ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW
ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot
Ko'proq ko'rsatish- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Ma'lumot yuklanmoqda...
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-lawየፌደራል ጠ/ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት በሰበር መ/ቁ. 231200 በአመልካች ጉምሩክ ኮሚሽንና በተጠሪ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ መካከል በተካሄደው ክርክር ጉምሩክ ኮሚሽን ከቀረጥና ታክስ ነጻ ሆነው ወደ አገር ውስጥ የገቡ ዕቃዎች ላይ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ መኖሩን እስካረጋገጠ ድረስ እነዚህን ዕቃዎች ተከታትሎ በመያዝ የሚፈለገውን ዕዳ የመሰብሰብ መብት ያለው መሆኑን በመጥቀስ የፋይናንስ ተቋማት ይህንን ዕቃ ለሰጡት ብድር በመያዣነት በእጅ ማድረጋቸው የሚያመጣው ለውጥ የለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጉም መስጠቱ ይታወሳል። ይህ ውሳኔ ሰበር ሰሚ ችሎቱ ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በሰ/መ/ቁ. 235004 ባንኮች ዋስትና በተቀበሉባቸው ሀብቶች ላይ የቀደምትነት መብት አላቸው ሲል ከሰጠው ውሳኔ ጋር ይቃረናል የሚሉ ሐሳቦች እየተስተዋሉ ነው። ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰ/መ/ቁ. 235004 የሰጠው ውሳኔ ባንኮች የታክስ ዕዳ እንደሌለበት በቅድሚያ አረጋግጠው በመያዣ የያዙትን ሀብት የሚመለከት ሲሆን የሰ/መ/ቁ. 231200 ደግሞ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ የገባ ዕቃ ላይ በጉምሩክ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ የሚሰበሰብበትን አግባብ የሚመለከት ነው። በጉምሩክ አዋጅ ቁ. 859/06 (እንደተሻሻለ) አንቀጽ 130(1)፣(2)፣(6) እና (7) እንደተመለከተው ከቀረጥና ታክስ ነጻ ሆኖ ወደ አገር የገባን ዕቃ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ተመሳሳይ የቀረጥ ነጻ መብት ለሌለው ሰው ማስተላለፍ፣ በሌሎች ሰዎች ይዞታና አገልግሎት ሥር ማዋል የተከለከለ ሲሆን ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በቀረጥና ታክስ አከፋፈሉ ረገድ ስምምነት ላይ ሳይደረስ ዕቃውን በዋስትና ማስያዝም አይቻልም። ዕቃውን ለሰጡት ብድር አከፋፈል በዋስትናነት መያዝ ይቅርና ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተሽከርካሪዎች የቀረጥና ታክስ አከፋፈል ለመወሰን የወጣው መመሪያ ቁጥር 52/2003 በአንቀጽ 5(1) እና (2) ላይ ማንኛውም መድን ሰጭ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ ለገባ ተሽከርካሪ የመድን ዋስትና ሲሰጥ የተገባው ዋስትና ተሽከርካሪው ለሚፈለግበት ቀረጥና ታክስ ጭምር መሆኑን የማረጋገጥና ይህንንም ለኮሚሽኑ የማሳወቅ ግዴታ የሚጥልበት ሲሆን ይህንን ሳያደርግ ቀርቶ ለተሽከርካሪው የመድን ዋስትና ቢሰጥና ተሽከርካሪው ከፍተኛ ጉዳት ቢያጋጥመው የመድን ድርጅቱ ለቀረጥና ታክስ አከፋፈሉ ተጠያቂ እንደሚሆን ደንግጓል፡፡ የባለቤትነት ሥም ዝውውር የሚመዘግብ ማናቸውም አካልም ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለበትን ዕቃ ሲመዘግብ ይህንን በባለቤትነት የምስክር ወረቀት ላይ መግለጽ የሚኖርበት ሲሆን ዕቃው ለ3ኛ ወገን ሲተላለፍም ቀረጥና ታክስ የተከፈለበት መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ አለበት። (እንደ ምሣሌ የተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመሪያና መመዝገቢያ አዋጅ ቁ. 681/02 አንቀጽ 7(1)(ረ) ይመለከቷል።) የሰ/መ/ቁ. 231200 ዋነኛ የትኩረት ነጥብ የጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ ቁጥጥር የማድረግ ሥልጣን እስከምን ድረስ ይሄዳል? የሚል ነው። መደምደሚያውም አንድ ዕቃ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ መግባቱ እስከተረጋገጠ ድረስና የሚፈለግበት የቀረጥና ታክስ ዕዳ እስካለ ድረስ ዕቃውን በእጁ ያደረገው ሰው ሊያነሳው የሚችለው ብቸኛ መከራከሪያ ዕቃው ቀረጥና ታክስ ተከፍሎበታል የሚል ብቻ ነው የሚል ነው። ባንኮች ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ የገባን ዕቃ በዋስትናነት ለመያዝ የማይችሉ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ባንኩ ለሰጠው ብድር በማካካሻነት ቢይዘው እንኳን የቀረጥና ታክስ ዕዳው ዕቃውን እየተከተለ የሚሄድ በመሆኑ በጉምሩክ ቁጥጥር የማድረግ ሥልጣን ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም የሚል ነው። ሰበር ሰሚ ችሎቱ ቃል በቃል እንዳስቀመጠው "ጉምሩክ ኮሚሽን ከአንድ ንብረት ላይ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ ስለመኖሩ እስካረጋገጠ ድረስ ንብረቱ በማናቸውም መንገድ ከተላለፈላቸው 3ኛ ወገኖች እጅ ጭምር በመያዝ መከፈል ያለበትን የመንግሥት ዕዳ የማስከፈል በሕግ የተረጋገጠ መብት አለው።" እንደ ሰበር ውሳኔው ከሆነ..ሦስተኛ ወገኖች ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለበትን ዕቃ በእጃቸው ያደረጉት በቅን ልቦና ስለመሆኑ ቢረጋገጥ እንኳን ዕቃው ላይ የሚሰጠው የውርስ ውሳኔ በጉምሩክ አዋጁ አንቀጽ 147(5) መሠረት ቀሪ ሆኖ ቀረጥና ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ግን የሚቋቋምባቸው ይሆናል። በሁለቱ የሰበር ውሳኔዎች ለክርክሩ መነሻ የሆኑት የታክስ ዓይነቶች የተለያዩ በመሆናቸውና ተከራካሪ ወገኖችም መብታቸውን ያገኙት ከተለያዩ ሕጎች በመሆኑ ውሳኔዎቹ ሰፊ ልዩነት ያላቸው ናቸው።
ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
Dedicated to empowering Ethiopian youth with knowledge of their fundamental rights.
https://linktr.ee/yhrethበመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች• የአዋጁ የተፈፃሚነት ወሰን ይህ አዋጅ ተፈፃሚ የሚሆነው ከአንድ ክፍል ጀምሮ ለመኖሪያ አገልግሎት የተከራየና ገንዘብ የሚከፈልበትን ማንኛውም ቤት ላይ ሲሆን በሆቴል፣ ሪዞርት፣ የእንግዳ ማረፊያ እና ሌሎች በንግድ ፈቃድ መሰረት በሚከራዩ ቤቶች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ • ስለመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ውል በፅሁፍ የሚደረግ ሆኖ በወረዳ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት፡፡ የኪራይ ክፍያውም በባንክ ወይም በሌላ ህጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ ብቻ የሚፈፀም ይሆናል። የአከራይ እና ተከራይ ውሉን ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በሁሉም ወረዳዎች ፅ/ቤቱ የማረጋገጥና የመመዝገብ ስራውን ተጀምሯል፡፡ ይህ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል አከራይና ተከራይ በተፈራረሙ 30 ቀናት ውስጥ የማረጋገጥ እና እንዲመዘገብ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ማንኛውም ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል። የማረጋገጥ እና የምዝገባ ግዴታን ያለመወጣት በአከራይ ወይም በተከራይ ላይ በተቆጣጣሪው አካል እስከ ሶስት ወር የሚደርስ በውሉ ላይ የተጠቀሰውን ገንዘብ ያስቀጣል፡፡ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በፅሁፍ የተደረገ የኪራይ ውል ካልሆነ በስተቀር የመኖሪያ ቤት ኪራይ የውል ዘመን ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም። እንዲሁም ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ውል ሲገባ አከራይ ከተከራይ ላይ ሊጠይቅ የሚችለው ቅድሚያ ክፍያ ከ2 ወር የቤቱ የኪራይ ዋጋ ሊበልጥ አይችልም። በዚህ የውል ዘመን ውስጥ ተከራይን ከቤት ማስወጣትም ሆነ በአዋጁ ከሚፈቀደው አግባብ ውጭ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይቻልም፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ የኪራይ ውል ላይ ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ የቤቱ የኪራይ ዋጋ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ አዲስ የሚወጣ የቤት ኪራይ ዋጋ አሁን ላይ የለም። አከራይ ለነባር ተከራይ ወይም ለአዲስ ተከራይ በሚያከራየው የመኖሪያ ቤት ላይ ቀደሞ በነበረው ኪራይ ላይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ቢሮ በአመት አንድ ጊዜ በሰኔ ወር ነባራዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሬ መሰረት በማድረግ ብቻ ነው። አዲስ የተገነባ ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ ለኪራይ የቀረበ የመኖሪያ ቤት በሚከራይበት ጊዜ የቤቱ የኪራይ ዋጋ በአከራይና በተከራይ ስምምነት የሚወሰን ይሆናል። ነገር ግን አከራይ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ ቤት ያለአገልግሎት ከስድስት ወር በላይ እንዲቀመጥ ካደረገ ቤቱ ቢከራይ ሊከፍል ይችል የነበረውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ገቢ ግብር ተሰልቶ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታ 1. የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል የኪራይ ዘመኑ ሳይጠናቀቅ በአከራዩና ተከራዩ ስምምነት፣ 2. ተከራይ ቤቱን መልቀቅ ሲፈልግ የሁለት ወር የቅድሚያ ማስታወቂያ በመስጠት 3. የአንድ ቤት ባለቤትነት በውርስ፣ በሽያጭ፣ በዕዳ ወይም በሌላ ማናቸውም ህጋዊ ምክንያት ለሌላ ወገን ከተላለፈ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውሉ ሊቋረጥ የሚችለው ቤቱ ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ የ6 ወር ማስጠንቀቂያ ለተከራዩ በመስጠት ነው። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ያለማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች 1. የቤት ኪራይ በውሉ በተመለከተው የመክፈያ ጊዜ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ከ15 ቀን ካሳለፈ 2. ለሁለተኛ ጊዜ ከሆነ 7 ቀን ካሳለፈ Source- Daniel Fikadu
ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. @AshenafiFisha
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.