cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለዓለም ትኑር!

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን(፫) ✝እንኳን ወደ ማህበራችን በሰላም መጣችሁ! 💐 ➢በዚህ ማህበር ውስጥ የክርስቶስን አምላክነት የቅዱሳን ገድላቸውንና አማላጅነታቸዉን እንድሁም የቤተክርስቲያን ታሪኮችንና ሌሎችን ሊያስተምሩ የሚችሉ ሃይማኖታዊ ጽሁፎችን እንጋራበታለን ሁሉን በሚገባ እንከታተል❗ ሃሳብና አስተያየታችሁን በ https://t.me/ZYeTewahdoLij አድርሱን 👏

Ko'proq ko'rsatish
Mamlakat belgilanmaganTil belgilanmaganToif belgilanmagan
Reklama postlari
526
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

እነርሱ እንደኛ ሰዎች ሆነው ሳለ በኖህ ዘመን እንደነበሩት ረዓይቶች ሰው ይበላሉ እንላቸዋለን። በእነርሱ ላይ ያደረስነው የስነልቦና ጫና ተመሣሣይነት የማይገኝለት ነው። በእኔ በኩል እስካሁን ስለ እነርሱ ከሚወራው ሁሉ ያረጋገጥኩት ነገር ቢኖር የጠቢቡ የሰሎሞን የግብር ልጆች ሰርቶ አዳሪ ጥበበኛ መሆናቸውን ብቻ ነው። (በዚህ ዙሪያ እናንተ የገጠማችሁንና የምታውቁትን ታሪክ ልታካፍሉኝ ትችላላችሁ። በየ አካባቢያችሁ ስለእነሱ ምን እንደሚወራ እንድሁም በተግባር ያረጋገጣችሁትን ነገር ካለም ልትነግሩኝ ትችላላችሁ) በመጨረሻም ይህ ሁሉ ጭቆና እንደሚደርስባቸው የተረዳው የእስራኤል ሕዝብ ሕዝቦቹን ከያሉበት ይሰበስባል። ነገር ግን ስለተዋለዱና ስለበዙ እስከአሁን ሁሉንም አጠቃለው መውሰድ አልቻሉም። እስከዛሬም ኦፕሬሽን ሞሰስ እና ኦፕሬሽን ሰሎሞን በተባሉ ተመቻዎች በብዙ ሽህዎች የሚቆጠሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊ እስራኤላውያን ወደ እስራኤል ተጓጉዘዋል። ከዚህ መገለልና ጭቆና እየተላቀቁ ከኢትዮጵያ በሚሄዱበት ጊዜም በፊት (እዚህ ኢትዮጵያ ሳሉ) በሀሰት ትርክት ሲያገላቸው፣ሲሰድባቸውና ሲያሸማቅቃቸው የነበረው ህዝብ በድጋሚ "ኢትዮጵያን ከድተው ሄዱ" በማለት በየሄዱበት እየተከተለ ይተቻቸዋል። ከምር ንስሓ ያስፈልገናል። በተዛባ የሐሰት ትርክት አንዳችን በአንዳችን ላይ እየተነሳን በሰዎች ላይ አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳት እያደረስን ያለን መሆናችንን በመገንዘብ ከስህተታችን ልንታረም ይገባናል። ክብር ሀገር ላቀኑ፣ሀገር ለገነቡና እስከዛሬም ድረስ በጥበባቸው እያገለገሉ ላሉ ጥበበኞች ይሁን! መልካም ቀን ✍ዜድ
Hammasini ko'rsatish...
ቤተ እስራኤላውያን እና የእጅ ጥበብ ባለሞያዎች (የብረት፣የቆዳና የሸክላ ሰራተኞች) ታሪኩን ለመረዳት ከጌታችን ልደት በፊት በእስራኤል ላይ ነግሦ የነበረውን የንጉሥ ዳዊት ልጅ የሆነውን የጠቢቡ ሰሎሞንን ታሪክ እና በኢትዮጵያ/በአቢሲኒያ የነገሠችውን የንግሥተ ሳባን ታሪክ ማየት ግድ ይለናል። እንድሁም ታራኩ ከታቦተ ፅዮን አመጣጥ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት ያለው ሲሆን በመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ምዕራፍ 10 ላይ እና በሌሎች አዋልድ መጻሕፍት ላይ ተፅፎ እናገኜዋለን። ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 12:42 ላይ "ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና" በማለት የጠቀሳት ንግሥተ ማክዳ ወይም ንግስተ ሳባ በወቅቱ የኢትዮጵያን/የአቢሲኒያን ሕዝብ የምታስተዳድር ንግሥት ነበረች፡፡ እንድሁም በጊዜው በእስራኤል ላይ ነግሦ የነበረውን የሰሎሞንን መንፈሳዊ ጥበብ በነጋደዎች በኩል ትሰማ ነበር። ዕለት ዕለትም የሰማችውን የሰሎሞንን ጥበብ እና ዝና ለማየት ትጓጓ ነበር፡፡ በዚህም የተነሣ የሰሎሞንን ጥበብ በአካል ታይ ዘንድ፣ በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ፣የሁለቱን አገራት ግንኙነት ታጠናክር ዘንድ በማሰብ ታምሪን በተባለ ነጋደ መሪነት ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘች፡፡ (መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ 10:1፤) ያለ አንዳች መሰናክልም ተጉዛ ኢየሩሳሌም ደረሰች፡፡ ለታቦተ ጽዮን ክብርና ለንጉሥ ሰሎሞንም ገጸ በረከት አቀረበች፡፡ ንጉሥ ሰሎሞንም እርሷንና ተከታዮቿን በጥሩ መስተንግዶ ተቀበላቸው፡፡ ንግሥት ሳባም የቤተ መንግሥቱን ሥርዓት ሥጋዊና መንፈሳዊ ጥበቡንም ሁሉ አስተዋለች። የጠየቀችውን እንቆቅልሽ ሁሉ ፈታላት፤ ሊፈታላት ያልቻለውና ከንጉሡ የተሰወረ ነገርም አልነበረም።" ንጉሡንም አለችው፦ "ስለ ነገርህና ስለ ጥበብህ በአገሬ ሳለሁ የሰማሁት ዝና እውነት ነው። እኔም መጥቼ በዓይኔ እስካይ ድረስ የነገሩኝን አላመንሁም ነበር፤ እነሆም፥ እኩሌታውን እንኳን አልነገሩኝም ነበር፤ ጥበብህና ሥራህ ከሰማሁት ዝና ይበልጣል።" አለችው። 1ኛ ነገሥት 10፥6-7 ንግሥተ ሳባ/ማክዳ በኢየሩሳሌም ቆይታዋ ከንጉሥ ሠሎሞን ቀዳማዊ ምኒልክን ፀነሰች፡፡ ወደ ኢትዮጵያም ተመልሳ ልጇን ምኒልክን ወለደች፡፡ ቀዳማዊ ምኒልክ በሀገሩ/በኢትዮጵያ ተወለዶ 12 ዓመት በሆነው ጊዜ ከእናቱ የተሰጠውን ለንጉሥ ሰሎሞንና ለታቦተ ጽዮን እጅ መንሻ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘ፡፡ ንግሥተ ሳባም ለንጉሥ ሠሎሞን “ንጉሥ ሆይ ልጄ ምኒልክ ሙሴ የጻፋቸውን ሕግጋትና ሥርዓተ ክህነት አስተምረህ ላክልኝ፡፡” የሚል መልእክትም አብራ ልካ ነበር፡፡ ቀዳማዊ ምኒልክም በኢየሩሳሌም ከአባቱ ዘንድ ለሦስት ዓመት ያህል የሙሴን መፃህፍት፣ ሕገ መንግሥትን፣ ሥርዓተ ክህነትንና የዕብራይስጥን ቋንቋ ከሊቀ ካህናቱ ከሳዶቅ እየተማረ ከቆየ በኋላ፤ ንጉሥ ሠሎሞን ልጁ ሮብኣም ገና ስድስት ዓመቱ ነበርና ምኒልክን አልጋ ወራሽ ሊያደርገው ቢያስብም ምኒልክ ግን ፈቃደኛ ስላልሆነና ወደ አገሩ ለመመለስ በመፈለጉ ምክንያት በካህኑ ሳዶቅ ቅብዓተ ንግሥ ተፈፅሞለት ከአስራ ሁለቱም ነገደ እስራኤላውያን የተውጣጡ 12,000 ከሚሆኑ የእስራኤል ሌዋውያን ካህናት እና ከቤተመንግሥት ሹማምንቶች የበኩር ልጆች ጋር ወደ አገሩ/ኢትዮጵያ ላከው። የእስራኤል የበኩር ልጆችም ወደማናውቀው አገር ስንሄድ ታቦተ ፅዮንን ትረዳናለችና እሷን ሳንይዝ አንሄድም በማለት ተመካክረው የእግዚአብሔርም መልካም ፈቃድ ሆኖ ምንልክም ሆነ ሌሎች እስራኤላውያን ሳያውቁ በሙሴ እጅ የተቀረፀችውን ፅላት ይዘዋት ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ንግሥት ሳባም ታቦተ ጽዮን መምጣቷን ስትሰማ ለእግዚአብሔር መስዋዕት አቀረበች፡፡ ሰዎችን መርጣ ታቦተ ጽዮንን እንዲጠብቁ አድርጋለች፡፡ የመንግሥቱን ሥልጣን በሙሉ ለቀዳማዊ ምኒልክ አስረክባ ከዚህ ዓለም በሞተ በተለየች ጊዜ በዚያው በአክሱም ተቀብራለች፡፡ ለእስራኤላውያን ብዙ ተአምራትን ያደረገች ይህችም ፅላት ለ3000 ዓመታት ያህል እስከዛሬ ድረስ በኢትዮጵያ በአክሱም ፅዮን ማርያም ትገኛለች፡፡ ታሪኩን ወደ ዋናው ርዕሳችን (ቤተ እስራኤላውያን) ስናመጣው እንድህ ነው። የመጀመሪዎቹ ቤተ እስራኤላዊያን ከእየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት ከንጉሥ ሠሎሞንና ከንግሥት ሳባ ልጅ (ከቀዳማዊ ምንልክ) ጋር ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የእስራኤል የሹማምንቶች የበኩር ልጆች ናቸው። በጊዜው የሰፈሩትም በኤርትራ፣በአክሱምና በትግራይ አካባቢዎች ይኖሩ የነበረ ሲሆን፤በኢትዮጵያ የክርሥትና ሃይማኖት የሀገሪቱ ብሔራዊ ሀይማኖት ሁኖ በታወጀበት ወቅት፣ የክርስትናን ሃይማኖትን አንቀበልም በማለታቸው ምክንያት ከአክሱም ተባረው በወገራ፣ ደምቢያ፣ ጭልጋ፣ ጣና ሀይቅ ዳር፣ እና በሰሜኑ ተራራማ ቦታዎች ላይ ሰፍረዋል። በህገ ኦሪት የሚመራ የራሳቸውን ስርወ መንግስትም አቋቁመዋል ነበራቸው። አንድ አሳዛኝ ነገር ግን አለ "ነቢይ በገዛ አገሩ አይከበር" ነውና ነገሩ የአይሁድ/የእስራኤል ሰዎች እምነታቸው ገና አምላክ/መሲህ ይመጣል ብለው የሚጠብቁ ናቸው። አሁን አሁን አብዛኞቹ ክርስትናን እየተቀበሉ ነው። ለምሳሌ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ እስራኤላውያን ክርስትናን ይዋጉት/ይቃወሙት እንዳልነበር ሁሉ አሁን ግን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ክርስትናን የተቀበሉ ሲሆን አልፎ አልፎም በዚያው በይሁዲነታቸው የቀጠሉና እስልምናን የተቀበሉም አሉ። ከጠቢቡ ሰሎሞን የተወለደው የንግሥተ ሳባ ልጅ በአሰስራኤል መሾምን ስላልፈለገ በኢትዮጵያ ይነግሥ ዘንድ ቅብአ መንግሥት ተቀብቶ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ሲመጣ ንጉሥ ሰሎሞንም የልጁን ስም ዳዊት ብሎ ሰይሞታል። ከእርሱ ጋር ከአስራ ሁለቱም ነገደ እስራኤላውያን የተውጣጡ 12,000 (አስራ ሁለት ሺህ) የእስራኤል የሌዋውያን ካህናት እና የመኳንንት የበኩር ልጆች ቀዳማዊ ምንልክን ተከትለው/አጅበው ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከቀዳማዊ ምንልክ ንግሥና በኋላም በኢትዮጵያ ግዛት ይኖሩ የነበሩ ሌሎች ሕዝቦች "ከምንልክ ጋር ኢትዮጵያ የገቡ እስራኤላውያን እርስታችንን እና መሬታችንን እንዳይጋሩን፤ተሹመውም እኛን ሊገዙን ወይም ሊያስተዳድሩን አይቹሉም" በማለት አደሙ። ከንጉሥ ምንልክ/ዳዊት ጋር ወደ ኢትዮጵያ የገቡ እስራኤላውያኑንም መሬት ሳያገኙ በእጅ የጥበብ ሥራቸው በሚሰሩት ማለትም በሸክላ ሥራ፣በብረታ ብረት ሥራ፣ በጡብ፣በቆዳ፣ በሸማና በመሣሠሉት ሥራዎቻቸው ከህዝብ ተሰብስቦ በሚከፈላቸው ደመወዝ ብቻ እንድኖሩ ተደረጉ። ከሌሎች ጎሳዎች ጋርም እንዳይጋቡና እንዳይባዙ ተደረገ። ከማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች እንዳይሳተፉ ማእቀብ ተጣለባቸው። ህብረተሰቡም እነሱን ያገላቸውና በመጥፎ ያያቸው ዘንድም ቡዳ ናቸው፣ ማታ ማታ ጅብ ናቸው፣ ሰው ይበላሉ እስከማለት ድረስ የደረሰ መጥፎ ፍረጃን እንድፈረጁ ተደረገ። ይህም እስከዛሬ ድረስ የዘለቀ። ነገር ግን እነርሱ የእጅ የጥበብ ባለሙያዎች ናቸው እንጅ እንደሚባለው ሰው የሚበሉ ጅቦች አይደሉም። እኛ ግፈኞቹ ግን እነርሱ በሰሩልን ማረሻ እያረስን እነርሱን እንሰድባለን፤ እነርሱ በሰሩልን ማጭድ እያጨድን፣ እነርሱ በሰሩልን ድስት እያበሰልን፣ እነርሱ በሰሩልን ቆዳ እየተገለገልን ፣ እነርሱ በሰሩልን ምጣድ እየጋገርን፣ እነርሱ የሰሩልንን ሸማ እየለበስን፣እነርሱ በሰሩልን መሣሪያ ጠላቶቻችንን ድል እየነሳን፣ እነርሱ በሰሩልን ቢለዋ እየበላን፣እነርሱ በሰሩልን እንስራ ውሀ እየቀዳን ወዘተ እኛ ግን ዛሬም አባቶቻችን ያወረሱንን መጥፎ ትርክት ተቀብለን እንተቻቸዋለን፣ እንሰድባቸዋለን፣እናገላቸዋለን።
Hammasini ko'rsatish...
የአላህ መልዕክተኛ (ማሜ) በህይወቱ 3 ነገሮችን አጥብቆ ይወድ ነበር 1, ሴት 2, ሽቶ 3, ምግብ ከተመኛቸው ነገሮች ሽቶ እና ሴት አግኝቷል። የነበሩትን 11 ሚስቶች ለማዳረስ ሌሊቱን ሁሉ ሲሮጥ ያድር ነበር የተመኘውን ያገኝ ዘንድም የተመረዘውን ምግብ ሳይቀር በልቶ ሞቷል
Hammasini ko'rsatish...
የረዓይቶች/የኔፍሊሞች ታሪክ በአጭሩ ⤵ 👉ቃየል እና ሉድ፣ አቤልና አቅሌማን የአዳምና የሔዋን የመጀመሪያ ልጆች ናቸው። 👉አዳም ዘርን ለማራራቅ የአቤልን መንትያ ለቃየል የቃየልንም መንትያ ለአቤል አድርጎ አጋባቸው። 👉ቃየል ግን በዚህ ደስተኛ አልሆነም። ምክንያቱም ከእሱ ጋር አብራ የተወለደችው (ሉድ) ቆንጆ ስለሆነች አቤል እንድያገባበት አልፈለገምና። 👉አዳምም መስዋዕት እንድያቀርቡና እግዚአብሔር መስዋዕቱን የተቀበለለት ቆንጆዋን ሴት/ሉድን ማግባት እንደሚችል ነገራቸው። 👉 አቤል በንፁህ ልብ ሆኖ መልካሙን መስዋዕት ከፀሎት ጋር አቀረበ። 👉ቃኤል ግን በንደት፣ በብስጭትና በቅንዓት ለእግዚአብሔርም ሳይጨነቅ አቀረበ። 👉 የአቤልን መስዋዕት ከሰማይ የተላከ እሳት አቃጠላት። ቃየን ይህንን እያየ ይበሳጭና ይቀና ነበር እንጅ እግዚአብሔር የእሱን መስዋዕትነት እንድቀበልለት አይፀልይም ነበር። 👉ቃየልም ወንድሙን በመግደል የወንድሙን ሚስት መውሰድ እንደሚችል ሠይጣን ነገረው/አስተማረው። አቤልንም ገደለው። 👉 አቤልንም ከገደለ በኋላ ከወላጆቹ ተለይቶ በኤዶም በስተ ምሥራቅ ባለች "ኖድ" በምትባል ሀገር ኖሯል። በኋላም ከተማዋን በልጁ ስም "ሔኖሕ" ብሎ ሰይሟታል። 👉 ቃየል ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ሲሄድ የአቤልንም ሚስት ያለወላጆቹ ፈቃድ ይዟት ሄዷል። 👉አዳምና ሄዋን ከ20 አመት በኋላ በሞተው በአቤል ፋንታ ወንድ ልጅን ወልደዋል። ስሙንም "ሴት"ብለው ጠሩት። 👉እግዚአብሔር ቃየልንና ዘሮቹን ረግሟቸዋልና የሴት ዘሮች ከቃየል ዘሮች ጋር ፍፁም አይገናኙም፣ አይጋቡም። 👉የሴት ልጆች ህግና ሥርአት እየተማሩና መሥዋዕት እያቀረቡ በደብር ቅዱስ ይኖሩ ነበር። 👉የሚኖሩበት ቦታ ከገነት 45 ክንድ ይርቃል። 👉የገነትን መዓዛ ነፋስ ያመጣው ነበር። 👉ከቅድስናቸው ብዛት መላዕክትን ሲወጡ፣ሲወርዱና ሲላኩ ያዩአቸው ነበር። 👉ለመላዕክትም የተገለጠ እውቀት ተገልጦላቸው ነበር። ለቁርባን የሚሆን እንጅ ለሚመገቡት የሚሆን ስንደን አያከማቹም ነበር። 👉ከዝሙት/ከወሲብ ተጠብቀው ይኖራሉ። 👉በህይወት ዘመናቸው ከሚስቶቻቸው ጋር 3 ጊዜ ብቻ ግንኙነት ያደርጋሉ። 👉የመጀመሪያው ልጅ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ ሲሆን ከሁለቱ መካከል ደግሞ አንዱ ለአባቱ አገልጋይ አንዷ ደግሞ ለእናቷ የምታገለግል ናቸው። 👉ከአዳም ጀምሮ እስከ ኖህ ድረስ ሁሉም አባቶች ልጆቻቸው ከቃኤል ዘሮች ጋር እንዳይገናኙና እንዳይጋቡ በእግዚአብሔር ስም፣ በአባታቸው በአዳም ስምና፣ በፃድቁ በአቤል ስም ያምሏቸው ነበር። 👉የሚኖሩት እድሜ እንደዛሬው አጭር ሳይሆን እስከ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ዘጠኝ ዓመት ያህል ይኖራሉ። 👉ለዚህም አዳም በህይወት እያለ የልጅ ልጆቹን እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ አይቷል። #አቆጣጠራቸውም 1,አዳም፣ 2,ሴት፣ 3,ሔኖስ፣ 4,ቃይናን 5,መላልኤል (ከዚህ በላይ ያሉት አዳም በህይወት እያለ የተወለዱ ናቸው) 6,ያሬድ 7,ሄኖክ 8,ማቱሳላ 9,ላሜህ 10,ኖህ እያለ ይቀጥላል . . . 👉ከዘመናት በኋላ በያሬድ ዘመን የነበሩ ሰዎች የአባቶቻቸውን ትዕዛዝና መሐላ እያፈረሱ ከደብር ቅዱስ እየወረዱ መቀላቀል ጀመሩ። 👉የቃኤል ዘሮች ቆንጆዎች ነበሩ፤ ያለ ህግ ልክ እንደ እንስሳ አንዳቸው በአንዳቸው ላይ እየተንጠላጠሉ ዝሙትን ይፈፅሙ ነበር። ይህንንም ያዬ ስማዝያ የተባለ ሰው በደብር ቅዱስ ያሉ ሁሉንም ቃል እያስገባ ወደ ጥፋት ወሰዳቸው። 👉እነዚያ የእግዚአብሔር ልጆች መላዕክት ተብለው የተጠሩት፤ ከሀጢያት እርቀው እግዚአብሔርን እያመሠገኑ በቅድስና ይኖሩበት ከነበረው ደብር/ ቅዱስ ተራራ ከስምንቱ የኖህ ቤተሰቦች በቀር አንድስ እንኳን ሳይቀር ሁሉም ወርደው ከበደለኞቹ ከቃኤል ልጆች ጋር በኀጢአት ወደቁ። 👉አንዳንዶች ከቃየል ልጆች ጋር የተጋቡት ከሰማይ የኮበለሉ መላዕክት ናቸው በማለት ይከራከራሉ። ለዚህም እንደማስረጃ የሚያቀርቡት በመፅሐፍ ቅዱስ አንዳንድ ቦታወች ላይ መላዕክት/የእግዚአብሔር ልጆች እያለ የሚጠራቸው ነው። ነገር ግን ስተዋል። በመሠረቱ መላዕክት ፆታ የላቸውም! አያገቡም አይጋቡምም። ማቴዎስ 22፥30 ። በተጨማሪም የሴት ዘሮች መላዕክት እየተባሉ የተጠሩት ከቅድስናቸው የተነሳ ነው። የሴት ልጆች እራሳቸውን ከኃጢአተኞቹ ከቃየል ዘሮች ለይተውና ከሀጢያት አርቀው እንደ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገንን እንኖራለን ብለው በብሔረ ብፁዓን ይኖሩ ስለነበር ነው። የቅድስናቸውን ዝርዝር ከላይ አስፍሬዋለሁ። ከቅድስናቸው የተነሳ ለመላዕክት የተገለጠ ምስጢር ሁሉ ተገልጦላቸዋል። ስለ ኔፍሊሞች/ስለ ረዓይቶች አብዝቶ የሚተነትነው መፅሐፈ ሔኖክም የእግዚአብሔር ልጆች/መላዕክት እየተባሉ የሚጠሩት ደቂቀ ሴት/የሴት ልጆች እንደሆኑ በተደጋጋሚ ይናገራል። 👉ከኀጢአት እርቀው ንፅህናቸውን ጠብቀው በደብር ቅዱስ ይኖሩ በነበረበት ወቅት የተገለጠላቸውን እውቀት ለቃኤል ልጆች አስተማሩ። 👉 ሠይጣን ለሄዋን እፀ-በለስ ክፉውንና ደጉን መለየት የምታስችል እፀዋት መሆኗን እንደነገራት ሁሉ፤ ደቂቀ ሴቶችም ለሰዎች የማይገባ የተሰወረ ጥበብን ሁለ ለደቂቀ ቃየል አስተማሯቸው። 👉ስር መማስን፣ቅጠል መበጠስን/መድኃኒት መቀመምን፣ የከበሩ ዕንቁዎችንና ማዕድናት ማውጣትን፣ ወዘተ ለቃየል ልጆች ነገሯቸው/አስተማሯቸው። 👉የቃኤል ልጆችም ሰው መግደልን ሾተል/ሰይፍ መስራትን ፅንስ ማስወረድን ወዘተ አስተማሯቸው። 👉ጻድቆቹ የሴት ዘሮች ከኀጢአተኞቹ ከቃየል ዘሮች ጋር ተጋብተው ልጆችን ወለዱ። 👉ነገር ግን የተወለዱት ልጆች ከተፈጥሮ ባህሪ ያፈነገጡ ነበሩ። 👉አጫጭሮቹም በሽምብራ ተክል ሥር የሚጠለሉ እጅግ በጣም ትንንሽ ሲሆኑ እረጃጅሞቹ ደግም እስከ 3,000 ክንድ ያህል የሚረዝሙና ደመናን የሚገፉ ሆኑ። 👉ወላጆቻቸውም እነርሱን መመገብ እስኪሳናቸው ድረስ ገዘፉ። ተፈጥሮ ያበቀለችውን ዛፍ ቅጠሉን ሁሉ በሉ። 👉እርሱም አልበቃቸውምና እርስ በእርሳቸው መበላላት ጀመሩ ትልቁ/ረጅሙ ሰው ትንሹን በላው። ወንድሞቻቸውን በሉ። እጅግ በጣም ኃያላንና ፅንዓን ነበሩ። 👉ስማቸውም ኔፍሊም/ረዓይት በመባል ያታወቃሉ። እግዚአብሔርም የሰዎች ልብ ፈፅሞ በክፋት የተሞላ እንደሆነ አየ። መጥፋታቸውንም አሰበና አዘነ። 👉በዘመኑ ለነበረው ለጻድቁ ለኖህም መርከብ እንድሰራ አዘዘው መርከቡም ተሰርቶ እስኪያልቅ 100 አመት ፈጄ ኖህም መርከቡን በሚሰራበት ወቅት ለንስሓ እንድመለሱ ደጋግሞ ይነግራቸው ነበር። እነርሱ ግን ትንሽ ጊዜ እንጨፍርና እንመለሳለን እያሉ ጊዜያቸውን ይጨርሱ ነበር። 👉የመጥፊያቸው ቀንም በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ለ40 ቀን እና ሌሊት ዝናብን አዘነበ። ከምድርም ወደላይ የሚወጣ ውሀ ነበር ተቀላቅለውም አጠፏቸው። 👉በመርከቡ ውስጥ ካሉ 8 ሰዎችና ኖሕ ተባዕትና እንስት እያደረገ በመርከቡ ውስጥ ካስገባቸው እንስሳቶች በቀር ከሰው እስከ እንስሳ፤በሰማይ ከሚበሩ በምድር ከሚሳቡ፣በባህር ከሚርመሠመሱ ከአእዋፍ እስከ አራዊትና እንስሳት ሁሉም ጠፋ። 👉ውሀው ከመሬት እስኪደርቅ አንድ አመት ያህል ፈጀ ዓለምም እንደገና በ8 ሰዎች ኑሮን ጀመረች 👉ከዚያም በኋላ ሰዎች ዘእግዚአብሔርም ዓለምን ዳግመኛ በውኃ ጥፋት እንደማያጠፋት ለኖህ በዝናብ ወቅት የምናየውን ቀስተ ደመና የቃል ኪዳን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ለሰው ልጆች ምልክትን ሰጠ። #ሼር ምንጭ:- መፅሐፍ ቅዱስ እና ሌሎች አዋልድ የትርጓሜ መጻሕፍት ላይ ካነበብኳቸው
Hammasini ko'rsatish...
++ አበው ስለ እመቤታችን ዕረፍት እንዲህ አሉ ++ ‹ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች 'ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ‹‹ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው … በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው … በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው … በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ … አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ›› ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ (Homily on the Dormition) ‹‹የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው›› ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ (aka Doctor of Dormition) ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ አስተ ር እዮ ማርያም ጎተበርግ ስዊድን
Hammasini ko'rsatish...
በረውን የወንጌል ብርሃን የበለጠ እንዲበራ አድርጓል፡፡ ከጃንደረባውም ጋር ሆነው በብዙ ቦታዎች አብረው ወንጌልን ሰብከው አምልኮተ ጣዖትን አጥፍተዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ባኮስ ወደ የመን በመሄድ በዚያም ክርስትናን በማስተማር ብዙዎችን አሳምኖ ካጠመቀ በኋላ ወደ ፐርሺያ ከዚያም ወደ ሕንድ በመሄድ ሐዋርያዊ አገልግሎቱን ፈጽሟል፡፡ በመጨረሻም ጥንት ታፕሮባና (taprobana) ዛሬ ሲሎን በምትባለው ደሴት ወንጌልን በማስተማር ላይ እያለ በሰማዕትነት እንዳረፈ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ (lives of the most eminent fathers of the church, page 87) በሌላም በኩል ሐዋርያው ባኮስ (አቤላክ) ከመጠመቁ በፊት 35 ዓመት ከተጠመቀ በኋላ ደግሞ 41 ዓመት ኖሮ በኢየሩሳሌምም 3 ዓመት ተቀምጦ ወንጌልን ዞሮ ካስተማረ በኋላ በመጨረሻ በ79 ዓመቱ ጥር 18 ቀን በሰሜን ተራራዎች ላይ ቅዱስ ያሬድ በተሰወረበት ቦታ እንደተሰወረ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ጽፈዋል፡፡ የቅዱስ አቤላክ (ባኮስ) ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
Hammasini ko'rsatish...
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን ጥር 18-ፀሐይ ዘልዳ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐፅሙ ተቃጥሎ አጥንቱ ተፈጭቶ በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የተበተነበት ዕለት ነው፡፡ + በ34 ዓ.ም ጥምቀትን ያመጣልን ለሀገራችንም ሆነ ለአፍሪካ የመጀመሪያ ሐዋርያችን የሆነው ቅዱስ አቤላክ (ባኮስ) በዚህች ዕለት በሰሜን ተራራዎች ላይ ቅዱስ ያሬድ በተሰወረበት ቦታ ተሰወረ፡፡ እርሱም በጌታችን የተመረጡ የከበሩ ሐዋርያት እንኳን ወንጌልን በዓለም ለመስበክ ገና ከኢየሩሳሌም ባልወጡበት ወቅት ወደ አፍሪካ መጥቶ ወንጌልን የሰበከ ነው፡፡ + ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ መምህሩ የሆኑት አባ ያዕቆብ ዕረፍታቸው ነው፡፡ + ጌታችን ከሞት ያስነሣው የቅዱስ አልዓዛር እኅቶች ማርያምና ማርታ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡ አባ ያዕቆብ፡- በገድል ተጠምደው የኖሩ እጅግ የከበሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ተወልደው ያደጉት ንጽቢን በምትባል ከተማ ቢሆንም ሶርያዊ ተብለው ይጠራሉ፡፡ የሀገረ ንጽኒቢን ኤጲስ ቆጶስ ሲሆኑ የእመቤታችንን ውዳሴ ለደረሰው ታላቅ አባት ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ መምህሩ ናቸው፡፡ ይህ ታላቅ አባት ከልጅነታቸው ጀምሮ ዓለምን ንቀው በመንኩስና መኖርን መርጠው መንኩሰዋል፡፡ በጠጉር ከተሠራ ማቅ በቀር ሌላ ልብስ ለብሰው አያውቁም፡፡ በቀን በሌሊት፣ በበጋ ሐሩርም ይሁን በክረምት ቁር ቢሆን ይህንን ልብሳቸውን አውልቀውት አያውቁም፡፡ ምግብም ከቅጠላ ቅጠል ውጭ ተመግበው አያወቁም፡፡ የሚጠጡትም የዝናብ ውኃ ብቻ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ሀብተ ትንቢትና ሀብተ ፈውስ ተሰጥቷቸው እጅግ አስገራሚ የሆኑ ተአምራትን ያደርጉ ጀመር፡፡ በአንዲት ዕለት ሴቶች በውኃ ምንጭ ላይ እርቃናቸውን ያለ ማፈር ሲጫወቱና ሲሳለቁ አይተው የውኃውን ምንጭ ወዲያው እንዲደርቅ አድርገውታል፡፡ የሴቶቹንም የራሳቸውን ጸጉር በተአምራት ነጭ ሽበት አደረጉባቸው፡፡ ሴቶቹም ተጸጽተው በአባታችን እግር ሥር ወድቀው በለመኗቸው ጊዜ የውኃውን ምንጭ መልሰው አፈለቁላቸው፡፡ እንዳይታበዩ ሲሉ ግን የራሳቸውን ጸጉር ለምልክት ነጭ አድርገው ተውላቸው፡፡ ትሩፋታቸውና ዜናቸው በበየቦታው በተሰማ ጊዜ አቡነ ያዕቆብን በንጽቢን ሀገር ላይ ኤጲስ ቆጶስነት ሾሟቸው፡፡ ጻድቁ ንጉሥ ታላቁ ቈስጠንጢኖስ 318ቱን የከበሩ አባቶች በኒቅያ እንዲሰበሰቡ ሲያደርግ ገድላኛ የሆኑት ይህ ታላቅ አባትም አንዱ ነበሩ፡፡ በጉባኤውም መካከል ሙት አስነሥተው እንዲመሰክር አድርገውታል፡፡ እርሳቸውም አርዮስን አስተምረው መክረው እምቢ ቢላቸው ረግመው አውግዘውታል፡፡ የፋርስ ንጉሥ መጥቶ ሀገረ ንጽቢን ሊወር አስቦ በከበባት ጊዜ አቡነ ያዕቆብ በጸሎታቸው የጭጋግ ደመና በሠራዊቱ ላይ አመጡባቸው፡፡ ተናዳፊ ትንኞችም ፈረሶቻቸውንና ወታደሮቻቸውን ሁሉ ነደፏቸው፡፡ ፈረሶቹም ማሠሪያቸውን እየበጠሱ ፈርጥተው ጠፉ፡፡ ንጉሡም ይህን ተአምር አይቶ እጅግ ፈርቶ ወደ ኋላው ተመልሶ ሄዷል፡፡ ጻድቁ ሕዝበ ክርስቲያኑንና ሀገራቸውን በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በጽድቅ ሲያገለግሉ ኖረው በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን! + + + ስብረተ ዐፅሙ ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡- ከሃዲው ንጉሥ ዱድያኖስ እጅግ አሠቃቂ በሆኑ ብዙ መከራዎች እያሠቃየ ሦስት ጊዜም ቢገድለው ጌታችን ግን ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሞት እያስነሣው ከሃድያንን ያሳፍራቸው ነበር፡፡ ንጉሥ ዱድያኖስ የሚያደርገው ቢያጣ ጭፍሮቹን ‹‹በመንኰራኩር ፈጭታችሁ አጥንቱን ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ ወስዳችሁ ዝሩት›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥጋ በመንኰራኩር ፈጭተው ወስደው በተራራው ላይ ቢረጩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣ ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ ‹‹ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣ ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር›› እያሉ አመስግነዋል፡፡ አሁንም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣውና ሥጋውን ፈጭተው በተራራም ላይ ሥጋውን በትነውት ወደ ንጉሡ የሚመለሱትን ወታደሮች በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ ደረሰባቸውና ‹‹ቆዩኝ ጠብቁኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እጅግ ደንግጠው ይህ እንዴት እንደሆነ ሲጠይቁት ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› አላቸው፡፡ ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠው ከእግሩ ስር ወድቀው ‹‹ይቅር በለን›› ብለው በአምላኩ እንደሚያምኑ መሰከሩለት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከመሬት ላይ ውሃ አመንጭቶ በጸሎት ጌታችንን ቢጠይቅ ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ አጥምቋቸዋል፡፡ እነርሱም በንጉሣቸው ፊት ሄደው ስለጌታችን በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐፅሙ ተቃጥሎ አጥንቱ ተፈጭቶ በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የተበተነው በዚህች ዕለት ነው፡፡ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን! + + + የመጀመሪያው የአፍሪካ ሐዋርያ ቅዱስ አቤላክ (ባኮስ)፡- ይኽም ጃንደረባ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ ንግሥት የሆነችው የህንደኬ የገንዘቧ ሁሉ ኃላፊና አዛዥ የነበረ ነው፡፡ ከአባቱ እብነ መላክ ከእናቱ ስሂነ ሕይወት ታኅሣሥ 29 ቀን ተወለደ፡፡ ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ ወደ ኢየሩሳሌም በመጓዝ ለበዓለ ፋሲካ በቤተ መቅደስ ይሰግዱ እንደነበረው ሁሉ ይኽም ጃንደረባ ከ4 ሺህ ማይልስ በላይ ተጉዞ ኢየሩሳሌምን ተሳልሞ በመለስ ላይ ነበረ፡፡ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ በተለይም ስለ ጌታችን መከራ መስቀል በዝርዝር የሚናገረ ውን ክፍል 53ኛውን ምዕራፍ ያነብ ነበር ነገር ግን ጃንደረባው ስለማን እንደሚናገር አልገባውም ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ እግዚአብሔር በአካባቢው ወንጌልን ይሰብክ የነበረውን ሐዋርያውን ቅዱስ ፊሊጶስን ላከለት፡፡ እርሱም ጃንደረባው ያነበው የነበረውን መጽሐፍ ተረጎመለት፣ የከበረች ወንጌልን ሰበከለት፣ በመጨረሻም አጠመቀው፡፡ ሐዋርያው ባጠመቀውም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በጃንደረባው ላይ ወረደ፡፡ ሐዋ 8፡26-40፡፡ ይህን ለእኛ ለኢትዮጵያውን እጅግ የሚያኮራን ታሪካችን ነው፡፡ ዛሬ በእጃችን ላይ በመገኘው መጽሐፍ ውስጥ ባይኖርም በቆዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዞች ላይ ግን ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ጃንደረባውን ባጠመቀውም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያው ጃንደረባ ላይ እንደወረደ ተጽፏል፡፡ (ዝኒ ከማሁ ገጽ 87፣ v.39.cord.alexand. in bible reg. angl-alique plures codd.mss) ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ ጃንደረባውን ያጠመቀበት ወንዝ ‹‹ቤተ ሳሮን›› በተባለችውና እስከዛሬም ድረስ ከኢየሩሳሌም 20 ማይልስ ርቀት በምትገኘው መንደር በኬብሮን መካከል ባለው ኮረብታ ሥር የሚመነጭ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ጸሐፊ የሆነው ሊቁ ቅዱስ ጀሮም ጃንደረባውን ‹‹የኢትዮጵያውያን ሐዋርያ›› በማለት ይጠራዋል፡፡ በሰፊው ለኢትዮጵያውያን ወንጌልን የሰበከ እርሱ ነውና፡፡ ጌታችን የመረጣቸው የከበሩ ሐዋርያት እንኳን ወንጌልን በዓለም ለመስበክ ገና ከኢየሩሳሌም ባልወጡበት ወቅት በ34 ዓ.ም ነው ቅድስት አገራችን ኢትዮጵያ በክርስቶስ አምና ወንጌልን የተቀበለችው፡፡ በምድሪቱም ላይ ወንጌል መነገር የጀመረው ከዚሁ ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ሐዋርያው ባኮስ (አቤላክ) ከኢየሩሳሌም ወንጌልን ተምሮና ተጠምቆ ወደ አክሱም እንደተመለሰ በመጀመሪያ ያጠመቀው ንግሥቲቷን ሕንደኬን ነው፡፡ ከእርሷም በኋላ መኳንንቱና መሳፍንቱ ሁሉ አምነው በባኮስ እጅ ተጠመቁ፡፡ ይኸውም በ34 ዓ.ም ነው፡፡ ከዚህም በኋላ ባኮስ እስከ ኑብያ ድረስ ሄዶ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቋል፡፡ በዚህም ጊዜ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በባኮስ እየተሰጠ የነ
Hammasini ko'rsatish...
+ ለምን ትቀናለህ? + በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡ አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡ ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው:: ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡ ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡ ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡ የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡ ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡ የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡ ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡ ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡ በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡ ‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13 ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ አለታ ወንዶ ኢትዮጵያ ጥር 5 2013 ዓ.ም. መነሻ ሃሳብ:- የአንድ በቅናት ጦስ ሊያበሩ ሲችሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ ቤተሰቦች ታሪክ ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.