cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ننجح

🌺🌺إذا أردت أن تعرف مستقبل أمة فانظر ماذا يفعل شبابها🌺🌺

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
178
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

SCHOLARLY ADVICE ON HOW TO GET BACK JERUSALEM. The great scholar and Muhaddith of this era Sheikh Al-Albânee Rahimahullahu said: "If Muslims want Jerusalem back then let them rectify their Aqeedah and Evil Character." (Al Qurʾān 24:55) "Allah has promised those who have believed among you and done righteous deeds that He will surely grant them succession [to authority] upon the earth just as He granted it to those before them and that He will surely establish for them [therein] their religion which He has preferred for them and that He will surely substitute for them, after their fear, security, [for] they worship Me, not associating anything with Me. But whoever disbelieves after that – then those are the defiantly disobedient" The Prophet of Allah (sallallaahu alayhiwa sallam) walked in and took back the sacred city of Makkah within ten years. The Conquest of Makkah, according to most scholars, took place in the 8th Year of Hijri. The proper Aqeedah and Manhaj imparted to the Sahabah both in Makkah and Madinah aided them to strike a decisive defeat on the polytheists and the kafiroon. Let's all go back to Allah and desist from all hue and semblances of Shirk, Kufr, Bid'ah including Fanatical Blind Following.
Hammasini ko'rsatish...
ኢድ ሙባረክ! የሸዋል ወር ጨረቃ በሳኡዲ አረቢያ ባለመታየቷ የኢድ አል ፊጥር በዓል ሃሙስ መሆኑ ታውቋል! ነገ እሮብ የረመዳን የመጨረሻ ቀን ይሆናል! አላህ መልካም ስራችን ይቀበለን! አቡ ዳውድ ኡስማን
Hammasini ko'rsatish...
T.me/ahmedin99 የጎዳና ላይ ኢፍጣር ዝግጅቱ ነገ ግንቦት 03/2013 በዚያው አደባባይ ከቀኑ በ10 ጀምሮ በመንግስት ሙሉ ወጪ በጸጥታ ኃይሉ ጥበቃና አጀብ ይደረጋል።አንድ ሆነን በጋራ ከቆምን ሌሎች ጥያቄዎቻችንንም እንዲሁ እናስመልሳለን። ✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳✳ Sagantaan Ifxaaraa kaleesaa dhorkamee bakkuma sila karoorfameetti bor caamsaa 03/2013 baasii guutu mootumaadhaan Qaama nageenyyatiin kabajaan eegamaa sa'a 10 irraa kaasee ni godhama. Tokko taanee yoo waliin dhaabbannee gaaffilee keenyas akkasuma debisiifna.
Hammasini ko'rsatish...
📌 የኸይሩ ገበያ ለሁሉም ክፍት ነው! ★ T.me/ahmedin99 የመልካም ስራ አጋጣሚዎች ላይ ማንም ሊዘናጋ አይገባም። ነጋዴ በገበያ ቀን አይተኛም!፣ አያረፍድም!፣ይበቃኛል ብሎም በጊዜ ዘግቶ ወደ ቤቱ አይገባም! ይልቅ ጎበዝ ነጋዴ ሰዓቱን ጠብቆ ወደ ገበያ ገብቶ የሚወጣው ስራውን ሲያጠናቅቅ ነው። ሰዎች ሲዘሩ የተኛ ሰውም መጨረሻ ላይ እርሱ ቁጭትን ያጭዳል!ስለዚህ በተቀሩት የረመዷን ቀናት ነገ ኣኺራ ላይ ምርቱን የምናነሳ መልካም ስራ በብዛት እንዝራ! 🛑 ለይለተል-ቀድርን ለማግኘት በነጠላ ለሊቶች ብቻ እየተጋን ጥንድ ለሊቶች ላይ አንስነፍ! አንዳንዴ እኮ ሰዎች የማያውቁት የአቆጣጠር ክፍተት ኖሮ ጥንድ ያሉት ቀን ነጠላ ሊሆን ይችላል!! የሀገራት የረመዷን አጀማመር ልዩነት መኖሩም የሚታወቅ ነው! ስለሆነም አስሩን ውድ ቀናት ሁሉንም ቀን ከለሊት በዒባዳ እናክብራቸው። ነገ አላህ ዘንድ ያስከብሩናል! 🛑 ቀንም ሌሊትም ሱንና ሰላቶችን እናብዛ፣ 🛑 ቁርኣን ደጋግመን ለማኽተም እንጣር፣ 🛑 ቁርኣን የመቅራት ችሎታ ባለመኖር ወይም በሌሎች ምክንያቶች መቅራት ያልቻለ ሰው ሱረቱል-ኢኽላስ (ቁል ሁወልላሁ አሐድ'ን) ሳይሰላች ይደጋግም። ይህን ምዕራፍ 3 ጊዜ መቅራት ምንዳው ሙሉ የቁርኣን ምዕራፎችን የመቅራት ያህል እንደሆነ ነቢዩ ﷺ ተናግረዋል። 📌 እንዲሁም ሰላት ላይ ፋቲሓን መቅራት ለማይችል ሰው በፋቲሓ ምትክ እንዲባል ነቢዩ ﷺ ያስተማሩትን የሚከተለውን ዚክር ይበል (سبحان الله، والحمد لله، ولا إله إلا الله، والله أكبر، ولا حول ولا قوة إلا بالله) (ሱብሓነላህ ወልሐምዱ ሊላህ ወላ-ኢላህ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወላ ሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ) ይህ ሰላት ላይ እንኳ ቁርኣን መቅራት ላልቻለ ሰው ቁርኣንን/ፋቲሓን የሚተካ ዚክር ነው! ከሰላት ውጪም ዘወትር ቢባል ይበልጥ ወደ አላህ ያቃርባል። 🛑 በሌላ በኩል ደግሞ "ከልጅና ከገንዘብ የሚሻሉ ጥሩ የኣኺራ ተስፋና ድልቦች" እንደሆኑም ቁርኣን ላይ የተነገረላቸው ታላቅና አላህ ዘንድ የተወደዱ ቃላቶች ናቸው። 🔖ተራዊሕም ተሀጁድም እንደ አቅምና የግል ሁኔታችሁ ስገዱ። (በአንድ ሌሊት ሁለቱ አይሰገድም) የሚባለው አባባል ትክክል አይደልም! ከዒሻ ሰላት ጀምሮ እስከ ፈጅር አዛን ድረስ ያለው ጊዜ በሙሉ የለይል ሰላት ጊዜ ነውና ሁሉም እንደ አቅምና ሁኔታው ሁለት ሁለት ረክዓ የፈለገውን ያክል መስገድ ይችላል። 🛑 በህመም፣ ሴት ልጅም በሐይድና በወሊድ ደም ምክንያትና ክብካቤ በሚሹ ህጻናት ምክንያት እንደልባቸው ዒባዳዎችን ማድረግ ያልቻሉ በመጀመሪያ ደረጃ ቢችሉ ለመስራት በመዘጋጀታቸውና በመልካም ኒያቸው አላህ ሙሉ ምንዳ እንደሚሰጣቸው ይወቁ!በተጨማሪም የሚችሉትን ያክል ያድርጉ። ቀሪውን አዛኙ አላህ ይሞላዋል። 🛑 ወደሱ አንድ ስንዝር ስንቀርብ እሱ ወደኛ አንድ ክንድ የሚቀረብና ለባሪያዎቹ በሙሉ መልካምን የሚወድ ጌታ ነውና! 🛑 ("የዱኒያ ህይወት መዘናጊያና መጫወቻ እንጂ ሌላ አይደለም! እውነተኛ ህይወት ማለት የኣኺራ ህይወት ነው! -ሰዎች ይህን ቢያውቁ- ዱኒያን ከኣኺራ ባላስበለጡ ነበር!") አል- ዐንከቡት 64 🛑 አላህ መልካም ስራ ላይ ያበርታን 🛑 ትንሿንም ይቀበለን ብዙውን ወንጀላችን ይቅር ይበለን 🛑 በሰላም ወደሱ የሚያደርሰውን መንገድ አስይዞን እዛ ላይም ያጽናን "ኣሚን" ምንጭ:– ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ አደም ★★★★★★★★★★ የአህመዲን ጀበልን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ። ለሌሎችም ሼር በማድረግ ያጋሩ። ★ T.me/ahmedin99
Hammasini ko'rsatish...
Ahmedin Jebel Official - አህመዲን ጀበል

ይህ ይፋዊ የአህመዲን ጀበል የቴሌግራም ገፅ ነው!

የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል:– "ለይለተል ቀድርን ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ዊትር(ጎዶሎ) ቀናት ውስጥ ተጠባበቋት።" ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
Hammasini ko'rsatish...
ይህ ምስል ተራራ ፣ ዋሻ ፣ መሿለኪያ መንገድ አሊያም በውኃ ጥም ብዛት ስንጥቁ የበዛ ምድረበዳ አይደለም። በቅርቡ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ሲሽከረከር የነበረውና በኢንጂነር ዐብዱልከሪም የተሰራው የደሴ-ኮምቦልቻ ተለዋጭ የዋሻ መንገድ ዲዛይንም አይደለም። እና ምን ይመስላችኀል ?? አንዲት ትንሽዬ መርፌ የሰው ቆዳ ውስጥ ዘልቃ በመግባት የፈጠረችውን ቀዳዳ በኤሌክትሮን ማይክሮስኮፕ 850 ጊዜ ያህል በማጉላት የተገኘ ምስል ነው። وَلَقَدْ خَلَقْنَا الإنْسَانَ مِنْ سُلالَةٍ مِنْ طِينٍ «በእርግጥም ሰውን ከነጠረ ጭቃ ፈጠርነው» ምዕራፍ አል ሙእሚኑን - 12 http://t.me/abuafnanmoh
Hammasini ko'rsatish...
ጠዋት ጠዋት ሁሌም በመስገጃቸው ላይ ሆነው ጸሐይ እስክትወጣ ድረስ አላህን ሲያወሱ ያገኟቸዋል፡፡ ዚክር ያበዛሉ፡፡ አይደክሙም። አይሰንፉም። አይዘናጉም። ምክንያቱን ሲጠይቋቸው ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ በማለት ይመልሱ ነበር፦ “ ይህች ቁርሴ ናት፤ እሷን ካልቀመስኩ መነሳት አልችልም፤ አቅም ያንሰኛልና ተልፈስፍሼ እወድቃለሁ” ወዳጆቼ! አላህን ከማውሳት ማዕድ እንቅመስ፡፡ ይጣፍጣል፣ ያረካልና ሥሙን እናውሳ፤ እንቀድሰው፣ እናወድሰው፡፡ መስገጃችን ምሸጋችን ይሁን፡፡ ሁሌም ዱዓ ይኑረን፡፡ እጃችን ከፍ ይበል ይዘርጋ፤ ሀሳባችን ይሰብሰብ፤ ዱዓ ያለው ሰው ነው ቆሞ የሚሄደው፡፡ ━━━━━━✦✿✦━━━━━━ #منقول
Hammasini ko'rsatish...
ሚስክ ሚስክ ሸቶኛል . የሚነፍሰው ንፋስ፣"ጥዑም" ጣእም አለው፤ ከቀናቶች ሁሉ፣ዋዜማው ልዩ ነው፤ መሀርታ ነው እዝነት ነው፣ብሩክ ነው ድምቀት ነው። ያሳደፍኳት ነፍሴ፣ደስ አላት ቦረቀች፤ ካስለመድኳት ውሸት፣ተፀፅታ ራቀች፤ እግሬም ተዘጋጀ፣ወደ መስጂድ ሊሮጥ፤ ለአንድዩ ቆሞ፣በዲስኩር ሊመሰጥ፤ የመስጂዱን ቅጥር፣አዘውትሮ ሊረግጥ። . ናፍቆት ነው ደስታ ነው፣ፍቅር ነው ውዴታ፤ ሸይጣንን አባሮ፣መስገዱ ለጌታ። ከአንድዬ ፊት ቆሜ፣እጄን ከፍ አድርጌ የሆዴን ላወጋው፤ ፀሎቴን አድምጦ፣ምልሰቴን ወዶልኝ መርጋቴን ሊያረጋው፤ መሻቴ እንዲሞላ፣እንቶ ፈንቶ አውጊ አንደበቴን ዘጋው፤ የዋዜማው አየር፣እንደ ሚስክ አውዶኝ ስለ ወሩ ጓጓው። . ሸጋ ነው ምልሰቴ፣ሰላም ነው ውበት ነው፤ የወሩ ዋዜማ፣"ጥዑም"ነው ልዩ ነው። ብስራትን ያዘለው፣ረመዳን ናፍቆኛል፤ ምጌ በምተፋው፣በዋዜማው አየር ሚስክ ሚስክ ሸቶኛል። ወሩስ እንዴት ይሆን? @deawa1 @deawa1 @deawa1
Hammasini ko'rsatish...
⭕️🛑ማሳሰቢያ🛑⭕️ ነገ ሰኞ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሚኒ ሲቴዲየም በሚካሆደው ትልቅ የሀይማኖቶች ፎረም ስብሰባ ላይ ሁሉም ሙስሊም ፣ ወንዱም ሴቱም እስልምናን የሚገልፅ ነገር ለብሶ ጠዋት 2:00 ላይ እንዲገኝ ስለተባለ ላልሰማ አሰሙ። Share share
Hammasini ko'rsatish...
የሁሉም የክልል ም/ቤት የኡለማና የቦርድ አባላት ጥሪ በአስቸኳይ እንዲጀመር በድጋሚ እያሳሰብን ጠቅላይ ም/ቤቱ እንደ ከዚህ ቀደሙ ጠቅላላ ጉባኤው በስድስት ሥራ ቀናት ውስጥ ሳይጠራና አዎንታዊ ምላሽ ሳይሰጥ ከቀረ በህዝብና በመንግስት የተጣለብንን ኃላፊነት ለመወጣትና ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ይኸው ተቋም በመፍረስ ሂደት ውስጥ ተባባሪ ላለመሆን ስንል እንደ የሐረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አስቸኳይ አጠቃላይ የኡለሞችና የሥራ አመራር ቦርደችን ጠቅላላ ጉባኤ እንደምንጠራ የየድርሻችንን እንወጣለን ። እንዲሁም ጠቅላላ ጉባኤው ጉዳዮቹን ተመልክቶ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤትን እውቅና ለመንፈግና ይፋዊ የሥራ ግንኙነታችንን ለማቋረጥ እንደምንገደድ ለማሳሰብ እንወዳለን ፡፡ ከሠላምታ ጋር ግልባጭ ለሁሉም ክልል የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶች ለሰላም ሚኒስተር ለጠቅላይ ሚኒስተር ፅ/ቤት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለሁሉም ክልላዊ መንግስታት ለሁሉም ሚዲያዎች
Hammasini ko'rsatish...