Ethiopian Catholic Charismatic
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
805
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
-130 kun
Postlar arxiv
#ለካርዝማቲክ_አባላት
የአባልነት ፎርም የሞላችሁ በሙሉ ሐምሌ 13 በቀጣይ ማህበሩ ስለሚያከናውናቸው መንፈሳዊ እንቅስቃሴዎች ከአባላቱ ጋር በመወያየት መስራት አስፈላጊ በመሆኑ በተጠቀሰው ቀን ሁሉም አባላት እንድትገኙ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን።
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሰሚናር ወስዳችሁ የአባልነት ፎርም ያልሞላችሁ ከተጠቀሰው ቀን በፊት ፎርሙን በመሙላት ፕሮግራሙን መሳተፍ ትችላላችሁ።
በዚህ ቀን ማህበሩ ልዩ የሆነ የምሳ ግብዣ እና የመዝናኛ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።
ቦታ ቅዱስ ሚካኤል Acs አዳራሽ
#ሐምሌ_13_ከጠዋቱ_3:30_እስከ_11:00
መቅረት በፍጹም አይቻልም
🙏ተሃድሶ (ሪቫይቫል) አንዲሆን ምን ማድረግ ይጠበቅብናል
3 #አለመርካት_ውስን_አለመሆን
ሐዋርያት 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።
⁴ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።
#ለመንፈስ_ቅዱስ አዲስ የሆነ አሰራር ትልቁ እንቅፋት በድሮ ታሪክ እና አሰራር መያዝ ነው። እግዚአብሔር ድሮ በሰራው ስራ አእምሮአችን ስለሚያዝ አሁን ላይ መሰራት የሚፈልገውን ነገር እንገድበዋለን። በበፊት ነገር እንዲህ ነበርን እያሉ በማውራት ሳይሆን #አሁንም_መንፈስ_ቅዱስ_ይሰራል ብለው በሚነሱ ሰዎች ሪቫይቫል ይሆናል።
#የተሐድሶ_ሰዎች መለኮታዊ ስርዓትን ከተቀበሉ በኋላ ገደብ የለሽ የሆነውን የመንፈሱን ኃይል በመገንዘብ በደረሱበት የስኬት ጫፍ ባለመርካት #ለሚሻል_ነገር መዘርጋት ይኖርባቸዋል። አሁን የያዝነው ነገር የበለጠ አይናችንን የሚከፍት እንጂ አይናችንን የምንጥልበት መሆን የለበትም #ለምሳሌ_ዛሬ_በሕይወታችን_እያየነው_ያለ_አስደሳች_ለውጥ_ሊኖር_ይችላል_በመንፈስቅዱስ_ከዚህ_የተሻለ_ነገር_ተዘጋጅቶልናል። ስለዚህ እኛም መንፈስ ቅዱስ በሰጠን አይን ማየት አለብን። በዚህ መርካት የለብንም እኛ ውስጥ ያለው አቅም ሲገለጥ ለዓለም የሚደርስ ታላቅ ጉልበት አለው። ሐዋርያት በኢየሩሳሌም በነበረው አገልግሎት የረኩ ይመስሉ ነበር ነገር ግነ የእነርሱ አገልግሎት ጌታም ቀድሞ ያላቸው #ወደ_ዓለም_ሁሉ_ሂዱ የሚል ነው። ነገር ግን እነርሱ ስደት መጥቶ እስኪያወጣቸው ድረስ ረክተው በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ነበር። ጌታ ሁልግዜ የሚፈልገው የእኛ ፋላጎት ድረስ እንድንሰራ ሳይሆን የመንፈስ ቅዱስ ፍላጎት ድረስ እንድንሰራ ነው። ስለዚህ እኛም እንደ ጌታ ፈቃድ ሁሉን ማድረግ የሚችለው የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ስለተቀበልን #በተቀበልነው_ልክ_ልንወጣ ይገባል።
#እሳቱ በጭራሽ በቃኝ አይልም በዓለም ያሉትን ሰዎች ሁሉ ቢደርስና እያንዳንዱን የምድር ነዋሪ ወደ ክርስቲያንነት ቢለውጥም እንኳን በጭራሽ በቃኝ አይልም። አንዳንድ ግዜ መንፈስ ቅዱስ ገና ስራ ሲጀምር በሚሆነው ነገር ረክተው በቃኝ የሚሉ እንደጨረሱ የሚቆጥሩ ሰዎች አሉ። ባመጡት አነስተኛ ተጽዕኖ ስኬት ይገደባሉ። በእንደዚህ ልንወስን አይገባንም #እኛ_የኢትዮጵያን_ቤተክርስቲያን_ብቻ_ሳይሆን_በሁሉ_ሀገር_ላለች_ቤተክርስቲያን_ለማቀጣጠል_ተጠርተናል።
#አዋጅ 🎷🎷🎷
#በውስጤ_ኃይለኛ እሳት አለ
#አልገድበውም_ይነዳል እኔን አልፎ ሌሎችንም ያቃጥላል
#በትንሽ_ነገር_አልወሰንም አልፌ እሄዳለው
#መንፈስ_ቅዱስ እንዳየው አያለው
#መንፈስ_ቅዱስ የነገረኝን እናገራለው
#መንፈስ_ቅዱስ የነገረኝን ነኝ
#ለብ ብዬ ሳይሆን በመቃጠል አገለግላለው
#የሚይዘኝ ምንም አይነት የምድር ኃይል የለም
#በኢየሱስ ስም !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!
#የተቆረጠ_የሪቫይቫል_ትኬት ተሰጥቶናል 2013
#ተነሱ_ጌጠኛ ልብሳችሁን ልበሱ!!!
#ተነሺ_አብሪ ዘመኑ ያንቺ ነው!!!
#ተነሳ_አብራ ዘመኑ ያንተ ነው!!!
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
ዛሬ ከ11:30 እስከ 1:30 ልዩ ምሽት ይኖረናል በቅዱስ ቁርባን ስግደት ጌታ በኃይል ይጎበኘናል የማይቀርበት ልዩ ፕሮግራም ከቅዱስ ቁርባን በሚወጣ ኃይል ፈውስና እረፍት ይሆናል። ስለ ምድራችን በተለይ ስለሀገራችን በልዩ ሁኔታ እንፀልያለን። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
🙏ተሃድሶ (ሪቫይቫል) አንዲሆን ምን ማድረግ ይጠበቅብናል
1 #መለኮታዊ_የመንፈስ_ቅዱስ_ምሪት -
ያለ መንፈስ ቅዱስ ምሪት ምንም ነገር ማድረግ ትርፉ ድካም እና ፍሬቢስ መሆን ነው። ሁልግዜ ተሃድሶ #መንፈስ_ቅዱስ የሚገልጠው ኃይል ነው። ስለዚህ የትኛውም መንፈሳዊ አገልግሎት #መንፈስ_ቅዱስን ያስቀደመ መሆን አለበት። ጳውሎስ ወይም ጴጥሮስ አደለም ኢየሱስ ራሱ በደንብ ያስጠነቀቀበት ነገር ቢኖር ኃይል ሳይቀበሉ ምንም አይነት አገልግሎት እንዳይጀምሩ ያዘዛቸው። “እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ።”
— ሉቃስ 24፥49
#የመንፈስ_ቅዱስን ኃይል ከተቀበሉ በኋላ ለዓለም የሚደረስ ተሃድሶ (ሪቫይቫል ) ነው የሆነው። ስለዚህ ከምንም በላይ መጀመሪያ ቅድሚያ መስጠት ያለብን #ለመንፈስ_ቅዱስ_ምሪት ነው። ለመንፈስ ቅዱስ ምሪት ራሳችንን ከሰጠን ከእኛ አልፈን ለሌሎች የሚተርፍ መንፈሳዊ ኃይል እንቀበላለን።
ዛሬ ላይ የምናየው መንፈሳዊ ውድቀት ሁሉ #ለመንፈስ_ቅዱስ ምሪት ክፋት አለማድረጋችን ነው።
2 #መኮታዊ #ስርዓትን_ማስተናገድ
ይህን ክፍል በጣም በጥንቃቄ እና በማስተዋል የምንመለከተው ክፍል ነው። የተሀድሶ እሳት የእግዚአብሔር #ሰማያዊ_ኃይል ነው። ስለሆነም በከፍተኛ ደረጃ እንዲሰራ #ሰማያዊ ስርዓት (Heavenly system ) ያስፈልገዋል #ሰማያዊ_የእግዚአብሔር_ኃይል በምድራዊ ወይም ሰብአዊ ስርዓት ውስጥ በኃይል ሊሰራ አይችልም። ይህን በግልፅ የምናየው ነው በስርዓት ተጠላልፈን መንፈስ ቅዱስ እንዳይሰራና እንዳይታወቅ ሆኗል። በከፍተኛ ጫናና ተፅእኖ ለማሳደር መለኮታዊ የሆነ ስርዓት መቀበል የግድ ነው። መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ለአዲስ ወይን አዲስ አቁማዳ ያስፈልገዋል።
“በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አቁማዳው ይፈነዳል፥ የወይን ጠጁም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል፤ ነገር ግን #አዲሱን_የወይን_ጠጅ_በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።”
— ማቴዎስ 9፥17
አሮጌው አቁማዳ አዲሱን ወይን ለመያዝ አይችልም ምክንያቱም አዲሱ ወይን በሚብላላበት ግዜ አብሮ መለጠጥ አይችልም። በተመሳሳይ መልኩ የሰው ስርዓት ሰማያዊውን የእግዚአብሔር ኃይል ሊሸከም አይችልም። ምክንያቱም ከሰማይ የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ ሙሉ ስለሆነ ሊቆጣጠረው የሚችል ምንም አይነት ምድራዊ ኃይል የለም።
“የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።”— ማቴዎስ 15፥9
“በአይሁድ ሥርዓት በፊት እንዴት እንደ ኖርሁ ሰምታችኋልና፤ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ያለ ልክ አሳድድና አጠፋ ነበር፥”
— ገላትያ 1፥13
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#የመንፈስ_ቅዱስ_ስራ_በአማኝ_ሕይወት
ማርቆስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።
¹⁶ ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።
¹⁷ ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥
¹⁸ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በእርግጥ በሐዋርያት ዘመን የነበሩ ድንቅ እና ተአምራት ቀርተዋል? በፍፁም አልቀሩም አብዛኛው ሰው ባልተጠቀመበት ነገር ላይ ወይም በስንፍናው ላይ ምክንያት አቅራቢ ነው። በእርግጥ ክፍሉን በማስተዋል ካየነው የሚያምኑትን ነው እነዚህ ምልክቶች ይከተሉዋቸዋል የሚለው። ስለዚህ በዚህ ዘመን በብዙ አማኝ ነኝ ባይ ውስጥ ያለው ችግር አለማመን ነው ማለት ነው። ብዙ እውነተኛ አማኝ ቀርቶ ሊሆን ይችላል እንጂ የመንፈስ ቅዱስ ስራ በፍፁም አልቀረም ይህ ደግሞ በግልፅ የሚታይ ሐቅ ነው። ከእምነት የጎደለ ሰው ደግሞ ምንም ነገር ሊያደርግ አይችልም። ምክንያቱም የክርስትና ድል በእምነት ውስጥ ያለ ድል ነው። ስለዚህ አሁንም ቢሆን የተሰጠንን ስልጣን ተጠቅመን እኛንም ብዙዎችን ልንጠቅም ይገባናል። ዛሬ በጣም ብዙ ሰዎች በችግር ውስጥ ይገኛሉ በመንፈሳዊም በስጋዊም ስለዚህ የተሰጠንን ስልጣን ተጠቅመን ሰዎችን ነፃ ልናወጣ ይገባል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ማንም አገልጋዮች ሳንጠብቅ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንዲገለጥብን መሆን ይቻላል። ምክንያቱም ይህ የአዲስኪዳን ዘመን ነው። እግዚአብሔር መንፈሱን ለሁሉም ነው የሰጠው። ላንተም ላንቺም!!! ስለዚህ አሁን በእምነት ሆናችሁ ስልጣናችሁን መለማመድ ጀምሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነው። እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የሆነ ሰው ደግሞ በብዙ ኃይል ይገለጣል። አምናችሁ ፀልዩ የመንፈስ ቅዱስን ድንቅ አሰራር ታያላችሁ። መንፈስ ቅዱስ በሰው አልፎ ሲጠቀም የሰውየውን ማንነት አያይም ትንሽ ነው አልተማረም በቂ እውቀት የለውም አይልም እኛ ልባችንን እኛነታችንን እንስጠው እንጂ እርሱ በኃይል ይጠቀምብናል።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
ይቅርታ የሚያደርገው ሰው ምን ይጠበቅበታል
ቆላ 3:13-14
13-እርስ በርሳችሁ ትዕግስትን አድርጉ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው ይቅር ተባባሉ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
14-በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍፃሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።
⨳ይቅር ስንል እግዚአብሔር በቃሉ እንደነገረን ሙሉ በሙሉ በንፁህ ልብ ቂም ሳንይዝ መሆን አለበት።
⨳እግዚአብሔር እኛን ይቅር ሲለን ምንም ነገር (ቂም) ሳይዝ ነው።ከልባችን ለገባነው ንስሃ እግዚአብሔር ሀጥያታችንን ይቅር ብሎ ይረሳዋል አያስታውሰውም ከበረዶ ይልቅ ነጭ ንፁህ ያደርገናል።
⨳እኛም ለሰዎች ይቅርታ በምናረግበት ጊዜ እግዚአብሔር እንዳስተማረን መሆን አለበት።
⨳ብዙ ጊዜ በልማድ ሰዎች ይቅርታ ካደረጉ በኋላ የሚሉዋት ቃል አለች። ይቅርታ አድርጌለታለሁ(ላታለሁ) ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሰላምታ ብቻ እንጂ በነበራቸው ግንኙነት ለመቀጠል አይፈልጉም።ለግንኙነታቸው ገደብ ያበጁለታል። ነገር ግን ይህንን ትክክለኛ ይቅርታ ነው ልንለው አንችልም። ምክንያቱም እግዚአብሔር ያስተማረን ይቅርታ ይቅር ከተባባልን እንደድሮ ከቻልንም ከድሮ በበለጠ በፍቅር እንድንኖር ነው እንጂ በፊት ከነበረን ፍቅር ቀንሰን (ገደብ) አበጅተንለት እንድንኖር አይደለም።
⨳እግዚአብሔር ይቅር ሲለን የበደልነውን ነገር ረስቶት ከነበረን ግንኙነት በይበልጥ ወደ እኛ ቀርቦ ነው።ደጋግመን እየበደልን እንኳን ይቅርታ መጠየቃችንን የሚናፍቅ እና ወደ እሱ ለይቅርታ ስንቀርብ በፍቅር ይቅርታችንን ተቀብሎም በደስታ ሚምረን አባት ነው።
⨳እኛ እንደ ሰው 1 ጊዜ ወይም 2 ጊዜ ይቅር ልንል እንችላለን። ሲደጋገም ግን አሁንስ በዛ ብለን እንሰለቻለን ይቅርታ ከማረግ ይልቅ ተራርቆ መኖርን እንመርጣለን።
⨳እግዚአብሔር ግን ደጋግመን ስናጠፋም እሱ ግን የሚፈልገው የእኛን መመለስ መለወጥ ነው። ይቅርታችንን የሚናፍቅ ለመማር (ይቅር ለማለት) የማይሰለች የማይታክት ነው።
⨳ይቅርታ #ለማድረግም #ለመጠየቅም አንሰልች።ምክንያቱም ይቅርታ መጠየቅም ማድረግም የአሸናፊነት የትልቅነት ምልክት ነው።
ኤፌ 2:4-5
4-ነገር ግን እግዚአብሔር በምህረቱ ባለፀጋ ስለሆነ
5-ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሳ በበደላችን ሙታን እንኳን በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ህይወትን ሰጠን በፀጋ ድናችኋልና።
⨳ስለዚህ እኛም አባታችን እንዳስተማረን ከልብ የሆነ ይቅርታን በማድረግ በፍቅር ተሳስረን በመኖር አባታችን እግዚአብሔርን እናስደስት።
እግዚአብሔር መሃሪ ነው
መልካም ቀን
የ 2013 ዓ.ም የበዓለሃምሳ (የጵራቅሊጦስ) የኖቬና ፀሎት ፕሮግራም ከነገ ጀምሮ እስከ በዓሉ ቀን ድረስ ለተከታታይ ቀናት ይኖረናል። ሰዓት ከ 11:30 እስከ 1:30
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
ቦታ ቅዱስ ሚካኤል
“የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።”
— ገላትያ 5፥22
በነዚህ ቀናት በእነዚህ ርእሶች ላይ እንወያያለን እንፀልያለን።
ዓርብ ሰኔ 11 ከ 11:30 እስከ 1:30 ልዩ የቅዱስ ቁርባን ስግደት (Adoration) ይኖረናል።
ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ምን ማድረግ ይጠበቅበታል
#ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ማድረግ ያለበት ነገሮች አሉ።እነዚህም:-
1)በመጀመሪያ ጥፋትን ማመን ያስፈልጋል።
መዝ 51:3-4
3-እኔ መተላለፌን አውቃለሁና ኃጥያቴም ሁልጊዜ በፊትህ ነውና
4-አንተን ብቻ በደልሁ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ በነገርህም ትፀድቅ ዘንድ በፍርድህም ንፁህ ትሆን ዘንድ
2)በሰራነው ጥፋት መፀፀት ያስፈልጋል።
ማቴ 26:75
75-ጴጥሮስም። ዶሮ ሳይጮኸ 3 ጊዜ ትክደኛለህ ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው። ወደ ውጭም ወጥቶ መራራ ለቅሶ አለቀሰ።
3)ይቅርታ ስንጠይቅ የምናገኘውን ደስታ እና እረፍት ማሰብ።
መዝ 51:7-8
7-በሂሶጵ እርጨኝ እነፃማለሁ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
8-ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።
4)ድጋሚ ላለመስራትና ቁርጥ ፍቃድ ማድረግና ከልብ የሆነ ይቅርታ መጠየቅ ያስፈልጋል።
መዝ 51:1-2
1-አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ እንደ ምህረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።
2-ከበደሌ ፈፅሞ እጠበኝ ከኃጥያቴም አንፃኝ።
⨳ከእግዚአብሔር ጋር ለምናረገው ንስሃ የምንከተላቸው መንገዶች አሉ።ከላይ እንዳየናቸው ጥፋትን ማሰብ(ማመን) , መፀፀት , ያንን ጥፋት ላለመድገም ቁርጥ ፍቃድ ማድረግና ከልብ ይቅርታ መጠየቅ ምህረትን መሻት ያስፈልጋል።
⨳ከሰው ጋር ለምናደርገው ይቅርታም ከላይ የጠቀስናቸው ያስፈልጋሉ። ጥፋታችንን ማመን ከዛም በጥፋቴ መፀፀት እና ድጋሚ ላለመፈፀም ቁርጥ ፍቃድ ማድረግ እና በቅን ልቦና ይቅርታውን በመሻት የበደልነውን ሰው ይቅርታ መጠየቅ ይኖርብናል።
እግዚአብሔር ይቅርባይ ነው
መልካም ቀን
ይቅርታ ለምን ያስፈልጋል
⨳ከልብ የሆነ ይቅርታ ለምን ያስፈልጋል?
-ይቅርታ ማለት የተፈጠረን ነገር ይቅር ብሎ የተፈጠረውን ነገር መርሳት ማለት ነው።
⨳ስለዚህ ይቅርታ ለማንኛውም ግንኙነት አስፈላጊ ነው። ከሰዎች ጋር ያለን ግንኙነት እንዳይበላሽና በፊት በነበረን ፍቅር እና እምነት አብረን ለመዝለቅ ይቅርታ አስፈላጊ ነው።
⨳ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ልጅና አባት ለመቀጠል ንስሀ ማድረግ አስፈላጊ ነው። ይቅርታ (ምህረት) መቀበል ያስፈልገናል።
#ለምን
ሮሜ 3:23
23-ሁሉ ሀጥያት ሰርተዋልና የእግዚአብሔር ክብር ጎድሎአቸዋል።
#ለምን ለሚለው ጥያቄ በሃጥያታችን ከእግዚአብሔር ክብር ጎለናል በሃጥያታችን ምክንያት ከእግዚአብሔር የሆኑትን በነፃ የተሰጡንን ፀጋዎች መጠቀም ስለማንችል በክርስቶስ በኩል ምህረትን አደረገልን። ከተከፈለልን ዋጋ በኋላ ለምንሰራው ሃጥያት ደግሞ ወደ ክብሩ ዙፋን እንድንደርስ የተሰጡንን ፀጋዎች በአግባቡ እንድንጠቀም ንስሃ ተሰቶናልና በንስሃ ከሃጥያታችን በመንፃት ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅ ያስፈልገናል።
⨳እኛም ከሰዎች ጋር ያለን ግንኙነት እነዳይበላሽ ስናጠፋ ይቅርታ መጠየቅ ላስቀየመን ሰውም ይቅርታ በማድረግ በንፁህ ፍቅር ለመዋደድ ይቅርታ ያስፈልጋል። ይህን በማድረጋችን እግዚአብሔር ማስደሰት እና የተሰጠንን የፀጋ ስጦታ መጠቀም እንችላለን።
እግዚአብሔር መሃሪ ነው
መልካም ቀን
#በአእምሮ_መታደስ
የግንቦት 29 የእሁድ እድገት ትምህርት
በአእምሮ መታደስ ምን ማለት ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
የሰው ድርጊቱ ሁሉ #የአእምሮ_እና_የሀሳቡ ውጤት ነው። ሰው በአእምሮው እና በሀሳቡ ከሳተ በድርጊቱም የሳተ ይሆናል። ሰው #አእምሮው እና ሀሳቡ መልካም ከሆነ ድርጊቱም ሕይወቱም መልካም ይሆናል። ለምሳሌ የአእምሮ ችግር ያለበት ሰው እግሩና እጁ የሚታሰረው እጁና እግሩ ስለታመመ አይደለም እጁ እግሩ ፍፁም ጤናማ ነው ነገር ግን እጁና እግሩን የሚያዘው ድርጊት ውስጥ የሚያስገባው አእምሮው ችግር ስላለ ነው ነው። ስለዚህ #አእምሮአችን ላይ ትልቅ ስራ ልንሰራ ይገባል። ዛሬ ላይ በዙ ሰው ላይ ያለ ሀዘን ጭንቀት ድብርት የተለያዩ ችግሮች ያልተለወጠ የአእምሮ ችግር ነው። የእግዚአብሔር ቃል የተሰጠን #አእምሮአችንን በማደስ እግዚአብሔር ባዘጋጀልን መልካም እና አስደሳች ሕይወት እንድንኖር ነው። “የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥16-17
የመልካም ስራ ሁሉ ብቃት የሚገኘው ከእግዚአብሔር ቃል በሚገኝ እውነት #አእምሮአችንን ስናድስ ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
የሁሉ ሰው ሕይወት በተፅዕኖ ስር ያለ ነው። በእግዚአብሔር ቃል ተፅዕኖ ወይም ደግሞ በአለም ተፅእኖ። ሰው ደግሞ ኑሮው ውስጡ ያለውን የተሞላውን ነው። ስለዚህ ዛሬ ምን ተሞልተናል ምን እየተሞላን ነው። ዛሬ ዓለም ብዙ የምትሞላው ነገር አላት በጓደኛ ፣ በፊልም ፣ ዙሪያ ባለ አካባቢ እነዚህ ሁሉ ተፅዕኖዎች ግን እረፍት እና ደስታ ሊሰጡን አልቻሉም። ስለዚህ እረፍት እና እውነተኛ ሰላም ደስታ ወደሚሰጠን ወደ እግዚአብሔር ልባችን እና አይናችንን ልንመልስ ያስፈልጋል።“በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና— ምሳሌ 23፥7
በውስጡ የተለወጠ ሰው በምንም አይነት መልኩ በውጪ ተፅእኖ አይያዝም። ዜናው ሁኔታው ብዙ አይነት ችግር እንዳይዘን ውስጣዊ ማንነታችን ላይ ልንሰራ ይገባል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
#በአእምሮ_መታደስ መለወጥ ማለት ለእግዚአብሔር መንግስት አሰራር ሁሉ ነገር በፈቃደኝነት መስጠት እና መገዛት ማለት ነው። የእግዚአብሔር መንግስት አሰራር በምድር ላይ ካሉ መንግስታት አሰራር ሁሉ የተለየ እና ለሰው ሁሉ የሚመች ሰላማዊ እና ንፁህ የሆነ ህግና ስርዓት ያለው ፍትህ የነገሰበት መንግስት ነው። በዚህ መንግስት ውስጥ ለመኖር ግብዣ ቀርቦልናል። ይህ መንግስት ለሀብታም ለድሀ ለባለሰልጣን ለተማረ ላልተማረ ሳይል ያለምንም መስፈርት የሚቀበለን አውነተኛ መንግስት ነው።
1 #በአእምሮ_መታደስ መለወጥ ውስጣዊ ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
እውነተኛው #በአእምሮ_መታደስ መለወጥ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳይሆን የፈለገውን ነገር አለማድረግ ወይም ማቆም ብቻ አይደለም። ከዚያም ያለፈ ነው። የሚከለከሉ ነገሮች አለማድረግ ለውጡ ውጫዊ ብቻ ይሆናል።መፅሐፍ ቅዱስ እንደዚህ አይነቱን ለውጥ አይደለም #በአእምሮ_መታደስ ተለወጡ የሚለው። በውስጣዊ ማንነት የሚሆን ለውጥ ነው። ትክክለኛ የአእምሮ መታደስ የትግል ሕይወት የለውም ውስጣችን አስጨንቀን አንኖርም። ኃጢአት ነው ኃጢአት አይደለም ልዋሽ አልዋሽ ላድርግ አላድርግ በሚል አይደለም። #በአእምሮ_መታደስ በነፃነት ትክክለኛውን ነገር እያደረጉ መኖር ነው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
2 እውነተኛ ተሀድሶ ከውስጣችን የሚወጣ እኛነታችን ሙሉ በሙሉ በመንፈስ በተወረሰ መልኩ የሚገለጥ የሕይወት ጉዞ ሊሆን ይገባል። #በአእምሮ_የታደሰ ሰው አስቦ አቅዶ የሚኖረው ሳይሆን ውስጡ ከሞላው ከተሰራበት ማንነት የተነሳ የሚኖረው ሕይወት ነው። ኑሮው ያለምንም እቅድ መንፈሳዊ ነው። የሚኖርበት እና የሚገለጥበት መንገድ ሰማያዊ መንግስት አረራር ነው። ስለዚህ በየዕለቱ በአእምሮ ልንታደስ ይገባል።
ይቀጥላል
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
