኛ ነው ። ይህም አባት ሊቀ ጵጵስና ከመሾሙ አስቀድሞ ወደ ህንድ አገር በባሕር ላይ በመርከብ እየሔደ ሁልጊዜ የሚነግድ ነጋዴ ሆኖ ነበር ከዚያ ፊት ግን በምስር ሀገር በሰማዕቱ በቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን በጸሐፊነት የሚያገለግል ዲያቆን ነው ጸሐፊነቱንም ትቶ የሚነግድ ሆነ። ❤ በዘጠኝ መቶ አራት ዓመተ ሰማዕታት የካቲት አራት በእሑድ ዕለት ኤጲስቆጶሳቱ መርጠው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በመልካም አጠባበቅም መንጋውን የሚጠብቅ ሆነ። ሊቀ ጳጳሳት ሆኖ ከመሾሙ በፊት ሃያ ሽህ ያህል የወርቅ ዲናር ነበረው ከመሞቱ በፊት ለድኆችና ለችግረኞች ለአብያተ ክርስቲያን ለገዳማትም ሁሉን ገንዘቡን ሰጥቶ ጨረሰ ። ❤ በሹመቱም ወራት ከሕዝብ ምንም ምን እጅ መንሻ አልተቀበለም በሹመቱም ሃያ ስምንት ዓመት ኖረ በዘጠኝ መቶ ሠላሳ ሁለት ዓመተ ሰማዕታት በዚች ቀን በጥምቀት በዓል አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑርለዘላለሙ አሜ።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_ወቅሪስ_ገዳማዊ፦ ይህም ቅዱስ አባት በባስልዮስ ዘንድ አደገ እርሱም ቅስና ሾመው ይህም ቅዱስ በደም ግባቱ በላሕዩ ደስ የሚል ፊቱም የሚአምር ነበር። ❤ በቀደመው ግብሩ ወጣት ሁኖ ሳለ የሹሙን ሚስት ተመኛትና እጅግም ወደዳት እርሷም ወደደችው ወደ ሌላ ቦታ ሂደው ፍላጎታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ ተማከሩ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ በሕልሙ ራእይን አየ። እርሱ ታሥሮ በፍርድ አደባባይ ቁሞ ነበር ሌሎችም ብዙዎች እሥረኞች ከእርሱ ጋር አሉ ስለ በደላቸውም እያንዳንዳቸውን ይመረምሯቸው ነበር እርሱም በልቡ "የታሰርኩት በምን ይሆን ባሏን ልነጥቀው ስለፈለግሁ ስለዚያች ሴት ነውን እርሱ ከስሶኝ ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ አደረሰኝን" አለ። ❤ በዚህም ነገር እየተሸበረ ሳለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና "የታሰርከው በምንድን ነው?" አለው ስለ ኃጢያቱ ስለ አፈረ ሊሰውረው ወደደ ግድ ባለውም ጊዜ እንዲህ ነገረው "ወዳጄ ሆይ እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ" በወዳጁ አምሳል ወደርሱ የመጣው መልአክም "ወዳጄ ሆይ! ይህን ሥራ እንዳትሠራ ወደ እርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ እኔም ዋስ እሆንሀለሁ" አለው በወንጌልም ማለለት በዚያንም ጊዜ ከእንቅልፉ ነቃ ያየው ራእይም እውነት እንደሆነ አወቀ። ስለዚህም አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሔደ በዚያም ስሟ ኄራኒ የሚባል እግዚአብሔርን የምትፈራ አንዲት ሴት አገኘ በተነጋገሩም ጊዜ የልቡን ሁሉ ነገራት እርሷም "እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው ተርታ ልብስንም ለብሰህ እግዚአብሔርን አገልግለው" አለችው።

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለዘመነ_ልደት_ሁለተኛ_ሳምንት ለዕለተ ለሰንበት (እሑድ) እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሃሌ ሉያ በ፪  "#ንጉሥኪ_ጽዮን ለትውልደ ትውልድ መጽአ ኀቤነ ዘኪያሁ ይሴፈዉ ሰማያት ወምድር ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይፀመድዎ #አክሊለ_ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዐምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ #ልሔም_ተወልደ_ወበናዝሬት_ተሐፅነ፣ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኃደገነ ፍሥሓ ኮነ #ዘውእቱ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ዘውእቱ_ኢየሱስ_ክርስቶስ"። ምልጣን፦ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኃደገነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ትርጉም፦ #ጽዮን ሆይ ንጉሥሽ ለልጅሽ ልጅ ወደ እኛ መጣ፣ ሰማያትና ምድር እርሱን ተስፋ የሚያደርጉ፣ የነገሥታት ልዕልና ከእርሱ ጋር ለሚጠመዱ ብርሃናቸው የሆነ #የሰማዕታት_አክሊላቸው_የካህናት_ሹመታቸው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምዷና መሠረቷ የሆነ #ክርስቶስ_በቤተ_ልሔም_ተወለደ_በናዝሬት_አደገ፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዚህ_ሳምንት_የዕለቱ_ምስባክ፦ "ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ። ወረከብናሁ ውስተ ኦመ ገዳም። ንበውዕ እንከሰ ውስተ አብያቲሁ ለእግዚአብሔር"። መዝ 131፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥1-14፣ 1ኛ ዮሐ 4፥14-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 13፥32-44። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ነው። መልካም የከተራ በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።               

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ጥር ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ለገሀድ (ጋድ) ጾመ፣ #ለከተራ_በዓልና #ለአባ_ታውብንጦ ለዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡ፦  #ከሰማዕት_ከጠምያኒ_ከኪናርያና #ከንግሥት_በጥሪቃ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                          ✝ ✝ ✝ ❤ #በዚች_ዕለት_ምንም_ምን_መብልን_ሳይቀምሱ #ምእመናን_ሁሉ_እስከ_ምሽት_ይጾሙ ዘንድ ከእኛ አስቀድመው የነበሩ ታላላቅ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓትን ሠሩ በምሽትም ቢሆን በታላቁ ጾም ከሚበላው በቀር ጥሉላትን እንዳይቀምሱ። በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንደመጾሙን ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና። ❤ እኛ በዚህ በኅላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው። እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው። ❤ በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥራ ቀን ነው በዋዜማው ዐርብ እስከ ምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾም ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ። ❤ በጥምቀትም ዕለት ከእኵለ ሌሊት በፊት ተነሥተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቊርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙ። ❤ የመለካውያን ወገኖች ግን የልደትና የጥምቀት ዋዜማ በቅዳሜ ቀን ወይም በእሑድ ቀን ቢሆን በሦስት ሰዓት ይቀድሳሉ ከወደዱም የተባረከ ኅብስት ተመግበው ውኃ ይጠጣሉ ከዚህም በኋላ ካህናቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነው በየሰዓቱ በመጸለይ ለበዓሉ የሚገባውን የነቢያትን ትንቢቶች ያነባሉ በዚያች ቀን በምሽት ይኸውም ጥር ዐሥር ነው በውኃው ላይ ይጸልያሉ ይህም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙት አልሆነም። እርሳቸው የኤጲፋንያን በዓል እንዲአክብሩ አዘዋል ይኸውም መድኃኒታችን የተገለጠበት ካኑን በሚባል በሮም ሁለተኛ ወር በሰባት ይህ ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው። ❤ መለካውያን ግን የከበሩ አባቶች የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘዙትን ይተላለፋሉ በልደትና በጥምቀት በዓል ዓርብም ረብዕም ቢሆን አስቀድመው በርሱ ፈንታ ሳይጾሙ በጥዋት ተነሥተው ይበላሉና። እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮርዳኖስም ወንዝ እንደ ተገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና ከቸር አባቱ ጋር ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ታውብንጦስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ አባ ታኡና በሚባል በሮሜው ሊቀ ጳጳሳት ቤት አደገ እርሱም የምንኵስናን ልብስ አለበሰው። መንፈሳዊ ዕውቀትና ኃይል እንደተሰጠው አይቶ ከእስክንድርያ አገር ውጭ ስሙ ጤናዲራን በሚባል ቦታ ኤጲስቆጶስነት ሹሞ የገዳም አበ ምኔት አደረገው ከእርሱ ሥር ያሉ መነኰሳትም ሰባት መቶ ናቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ጋር ላሉ መነኰሳት አለቃ የሆነ ኤጲስቆጶስ ታውብንጦስ ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ስለሆነው ሁከት በሰማ ጊዜ ሸሽቶ ወደ ደብረ ሲሐት ገዳም ሒዶ እግዚአብሔርን ከምትፈራ ከአንዲት ድንግል ዘንድ ተቀመጠ። በእርሷ ቤትም ብዙ ዘመናት ኖረ በመጀመሪያ ወደርሷ በገባ ጊዜ ግን ንጉሡን ስለ መፍራት ጣዖትን ስታመልክ አገኛትና የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስን ወደ ማመን መለሳት። ❤ ከዚያም ተርኑጥና መርኑስ ወደ ሚባሉ ገዳማት ሔደ የአብያተ ክርስቲያናትን ወሬ ይሰማ ዘንድ ፈልጎ በጾም በጸሎት ሌሊትም በመትጋት እያገለገለ በአንዲት ገዳም ውስጥ ሁለት ሦስት ቀን ተሠውሮ ያድር ነበር። የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ በላዩ እንዳደረ እግዚአብሔርም በእጆቹ ድንቆች ተአምራቶችን እንዳደረገ ከወንበዴዎችና ከዓመፀኞች ብዙዎችን መነኰሳትን አድርጎ ለክርስቶስ ወደ መገዛት እስከ መላሳቸው ድረስ መነኰሳቱ ሁሉ መሰከሩለት። ❤ ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ የሚሞትበትን ቀን ዐወቀ ልጆቹንም የክርስቶስ በሆነች በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ ትእዛዙንም እንዲጠብቁ አስተማራቸው ወዲያውኑ ጥር10 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ታውብጦስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር10 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_እብል_ለጾመ_ዕለት_ዋሕድ። #ዘስሙ_ገሀድ። መምህራነ ሥርዓት አቀሙ ለዘይመጽእ ትውልድ። እመባልዕት ጥሉላት ወእምነ ቅሡም ማዕድ። አንስት ይትሀረማ ወይጹሙ ዕድ። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_10።                          ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ለበስኩ ሠቀ ወኮንክዎሙ ነገረ። ላዕሌየ ይዛውዑ እለ ይነብሩ ውስተ አናቅጽ። ወኪያየ የኀልዩ እለ ይሰትዩ ወይነ"። መዝ68፥11-12። የሚነበበው ወንጌል ማር 1፥1-9።               

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፱ (9)። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያጻድቅ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዘአማኑኤል_ለዕረፍታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በፍቅር አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ዘአማኑኤል፦ የተባሉት ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ሀገራቸው ቦረና ሳይንት ሲሆን በዐፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው። ንጉሡ በወቅቱ በክፉዎች ምክር ተታሎ የአባቱን ቅምጥ ሲያገባ አቡነ ዘአማኑኤልም ሕገ እግዚአብሔር ተጣሰ ብለው ወደ ንጉሡ ዘንድ በመሔድ "የአባትህን ሚስት ማግባት ለአንተ አይገባም፣ ለምን እንዲህ ታደርጋለህ?፣ አሁንም እርሷ እንደ እናትህ ናትና ፍታት..." በማለት ነቢዩ ኤልያስ ንጉሥ አክዓብን እንደገሠጸው መጥምቁ ዮሐንስም ንጉሥ ሄሮድስን እንደገሠጸው አቡነ ዘአማኑኤልም ንጉሥ ዓምደ ጽዮንን ገሥጸውታል። ❤ በዚኽም ምክንያት ከሰማዕትነት በረከት ተካፍለዋል። መጽሐፍ "መምህር ወመገሥጽ ዘአማኑኤል) ይላቸዋል። ስንክሳሩም በስም ይጠቅሳቸዋል። በአቡነ ዘአማኑኤል ስም የተሠራው ቤተ ክርስቲያን ወለቃ ጋስጫ ከአባ ጊዮርጊስ ገዳም አጠገቡ ይገኛል። አቡነ ዘአማኑኤል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን።                 

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ጥር ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን ለከበሩ አባት ጌታችን በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጦ በቤታቸው ጣራ ለገባላቸው #ለአባ_አብርሃም_ግብፃዊ  ዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ አባቶች #ከአባ_ጊዮርጊስ_ከአባ_ኖስሞስና ከሮሜ ሰው #ዲዮስቅርስ ዕረፍት፣ #ከአባ_ኪናፎርያ_ከበጥሪቃና_ከጥምያኒ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_አብርሃም፦ የዚህም ቅዱስ ሰው አባቱ ድኆችን የሚወዳቸውና የሚራራላቸው ነው። በዘመኑም በግብጽ አገር ታላቅ ረሀብ ሆነ እጅግ ባለጸጋ ነበርና ከደግነቱና ከታማኝነቱ ብዛት የተነሣ እርሱ በአለበት አገር ዙሪያ ያሉ አገሮች ሁሉም የምድራቸው ፍሬ በእርሱ ዘንድ አደራ ያስቀምጡ ነበር ረሀቡም በጸና ጊዜ በእርሱ ዘንድ በአደራ የተቀመጠውን እህል ሁሉንም ለድኆች ሰጠ እግዚአብሔርም ስለ ምድራቸው ፍሬ ሁሉንም ክፉ ቃልን እንዳይናገሩት አደረጋቸው። በእርሱ ዘንድ ያኖሩትን የምድራቸውን ፍሬ ሽተው ወደርሱ በሚልኩ ጊዜ ተነሥቶ ወደርሳቸው ይሔዳል እነርሱም በየራሳቸው ለያንዳንዱ የምድራቸው ፍሬ እንደደረሳቸው አድርገው ይጽፉለታል እንጂ ምንም ምን አይናገሩትም። ❤ የዚህም ቅዱስ እናት እግዚአብሔርን የምትፈራ ምእመን ናት ሰይጣንም ቀናባት በአንድ ክፉ ሰው ልቡና አድሮ በፋርስ ሰዎች ዘንድ ነገር ሠራባት እነርሱም ማርከው ወደ አገራቸው ወሰድዋት በአንዲት ሌሊትም ራዕይን አየች ያ ነገር የሠራባት ሰው በሲኦል ውስጥ በእሳት ሰንሰለት ታሥሮ "እግዚአብሔር ያደረገልሽን ተመለከትሽን ነገር የሠራብሽን ያንን ሰው ተበቅሎታልና" ይላታል እርሷ ግን "ጌታዬ ሆይ መከራና ሥቃይ በርሱ ላይ እንዲደርስ አልሻም" ትላለች ያ የሚያሳያትም "አንቺ ግን ወደ አገርሽ ተመልሰሽ በቤትሽ ትኖሪ ዘንድ አለሽ" ይላታል እንዲሁም ሆነ። ❤ ባሏም በሞተ ጊዜ አብርሃም  ድኃ አደግ ሆነ እርሷም እናቱ ሚስት ልታጋባው አሰበች እርሱ ግን ይህን አልወደደም እናቱም እጅግ ደስ ተሰኘችበት። ወደ ገዳም ሒዶ ሊመነኵስ በፈለገ ጊዜ እናቱ ልትሸኘው ወጣች እጆቿንም ወደ ሰማይ አንሥታ በመጸለይ ልጇን ወደ እግዚአብሔር አደራ አስጠበቀች። "አቤቱ ጌታዬ ይህን ቊርባንን አድርገህ ተቀበለኝ" አለች። ❤ በዚያንም ጊዜ አባ አብርሃም ሔደ በአስቄጥስ በረሀ ውስጥ ተጒዞ በአባ ዮሐንስ አበ ምኔትነት ዘመን ወደ አባ መቃርስ ገዳም ደረሰ ወደርሱም ወደ አባ ዮሐንስ ገባ ተወዳጅ ልጅንም ሆነለት። በጎ ተጋድሎንም ጀመረ በአንዲት ሌሊትም ራዕይን አየ የበዓቱ ጣሪያ ተሰነጠቀ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጦ ወደርሱ ሲወርድ አየው ኪሩቤልም ያመሰግኑት ነበር እርሱም ፈርቶ ተንቀጠቀጠ ፈጥኖም ሰገደ ጌታችንም ባረከውና በታላቅ ክብር ወደ ሰማይ ዐረገ። ጌታችንም የወረደባት በቤቱ ጣሪያ የተሠነጠቀችው ምልክት ሁና እስከ ዛሬ በመታሰቢያነት አለች እርሷም ለመንፈሳዊ አባቱ ለአበ ምኔቱ አባ ዮሐንስ መኖሪያ ቅርብ ናት እርሷም በግቢግ ትባላለች። የእግዚአብሔርም መልአክ ሁል ጊዜ ይጐበኘዋል ብዙ ምሥጢራትንም ይገልጥለታል ያስገነዝበዋልም። ❤ ከዚህም በኋላ አባ አብርሃም ወደ ደብረ ኀርዮን ሔደ በዚያም አባ ገዐርጊን አግኝቶት ወደ አስቄጥስ ገዳም ከእርሱ ጋር ወሰደውና እስከ ዕረፍታቸው ጊዜ በዚያች በዓት ኖሩ። አበ ምኔቱ አባ ዮሐንስም በዐረፈ ጊዜ በአባ አብርሃም ላይ ሰይጣን ታላቅ ደዌ አምጥቶበት ዐሥራ ስምንት ዓመት በዚያ ደዌ ውስጥ ኖረ ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የጌታችንን ሥጋና ደም ያቀብሉት ዘንድ ወንድሞችን ለመናቸው ከተቀበለም በኋላ መንፈሳዊ አባቱ አባ ዮሐንስ ወደርሱ መጥቶ "እነሆ ወደ ታላቅ ሠርግ እግዚአብሔር ጠርቶሃል" አለው። ከዚህም በኋላ ዕድሜው ሰማንያ ዓመት ሁኖት ጥር8 ቀን በሰላም ዐረፈ በዓታቸውም እስከ ዛሬ የታወቀች ሁና ትኖራለች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና እኛንም በአባ አብርሃም በጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 9 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአብርሃም_ዘተሠጥቀ_ተድባቡ። #ለክርስቶስ_ይርአዮ እንዘ ይነብር ዲበ ኪሩቡ። አዕረፈ ዮም ለንብረተ ዓለም እምጻሕቡ። #በመንፈስ_ከመ ይቤሎ #ዮሐንስ_አቡ። #እግዚአብሔር ጸውዓከ ለዐቢይ ከብካቡ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_9።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ነገሥተ ተርሴስ ወደሰያት አምኃ ያበውዑ። ነገሥተ ሳባ ወዓረብ ጋዳ ያመጽኡ። ወይሰግዱ ሎቱ ኵሎሙ ነገሥተ ምድር"። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 5፥1-10፣ 1ኛ ዮሐ 2፥8-18 እና የሐዋ ሥራ 11፥27-ፍ.ም። መዝ 71፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥39-48። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ። መልካም የአቡነ አብርሃም የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።                

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ እስከ ዛሬ ድረስ ዓሣ ከሰማይ ለሚዘንብላቸው ለመናኔ መንግሥት #አቡነ_ኢዮስያስ_ለልደታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #መናኔ_መንግሥት_አቡነ_ኢዮስያስ፡- ትውልዳቸው ሸዋ ሲሆን የንጉሥ ዓምደ ጽዮን ልጅ ናቸው፡፡ ጥር 6 ቀን ሲወለዱ ቅዱሳን መላእክት ከበዋቸው ታይተዋል፡፡የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በዓለም ነግሠው መኖርን ንቀው በመመነን በመጀመሪያ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ገቡ፡፡ አቡነ ኢዮስያስ በሐይቅ ገዳም ለ14 ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ በዚያም ብሉይንና ሐዲስን፣ መጽሐፈ መነኰሳትንና መጽሐፈ ሊቃውንትን አጠናቀው ተምረዋል፡፡ በኋላም በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ ትግራይ ደብረ በንኰል ገዳም ሄዱ፡፡ በደብረ በንኰልም በታላቅ ተጋድሎ ኖረው በታላቁ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ መነኰሱ፡፡ ቆብ የተቀበሉት ግን ከአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡ ❤ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ሰባት ዓመት ከእሳቸው ጋር ካቆዩአቸው በኋላ አቡነ ኢዮስያስን ወንጌልን ዞረው እንዲሰብኩና ገዳም እንዲገድሙ በማዘዝ መርቀው ሸኝተዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢዮስያስም ወደ አዱዋ አውራጃ ዛሬ በስማቸው ወደተጠራው ገዳም ሄደው በቦታው ላይ በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ገዳሙንም ከገደሙት በኋላ በርካታ መነኰሳትን አፍርተዋል፡፡ ጻድቁ ያፈለቁት ጠበል በፈዋሽነቱ የታወቀ ነው፡፡ በየዓመቱ በዕረፍታቸው ዕለት ነሐሴ 6 ቀን ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ ይዘንባል፡፡ ይህ አሁንም ድረስ በየዓመቱ ነሐሴ 6 ቀን በግልጽ እየታየ ይገኛል፡፡ ❤ አቡነ ኢዮስያስን ከሃዲያን የሆኑ አረማውያን ቢያስቸግሯቸው ጻድቁም በጸሎት ቢያመለክቱ ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ነጭ የንብ መንጋ መጥቶ አረማውያኑን አንጥፍቶላቸዋል፡፡ ጻድቁ በጸሎታቸው አራት ሙታንን በአንድ ጊዜ ከሞት ያስነሡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ በገዳማቸው ውስጥ በበዓላቸው ቀን ገድላቸው ሲነበብ አጋንንት ከሰው ልቡና እንደ ትቢያ በነው ይጠፋሉ፡፡ ❤ ጻድቁን እንደ ረድእ ሆኖ የሚያገለግላቸው አንበሳ ነበራቸው፡፡ ወደ ገዳማቸው መጥቶ መካነ ዐፅማቸውን የተሳለመውን እስከ 14 ትውልድ ድረስ እንደሚምርላቸው ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ልጁን በስማቸው የሰየመ ቢኖር የሰይጣንን ፊት ፈጽሞ እንደማያይ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ከአቡነ ኢዮስያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።                   

❤ ወንድሙ የስብስጥያ ኤጲስቆጶስ ከሚስቱ ጋር በድንግልና ሲኖር ሕዝቡ ግን ያሙት ነበርና ቅዱስ ባስልዮስ መላእክት ሲጠብቋቸው እንደተመለከተ ለሕዝቡ ገልጦላቸው ሕዝቡ ከሐሜት ርቀው ንስሓ እንዲገቡ አድርጓቸዋል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ በተመለከተ ጊዜ "ይህ የቂሳርያው የባስልዮስ ነው" የሚል ቃልን ሰምቷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ወደ ቂሳርያ ሄዶ ከቅዱስ ባስልዮስ ዘንድ ዲቁናና ቅስና ተቀብሏል፡፡ ቅዱስ ባልዩስም በቅዱስ ኤፍሬም በላዩ ጸልዮለት የማያውቀውን አዲስ የዮናኒን ቋንቋን እንዲናገር አድርጎታል፡፡ ❤ ቅዱስ ባስልዮስ ሰው ሁሉ የሚያምንበትና በአቆጣጠሩም የሚታወቀውን ጠንቋይም በተአምሩ አሳምኖታል፡፡ ይኸውም ቅዱስ ባስልዮስ በታመመ ጊዜ የሚሞትበትን ጊዜ ዐውቆ ይህን ጠንቋይ ጠርቶ "ንገረኝ እስቲ መቼ እሞታለሁ?" አለው፡፡ ጠንቋዩም "ማታ ነፍስህ ከሥጋህ ትለያለች" አለው፡፡ እርሱም "እስከ ጠዋት ካልሞትኩ ክርስቲያን ትሆናለህ?" በማለት ቃል አስገባው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ወደ ጌታችን በመጸለይ በዕድሜው ላይ ሦስት ቀናት አስጨመረ፡፡ ያም ጠንቋይ ሥራው ከንቱ እንደሆነ ታወቀበትና እርሱም አምኖ ከነቤተሰቦቹ ተጠምቆ ክርስቲያን ሆነ፡፡ ❤ ሌላው ተአምር ለቅዱስ ባስልዮስ እመቤታችን ስለ ሥዕሏ የነገረችው ነው፡፡ ይህም ቅዱስ ባስልዮስ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ከሠራ በኋላ በውስጧ የሚያኖረውን የእመቤታችንን ሥዕል ሊያሠራ መሳያ ሠሌዳ ፈለገ፡፡ ሰዎችም በአንድ ባለጸጋ ቤት ጥሩ ሠሌዳ እንዳለ ነገሩትና ሄዶ ባለጸጋውን ሠሌዳውን እንዲሰጠው ለመነው፡፡ ባለጸጋውም የልጆቼ ነው አልሰጥም አለው፡፡ በትዕቢትም ሆኖ በታነጸቸው ቤተ ክርስቲያን ላይ የስድብን ነገር ተናገረ፡፡ ወዲያውም ወድቆ ክፉ አሟሟት ሞተና ልጆቹ ፈርተው ሠሌዳውን አምጥተው ለባስልዮስ ሰጡት፡፡ እርሱም ያንን ሠሌዳ የእመቤታችንን ሥዕል አሳምሮ ይስልበት ዘንድ ለሰዓሊ ወስዶ ሰጠው፡፡ በዚህም ጊዜ እመቤታችን በራእይ ለቅዱስ ባስልዮስ ተገለጠችለትና ከአመፀኛ ሰው የተገኘ ነውና በዚያ ሰው ሠሌዳ ሥዕሏን እንዳያስል ከለከለችው፡፡ ሥዕሏ የተሳለበትን ሠሌዳም የት እንደሚገኝ ነገረችውና ሄዶ በታላቅ ክብር አምጥቶ በቤተ ክርስቲያኑ አስቀመጠው፡፡ ከሥዕሉም ሥር ድውያንን ሁሉ የሚፈውስ የዘይት ቅባት መፍሰስ ጀመረ፡፡ በዚህም ብዙዎች ድንቅ የሆነ ፈውስን አገኙ፡፡ ይህም የተፈጸመው ሰኔ 21 ቀን ነው፡፡ ❤ ሌላም እንዲሁ ቅዱስ ባስልዮስ ያደረገው ተአምር የሰይጣንን የጽሕፈት ደብዳቤ በጸሎቱ የደመሰሰ መሆኑ ነው፡፡ አንድ ጎልማሳ አገልጋይ የጌታውን ልጅ ስለወደዳት ወደ አንድ ሥራይኛ ዘንድ ሄደ፡፡ ሥራይኛውም የክህደት ደብዳቤ ጽፎ ሰጠውና ወደ አረሚ መቃብር ሄዶ በመንፈቀ ሌሊት ደብዳቤዋን ይዞ በመቃብሩ እንዲቆ ላይ አዘዘው፡፡ ወጣቱም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ከሰይጣናትም አንዱ መጥቶ ወደ ወደ አለቃቸው አደረሰው፡፡ ያችንም የክህደት ደብዳቤ ከእጁ ወሰዳት፡፡ ሰይጣንም "የፈለከውን አደርግልሃለሁ ነገር ግን አምላክህን ክርስቶስን ትክደዋለህ ፈቃድህን ከፈጸምኩልህ በኋላም ወደ እርሱ አትምለስም" ሲለው ወጣቱም በልጅቷ ፍቅር አብዶ ነበርና "አዎን ጌታዬ ያዝከኝን ሁሉ አደርጋለሁ" አለው፡፡ ሰይጣኑም "ይህን ልታደርግ በእጅህ ጻፍልኝ" አለውና አጻፈው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በጌታው ሴት ልጅ ልብ ውስጥ አደረና ያንን ወጣት እጅግ ወደደችው፡፡ የፍትወት እሳትንም በልቧ ላይ ስላነደደባት መታገስ አልቻለችምና ወደ አባቷ ቀርባ ልጁን አጋባኝ አለችው፡፡ የልጁም ፍቅር በየዕለቱ ይጨምርባት ነበርና ራሷን እንዳታጠፋ ቤተሰቦቿ አጋቧት፡፡ ከእርሱ ጋር መኖር ከጀመረች በኋላ ሲያማትብ እንኳን አይታው አታውቅም ነበርና ስትመረምረው ክርስቲያን አለመሆኑንና ያደረገውንም ሁሉ ነገራት፡፡ ይህንንም ስትሰማ እጅግ ደንግጣ ወደ አገሯ ሊቀ ጳጳስ ወደ ባስልዮስ ዘንድ ሄዳ ከእግሩ ሥር በመውደቅ የደረሰባትን በመንገር ከሰይጣን እጅ እንዲያድናት ለመነችው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም በሏ የሆነውን የአባቷን ባርያ አስመጣውና በንስሓ ተመልሶ ክርስቲያን መሆን እንደሚፈልግ ጠየቀው፡፡ ወጣቱም ፈቃደኝነቱን ሲገልጥለት በአንድ ቦታ ውስጥ አስገብቶ ዘጋበትና ከላይ በመስቀል ምልክት አተመበት፡፡ እንዲጸልይም አዘዘው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ስለ ወጣቱ ብዙ ጸለየ፡፡ ከሦስት ቀንም በኋላ ጎበኘውና በ3ቱ ቀን የደሰበትን ጠየቀው፡፡ ወጣቱም በላዩ በመጮህ ሰይጣናት ሲያስፈራሩት ያንንም ደብዳቤ ሲያሳዩትና በእርሱ ላይ ሲቆጡ በመከራ ውስጥ እንደኖረ ነገረው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም "ከሰይጣናቱ ቁጣ የተነሣ አትፍራ አይዞህ እግዚአብሔር ይረዳናል" ብሎ ጥቂት ከመገበው በኋላ መልሶ ዘጋበትና ሄዶ ይጸልይለት ጀመር፡፡ ❤ ዳግመኛም ከ3 ቀን በኋላ መጥቶ ጠየቀው፡፡ ወጣቱም "የአጋንንቱን ጩኸታቸውን እሰማዋለሁ ነገር ግን አላያቸውም" አለው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ አሁንም ጥቂት ከመገበው በኋላ መልሶ ዘጋበትና እስከ 40 ቀን ድረስ እንዲሁ አደረገ፡፡ ከ40 ቀንም በኋላ መልሶ ሲጠይቀው ወጣቱ "ቅዱስ አባቴ ሆይ ስለ እኔ ሰይጣንን ስትጣላውና ድል አድርገህ ጥለህ ስትረግጠው በዛሬዋ ሌሊት አየሁ" አለው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ይህን ሲሰማ እጅግ ደስ አለው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንም ጠርቶ እግዚኦታ አደረሱና ከእግዚኦታው በኋላ ያ ወጣት ጽፎ ለሰይጣን የሰጠው የክህደት ደብዳቤ ከሰይጣን እጅ ተወስዶ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ወደቀ፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ይኸውም የተደረገው መስከረም 13 ቀን ነው፡፡ ❤ አንዲት ሴት ኃጢአቷን ሁሉ በዝርዝር ጽፋ በክርስታስ አሽጋ እንዲጸልይላት ቅዱስ ባስልዮስን ለመነችው፡፡ እርሱም ከአንዲት ኃጢአቷ በቀር ሁሉንም በጸሎቱ ደመሰሰላት፡፡ ስለ አንዲቱም ኃጢአቷ ወደ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲትሄድ አዘዛት፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም "ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ሳይሞት ፈጥነሽ ተመለሽ የካህናት ሁሉ አለቃ ስለሆነ የቀረች ኃጢአትሽን የሚደመስስልሽ እርሱ ነው" ብሎ መለሳት፡፡ በተመለሰችም ጊዜ ቅዱስ ባስልዮስ ዐርፎ ሊቀብሩት ሲወስዱት አገኘችው፡፡ እርሷም መሪር ልቅሶን ካለቀሰች በኋላ በእምነት ሆና ያንን ክርስታስ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችው፡፡ ስለ እምነቷም ጽናት ያች የቀረች በደሏ ተደመሰሰችላት፡፡ ❤ ይህም የከበረ ቅዱስ ባስልዮስ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከጻፍነው ሌላ ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን አድርጓል ብዙዎችንም ተግሣጻትንና ድርሳናትንና ለመነኰሳትም ትምህርቶችን ደርሷል፡፡ ከብሉይና ከሐዲስም አምላካውያን የሆኑ ብዙ መጻሕፍቶችን ተርጒሟል ሥርዓቶችንም ሠራ እነርሱም በሁሉ ቦታ ይገኛሉ ከዚህም በኋላ ጥር6 በሰላም ዐረፈ በክብር በብዙ ምስጋና ቀበሩት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ባስልዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 6 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤  "#ሰላም_እብል_ለኖኅ_በሕቁ። ምስለ ብእሲቱ ወደቂቁ። በገቢረ ታቦት ላዕሌሁ እለ ተሣለቁ። በዝናመ ድምሳሴ ወበማየ አይኅ ኀልቁ። ውእቱሰ እምሠጠ በጽድቁ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_6።                

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ከአዳም_ዐሥረኛ_ትውልድ ለሆነው ለታላቁ አባት #ለጻድቁ_ለቅዱስ_ኖኅ_ለዕረፍቱ መታሰቢያ፣ #ለታላቁ_ነቢይ_ለቅዱስ_ኤልያስ በሕይወት ሳለ በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ #ለዐረገበት_ከሞት_ለተሰወረበት መታሰቢያ በዓል፣ ለከበረና  ለታላቁ አባት #ለቂሣርያ_ኤጲስቆጶስ_ለአቡነ_ባስልዮስ_ለዕረፍት በዓል መታሰቢያና #ለታላቋ_ሰማዕት_ለቅድስት_አርሴማ_ለልደቷ በዓልና እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክንድርያ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ወርክያኖስ ዕረፍትና በበረሀ ስልሳ ዘመናት ከኖረ #ከአባ_ሙሴ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #የነቢዩ_ቅዱስ_ኤልያስ_ዕረገት፦ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ኤልያስን ወደ ሰማይ በሚወጣባት ጊዜ ኤልሳና ኤልያስ ከገልገላ ተነሥተው ሔደወሰ ወደ ዮርዳኖስ ደረሱ ኤልያስም መጠምጠሚያውን አውርዶ ጠቅሎ የዮርድያኖስ ውኃ መታበት ውኃውም ተከፍሎ ወዲያና ወዲህ ቆመ ሁለቱም ሁሉ በደረቅ ተሻገሩ ወጥተውም በምድረ በዳ ቆመ። ❤ ኤልያስ ኤልሳን "ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳልወጣ አደርግልህ ዘንድ የምትሻውን ለምነኝ" አለው ኤልሳዕም ኤልያስን "በአንተ ያደረ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ዕጥፍ ሁኖ ይደርብኝ" አለው። ኤልያስም ኤልሳን "ድንቅ ነገርን ለመንከኝ ነገር ግን ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳርግ ብታየኝ ይሁንልህ ባታየኝ ግን አይሆንልህ" አለው። በዚያንም ጊዜ የእሳት ሠረገላና የእሳት ፈረስ መጣ ወደ መካከላቸውም ገብቶ አራራቃቸው ኤልያስም እንደዚህ በንውጽውጽታና በጥቅል ነፋስ ወደ ሰማይ ዐረገ። ኤልሳዕም አይቶ "የእስራኤል ኃይላቸውና ጽናታቸው አባ አባ ብሎ ጮኸ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ አላየውም ልብሶቹንም ለሁለት አድርጎ ከፈላቸው ኤልያስም ለኤልሳዕ መጠምጠሚያውን ጣለለት በኤልሳዕም ራስ ላይ ወረደ የኤልያስም ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በኤልሳዕ ላይ ዕጥፍ ሁኖ አደረ ኤልያስም የሠራውን ተአምራት ኤልሳዕ ዕጥፍ አድርጎ ሠራ። ❤ ይህም ኤልያስ በኋላ ዘመን ከኄኖክ ጋር ይመጣ ዘንድ አለው ሐሳዊ መሢሕንም ይቃወሙታል እርሱም ይገድላቸዋል በድናቸውም በአደባባይ ተጥሎ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይቆያል ከዚህም በኋላ ይነሣሉ የሙታን ትንሣኤም ይሆናል ይህም ኤልያስ እውነተኛ ነቢይ አስቀድሞ የነበረ በኋላም የሚገለጽ ነው በብሉይ ዘመንም ኑሮው በበረሃ ውስጥ ነበር። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢይ በቅዱስ ኤልያስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #አባታችን_ጻድቁ_ቅዱስ_ኖኅ፦ እርሱም ከአባታችን አዳም ዐሥረኛ ትውልድ ነው። እርሱም ከታናሽነቱ ጀምሮ ኃጢአት እንደሚበዛ ክፋትም እንደሚመላ ደጋጎች እንደሚያንሱ ሥጋ የለበሰ ሁሉ በጥፋት ውኃ እንደሚመሰስ አምላካዊ ምሥጢርን የሚያይ ሆነ ስለዚህም ፊቱ የተቋጠረ ሁኖ ፈጽሞ ያለቅስ ነበር። ❤ አምስት ዓመት ድንግልናውን ጠብቆ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ለአባታችን አዳም ሥጋ ሲያገለግል ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ ሚስት እንዲያገባ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ ሥጋ የለበሰ ሁሉ እንደሚደመሰስ ከእርሱ ዘር በቀር የሚተርፍ እንደሌለ ነገረው፡፡ ጻድቁ ኖኅም የአቡዚር ልጅ የሆነች ሐይከል የምትባል ሴት አግብቶ ወደ እርሷ ሦስት ጊዜ ቢገባ ሦስት ልጆችን ሴም ካም ያፌትን ወለዳቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ለኖኅ ከደብር ቅዱስ ዕንጨት ቆርጦ መርከብን እንዲያሠራ ካዘዘው በኋላ አሠራሯን በዝርዝርና በጥልቀት አስረዳው፡፡ የቃየል ልጆችም ኖኅን መርከብ ሲሠራ አይተው ዘበቱበት፡፡ የአዳምንም ሥጋ ወስዶ በውስጡ አኖረ፡፡ ሴም ወርቁን፣ ካም ከርቤውን፣ ያፌት ዕጣኑን ወስደው ወደ መርከብ አስገቡ፡፡ ኖኅም ከልጆቹና ከሚስቶቻቸው ጋራ ወደ መርከቡ ገባ፡፡ ንጹሐን የሆኑት እንስሳትና አእዋፋት ሴትና ወንድ ሰባት ሰባት፣ ንጹሐን ካልሆኑት ደግሞ ሁለት ሁለት ሴትና ወንድ አስገባ፡፡ ከዚያም ሰማይ ተከፍቶ የምድርም ምንጮች ሁሉ ተነድለው ራጃጅም ተራራዎችም እስኪሸፈኑ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ዘነመ፡፡ ውኃውም በላያቸው 15 ክንድ ከፍ አለና ሥጋ የለበሰ ሁሉ ሞተ፡፡ ❤ ከመቶ ሃምሳ ቀንም በኋላ እግዚአብሔር ኖኅን አስቦ ነፋስን በምድር ላይ አመጣና ውኃውን አጎደለ፡፡ ምንጮች ተደፍነው የሰማይ መስኮት ተዘጋ፡፡ መርከቢቱም በ7ኛው በ12ው ቀን አራራት ተራራ ላይ አረፈች፡፡ ከጊዜም በኋላ እግዚአብሔር ኖኅን ከነቤተሰቡ አንድ ላይ ከመርከቡ እንዲወርዱ አዘዘው፡፡ ኖኅም መሠዊያን ሠርቶ ንጹሕ ከሆኑት ሁሉ ወስዶ መሥዋዕት ባቀረበ ጊዜ እግዚአብሔር መልካም መዓዛን አሸተተ፡፡ ዳግመኛም ምድርን በንፍር ውኃ እንዳያጠፋ ቃልኪዳን ገባለት፡፡ ምድር ፀንታ በምትኖርበት ዘመን ሁሉ ዘር መከር፣ ቅዝቃዜና ሙቀት፣ በጋና ክረምት፣ መዓልትና ሌሊት እንደማይቋረጥ ቃልኪዳን ገባለት፡፡ እግዚአብሔርም ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው፡፡ ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉዋት ግዟት አላቸው፡፡ ❤ ኖኅም ምድርን ያርሳት ይቆፍራም ጀመር፡፡ ወይንም ተክሎ ከእርሶ ፍሬውን አድርሶ ወይን ጠጥቶ በሰከረና ራሱን በሳተ ጊዜ የከነዓን አባት ካም የኖኅን ራቁትነት አይቶ ሳቀ፣ ሄዶም ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ ያፌትና ሴምም ልብስ ወስደው የአባታቸውን ርቃን ሸፈኑ፡፡ ኖኅም ከስካሩ በነቃ ጊዜ ሁሉም ያደረጉትን ዐወቀ፡፡ "ከነዓን የተረገመ ይሁን፣ ለወንድሞቹም ተገዥ አገልጋይ ይሁን" ብሎ ከረገመው በኋላ "የሴም ፈጣሪ እግዚአብሔር ይመስገን፣ እግዚአብሔርም የያፌትን አገር ያስፋ፣ በሴም ቤትም ይደር ከነአንም አገልጋይ ይሁን"። ❤ አባታችን ቅዱስ ኖኅም ከጥፋት ውኃ በኋላ ሦስት መቶ ኅምሳ ዓመት ኖረ የኖኅም መላ ዕድሜው ዘጠኝ መቶ ኃምሳ ሆነ በሰላምም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን በጻድቁ ኖኅ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሣርያ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ኤስድሮስ ይባላል እርሱም ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ቄስ ነው አምስት ልጆችንም ወልዶአል እነርሱም ባስልዮስ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጴጥሮስ፣ ኬርዮን፣ መክርዮን ናቸው ሁሉም ከፍጹማንነት የደረሱ ቅዱሳን ናቸው። ❤ በዚህም በከበረ ባስልዮስ ላይ መንፈስ ቅዱስ መልቶበት በሁሉ ዘንድ የታወቀች ቅዳሴውን ደረሰ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊሠርቁ የመጡትን ሌቦች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ በጸሎቱ በሩን ዘግቶባቸዋል፡፡ በኋላም ምእመናን ሲመጡ በሩን ከፍቶላቸዋል፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ መሆኑን ነው፡፡ የታላቁ አባት የቅዱስ ኤፍሬምም መምህሩ ነው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ያደረጋቸው ተአምራት ስፍር ቁጥር የላቸውም፡፡

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን #ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለንዑስ_በዓል ለአንዱ #ለግዝረት_ለኢየሱስ ዓመታዊ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                                                 ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ #በሥጋው_ወደ_ቤተ_ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ ልሳነ ዕረፍት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ" ብሎ እንደተናገረ። ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር እነርሱ እንዳሰቡት ሁኖ ቢሆን ኑሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን የሚያገኙ በሆኑ ነበር ጌታችን ግን ግዝረትን ሕግ ፈጸመ ለእኛ በግዝረት ፈንታ የክርስትና ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ በላ በእርሱም ፈንታ ሥጋውንና ደሙን ሰጠን። ❤ የከበረ ወንጌል "ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜም ሕፃኑን ሊገዝሩት ወሰዱት ሳትፀንሰው መልአኩ እንዳወጣለት ስሙን ኢየሱስ አሉት" እንዳለ ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን "እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የሆነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ" አለችው። ዮሴፍም ሔዶ የሚገርዝ ባለሙያ አመጣ ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው "እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቆ ያዙት" አላቸው። ሕፃን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መልሶ እንዲህ አለው "ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን በዚያች ዕለት ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኃና ደም ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች መድኃኒት ይሆናል"። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ያ ባለሙያ በሰማ ጊዜ አደነቀ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር በታች ሰገደ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጆቹ ላይ ቀልጠው እንደ ውኃ ሆኑ የከበረች ድንግል እመቤታችን ማርያም "ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው" አላት። ❤ ሕፃኑም ለዚያ ባለሙያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው "እኔ ነኝ ትገዝረኛለህ ወይስ ተውክ ወይም ያባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ" ያም ባለሙያ "የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው?" አለው ሕፃን ጌታችንም "አብርሃም፣ይስሐቅ ያዕቆብ የሕዝቡ ሁሉ አባቶች የሆኑ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው" ባለሙያውም "እኔ ከአንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና" አለው። በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ "አባት ሆይ ለአብርሃም፣ለይስሐቅ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ" አለ። ያን ጊዜ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች። ❤ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማሕፀን እንደ መውጣቱ የጌታችን ግዝረቱ የማይመረመር ሆነ እንዲሁ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እንዲሁ እንደ ፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ። አዳምንና ልጆቹን ያድናቸው ዘንድ በፈቃዱ ከጐኑ በመስቀል ላይ የሚፈሰው ደምና ውኃ ካልሆነ በቀር ብዙም ሆነ ጥቂት ሊሆን አይችልም እርሱ በፈቃዱ ሕጉ እንዲፈጸም አስቀድሞ አዘዘ እንጂ። ❤ ያም ባለሙያው ገራዥ ይህን ተአምር ባየ ጊዜ የሕፃኑንም ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና "በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ" አለው። ከዚህም በኋላ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተአምራቱ ያየውንና የሰማውን እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ ለእርሱም ለጌታችን ከቸር አባቱ ጋራ ማሕየዊ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋራ ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 6 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይከውን ቡሩከ ስሙ ለዓለም። እምቅድመ ፀሐይ ሀሎ ስሙ። ወይትባረኩ ቦቱ ኵሎሙ አሕዛብ ምድር። መዝ 71፥17-18።  የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 2፥8-22።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወገሠጸ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ 104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥8-14፣ 2ኛ ጴጥ 2፥1-9፣ የሐዋ ሥራ 7፥2-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 4፥24-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የኢየሱስ ክርስቶስ በዓል፣ የነቢዩ ኤልያስ የዕረገት በዓል፣ የጻድቁ ኖኅ የዕረፍት በዓል፣ የቅዱስ ባስልዮስ የዕረፍት በዓልና የቅዱስ አርሴማ የልደት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለፅንሰትከ_በብሥራተ_መልአክ ሐዲስ። #ወለልደትከ_ሰላም_በወርኀ_ታኅሣሥ። #ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ አበውእ ወርቀ አምኀ ልብ ወከርሥ። #በእንደ_ልደቱ ከመ አብአ ተርሴስ። ለቤዛ ኵሉ ዓለም #ኢየሱስ_ክርስቶስ"። ትርጉም፦ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_ሆይ_በብሥራተ_መልአክ_ለተጸነስከው_መጸነስና በወርኀ ታኅሣሥ #ለተወለድከው_ልደት_ሰላም_እላለሁ። ክብሩ አባት ሆይ ስለ #ዓለሙ_መድኀኒት_ኢየሱስ_ክርስቶስ ስለ #ጌትነቱ_ልደት_ተርሴስ_ግብር እንደገበረ እኔም ፍጹም ልባዊ የሆነ የእጅ መንሻ ወርቅ አቀርብልሃለሁ። #መልክዐ_አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ።               

❤ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል ሲያርፍ ኤጲስቆጶሳቱ በራእይ ተረድተው አባ ማቴዎስን ያለ ፈቃዱ በግድ ሊሾሙት ተስማሙ፡፡ እምቢ ባላቸውም ጊዜ በላዩ ላይ ጠባቂዎችን አኖሩ፡፡ አባ ማቴዎስም እንደማይተውት ዐውቆ ምላሱን ጎትቶ በማውጣት ምላጭ ቆረጣት፡፡ በዚያችም ሌሊት እመቤታችን ወደ እርሱ መጥታ ተገለጠችለትና የሚያድን ቅባትን ቀብታ ምላሱን እንደቀድሞው አድርጋ ፈወሰችለት፡፡ ኤጲስቆጶሳቱም በግዴት ወደ እስክንድርያ ወሰዱትና በእመቤታችን ዓመታዊ በዓሏ ቀን በቅዱስ ማርቆስ መንበር 87ኛ ሊቀጳጳሳት አድርገው ሾሙት፡፡ በዚህም ጊዜ "ይገባዋል ይገባዋል" የሚል ድምጽ ከሰማይ ተሰማ፡፡ በክንዱም ላይ ያደርጉ ዘንድ የወንጌላዊ የቅዱስ ማርቆስን ራስ አመጡ፡፡ እርሷም ተነጥቃ ወደላይ በረረችና የአባ ማቴዎስን አፉን ሳመችው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ ማቴዎስ ዐርብና ረቡዕ በዓቱን ዘግቶ ሲጸልይ የሚውል ስለሆነ ማንም ወደ እርሱ አይገባም ነበር፡፡ ከራሱ ላይ በሚያደርገው ቀጸላ ብዙ ሕሙማንን ፈወሰበት፡፡ ሙታንንም በማስነሣት ብዙ ድንቅ ተአምራትን አደረገበት፡፡ በወቅቱም በእኛ አገር በኢትዮጵያ ውድም አስፈሬ ነግሦ ሳለ ይህ አባ ማቴዎስ ንጉሥ ዳዊት እንደሚነግሥ ትንቢትን ተናገረ፡፡ እንደትንቢቱም በኋላ ላይ ደገኛው ዐፄ ዳዊት ነግሠዋል፡፡ ❤ በአባ ማቴዎስ ዘመንም በምስር አገር ክፉ ገዥ ተሾመና አባ ማቴዎስን ከአቅሙ በላይ ግብርን ጠየቀው፡፡ የተጠየቀውንም ብዙ ግብር መክፈል እምቢ ባለ ጊዜ ገዥው አባ ማቴዎስን በጽኑ ድብደባ አሠቃየው፡፡ ተሸክመውት ወደ ቤተ ክርስያን ባደረሱት ጊዜ በእመቤታችን ሥዕል ፊት ወድቆ "ምነው እመቤቴ ሆይ ነፍሴን ወስደሻት ከዚህ ክፉ ዓለም ብታሳርፊኝ" ብሎ ተማጸናት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ተገለጠችለትና "አይዞህ አትዘን፣ በ8ኛው ቀን በሰላም ታርፋለህ" አለችው፡፡ ወዲያውም ኤጲስቆጶሳቱን፣ ዲያቆናቱንና ምእመኑን ሁሉ ጠርቶ የዕረፍቱን ጊዜ ነገራቸውና እስከ መጨረሻው ድረስ በሃይማኖት እንዲጸኑ መከራቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ጊዜው ደርሶ ሕማሙ በጸናበት ጊዜ  የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አንሥቶ ይዞ ለረጂም ጊዜ ጸለየ ሥዕሊቱም ተሳልሞ ሳማት ፊቱንም በመስቀል ምልክት አማተበ ክርስቶስን የሚያምኑ ምእመናን ያሉበትን አገር ሁሉ ባረከ በእሑድ ጥር5 ቀንም በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 5 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአውስግንዮስ_ለምሥጢረ_መስቀል ዘተርጐሞ። #አመ_ቈስጠንጢኖስ ርእየ ማዕተበ ከዋክብት ቀዊሞ። እንበለ ያጽዕቆ ልሕቅና ወእንበለ ርሥአን ያድክሞ። ምእተ ወዐሠርተ ዓመተ መዋዕለ ሕይወቱ ፈጽሞ። በእንተ ክርስቶስ ተመትረ ወከዐወ፡ደሞ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር _5።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 2፥11_ፍ.ም፣ ያዕ 3፥5_13 እና የሐዋ ሥራ 7፥55_ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ18፥33-38። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልዕ ቅዳሴ ነው። መልካም የበዐለ ልደቱ ሰሞን ለሁላችንም ይሁንግል።             

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን በከሀዲው ዑልያኖስ ዘመነ መንግሥት ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለከበረ_ለቅዱስ_አውስግንዮስ ለዕረፍቱ በዓልና ለእስክድርያ ሰማንያ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ማቴዎስ_ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከያሬውንዮስ ከሌሎችም ከሴቶችና ወንዶች #ከሮማዊው_ለንጊኖስ_ከአባ_አርሳኒን ከጐበኘችው #ከእስክንድርያና_ከአውስያ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_አውስግንዮስ፦ ይህም ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ጭፍሮች ውስጥ ነው እርሱም እግዚአብሔርን የሚያመልከው ለድኆችና ለምስኪኖች የሚመጸውት ነው መስቀልም እንደ ክዋክብት በሰማይ እያበራ ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከማመኑ በፊት በተገለጠለት ጊዜ ይህ ቅዱስ አውስግንዮስ ወደ ንጉሡ ቀርቦ እንዲህ አለው "ይህ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ምልክቱ ነው በዚህም ጠላቶችህን ታሸንፋለህ። ያን ጊዜ ከቈስጠንጢኖስ ሥራዊት ውስጥ ከዚህ ቅዱስ ሰው በቀር የክርስቶስን ስም ይጠራ ዘንድ የደፈረ የለም። ❤ ቈስጠንጢኖስም በከበረ መስቀል ምልክት ጠላቶቹን ድል በአደረገ ጊዜ ዕውነተኛ ክርስቲያን ሆነ የሃይማኖትንም ሥልጣን አቁሞ ከፍ ከፍ አደረገ። ይህም ቅዱስ አውሰሰግንዮስ እድሜው መቶ ዐሥር ዓመት እስከ ሆነው ከቈስጠንጢኖስና ከልጆቹ ዘመነ መንግሥት በኋላ እስከ ከሀዲው ዑልያኖስ ዘመን ኖረ። በአንዲት ዕለትም በአንጾኪያ ከተማ በአደባባይ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ሲመላለስ ሁለት ሰዎች እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አግኝቷቸው ሊአስታረሰቃቸው በመካከላቸው ሰላም ሊያደርግ ወዶ አስታረቃቸው በመታረቃቸውም ደስታ አደረጉ እርሱ የከበረ አረጋዊ ሰው ነውና። ❤ ከዚያም አንድ ክፉ ሰው ወደ ንጉሥ ዑልያኖስ ሒዶ ነገር ሠራበት እንዲህም አለው "አውስግንዮስ በራሱ ፈቃድ ገዥና ፈራጅ ዳኛ ሆነ"። ንጉሥም ይህን ቅዱስ ወደርሱ አቅርቦ ገሠጸው "ገዥና ፈራጅ ዳኛ አድርጎ የሾመህ ማነው" አለው። የከበረ አውስግንዮስ መልሶ "ነፍስህ በእጁ የተያዘች የእግዚአብሔርን አምልኮት ትተህ አንተ ለረከሱ ጣዖታት ለምን ሰገድክ ከአንተ በፊት የነበሩ ነገሥታትን ለምን አልተከተልካቸውም እኔም እንዳንተ ወታደር ሁኜ ከቈስጠንጢኖስ ጋር ሃያ ዓመት ኖርኩ ከልጆቹም ጋር ነበርኩ እነርሱ ውስጥ እንዳንተ ያለ ጠባየ ክፉ የለም" አለው። ❤ ዑልያኖስ በቅዱስ አውስግንዮስ ላይ እጅግ ተቆጣ ይሰቅሉት ዘንድ በጐኖቹም ውስጥ መብራቶችን አስገብተው እንዲለበልቡት አዘዘ እነርሱም ስለ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህን ሁሉ ታገሠ። ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ ወታደሮችም ሊቆርጡት በመጡ ጊዜ እስኪጸልይ ይታገሡት ዘንድ ለመናቸው ጸሎቱንም ሲፈጽም የከበረች ራሱን ቆረጡት ጥር5 ቀን የምስክርነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማይያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውስግንዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ማቴዎስ፡- የዚህም የአባ ማቴዎስ ወላጆቹ ከእስራኤል ነገድ የሆኑ ክርስቶስ የሚያምኑ በበጎ ሥራዎችም ፍጹማን የሆኑ ናቸው። የአባቱም ስም ስምዖን የእናቱም በርባራ ይባላል እግዚአብሔርም ሁለት ዘርን ሰጣቸው የታላቁም ስም ያዕቆብ የታናሹም ስም ማቴዎስ ነው፡፡ ይህም ቅዱስ ማቴዎስ ገና በእናቱ ሆድ ውስጥ ሳለ የአቡፌስ አገር ኤጲስቆጶስ የከበረ አባ ጴጥሮስ እናቱን ባገኛት ጊዜ ከበቅሎው ላይ ወርዶ በክብር ሆዷን ሳማትና "አንቺ ሴት የተባረክሽ ነሽ፣ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፡፡ እነሆ እንደ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ በትምህርቱ ለሰው ሁሉ የሚያበራ ብሩህ ኮከብ ካንቺ ይወጣል" አላት፡፡ አባ ማቴዎስም ተወለደ፡፡ በ15 ዓመቱ ወላጆቹ ከሞቱ በኋላ ወደ ገዳም ገብቶ ሊመነኩስ ወሰነ፡፡ በቅዱስ አቡፋና ገዳም ገብቶ አባ አብርሃምን "አመንኵሰኝ" ቢለው "ከታላቅ ወንድምህ ተማከረህ ና" አሉት፡፡ ወደቤቱም ተመልሶ ሲሄድ በመንገድ ላይ ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለትና ሊቀ ጳጳሳት እንደሚሆንና በእጆቹም ብዙ ተአምራትን እንደሚያደርግ ነገረው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ከታላቅ ወንድሙ ጋር ስለምንኵስና ተማክሮ ተመልሶ በቅዱስ አቡፋና ገዳም መነኮሰና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ❤ ቅዱስ ማቴዎስ አንድ ዓመት በሆነው ጊዜ ኤጲስቆጶሱ አባ ጴጥሮስ ወደ አባ አብርሃም መጣና የቅዱስ ማቴዎስን ረዳት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ ለመነው፡፡ እርሱም ፈቀደለትና ወሰደው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ፀሐይ ስትገባ ጀምሮ እስክትወጣ ድረስ ለኤጲስቆጶሱ ጋር በጸሎት እየተጋ ያድራል፡፡ 15 ዓመትም በሆነው ጊዜ ሳይወድ በግድ ቅስና ሾመው፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣን በቅናት ተነሳበትና በዝሙት ፈተነው፡፡ ሰይጣንም በአንዲት ባማረች ሴት ልብ አድሮ ብዙ ፈተነው፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ማቴዎስ እያለወሰ ወደ እግዚአብሔር ይለምን ነበር፡፡ ኤጲስቆጶሱንም ወደ ገዳሙ መልሶ ይልከው ዘንድ ለመነው፡፡ እርሱም ማሰናበትን እምቢ አለው፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም በዚህ ተናዶ የኤጲስቆጶሱን መቀደሻ ልብሶች በምላጭ ይቀድ ጀመር ይህም ኤጲስ ቆጶሱ እንዲበሳጭና እንዲልከው ነው፡፡ ነገር ግን መቶ መቶ እንዲሠግድ ቀኖና ሰጠው እንጂ አላሰናበተውም፡፡ በኋላም ትዕግስቱንና ቅንነቱን አይቶ ፍትሃትና ቡራኬ ሰጠው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላም ወንድኑ ወደ ገዳም መጥቶ በመመንኰስ ሰይጣንን ድል እስከያደርገው ድረስ ተጋደለ፡፡ አባ ማቴዎስም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሄዶ በታላቅ ተጋድሎ ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ በገዳሙ ያሉ አባቶችም ቅዱሳን መላእክት ለአባ ማቴዎስ ሲገለጡለትና ሲያከብሩት በራእይ ስላዩ አባ ማቴዎስ ውዳሴ ከንቱን በመጥላት ከአንዱ ገዳም ወደ አንዱ ገዳም የሚዘዋወር ሆነ፡፡ በአንዲት ዕለትም በቅዳሴ ላይ ሲያገለግል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በታናሽ ሕፃን አምሳል በመሠዊያው ላይ ተቀምጦ አየው፡፡ ይህንንም ባየ ጊዜ ከታላቅ ለቅሶ ጋር አገልግሎቱን ፈጸመ እንጂ ለማንም አልተናገረም፡፡ አበ ምኔቱም አባ ማቴዎስን ለረጅም ሰዓት ቆሞ ባየው ጊዜ አንዳች ምሥጢር እንዳቆመው ዐውቆ ይህንን ይገልጥለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ፡፡ በአንዲት ዕለትም አባ ማቴዎስ እንደልማዱ ይቀድስ ዘንድ ገባ፡፡ ጌታችንም በሕፃን አምሳል በጻሕሉ ውስጥ ተኝቶ ኅብስትንም መስሎ በአባ ማቴዎስ እጅ ሲቆረስ ለአበ ምኔቱ ታየው፡፡ እርሱም ይህን በማየቱ እጅግ አደነቀ፡፡ "ለእኛ ለሰው ልጆች ይህን ጸጋ ለሰጠኸን አቤቱ ለአንተ ምስጋና ይገባሃል" አለ፡፡ ❤ አባ ማቴዎስም ይህን ባየጊዜ ታላቅ የብረት ችንካር አምጥቶ ተልቶ ከእርሱ ትል እስኪወጣ ድረስ ችንካሩን በጉልበቱ ውስጥ ቀረቀረው፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ደብረ ቁስቋም ገብቶ በዚያም እየተጋደለ ኖረ፡፡ ወደላይም ቀና ብሎ በተመለከተ ጊዜ የክብርን ባለቤት ጌታችንን በአባቱ ቀኝ ተቀምጦ አየው፡፡ ወደታችም ሲመለከት በውቅያኖስ ጥልቅ ውስጥ በጌትነቱ ክብር የሚያየው ሆነ፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት "ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ አለህ፣ ወደ ሲኦልም ብወርድ በዚያ አለህ" እንዳለ፡፡ መዝ 139፥8፡፡