uz
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Kanalga Telegram’da o‘tish
805
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
-130 kun
Postlar arxiv
ኢሳይያስ 48 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ። ¹⁸ ትእዛዜን ብትሰማ ኖሮ፥ ሰላምህ እንደ ወንዝ ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር፤ ¹⁹ ዘርህም እንደ አሸዋ የሆድህም ትውልድ እንደ ምድር ትቢያ በሆነ ነበር፥ ስሙም ከፊቴ ባልጠፋና ባልፈረሰ ነበር። እግዚአብሔር የነገረንን በማድረግ ስኬታማ እና ደስተኛ ሕይወት መኖር እንችላለን አብዛኞቻችን ቤተክርስቲያን የምንሄድ ቢሆንም ከእግዚአብሔር የሚገኘውን ታላቅ የሆነ በረከት እየተጠቀምንበት አይደለም። ያልተጠቀምንበት ምክንያት ደግሞ እኛ የምንፈልገውን ነው እንጂ የምናደርገው እግዚአብሔር የሚፈልገውን አለማድረጋችን ነው። ሕይወት ስኬታማና ደስተኛ የሚሆነው እግዚአብሔር የነገረንን በማድረግ ብቻ ነው። እግዚአብሔር የነገረንን ለማድረግ ከስጋችን ጋር ከፍተኛ ትግል ልናደርግ እንችላለን ነገር ግን አሸናፊ የምንሆነው እግዚአብሔር በነገረን ቃል ላይ ስነፀና ብቻ ነው። እግዚአብሔር በሁሉ አካሄዳችን መንገድ ያሳየናል እኛም መንገዱን ለመከተል ፈቃደኛ ሆነን ከተከተልነው ሕይወታችን የስኬት የደስታ የሰላም የዕረፍት ይሆንልናል። “የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።” — መዝሙር 16፥11 https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

4.jpg2.84 MB

#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_መነቃቃት 2015 ዓ.ም ሴሚናር መስከረም 29 ይጀምራል ወደ መንፈሳዊ መነቃቃት የሚያደርሱ መንገዶች 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 መንፈሳዊ መነቃቃት ለብዙ ክርስቲያኖች ከሁሉም የላቀ አስፈላጊ ነገር ነው። ዛሬ እንዴት እናገኘዋለን? በራሳችን ሕይወትም ሆነ በሌሎች ሰዎች እነኚህ የመነቃቂያ መንገዶች ምን ምን ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስቀምጣቸው ሶስት ደረጃዎች እንመልከት። 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 1 የመጀመሪያው ደረጃ መንፈሳዊ ድህነታችንን መቀበል ነው። ብዙ ግዜ መንፈሳዊ ጉድለታቸውን ለማየት እስኪሳናቸው ድረስ እንደታወሩት የሎዶቅያ ክርስቲያኖች እንመስላለን። “ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥”— ራእይ 3፥17 ያለንበትን መንፈሳዊ ሕይወት ልንገመግም ያስፈልጋል። ራሳችንን በተለያዩ መንፈሳዊ ልማዶች እየከለልን እግዚአብሔር ካስቀመጠልን የከበረ እና የተሻለ ሕይወት ልንጎድል አይገባንም። አንዳንድ ሰዎች ቤተክርስቲያን ስለሄዱ ብቻ ጥሩ መንፈሳዊ ሕይወት ያላቸው ይመስላቸዋል አንዳዶች ስለዘመሩ መንፈሳዊ እድገት መስሏቸው ይታለላሉ። ማገልገል መልካም ቢሆንም እንደ እግዚአብሔር ሃሳብ አለማገልገል ኪሳራ ነው። ስለዚህ ራሳችንን ቆም ብለን እንይ። እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ ነው ወይ መንፈሳዊነቴ አገልግሎቴ? 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 2 ለመንፈሳዊ መነቃቃት ሁለተኛው ደረጃ መናዘዝ እና ንስሐ መግባት ነው። ኃጢአት እንደፈፀምን ልናውቅ እንችላለን ነገር ግን ስለዚያ ምንም አናደርግም ይሆናል። ነገር ግን ኃጢአታችንን በእርሱ ፊት መቀበል ብቻ ሳይሆን ከኃጢአታችን በመመለስ እና ለእርሱ ለመታዘዝ በመሻት ኃጢአታችንን በኑዛዜ እና ንስሐ በመግባት ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ማምጣት አለብን። ከመፅሐፍ ቅዱስ ታላላቅ የተስፋ ቃሎች አንዱ 1ኛ ዮሐንስ 1:9 ነው። “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።”— 1ኛ ዮሐንስ 1፥9 ነብዩ ኢሳያስ የንስሐ አስፈላጊነት ያስረዳናል። “ክፉ ሰው መንገዱን በደለኛም አሳቡን ይተው፤ ወደ እግዚአብሔርም ይመለስ እርሱም ይምረዋል፥ ይቅርታውም ብዙ ነውና ወደ አምላካችን ይመለስ።” — ኢሳይያስ 55፥7 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 3 ሶስተኛው ደረጃ ባንተ በኩል የእግዚአብሔር ፈቃድ ለመሻትና ለመፈፀም ቃልኪዳኑን ማደስ ነው ። ስለ ኃጢአታችን ልንወቀስ ልንፀልይ እና ኃጢአታችንን ልንናዘዝ ንስሐ ልንገባ እንችላለን ዳሩ ግን እውነተኛ መለኪያው ለመታዘዝ ፈቃደኛ መሆናችን ነው። ሁልግዜም እውነተኛ መነቃቃት ለፅድቅ የሚኖረንን አዲስ ረሀብ መፍጠሩ ነው። በመንፈስ ቅዱስ የተዳሰሰ ሕይወት ኃጢአት ሊታገስ አይችልም። ይህ ሕይወት ረሃቡም ጥማቱም መንፈሱ እና ቃሉ ነው። እዚህ ሕይወት ውስጥ እውነተኛ ደስታና ሀሴት አለ። “እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”— ዕብራውያን 12፥1-2 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ጎዶሎ ለብ ያለና ለክርስቶስ እና ለሌሎች ፍቅር የሌለው የክርስትና ሕይወት እየመራህ ይሆን? መንፈሰ ቅዱስ ኃጢአትህን በመናዘዝ እና ፊቱን በመሻት ወደ እግዚአብሔር እንድትመጣ ይርዳህ። ራስህን ለእርሱ በመስጠት ይዳስስህ ይፈውስህ። ዛሬ በዓለም እጅግ የሚፈለገው ነገር ሙሉ ለሙሉ በመንፈስ ቅዱስ በመነቃቃት ራሳቸውን የሰጡ ክርስቲያኖች ማግኘት ነው። አንተም ከእነዚህ አንዱ ለመሆን ያብቃህ። ንቃ እድሉ አለህ። ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሰሚናር እንድትወስድ እንጋብዝሀለን። #ሰሚናር_እንዲማር_ለሚጋብዙት_አንድ_ሰው_ሼር_ያድርጉት_እርሶም_ይባረኩበታል። https://t.me/eccrm https://t.me/eccrm

#2015_የጨከኑ_የሚቆረቆሩ_የወንጌል_ሰራተኞች አብርሃም ተቆረቆረና ሎጥን ከሰዶም አዳነው (ዘፍ 18-19) ሙሴ ተቆረቆረና እስራኤላውያንን ከግብፅ አወጣቸው ዳዊት ተቆረቆረና ሕዝቡንና መንግስቱን ወደ
#2015_የጨከኑ_የሚቆረቆሩ_የወንጌል_ሰራተኞች አብርሃም ተቆረቆረና ሎጥን ከሰዶም አዳነው (ዘፍ 18-19) ሙሴ ተቆረቆረና እስራኤላውያንን ከግብፅ አወጣቸው ዳዊት ተቆረቆረና ሕዝቡንና መንግስቱን ወደ እግዚአብሔር መልሶ አመጣቸው። አስቴር ተቆረቆረችና ሕይወቷን ለአደጋ አጋልጣ ሕዝቧን ከእልቂት አዳነቻቸው። ጳውሎስ ተቆረቆረና ወንጌልን በመላው የሮም ግዛት አሰራጨው። ኢየሱስ ተቆረቆረና ስለ ጠፊው ዓለም ሲል ሞተ። እግዚአብሔር ተቆርቋሪ ሰዎችን በመፈለግ ላይ ነው። ስለ እውነት በመፈለግ የሚቆረቆሩ ስለ ትውልድ ሕይወት በመቆርቆር የሚያለቅሱ ስለ ወንጌል ስራ በመቆርቆር በፀሎት የሚተጉ የፈረሰውን ቅጥር ለመገንባት የሚተጉ እንደ ነህምያ አይነቱን ሰው ለማግኘት እግዚአብሔር እየፈለገ ነው። እነሆ እኔን ላከኝ የሚል የጨከነ ትውልድ በ2015 ጌታ በብዛት ያስነሳ

የ2014 የዓመቱ መዝጊያ የምስጋና ፕሮግራም በጣም ደስ በሚል መልኩ አሳልፈናል እግዚአብሔር ይመስገን። ቀጣዩንም ዓመት በልዩ ምስጋና እንገባለን።
የ2014 የዓመቱ መዝጊያ የምስጋና ፕሮግራም በጣም ደስ በሚል መልኩ አሳልፈናል እግዚአብሔር ይመስገን። ቀጣዩንም ዓመት በልዩ ምስጋና እንገባለን።

ሰላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እሁድ በሚኖረን ልዩ የምስጋና ፕሮግራም #የሀገር #ልብስ ለብሰን በመምጣት በዓላችንን ድምቅ እንድናደርግ እንጠየቃለን መልካም የምስጋና ፕሮግራም ይሁንልን።

እምነታችንን መገንባት ያለብን ቃሉ ላይ ነው “ቃሉ የታመነ ነው። እግዚአብሔርንም የሚያምኑት በመልካም ሥራ በጥንቃቄ እንዲጸኑ፥ እነዚህን አስረግጠህ እንድትናገር እፈቅዳለሁ። ይህ መልካምና ለሰዎች የሚጠቅም ነው፤” — ቲቶ 3፥8 ማንኛውም ቤት የሚሰራ ሰው መሰረቱን አስተማማኝ መሆኑን ካለመነ ቀጣዪን ግንባታ መስራት አይችልም የላዩን የሚይዘው ታች ያለው መሰረት ስለሆነ። ስለዚህ የእኛም ሕይወት መገንባት ያለበት ቃሉ ላይ ነው እንጂ ሌሎች ነገሮች ላይ ሊሆን አይገባም ቃሉ ለክርስትና ጉዞአችን መሰረት ነው። ቃሉን መሰረት አድርጎ ለማይኖር ክርስቲያን ጉዞው ሁሉ የስሜት እና የምልልስ የልምድ ክርስቲያን ይሆናል ስለዚህ ቃሉ ላይ እንመስርት። የቃሉን ሀይል የተረዳ ክርስቲያን የማያቋርጥ መንፈሳዊ እድገት አለው። “ይህ ቃል የታመነ ሁሉም እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥9

ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የጌታ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ። ቀጣይ #ቅዳሜ ተብሎ የነበረው ፕሮግራም #ቀርቶ እሁድ ከጠዋቱ 4:30 ጀምሮ ሙሉ ቀን እንዲሆን ስለተደረገ ሁላችሁም ላልሰማ እንድታሰሙ በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን

Untitled-1.jpg1.74 MB

የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም። በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል 👉7ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 “የእግዚአብሔር መንፈስ፥ የጥበብና የማስተዋል መንፈስ፥ የምክርና የኃይል መንፈስ፥ የእውቀትና እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ ያርፍበታል።” — ኢሳይያስ 11፥2

የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም። በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል 👉6ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 “ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።” — ሐዋርያት 1፥8 አንድ ሰው ትክክለኛ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ሲያገኝ በሕይወቱ ላይ የሚታዩ የለውጥ ምልክቶች በጥቂቱ 1 ለፅድቅ ሕይወት ልዩ ቦታ መስጠት 2 አዲስ የፀሎት ሕይወት ልምምድ 3 የእግዚአብሔርን ቃል መረዳት (መገለጥ) 4 ከማይጠቅመው ነገር ይለያል 5 የመመስከር ድፍረት ያገኛል 6 ዓለማዊነትን የማሸነፍ ጉልበት ያገኛል በዚህ ርዕስ ላይ ምሽት 3:30 ጀምሮ ፀሎትና ውይይት ይኖረናል።

የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም። በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል 👉5ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 “በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።” — ዮሐንስ 15፥7 በእግዚአብሔር የሚኖር የእግዚአብሔር ቃል እንዲኖርበት የፈቀደ ሰው ሁልግዜም የምስጋና ሕይወት አለው። ፀሎቱ እንደተሰማ ስለሚረዳ በምስጋና ይኖራል። እግዚአብሔር ሆይ ትውልድ የአንተን ቃል ተረድቶ እንዲኖር እንፀልያለን።

የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም። በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል 👉4ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 1ኛ ዮሐንስ 4 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና። ¹⁰ ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። ምንያህሎቻችን የእግዚአብሔርን ፍቅር ተረድተን እንኖራለን ለሁሉ ሰው የእግዚአብሔርን ፍቅር መረዳት እንዲሆን እንፀልያለን።