cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ኦርቶዶክስ መረጃ 2

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 205
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
-730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

#ሰበር_ዜና ዛሬ ከምሽቱ 1:30 ላይ በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል የአዲስ አበባ የቀድሞው ስራ አስኪያጅ የነበሩት ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ እና የመናገሻ አምባ ማርያም እና የጋራው መድኃኔዓለምና ደ/ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አባ ሞገስ ኃ/ማርያም ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት አስኬማቸውንና አርዌ በትሩን ለሕጋዊዋ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሢኖዶስ ለማስረከብ እንዲሁም ቅድስት ቤተክርስቲያንንና ምዕመናንን ይቅርታ ለመጠየቅ በጉዞ ላይ እያሉ በህገ ወጡ ቡድን ግብረ አበሮች ተይዘው ወደ እስር ቤት እንደተወሰዱ ተገለፀ። መረጃውን ያወጣው 'የሰንበት' ትምህርት ቤት ሚዲያ ማዕከል'' ነው! @ORTODOX_MERJA @ORTODOX_MERJA2
Hammasini ko'rsatish...
እኛ ላዘንነው ከጎናችን መሆን ባትችሉ እንኳን ዝምታን ሳትመርጡ በንፁሀን ደም የተሳለቃችሁ ነጭ የለበሳችሁ ሁሉ የቤተክርስቲያንን መከፈል እና መፍረስ የተመኛችሁ ደስም የተሰኛችሁ ሁሉ እንድትፈርስም የአቅማችሁን የጣራችሁ በትንሽ ዳቦ የለወጣችሁ ነገን እጠግብ ብላችሁ ዛሬን በሰው ደም በሺህ አመታት ታሪክ ላይ የተረማመዳችሁ መሸሸጊያ ባጣችሁ ጊዜ ያስጠጋቻችሁን ቤተክርስትያን የገፋችሁ ሀገር ፊደል ቁጥር ቋንቋ ባህል ሰጥታችሁ ሰው ያረገቻችሁን ቤተክርስትያን ላይ ፊታችሁን ያዞራችሁ ሀዘንሽ የግልሽ ያላችሁ ልጆቿ ሲያለቅሱ ማቅ ስተለብስ በየSocial mediaw የተዘባበታችሁ ሀገርን ከነ ክብሯ ጠብቃ በጥቁር ህዝብ ታሪክ የሌለን ጥበብ ለዓለም ያበረከተችን ቤተክርስቲያን ሀዘንሽ ሀዘኔ አደለም ያላችሁ ሁሉ ታሪክሽ ተረት ነው እምነትሽም ጣዖት ነው ያላችሁ ሁሉ ስናዝን አይዟችሁ ያላላችሁ ሁሉ ከዚች ቀን አንስቶ እኔ አላውቃችሁም እናንተም የኔ ሰዎች አይደላችሁም፡፡ ፈጣሪም እምባዋን ቆጥሮ ፍርዱን በህይወት እያላችሁ ይስጣችሁ፡፡ አመሰግናለሁ ፡፡ YILIKAL GETU @ORTODOX_MERJA
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰበር ዜና ብፁዑ አቡነ ናትናኤል «መንግስት ቃሉን የማያከብር ከሆነ፣ በቤተክርስቲያን ድርድር ስለሌለ ምዕመናን ልጆቻችን በተጠንቀቅ በመቆም አይናቸውን ቤተክርስቲያን ላይ ጆሯቸውን ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ አድርገው የአባቶችን ድምፅ ይጠብቁ» በማለት አሁን ቀጥታ እየተላለፈ ባለው መግለጫቸው አስጠነቀቁ! ይሄ ነው የምንፈልገው!!! አዛምቱ!!! @ORTODOX_MERJA
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
አስረኛ ጊዜ እያየሁት ነው 🤣 https://youtu.be/vHDcgnxy2hc https://youtu.be/vHDcgnxy2hc
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የመምህር ምህረት አሰፋ ቤት ተከቧል ከሰዓታት በፊት በቀጥታ ስርጪት የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ እየተናገረ እና ምዕመኑን እያጽናና በነበረበት በመኖሪያ ቤቱ ሳለ በደንገት ሁለት ፓትሮል መኪና መጥቶ ቤቱን ከቦታል ምንጪ ያሬድ (ያያ) ሁለቱም CHANNEL ተቀላቀሉ @ORTODOX_MERJA @ORTODOX_MERJA2
Hammasini ko'rsatish...
የብሄር ብሄረሰቦች ተብሎ የተቋቋመው የጨበራ ሲኖዱስ እንዲፈርስ ተወስኗል፡፡ ሰልፉን ቤተ ክርስትያኒቱ ማድረግ ከፈለገች መቀጠል እንደምትችል ከስምምነት ላይ ተደርሷል!! በህገወጥ መንገድ የተሾሙት 25 ጳጳሳት ቆብ እና መስቀላቸውን ያስረክባሉ። ሶስቱ አባቶች በይቅርታ ይመለሳሉ ተብሏል። ዝርዝር መረጃ ከመግለጫው የምንሰማው ይሆናል። #ሼር @ORTODOX_MERJA
Hammasini ko'rsatish...
#Update: ቅዱስ ሲኖዶሱ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር በቤተመንግስት ውይይት አድርገው ወደ መንበራቸው በሰላም ተመልሰዋል። ስለነበራቸው ውይይት አጠቃላይ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። @ORTODOX_MERJA @ORTODOX_MERJA2
Hammasini ko'rsatish...
መረጃ‼️ 15 ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ በደራርቱ ቱሉ የሚመራው የሀገር ሽማግሌዎች ህብረት ከጠ/ሚ አብይ ጋር ፊት ለፊት ማነጋገር ጀምሯል። ስብሰባው አሁን ተጀምሯል። መንበረ ፓትርያርክ (የፓትርያርኩ መኖርያ) በፌደራል ፖሊሶች ተሞልቷል። ልንጠብቃችሁ ነው የመጣነው የሚል ምክንያት ከፖሊሶቹ ተሰጥቷል። የካቲት 3/2015 ዓ.ም @ORTODOX_MERJA @ORTODOX_MERJA2
Hammasini ko'rsatish...
#Update ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ " ትላንት ምሽት የመንግስት የጋራ ግብረኃይል የሰጠውን የ " ሰልፍ ክልከላ መግለጫ " እንደማይቀበለው አስገንዝቧል። ቅዱስ ሲኖዶስ የትላንቱ የመንግስት መግለጫ " መንግሥት አሁንም ችግሩን ለመፍታት ሳይሆን ቤተክርስቲያኒቱን ለአንዴና ለመጨረሻ ለማውደምና ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማጥፋት የታወጀ አዋጅ መሆኑን በጽኑ እንድናምን አድርጎናል " ብሏል። (ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል) ሁለቱም CHANNEL ተቀላቀሉ @ORTODOX_MERJA @ORTODOX_MERJA2
Hammasini ko'rsatish...