ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC
እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ ! የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከልን የቴሌግራም ቻናል ድረ ገፃችንን - www.tmceth.com ይጎብኙ የዩቲዩብ ቻናላችን https://www.youtube.com/channel/UCKqL7UekDOyp6q4j7ObVf9Q
Ko'proq ko'rsatish12 224
Obunachilar
+924 soatlar
-17 kunlar
-6330 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
የመ/ር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ።
ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት የዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ አዘጋጅ መ/ር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሰሜን ጎጃምና የባሕር ዳር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የመምህር ሥዩም ጉልላት ቤተሰቦችና ዘመዶች በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
በሥርዓተ ቀብሩ ጸሎተ ፍትሐት የተከናወነ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ትምሕርተ ወንጌል ተሰጥቷል።
በትምህርታቸውም አሽከርካሪዎችና እግረኞች በመንገድ አጠቃቀም ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
መ/ር ሥዩም ጉልላት ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት የነበሩ ሲሆን በ 37 ዓመታቸው በመኪና አደጋ ሕይታቸው ማለፉ ይታወሳል።
©EOTC TV
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
ዜና ዕረፍት
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት የዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ አዘጋጅ መ/ር ሥዩም ጉልላት በደረሰበባቸው የመኪና አደጋ ሐምሌ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል !
የመምህር ሥዩም ጉልላት ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ሠራተኞች በተገኙበት የሚፈጸም መሆኑ ታውቋል።
🙏 13👍 1
በሸካ ቤንች ማጂ ሸኮ ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ኢ-አማንያን ተጠመቁ።
ሐምሌ 08 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሸካ ቤንች ሸኮ ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በቤንች ወረዳ ቤተ ክህነት በጊዲ ቤንች ወረዳ ከጻት ቀበሌ፣ ከተኩስ ቀበሌ እና ከጋጫ ቀበሌ የተወጣጡ ምዕመናን ሐምሌ ሰባት ቀን በቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል ከኢ-አማኒነት እና ከባዕድ አምልኮ በመውጣት የቅድስት ሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል።
ምዕመናኑ ለአንድ ወር መሠረታዊ ትምህርት ሲከታተሉ ቆይተዉ በትላንትናው ዕለት በዲዙ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ተጠምቀዉ ሀብተ ወልድ እና ስመ ክርስትናን አግኝተዋል።
መረጃውን ያደረሱን የቤንች ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ፀሐፊ እና ሰባኬ ወንጌል መምህር ዲያቆን ግርማ አይበራ ናቸው።
👍 6❤ 1👏 1
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረጉ !
ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዛሬው ዕለት ለሐዋርያዊ ጉዞ ወደ ሰሜን አሜሪካ አቅንተዋል።
የቅዱስነታቸው የክብር አሸኛኘትም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ሓላፊዎች በተገኙበት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ፤ በመቀጠልም በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፓርት ተከናውኗል፡፡
ቅዱስነታቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜን አሜሪካ ተመሳሳይ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡
👍 10
የተለያየ ዜግነት ያላቸው 14 ጃማይካውያን በጥምቀት ከበሩ።
ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዐት መሠረት ጥምቀት የክርስትና መግበያ በር ናት፡፡ ጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ተወልደን የሥላሴ ልጅነት የምናገኝበት (ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና) ምስጢር ነው፡፡
በመሆኑም ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጃማይካውያን፣ እንግሊዛውያን፣ አሜሪካውያን ዜግነት ያላቸው ጃማይካውያን እና በኢትዮጵያ በሻሸመኔ የሚኖሩ 14 ጃማይካውያን ተጠምቀው ከሥላሴ ልጅነትን አግኝተዋል፡፡ የተጠማቂዎቹ ዕድሜያቸው ከ1 ዓመት ሕጻን እስከ 68 ዓመት ያሉ አረጋውያን የሚገኙበት ነው፡፡
ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ሢራክ አድማሱ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ እንደተናገሩት “እነዚህን የውጭ ዜግነት ያላቸውን ሰዎች ቤተክርስቲያን አስተምራ ስታስጠምቅ የሚያስደስት ነው፡፡ ለተጠማቂዎቹም በእንግሊዝኛ ቋንቋ እና በአስተርጓሚ በአማርኛ ቋንቋ መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርት ተምረው ተጠምቀዋል፤ ወደፊትም ተከታታይነት ያለው ትምህርት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ማስተማር ይገባል” ብለዋል፡፡
በካቴድራሉ በልማት ኮሚቴ ውስጥ የሚያገለግሉት ወይዘሮ ዐሥራት የውጭ ዜጎቹ ወደ ካቴድራሉ መጥተው እንዲጠመቁ ከማድረግ አንጻር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ናቸው፡፡ “በተለይም ዛሬ ተጠምቀው ሳይ በጣም ከፍተኛ ደስተኛ ተሰምቶኛል” ብለዋል፡፡
ተጠማቂዎቹ ጃማይካውያን አባቶች እንደተናገሩት “የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትልቅ ታሪክ ያላት ታላቅ ቤተክርስቲያን ናት፡፡ በዚህች ቤተክርስቲያን መጥተን ተምረን ተጠምቀን ከሥላሴ ልጅነት በማግኘታችን ተደስተናል፤ በአዲስ ሕይወት ውስጥ ነው ያለነው” በማለት አስተያታቸውን ሰጥተዋል፡፡ አያይዘውም “በቀጣይም ለወንድሞቻችንና ለእኅቶቻችን ስለ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እንመሰክራለን፤ ወደዚህ ቅድስት ስፍራም መጥተው እንዲጠመቁ እናደርጋለን” ብለዋል፡፡
©EOTC TV
❤ 13👍 3👏 1
Boshqa reja tanlang
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.