cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW

ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot

Ko'proq ko'rsatish
Efiopiya1 718Til belgilanmaganQonun629
Reklama postlari
13 343
Obunachilar
+224 soatlar
+267 kunlar
+11730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

የፌደራል ጠ/ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት በሰበር መ/ቁ. 231200 (ጉምሩክ ኮሚሽን ከንብ ባንክ) እና በሰበር መ/ቁ. 235004 (ገቢዎች ሚኒስቴር ከዳሽን ባንክ) የሰጣቸውን ውሳኔዎች ተንተርሰው የሚነሱ ሐሳቦች By- Tsegazeab Zerihun Gebeyehu, an Attorney for FDRE Customs Commission.
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
የፌደራል ጠ/ፍ/ቤት ሰ/ሰ/ችሎት በሰበር መ/ቁ. 231200 በአመልካች ጉምሩክ ኮሚሽንና በተጠሪ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ መካከል በተካሄደው ክርክር ጉምሩክ ኮሚሽን ከቀረጥና ታክስ ነጻ ሆነው ወደ አገር ውስጥ የገቡ ዕቃዎች ላይ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ መኖሩን እስካረጋገጠ ድረስ እነዚህን ዕቃዎች ተከታትሎ በመያዝ የሚፈለገውን ዕዳ የመሰብሰብ መብት ያለው መሆኑን በመጥቀስ የፋይናንስ ተቋማት ይህንን ዕቃ ለሰጡት ብድር በመያዣነት በእጅ ማድረጋቸው የሚያመጣው ለውጥ የለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጉም መስጠቱ ይታወሳል። ይህ ውሳኔ ሰበር ሰሚ ችሎቱ ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በሰ/መ/ቁ. 235004 ባንኮች ዋስትና በተቀበሉባቸው ሀብቶች ላይ የቀደምትነት መብት አላቸው ሲል ከሰጠው ውሳኔ ጋር ይቃረናል የሚሉ ሐሳቦች እየተስተዋሉ ነው። ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰ/መ/ቁ. 235004 የሰጠው ውሳኔ ባንኮች የታክስ ዕዳ እንደሌለበት በቅድሚያ አረጋግጠው በመያዣ የያዙትን ሀብት የሚመለከት ሲሆን የሰ/መ/ቁ. 231200 ደግሞ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ የገባ ዕቃ ላይ በጉምሩክ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ የሚሰበሰብበትን አግባብ የሚመለከት ነው። በጉምሩክ አዋጅ ቁ. 859/06 (እንደተሻሻለ) አንቀጽ 130(1)፣(2)፣(6) እና (7) እንደተመለከተው ከቀረጥና ታክስ ነጻ ሆኖ ወደ አገር የገባን ዕቃ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ተመሳሳይ የቀረጥ ነጻ መብት ለሌለው ሰው ማስተላለፍ፣ በሌሎች ሰዎች ይዞታና አገልግሎት ሥር ማዋል የተከለከለ ሲሆን ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በቀረጥና ታክስ አከፋፈሉ ረገድ ስምምነት ላይ ሳይደረስ ዕቃውን በዋስትና ማስያዝም አይቻልም። ዕቃውን ለሰጡት ብድር አከፋፈል በዋስትናነት መያዝ ይቅርና ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተሽከርካሪዎች የቀረጥና ታክስ አከፋፈል ለመወሰን የወጣው መመሪያ ቁጥር 52/2003 በአንቀጽ 5(1) እና (2) ላይ ማንኛውም መድን ሰጭ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ ለገባ ተሽከርካሪ የመድን ዋስትና ሲሰጥ የተገባው ዋስትና ተሽከርካሪው ለሚፈለግበት ቀረጥና ታክስ ጭምር መሆኑን የማረጋገጥና ይህንንም ለኮሚሽኑ የማሳወቅ ግዴታ የሚጥልበት ሲሆን ይህንን ሳያደርግ ቀርቶ ለተሽከርካሪው የመድን ዋስትና ቢሰጥና ተሽከርካሪው ከፍተኛ ጉዳት ቢያጋጥመው የመድን ድርጅቱ ለቀረጥና ታክስ አከፋፈሉ ተጠያቂ እንደሚሆን ደንግጓል፡፡ የባለቤትነት ሥም ዝውውር የሚመዘግብ ማናቸውም አካልም ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለበትን ዕቃ ሲመዘግብ ይህንን በባለቤትነት የምስክር ወረቀት ላይ መግለጽ የሚኖርበት ሲሆን ዕቃው ለ3ኛ ወገን ሲተላለፍም ቀረጥና ታክስ የተከፈለበት መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ አለበት። (እንደ ምሣሌ የተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመሪያና መመዝገቢያ አዋጅ ቁ. 681/02 አንቀጽ 7(1)(ረ) ይመለከቷል።) የሰ/መ/ቁ. 231200 ዋነኛ የትኩረት ነጥብ የጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ ቁጥጥር የማድረግ ሥልጣን እስከምን ድረስ ይሄዳል? የሚል ነው። መደምደሚያውም አንድ ዕቃ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ መግባቱ እስከተረጋገጠ ድረስና የሚፈለግበት የቀረጥና ታክስ ዕዳ እስካለ ድረስ ዕቃውን በእጁ ያደረገው ሰው ሊያነሳው የሚችለው ብቸኛ መከራከሪያ ዕቃው ቀረጥና ታክስ ተከፍሎበታል የሚል ብቻ ነው የሚል ነው። ባንኮች ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልበት ወደ አገር ውስጥ የገባን ዕቃ በዋስትናነት ለመያዝ የማይችሉ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ባንኩ ለሰጠው ብድር በማካካሻነት ቢይዘው እንኳን የቀረጥና ታክስ ዕዳው ዕቃውን እየተከተለ የሚሄድ በመሆኑ በጉምሩክ ቁጥጥር የማድረግ ሥልጣን ላይ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም የሚል ነው። ሰበር ሰሚ ችሎቱ ቃል በቃል እንዳስቀመጠው "ጉምሩክ ኮሚሽን ከአንድ ንብረት ላይ የሚፈለግ ቀረጥና ታክስ ስለመኖሩ እስካረጋገጠ ድረስ ንብረቱ በማናቸውም መንገድ ከተላለፈላቸው 3ኛ ወገኖች እጅ ጭምር በመያዝ መከፈል ያለበትን የመንግሥት ዕዳ የማስከፈል በሕግ የተረጋገጠ መብት አለው።" እንደ ሰበር ውሳኔው ከሆነ..ሦስተኛ ወገኖች ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለበትን ዕቃ በእጃቸው ያደረጉት በቅን ልቦና ስለመሆኑ ቢረጋገጥ እንኳን ዕቃው ላይ የሚሰጠው የውርስ ውሳኔ በጉምሩክ አዋጁ አንቀጽ 147(5) መሠረት ቀሪ ሆኖ ቀረጥና ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ግን የሚቋቋምባቸው ይሆናል። በሁለቱ የሰበር ውሳኔዎች ለክርክሩ መነሻ የሆኑት የታክስ ዓይነቶች የተለያዩ በመሆናቸውና ተከራካሪ ወገኖችም መብታቸውን ያገኙት ከተለያዩ ሕጎች በመሆኑ ውሳኔዎቹ ሰፊ ልዩነት ያላቸው ናቸው።
Hammasini ko'rsatish...
ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW

ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot

👍 8 4🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
The International Organizations Interest Groups (IOIGs) of ASIL and the European Society of International Law are thrilled to announce a call for proposals for our biannual virtual workshop on the law and practice of international organizations. Don't miss this opportunity to receive feedback from peers and experts in the field! JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://lnkd.in/du4VqNXb Facebook- https://lnkd.in/dcPghmjG LinkedIn- https://lnkd.in/dW6tGf_e
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
የሰበር መ/ቁ 227978 ሕዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም የፋይናንስ ተቋማት ለሰጡት ብድር አከፋፈል በመያዣነት የያዙት ተሽከርካሪ የጦር መሣሪያ ጭኖ በመገኘቱ የተነሳ በጉምሩክ ኮሚሽን ሲወረስ የተሽከርካሪው ባለቤት (ተበዳሪው) የውርስ ውሳኔውን ሕጋዊነት በመቃወም ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በሚያቀርበው የይግባኝ አቤቱታ ጣልቃ በመግባት የክርክሩ ተካፋይ መሆን ይችላሉ ወይስ አይችሉም? የፋይናንስ ተቋማት ለሰጡት ብድር በመያዣነት የያዟቸው ተሽከርካሪዎች ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ለማዘዋወር ድርጊት መፈጸሚያነት ውለው ሲገኙ በጉምሩክ ኮሚሽን አስተዳደራዊ ውሳኔ ውርስ የሚደረጉ ሲሆን የፋይናንስ ተቋማቱም የውርስ ውሳኔው በተሽከርካሪዎቹ ላይ ያላቸውን የቀደምትነት መብት ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነው የሚል ክርክር ያቀርባሉ። በጉምሩክ አዋጅ ቁ. 859/06 አንቀጽ 153 መሠረት የጉምሩክ ጉዳዮች አቤቱታ አጣሪ የሥራ ክፍል የውርስ ውሳኔውን በማጽናት በሰጠው ውሳኔ ላይ የተሽከርካሪው ባለቤት ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በሚያቀርበው ይግባኝ ላይ አበዳሪው ባንክ በታክስ ይግባኝ ኮሚሽኑ የአሰራር መመሪያ ቁ. 02/11 አንቀጽ 16(1)(ሀ) መሠረት የጣልቃ ገብ አቤቱታ በማቅረብ የክርክሩ ተካፋይ መሆን ይችላል? ወይስ ጉዳዩ በቀጥታ ለመደበኛ ፍ/ቤቶች የሚቀርብ ነው? በሚለው ጉዳይ ላይ ግልጽነት ባለመኖሩ ለክርክር በር ሲከፍት ቆይቷል። የታክስ ይግባኝ ኮሚሽኑ የፋይናንስ ተቋማቱ የሚያቀርቡትን የጣልቃ ገብ አቤቱታ ተቀብሎ የማየት ሥልጣን በሕግ ያልተሰጠው መሆኑን በመጥቀስ አቤቱታውን ውድቅ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን ጉዳዩን በይግባኝ የሚመለከቱ መደበኛ ፍ/ቤቶች ደግሞ የጉምሩክ ጥፋት መፈጸሙን ተከትሎ የሚጣሉ አስተዳደራዊ ቅጣቶችንና የውርስ ውሳኔዎችን ሕጋዊነት በመቃወም የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ተቀብሎ የማየትና መርምሮ በጉዳዩ ላይ ውሳኔ የመስጠት የመጀመሪያ ደረጃ የሥረ ነገር ሥልጣን ለጉምሩክ ኮሚሽን አቤቱታ አጣሪ የሥራ ክፍሎች የተሰጠ በመሆኑና በጉምሩክ አዋጁ የተዘረጋው የቅሬታ አቀራረብ ሥነ ሥርዓት በጉዳዩ ላይ ያገባናል የሚሉ ሦስተኛ ወገኖች ወደ ክርክሩ በመግባት መብትና ጥቅማቸውን ለማስከበር የሚችሉበትን አሠራር ያልዘረጋ በመሆኑ ተበዳሪው (የተሽከርካሪው ባለቤት) ለታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በሚያቀርበው የይግባኝ አቤቱታ ላይ የፋይናንስ ተቋሙ የክርክሩ ተካፋይ ሊሆን ይገባል የሚል አቋም ያንጸባርቃሉ። ይህንን በሚመለከት የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 227978 አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል። ሰ/ሰ/ችሎቱ - በታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በሚካሄዱ ክርክሮች የሚያከራክረው ጉዳይ ተሽከርካሪው የጦር መሣሪያ ጭኗል? አልጫነም..ሊወረስ ይገባል? አይገባም የሚል ክርክር በመሆኑና የፋይናንስ ተቋማቱም የቀዳሚነት መብት ያላቸው ስለመሆኑ ከማንሳት በስተቀር ተሽከርካሪው የጦር መሣሪያ ጭኗል ወይስ አልጫነም በሚለው የክርክር ፍሬ ጉዳይ ላይ የሚያቀርቡት ክርክር አለመኖሩን፤ በመሆኑም ለክርክሩ ምክንያት በሆነው ፍሬ ጉዳይ ላይ መብት ወይም ጥቅም የሌላቸው መሆኑን... - የቀዳሚ መብት ጥያቄ የሚነሳው በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 3059(1) መሠረት በመያዣ የተያዘው ንብረት በሌሎች ገንዘብ ጠያቂዎች ተይዞ ንብረቱ በሀራጅ ከተሸጠ በኋላ የተገኘው ገንዘብ የሁሉንም ዕዳ መሸፈን በማይችል ጊዜ መሆኑንና የቅድሚያ መብት አቤቱታ በዚህ ደረጃ የሚነሳ አለመሆኑን፤ የፋይናንስ ተቋማት ወደ ክርክሩ እንዲገቡ በሚል በሥር ፍ/ቤቶች የሚሰጥ ውሳኔ በባንኩና በተበዳሪው መካከል ያለውን የብድር/መያዣ ውል መሰረት ያደረገ አለመሆኑን በማንሳት ....ባንኩ የብድር ውሉን መሠረት በማድረግ የሚያቀርበውን የመብት ጥያቄ ግን በመጠበቅ ውሳኔ ሰጥቷል። በመሆኑም የፋይናንስ ተቋማት በመያዣነት የያዙት ተሽከርካሪ የውርስ ውሳኔ ሲተላለፍበት የመያዣ ውሉን መሠረት አድርገው በመደበኛ ፍ/ቤቶች ክስ ከሚመሰርቱ በስተቀር የውርስ ውሳኔውን ሕጋዊነት ብቻ በሚመለከተው በታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በተሽከርካሪው ባለቤትና በጉምሩክ ኮሚሽን መካከል በሚካሄድ ክርክር ጣልቃ ገብተው ለመከራከር አይችሉም።
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
Hammasini ko'rsatish...
ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW

ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. Contact us @AshenafiFisha Vist our legal database via- @aboutethiopialaw_bot

👍 19 1
Photo unavailableShow in Telegram
Are you an African between the ages of 18-30? Here is your chance to share your ideas on advancing the AfCFTA through the free movement of persons. Applications are now open for the Inaugural African Youth Essay Competition organised by AfCFTA Dialogues in partnership with Afronomicslaw. Submit your essays latest by 11:59 p.m. WAT on July 8, 2024, for a chance to win a N100,000 (One Hundred Thousand Naira) (or its equivalent in your local currency) and get published on the Afronomicslaw Blog! Theme: “Open Africa to Africans: Advancing the Implementation of the AfCFTA through the Free Movement of Persons” Access the detailed Call for Submissions here: 🔗https://lnkd.in/gp7Mm7v6 Submit your essays here: 🔗 https://lnkd.in/g62WusEH Follow AfCFTA Dialogues on our social media pages for updates
Hammasini ko'rsatish...
👍 5 1
ከተጨማሪ እሴት ነፃ የሆኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ዝርዝር መመሪያ ቁጥር 1006/2016
JOIN ስለ-ህግ ABOUT-LAW Telegram- https://telegram.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
Hammasini ko'rsatish...
1719259594642.pdf8.66 KB
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
መቃወሚያ አቤቱታ
Hammasini ko'rsatish...
👍 9 2
Hammasini ko'rsatish...
Youth for Human Rights Ethiopia

Dedicated to empowering Ethiopian youth with knowledge of their fundamental rights.

https://linktr.ee/yhreth

3👍 1
Chokie Journal of Law of Debre Markos University is accepting manuscripts for the upcoming issue. You can send us articles or commentaries via [email protected] or [email protected]
Hammasini ko'rsatish...
Chokie JoL V1 Issue 1.pdf1.38 MB
😍 1
አዲሱ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ሞዴል ውል.pdf2.62 KB
👍 5
በመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች
• የአዋጁ የተፈፃሚነት ወሰን ይህ አዋጅ ተፈፃሚ የሚሆነው ከአንድ ክፍል ጀምሮ ለመኖሪያ አገልግሎት የተከራየና ገንዘብ የሚከፈልበትን ማንኛውም ቤት ላይ ሲሆን በሆቴል፣ ሪዞርት፣ የእንግዳ ማረፊያ እና ሌሎች በንግድ ፈቃድ መሰረት በሚከራዩ ቤቶች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም፡፡ • ስለመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ውል በፅሁፍ የሚደረግ ሆኖ በወረዳ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት፡፡ የኪራይ ክፍያውም በባንክ ወይም በሌላ ህጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ ብቻ የሚፈፀም ይሆናል። የአከራይ እና ተከራይ ውሉን ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በሁሉም ወረዳዎች ፅ/ቤቱ የማረጋገጥና የመመዝገብ ስራውን ተጀምሯል፡፡ ይህ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል አከራይና ተከራይ በተፈራረሙ 30 ቀናት ውስጥ የማረጋገጥ እና እንዲመዘገብ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ማንኛውም ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል። የማረጋገጥ እና የምዝገባ ግዴታን ያለመወጣት በአከራይ ወይም በተከራይ ላይ በተቆጣጣሪው አካል እስከ ሶስት ወር የሚደርስ በውሉ ላይ የተጠቀሰውን ገንዘብ ያስቀጣል፡፡ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በፅሁፍ የተደረገ የኪራይ ውል ካልሆነ በስተቀር የመኖሪያ ቤት ኪራይ የውል ዘመን ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም። እንዲሁም ማንኛውም የመኖሪያ ቤት ውል ሲገባ አከራይ ከተከራይ ላይ ሊጠይቅ የሚችለው ቅድሚያ ክፍያ ከ2 ወር የቤቱ የኪራይ ዋጋ ሊበልጥ አይችልም። በዚህ የውል ዘመን ውስጥ ተከራይን ከቤት ማስወጣትም ሆነ በአዋጁ ከሚፈቀደው አግባብ ውጭ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይቻልም፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ የኪራይ ውል ላይ ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ የቤቱ የኪራይ ዋጋ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ አዲስ የሚወጣ የቤት ኪራይ ዋጋ አሁን ላይ የለም። አከራይ ለነባር ተከራይ ወይም ለአዲስ ተከራይ በሚያከራየው የመኖሪያ ቤት ላይ ቀደሞ በነበረው ኪራይ ላይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ቢሮ በአመት አንድ ጊዜ በሰኔ ወር ነባራዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሬ መሰረት በማድረግ ብቻ ነው። አዲስ የተገነባ ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ ለኪራይ የቀረበ የመኖሪያ ቤት በሚከራይበት ጊዜ የቤቱ የኪራይ ዋጋ በአከራይና በተከራይ ስምምነት የሚወሰን ይሆናል። ነገር ግን አከራይ ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ ቤት ያለአገልግሎት ከስድስት ወር በላይ እንዲቀመጥ ካደረገ ቤቱ ቢከራይ ሊከፍል ይችል የነበረውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ገቢ ግብር ተሰልቶ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ስለሚቋረጥበት ሁኔታ 1. የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል የኪራይ ዘመኑ ሳይጠናቀቅ በአከራዩና ተከራዩ ስምምነት፣ 2. ተከራይ ቤቱን መልቀቅ ሲፈልግ የሁለት ወር የቅድሚያ ማስታወቂያ በመስጠት 3. የአንድ ቤት ባለቤትነት በውርስ፣ በሽያጭ፣ በዕዳ ወይም በሌላ ማናቸውም ህጋዊ ምክንያት ለሌላ ወገን ከተላለፈ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውሉ ሊቋረጥ የሚችለው ቤቱ ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ የ6 ወር ማስጠንቀቂያ ለተከራዩ በመስጠት ነው። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ያለማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች 1. የቤት ኪራይ በውሉ በተመለከተው የመክፈያ ጊዜ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ ከ15 ቀን ካሳለፈ 2. ለሁለተኛ ጊዜ ከሆነ 7 ቀን ካሳለፈ Source- Daniel Fikadu
Hammasini ko'rsatish...
ስለ-ሕግ ⚖️ ABOUT-LAW

ABOUT-LAW is a premier e-legal service platform established in October 2020. Whether you need legal advice, legal documents, , or any other legal assistance, we are here to help. @AshenafiFisha

👍 10 2👏 1
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.