አቡ አዩብ ሙሃመድ ሰይድ ሙሃመድ
Kanalga Telegram’da o‘tish
قال الإمام مالك ((لايصلح آخر هذه الأمة إلا بماصلح به أولها))
Ko'proq ko'rsatish8 721
Obunachilar
+11724 soatlar
+1367 kunlar
+12730 kunlar
Postlar arxiv
8 716
በዱንያ ላይ እያለን ሌሎች ነገሮችን
ማንበብ ችለን የአላህ ቃል(ቁርኣንን)
ጊዜ ሰጥተን ባለመማራችን እና
ባለመቅራታችን አላህ ዘንድ ምክንያታችን ምን ይሆን⁉️
🎙🎙 ታላቅ ብስራት ለቁርኣን እውቀት ፈላጊዎች በሙሉ📣
መርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሂፍዝ ማዕከል ⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
✔️ጊዜና ቦታ ሳይገድብዎ፣ ባሉበት ሆነው በሚመቾት ሰዓት ቁርኣንን በኦንላይን እኛ ጋር ይማሩ።
🌍በየትኛውም የአለማችን ክፍል ሆነው፣ በተመቾት የቂርኣት ሰዓት፣ በቀላል መንገድ፣ ብቁ በሆኑ እና መልካም ስነምግባርን በተላበሱ እንዲሁም በማስተማር የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው ኡስታዞች የኢስላማዊ እውቀት ፍላጎትዎን ለማርካት ተዘጋጅተናል።
✔️ በተቋሙ የሚሰጡት ትምህርቶች :- ⏬
👉📘ቃኢደቱ ኑራኒያ ለጀማሪዎች
👉📖ነዘር ከመሰረታዊ ተጅዊድ ጋር
👉📖የተሟላ የተጅዊድ ትምህርት
👉የቁርዐን ሂፍዝ ከሙራጀዐ ጋር
👉 የሙራጀዓ ፕሮግራም በግል እንሰጣለን።
✔️እኛ ጋር ሲማሩ(ሲቀሩ)⏬
✅በየትኛውም የእድሜ ክልል ቢሆኑ ይስተናገዳሉ
✅በዘርፉ ብቁ በሆኑ ኡስታዞች
✅በየትኛውም የአለማችን 🌍ክፍል ሆነው
✅በመረጡት ቋንቋ"አማረኛ,ኦሮመኛ,አረበኛ,ኢንጊሊዘኛ"
✅በተመቾት ሰአት
✅በቀላልና ውጤታማ በሆነ መንገድ የቁርኣን ንባብ ትምህርትን እኛ ጋር ያገኛሉ።
✅የማዕከሉ ሎጎ ስምና ማህተም ያለበትን ሸሃዳ(Certificate) ያገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃ⏬
➡️በ0925887118 በመደወል ያናግሩን።
❤️በቴሌግራም አድራሻችን⏬
✈️@Attewhid11 ያናግሩን።
⚡️የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል
https://telegram.me/abutoiba
8 716
ራሳቸውን ወደ ሱና በሚያስጠጉ አካላት ላይ በሰፊው ከሚታዩ ነውረኛ ተግባራት ውስጥ አንዱ ሰዎችን በተመለሱበት ጉዳይ መክሰስ ነው። አንድ ሰው ከሆነ የተሳሳተ አቋም ወይም ጥፋት ከተመለሰ ያንን ጉዳይ #እያወቀ ሆነ ብሎ በሱ ላይ የሚለጥፍ ሰው
1ኛ፦ ዋሾ ነው።
2ኛ፦ ውሸትን የደዕዋው መንገድ አድርጎ የያዘ መጥፎ ሰው ነው።
3ኛ፦ ዓላማው ዲን ሳይሆን ቂም ማወራረድና ብሸሸቅ ነው።
ይሄ ነገር የሰውየውን መመለስ #ሳናውቅ ሊገጥመን ይችላል። መመለሱን ካወቅን በኋላ በተመለሰበት ጉዳይ መወንጀል ግን ያለ ወንጀሉ ሰውን መክሰስ ነው። ቡድናዊ ሽኩቻ ላይ ያነጣጠሩ "ረዶች" በብዛት ይሄ ችግር ጎልቶ ይታይባቸዋል።
ሰውን በተመለሰበት ጥፋት መክሰስ ባልፈፀመው ጥፋት እንደ መክሰስ ነው። ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ይላል:-
{ وَٱلَّذِینَ یُؤۡذُونَ ٱلۡمُؤۡمِنِینَ وَٱلۡمُؤۡمِنَـٰتِ بِغَیۡرِ مَا ٱكۡتَسَبُوا۟ فَقَدِ ٱحۡتَمَلُوا۟ بُهۡتَـٰنࣰا وَإِثۡمࣰا مُّبِینࣰا }
"እነዚያንም ምእምናንንና ምእምናነትን ባልሰሩት ነገር (በመዝለፍ) የሚያሰቃዩ ዕብለትንና ግልጽ ኃጢአትን በእርግጥ ተሸከሙ፡፡" [አልአሕዛብ: 58]
ነብያችንም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
من قال في مؤمنٍ ما ليس فيه أسكنه اللهُ رَدْغَةَ الخَبالِ حتّى يخرُجَ ممّا قال
"በአማኝ ላይ የሌለበትን የተናገረ ሰው አላህ የጥፋት ማጥ ውስጥ ያኖረዋል፣ ከተናገረው ነገር እስከሚወጣ ድረስ።" [ሶሒሑ ተርጊብ: 2845]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
8 716
📚 سفينة النجاة
📌ክፍል አራት
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6071
https://t.me/abutoiba/6071
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
قال الشيخ إبن عثيمين رحمه الله :
" ينبغي للإنسان أن يراعي قلوب الناس ، فإذا انكسر قلب شخص فليحرص على جبره بما استطاع ، لأن في هذا فضلاً عظيماً ".
ሰው የሌሎችን ስሜትና ልብ ሊያከብር ይገባዋል። የአንድ ሰው ልብ ከተሰበረ ወይም ከተጎዳ፣ የሚችለውን ሁሉ በማድረግ ልቡን ለማጽናናትና ለማስደሰት ይጣር፤ ምክንያቱም ይህ በአላህ ዘንድ ታላቅ ምንዳና ክብር ያለው መልካም ሥራ ነው።
شرح بلوغ المرام [11 / 333]..
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
متى تكون الزوجة قرة عين لزوجها ؟
تكون الزوجة قرة عين لزوجها والزوج قرة عين لزوجته إذا قاما بما يجب عليهما في دين الله.
ባልና ሚስት አላህን በመፍራት የዲናቸውን ግዴታ በታማኝነት ሲፈጽሙ፣ እያንዳንዳቸው ለሌላው የዓይን ደስታና የልብ እረፍት ይሆናሉ።
[اللقاء الشهري للشيخ العثيمين(٥/٤٠)].
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
*يتساهل بعض النساء بالسفر بلا محرم (للنزهة وغير ذلك من المباحات) .*
*وهذا محرم بالإجماع، ولحديث "لا تسافر امرأة إلا مع ذي محرم" رواه البخاري ومسلم .*
د. عبدالعزيز الريس .
8 716
አዲስ የምንጀምረው የአደብ ኪታብ
📚مختصر حلية طالب العلم
📌قال عبد الله بن المبارك رحمه الله:
«نحن إلى قليلٍ من الأدب أحوجُ منا إلى كثيرٍ من العلم.»
"ከብዙ ዕውቀት ይልቅ ትንሽ አደብ ማግኘት ለእኛ ይበልጥ አስፈላጊ ነው።"
አላህ አደብን ይወፍቀን
አሚን
አድራሻ : መርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታዊ የሸሪዓ እውቀቶች ማዕከል
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
🕌خطبة الجمعة في مركز أبي أيوب لتحفيظ القرآن الكريم والمبادئ الشرعية في مدينة كومبلشا
በኮምቦልቻ ከተማ በአቡ አዩብ የቁርዓን ሂፍዝ እና የሸሪዓ መርሆዎች ማእከል የቀርበ
📌العنوان :"أنفاس لاتعود وهي الوقت "
"የማትመለስ እስትንፋስ "ግዜ" "
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📚 سفينة النجاة
📌ክፍል ሶስት
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6071
https://t.me/abutoiba/6071
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📚 سفينة النجاة
📌ክፍል ሁለት
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6071
https://t.me/abutoiba/6071
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
ያ አላህ!
ምን ዓይነት ዘመን ላይ ደርሰናል?
አንዳንድ ሰዎች በከባድ ኃጢአት መውደቃቸው በሕዝብ መካከል ሲወራ፣ ሳይታወቅ ወደ አላህ በእውነተኛ ተውባ መመለሳቸው፣ ሳይታይ የሕይወታቸው ለውጥ፣ እንደገና "ዳዕዋ" በሚል ስም በሰዎች ፊት ቆመው "አላህን ፍሩ!" ሲሉ መስማት ልብን ያሳዝናል።
ዳዕዋ ትልቅ አደራ ናት፤ የነቢያት መንገድ ናት። ወደ አላህ የሚጠራ ሰው ከሁሉ በፊት ራሱን ሊመረምር፣ ከኃጢአት ሊጸጸት፣ በእውነተኛ ተውባም ወደ አላህ ሊመለስ ይገባዋል። ቃልና ተግባር ሲለያዩ ዳዕዋው ተፅእኖውን ያጣል፣ ሰዎችም በእስልምና ላይ ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው ምክንያት ይሆናል።
እኛም ሰዎችን ከመወንጀልና ከማስተላለፍ እንጠንቀቅ። ለሁሉም ሰው የተውባ በር ክፍት ነው፤ እውነተኛ ተውባ ያደረገ ሰው በአላህ ፈቃድ ይቅር ይባላል።
ለራሳችንም በተግባር አርአያ ለመሆን እንጣር።
አላህ ሁላችንን በእውነት ላይ ያጽናን፣ ከግልጽና ከስውር ኃጢአት ይጠብቀን፣ በቅን ተውባ ወደ እርሱ ከሚመለሱት ባሮቹም ያድርገን። አሚን።
=
አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ ሙሐመድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📌قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله:
اعلموا أن الدنيا متاع قليل ، سريعة الزوال والانهيار،
واسألوا ربكم الثبات على الحق إلى الممات "
«ይህን ዕወቁ፤ የዱንያ ሕይወት ጥቂትና ጊዜያዊ ጥቅም ብቻ ናት፤ ፈጥና ታልፋለች እና ትጠፋለች። ስለዚህ አላህን እስከ ሞት ድረስ በእውነት ላይ እንዲያጸናችሁ ለምኑት።»
📚الفتاوى (٣٨٩/٢٠)
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📚 سفينة النجاة
📌ክፍል አንድ
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6071
https://t.me/abutoiba/6071
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
🕌 የኸይር ጥሪ፡ ለመርከዝ አል-ሂዳያ ግንባታ በጋራ እንረባረብ! 🕌
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
"አሏህን ተውክለን፣ እናንተንም ደግፈን ለመጀመር ያቀድነው ታላቅ የኸይር ስራ!"
በወለኔ ልዩ ከተማ፣ ከኢንጌ ወረድ ብሎ "ቤደር" በምትባል መንደር ላይ ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚጠቅም "መርከዝ አል-ሂዳያ" የተሰኘ ትንሽዬ መርከዝ ለመገንባት አቅደን ተነስተናል።
አልሐምዱሊላህ! የአካባቢው ህዝብ ከበቂ በላይ የሆነ ትልቅ ቦታ በነጻ ሰጥቶናል።
አሁን ላይ ቦታው በኢንጂነር ተለክቶ ቀለል ያሉ እንጨቶች በህዝቡ ኒያ (በነጻ) እየተሰበሰቡ ይገኛሉ። እኛ ደግሞ የቀረውን ወጪ በጋራ ለመሸፈን ተረባርበናል።
📊 የወጪዎች ዝርዝር እና አሁን ያለንበት ደረጃ፦
➠ የግድግዳ እንጨት (700 ፍሬ)፦ 100,000 ብር (አልሃምዱሊሏህ 50,000 ብሩ ተከፍሏል!)
➠ ቆርቆሮ (400 ፍሬ)፦ የአንዱ ዋጋ 1,500 ብር (አልሃምዱሊሏህ 40 ቆርቆሮ ተገዝቷል!)
➠ ሚስማር (75 ካርቶን)፦ የአንዱ ዋጋ 1,200 ብር ➡️ ጠቅላላ 90,000 ብር
የሰራተኛ ወጪ (3 ሰራተኛ ለ2 ወር)፦ በቀን 700 ብር ➡️ ጠቅላላ 126,000 ብር
➠ 💰 ለግንባታው የሚያስፈልገው ጠቅላላ ድምር ሂሳብ፦ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር ነው።
🤝 የእርስዎ እገዛ ያስፈልገናል!
የዚህ ታላቅ የኸይር ሰበብ እንድንሆን ትንሽ ትልቅ ሳንል በገንዘብም ሆነ በአይነት (ቆርቆሮ፣ ሚስማር፣ እንጨት...) በመለገስ እንተባበር። አላህ መልካም ስራችሁን በዱንያም በአኼራም ይክፈላችሁ።
💳 የባንክ አካውንት መረጃ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000675591664
የአካውንቱ ስም፦ ሱፉያን ሱልጣን እና ቀድሪያ ኸድር
📞 ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ፦
📱 ኡሙ ዩሱፍ፦ 00971557567358
📱 መሀመድ ኸድር፦+251912716572
📱አብዶ ሁሴን፦+251910818422
📱ኡሙ አፊፍ፦ +251925227703
🔗 የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ፦
👉 እዚህ በመጫን ግሩፑን ይቀላቀሉ
https://t.me/+A7C8Hfr93zc3OTlk
ይህንን መልእክት ለሌሎችም በማጋራት (Share በማድረግ) የኸይሩ ተሳታፊ ይሁኑ!
8 716
የምድር ሕይወት ተለዋዋጭ ናት፤ ዛሬ ያለን ነገ ላይኖረን ይችላል።
በዚህ ዓለም ላይ የማይለወጥ ነገር የለም። ደስታና ሀዘን፣ ማግኘትና ማጣት፣ ከፍ ማለትና ዝቅ ማለት የሕይወት አካል ናቸው። ስለዚህ አላህ የተሻለ ቦታ ላይ ያደረሳችሁ ወንድሞችና እህቶች፣ እባካችሁ ትናንታችሁን አትርሱ።
አንድ ጊዜ እናንተም ዛሬ በምታዩት ቦታ አልነበራችሁም። ፈተና አልፋችኋል፣ ችግር አይታችኋል፣ ተስፋ የቆረጣችሁባቸው ቀናትም ነበሩ። አላህ በቸርነቱ ከዚያ አውጥቶ ዛሬ ወደተሻለ ሁኔታ አድርሷችኋል። ይህ ግን ከኋላችሁ ያሉትን ወንድሞቻችሁንና እህቶቻችሁን እንድትረሱ አያደርጋችሁም።
ወላሂ! ዛሬ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በጣም ጥሩ ውጤት አምጥተው የተመረቁ ብዙ ወጣቶች አሉ፤ ዶክትሬት፣ ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒውተር፣ ማኔጅመንት፣ ኢኮኖሚክስ፣ አካውንቲንግ፣ ዐረቢክ እና ሌሎችም ዘርፎችን ተምረው ሥራ ፍለጋ እየተንከራተቱ ይገኛሉ። ችግራቸው ችሎታ ማጣት ሳይሆን መረጃ ማጣትና ዕድል አለመድረስ ነው።
ስለዚህ የምንጠይቀው ሙስና አይደለም፣ ለእኛ ብቻ ቅድሚያ እንዲሰጠንም አይደለም። የምንጠይቀው አንድ ቀላል ነገር ብቻ ነው፤ መረጃውን አድርሱን፣ የሥራ ዕድሎችን አሳውቁን፣ አብሽሩ በሉን። አንድ መረጃ የአንድን ሰው ሕይወት ሊቀይር ይችላል። ተስፋን መስጠት ራሱ ትልቅ ምጽዋት ነው፤ የአእምሮም እረፍት ነው።
ትናንት አብረን በልተናል፣ አብረን ጠጥተናል፣ አብረን ተምረናል፣ አብረን አድገናል። ዛሬ የተሻለ ቦታ ላይ የደረሰ ሰው ወደ ኋላ ተመልሶ ወንድሙን ከፍ ማድረግ ይገባዋል፤ ያ የክብር ምልክት ነው።
ከሁሉ የሚያሳዝነው ግን፣ ታማኝ፣ በዲኑ የጠነከሩ፣ በመልካም ሥነ ምግባር የሚታወቁ ብዙ ወንድሞችን በችግርና በተስፋ መቁረጥ ምክንያት እያጣናቸው መሆኑ ነው። ከሄዱ በኋላ በመጸጸት ፋይዳ የለውም፤ መፍትሔ መፈለግ ያለብን ዛሬ ነው።
አላህ የሰጠንን እድል ለሌሎች የመልካም መንገድ እናድርግ። አንድ መረጃ፣ አንድ ምክር፣ አንድ የማበረታቻ ቃል ወይም አንድ የእገዛ እጅ የአንድን ሰው ሕይወት ሊለውጥ ይችላል። እንተሳሰብ፣ እንረዳዳ፣ እንተባበር፤ ምክንያቱም ዛሬ ያለን ቦታ ነገ ላይኖረን ይችላል፣ ዛሬ የሚያስፈልገው ወንድማችን ደግሞ ነገ እኛን ሊያስፈልገን ይችላል።
አላህ ሁላችንንም ለበጎ ነገር ይጠቀምብን፣ የወንድሞቻችንንና የእህቶቻችንን ጭንቀት ያስወግድ፣ ለሁሉም ሐላል ሥራና ሰፊ ሪዝቅ ይወፍቅ። አሚን።
=
አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ ሙሐመድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📚 درة المبتدئ في التجويد
📌ክፍል አስራ አራት"የመጨረሻው ክፍል"
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
تمت بحمد الله
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6002
https://t.me/abutoiba/6002
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
📚 درة المبتدئ في التجويد
📌ክፍል አስራ ሶስት
🎙አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
የኪተቡ pdf
https://t.me/abutoiba/6002
https://t.me/abutoiba/6002
🌐ለመርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሒፍዝ እና መሰረታ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል ተማሪዎች መሰጠት የያዘ ትምህርት
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
8 716
ያ አላህ! አንዳንድ አጋጣሚዎች ትልቅ ትምህርትን ይዘው ይመጣሉ። ከብዙ ጊዜ በኋላ አንድ መርከዝ ሳስተምረው የነበረ ወንድሜን አገኘሁት። በወሬ መካከል እንዲህ አለኝ፦
“በዒባዳዬ ላይ ራሴን ማስተካከል አለብኝ ብዬ፣ ካለፈው ረመዳን ጀምሮ ተክቢረቱል ኢሕራም አልፎኝ አያውቅም።”
ወላሂ! በጣም ደነቀኝ። የሚያስደንቀው ቃሉ ብቻ አልነበረም፤ በዒባዳ ላይ ያለው ቁርጠኝነትና ቋሚነት ነበር።
እውነትም ትናንሽ መልካም ስራዎች በቀጣይነት ሲደረጉ በአላህ ዘንድ ትልቅ ይሆናሉ። አላህ በዒባዳችን ላይ ቋሚነትን ይስጠን፣ አሚን።
=
አቡ አዩብ ሙሐመድ ሰዒድ
https://telegram.me/abutoiba
https://telegram.me/abutoiba
