cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 🚶‍♂️እንኳን ደህና መጡ👋 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶችን መዝሙሮች ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። 👥 ✅ @yemezmurgetemoche 📝ለማንኛውንም ሀሳብናአስተያየት ✅ @KIDAN_MEHRET_ENATEbot ለማስታወቂያ ስራዎች ✅ @gutaitagu16 የቻናላችን ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
19 059
Obunachilar
+4824 soatlar
+4197 kunlar
+1 44030 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ምክረ አበው
የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ።(መጽሐፈ ምክር)
"አንደበቱን ከቧልት ያየውን ሚስጥር ከመናገር የሚከለክል ሰው ልቦናውን ከኅልዮ ኃጢአት ያርቀዋል ።(አረጋዊ መንፈሳዊ)
ጸጋ ቢሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እዳታጣ " (ማር ይስሃቅ)
‹‹ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ‹ጥበብ ይለየዋል።›› /አረጋዊ መንፈሳዊ/
‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ።›› /አባ እንጦንስ/
‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል።›› /ቅዱስ አትናቴዎስ/
‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል።›› /ቅዱስ ሚናስ/
‹‹በማንም ላይ ክፈትን አትስሩ አትፍርዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና።›› /ታላቁ አባ መቃርስ/
‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም።›› /ቅዱስ አርሳንዮስ/
‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል።›› /ቅዱስ እንድርያስ/
‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን።›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/
‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/
‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ።›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/
‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ፀሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትፀልይ እደር።›› /ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ/
‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል።›› /ቅዱስ እንጦስ/
Hammasini ko'rsatish...
🥰 12👍 5🙏 5🔥 4 3👌 3👏 2😱 2
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሰኔ_14_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ዕብራውያን 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርግላችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው? ⁸ ነገር ግን ሁሉ የቅጣት ተካፋይ ሆኖአልና ያለ ቅጣት ብትኖሩ ዲቃላዎች እንጂ ልጆች አይደላችሁም። ⁹ ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን? ¹⁰ እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል። ¹¹ ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል። ¹² ስለዚህ የላሉትን እጆች የሰለሉትንም ጉልበቶች አቅኑ፤ ¹³ ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ። ¹⁴ ከሰው ሁሉ ጋር ሰላምን ተከታተሉ ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ 2ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹-¹⁰ ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል። ደፋሮችና ኵሩዎች ሆነው ሥልጣን ያላቸውን ሲሳደቡ አይንቀጠቀጡም፤ ¹¹ ዳሩ ግን መላእክት በኃይልና በብርታት ከእነርሱ ይልቅ ምንም ቢበልጡ በጌታ ፊት በእነርሱ ላይ የስድብን ፍርድ አያመጡም። ¹² እነዚህ ግን ለመጠመድና ለመጥፋት በፍጥረታቸው እንደ ተወለዱ አእምሮ እንደ ሌላቸው እንስሶች ሆነው፥ በማያውቁት ነገር እየተሳደቡ በጥፋታቸው ይጠፋሉ፤ ¹³ የዓመፃቸውን ደመወዝ ይቀበላሉ። በቀን ሲዘፍኑ እንደ ተድላ ይቆጥሩታል፤ ነውረኞችና ርኵሳን ሆነው ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣ ይዘፍናሉ፤ ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ሐዋርያት 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ወደ ኢጣሊያም በመርከብ እንሄድ ዘንድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎችን እስረኞች ከአውግስጦስ ጭፍራ ለነበረ ዩልዮስ ለሚሉት ለመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጡአቸው። ² በእስያም ዳርቻ ወዳሉ ስፍራዎች ይሄድ ዘንድ ባለው በአድራሚጢስ መርከብ ገብተን ተነሣን፤ የመቄዶንያም ሰው የሆነ የተሰሎንቄው አርስጥሮኮስ ከእኛ ጋር ነበረ። ³ በነገውም ወደ ሲዶና ስንደርስ ዩልዮስ ለጳውሎስ ቸርነት አድርጎ እርዳታቸውን ይቀበል ዘንድ ወደ ወዳጆቹ እንዲሄድ ፈቀደለት። ⁴ ከዚያም ተነሥተን ነፋሱ ፊት ለፊት ነበረና በቆጵሮስ ተተግነን ሄድን፤ ⁵ በኪልቅያና በጵንፍልያም አጠገብ ያለውን ባሕር ከተሻገርን በኋላ በሉቅያ ወዳለ ወደ ሙራ ደረስን። ⁶ የመቶ አለቃውም በዚያ ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያውን መርከብ አግኝቶ ወደ እርሱ አገባን። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሰኔ_14_ቀን_የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባእ ቅድሜከ ገዓሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። "አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ይወቁ። የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት ሊገደሉ የተፈረደባቸውን አድን። መዝ 78፥10-11። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሰኔ_14_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇 ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ ሉቃስ 21 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤ ¹³ ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ የሚቀደሰው ቅዳሴ የ #ቅዱሳን_የሠለስቱ_ምዕት_ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የበዓለ ዕርገቱ ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን። ✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
Hammasini ko'rsatish...
🙏 5👍 3
#ሰኔ_14 #ቅዱሳን_አባ_አክራና_ዮሐንስ_አብጥልማና_ፊልጶስ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ዐሥራ አራት በዚች ቀን ቅዱሳን አባ አክራና፣ ዮሐንስ፣ አብጥልማና ፊልጶስ በሰማዕትነት ሞቱ። ይህም ቅዱስ አክራ ከግብጽ ደቡብ ይምንሑር ከሚባል አገር ሰዎች ወገን ነው ስሙ ፊልጶስ የሚባል ወንድም ነበረው እነርሱም ባለጸጎች ነበሩ ስማቸው ዮሐንስና፣ አብጥልማ ከሚባል ሁለት ቀሳውስት ጋራ ሰማዕታት ይሆኑ ዘንድ ተስማሙ አራቱም ቀርጥስ ወደሚባል አገር ሔዱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በመኰንኑ ፊት ታመኑ። መኰንኑም በቀስቶች እንዲነድፏቸው አዘዘ ግን ቀስቶች አልነኳቸውም። ሁለተኛም እሳትን አንድደው በሚነድ የእሳት ምድጃ ውስጥ ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው ጌታም መልአኩን ልኮ አዳናቸው። ከዚህም በኋላ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው ከቀርጥስ ከተማ እስከ ይምንሑር አገር ድረስ ይጐትቷቸው ዘንድ አዘዘና ይህንንም አድረጉባቸው ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰባቸውም። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧችው አዘዘ ከይምንሑር ከተማም አውጥተው ራሶቻቸውን ቆረጡአቸው። ፃ ከሚባል አገር ሰዎች መጥተው የቅዱስ አባ አክራን ሥጋውን ወሰዱ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት በብዛት ተገለጡ። እንዲሁም የእነዚያን የሦስቱን ቅዳሳን የፊልጶስን፣ ለአብጥልማንና የዮሐንስን ሥጋቸውን ከይምንሑር ከተማ ሰዎች መጥተው ወሰዱ በመልካም ልብሶችም ገነዙአቸው ጥሩ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ ከእነርሳቸውም ቁጥር የሌለው ድንቅ ተአምር ተገለጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን። በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ_14)
Hammasini ko'rsatish...
1
✝️ እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል እና ለጻድቁ አባ ዮሐንስ ዓመታዊ በዓልና ለሁሉም በዛሬው ዕለተ ታስበው ለዋሉት ዓመታዊ እና ወርኀዊ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት : የአባ ዮሐንስ በረከት አይለየን:: 🌹❤️🌹............. ሰኔ 13
Hammasini ko'rsatish...
🙏 22 15🥰 6👍 4👏 4🕊 3
✝️ እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል እና ለጻድቁ አባ ዮሐንስ ዓመታዊ በዓልና ለሁሉም በዛሬው ዕለተ ታስበው ለዋሉት ዓመታዊ እና ወርኀዊ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት : የአባ ዮሐንስ በረከት አይለየን:: 🌹❤️🌹............. ሰኔ 13
Hammasini ko'rsatish...
11❤‍🔥 2🥰 2
ከዚህም በኋላ አቡነ ማትያስ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምረው በጾም በጸሎት ተወስነው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን እየተቀበሉ ማገልገል ጀመሩ። በዚኸም ጊዜ ሰይጣን በሥጋቸው ፈተናቸው። እርሳቸውም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው "ኦ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ነፍሴን ተቀበላት፣ ግደለኝ፤ እንዴት ከተወለድኹ ጀምሮ እስከዛሬ ፍጹም የማላውቀው መጥፎ ሀሳብ ከሚመጣብኝ ሞት ይሻለኛል፣ ግደለኝ.. እያሉ ሲጸልዩ የክብር ባለቤት ጌታችን በአካል ተገልጦላቸው በመለኮታዊ እጆቹ ዳስሶ ፈጽሞ አዳናቸው። ከዕለታት በአንደኛው ቀን አቡነ ማትያስ ከአንድ መነኵሴ ጋር ለገዳሙ ማኅበር ምግብ ለማዘጋጀት ወደ በረሓ እንደደረሱ የሚጠጡት ውኃ ሲያጡ አባታችን ማትያስ ጸሎት ካደረሱ በኋላ በበትራቸው መሬትን ባርከው እንደ ሊቀ ነቢያትሙሴ ውኃ አፈለቁ። እነርሱም የማኅበሩን ምግብ ይዘው ሲመለሱ በመንገድ ላይ ሽፍቶች አግኝተዋቸው ምግቡን ወሰዱባቸው፤ አባታችንም ጸሎት ቢያደርጉ ወዲያው እነዚያ ሽፍቶች ታመው ወደቁ። ከዚያም ሽፍቶቹ "እናንት የአምላክ ሰዎች ሆይ! እባካችሁ ይቅር በሉን፣ የወሰድንባችሁንም እንኩ ውሰዱ፣ እኛንም እርዱን…" እያሉ ለመኗቸው። አባታችንም ምራቃቸውን እንትፍ ብለው በትእምርተ መስቀል አማትበው በእርሱ ዳበሷቸውና ሽፍቶቹ ዳኑ። ዳግመኛም በአንደኛው ቀን መነኰሳቱ ሁሉም ሥራ ጨርሰው ተኝተው ሳለ አቡነ ማትያስ ግን ደከመኝ ሳይሉ መቶ ሃምሳውንም መዝሙረ ዳዊት ሲደግሙ አደሩ እግዚአብሔርም መላእክቱን ልኮ አንድ ፈረስ ሰጣቸው። አባታችንም በዚህ ተደስተው ለኹለተኛ ጊዜ መቶ ሃምሳውን መዝሙረ ዳዊት ሲደግሞ አሁንም ለኹለተኛ ጊዜ ፈረስ ተላከላቸው። ከእርሳቸውም ጋር የነበሩት መነኰሳት ምን እንደተፈጠረ ሳያውቁ ተኝተው አደሩ። አቡነ ማትያስን መላእክት ወደ ሰማያት አውጥተዋቸው በገነት ተድላ ያሉ ጻድቃንን አሳይተው ዳግመኛም የኀጥአንን ፍዳና መከራ አሳዩዋቸው። አባታችንም የኀጥአንን መከራ አይተው አዝነው ደንግጠው አለቀሱ። በዚህም ጊዜ "የተመረጥህ ማትያስ ሆይ! አትፍራ፣ እነዚህ ሕጌን የማያከብሩ ትእዛዜን ያፈረሱ ናቸው፣ በተድላ ገነት ያየኻቸውም ጻድቃን ናቸው" የሚል ቃል አጽናናቸው። ከዚህም በኋላ አባታችን ወደ ምድር ተመልሰው በመጡ ጊዜ አበ ምኔቱ አባ ተወልደ ምድኅን ዐርፈው በእርሳቸው መንበር አባ ፊቅጦር ተተኩ፤ ከአባ ፊቅጦርም በኋላ አስቀድሞ በተነገረው ትንቢት መሠረት አቡነ ማትያስን መርጠው ለመሾም ተስማሙ ነገር ግን አባታችን ማትያስ ሹመቱን እምቢ ሲሉ እጅና እግራቸውን አሥረው በግድ አበ ምኔት አድርገው ሾሟቸው። አቡነ ማትያስም ወደ ሰማያት ወጥተው የጻድቃንን ደስታና የኀጥአንን ፍዳ መከራ ከተመለከቱና ወደምድር ተመልሰው ከመጡ በኋላ መነኰሳቱን ሁሉ ሰብስበው ሕግንና ሥርዓትን ተግብረው ይኖሩ ዘንድ ስለነገሯቸው ከእነርሱ ውስጥ አንዳንድ ክፉዎች ወደ ንጉሡ ዘንድ ሔደው በብዙ ነገር በሐሰት ከሰሷቸው። ንጉሡም የተነገረው ሁሉ እውነት መስሎት አባታችንን ከሥልጣን አወረዳቸውና አሳደዳቸው። አቡነ ማትያስም ከገዳሙ ወጥተው ሲሔዱ "ከአንተ ከአባታችን አንለይም ብለው 230 መነኰሳት አብረዋቸው ሔዱ። ከዚህም በኋላ "ትኹል ጎዳዕ፣ ጨዓት፣ ቃቕብዳ፣ ኣቄታብ፣ ወኪ፣ ምድረ ባሕር" ወደተባሉ የተለያዩ | ቦታዎች ሔደው በተጋድሎ ኖሩ። በየበረሓውም ሲጓዙ ልጆቻቸው ውኃ ሲጠማቸው አባታችን መሬትን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠጧቸው። አባታችንም በምድረ ባሕር ሣሉ እህል ሳይቀምሱ በአንዲት ዋሻ ለኹለት ሳምንት ከቆዩ በኋላ በዚኸች ቦታ ላይ በሞት ማረፍ ፈለጉ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ "ለአንተ የምትሆን ምድር አዘጋጅቼልሃለሁና ወደልጆችህ ተመለስ" አላቸው። አባታችን ዳግመኛም ከልጆቻቸው ጋር ሆነው ወደ ዓንደቕ ከዚያም ወደ ዒላ ሔደው ለ66 ቀናት ከቆዩ በኋላ ደብረ ብርሃን ደረሱ። አባታችንም ይኸችን ቦታ "እግዚአብሔር የሰጠን ገዳማችን ናት" አሉ። ቦታዋንም ደብረ በረከት ብለው ሰየሟት። የዕረፍታቸውም ጊዜ ሲደርስ ልጆቻቸውን ሰብስበው በቃለ እግዚአብሔር አጽናንተው "በሥጋ ብለያችሁም በመንፈስ ግን ከመካከላችሁ አልለያችሁምና አትፍሩ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ፣ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስንና የአቡነ አብሳዲን ሥርዓት ጠብቁ…" ብለው ከመከሯቸው በኋላ በእርሳቸው ቦታ ዮሐንስን ሾመውላቸው ከጌታችን ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ሰኔ 13 ቀን በሰላም ዐረፉ። አቡነ ማትያስም ካረፉ በኋላ ለልጆቻቸው በአካለ ነፍስ እየተገለጡ አጽናንተዋቸዋል ። ከማረፋቸውም በፊት "አስቀድመው .....ከእናንተ ውስጥ የሚማረኩ አሉ፣ ነገር ግን እኔ አድናችኋለሁ" ብለዋቸው ስለነበር ትንቢታቸው ደርሶ ኹለቱ መነኰሳት ተማረኩ ነገር ግን በአባታችን ጸሎት ወደ ገዳማቸው ተመለሱ። ዳግመኛም ከመነኰሳቱ ውስጥ ሰባቱን ዐረማውያን ማረኳቸው፣ ንብረታቸውንም ወስደው ኹለቱን ገድለው፣ አምስቱን በባሕር ውስጥ ጣሏቸው፤ በዚኸም ጊዜ አባታችን ማትያስ በአካለ ነፍስ መጥተው "ልጆቼ አይዟችሁ፣ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና አወጣችኋለሁ፣ ባሕሩንም በእሳት አቃጥለዋለሁ" ብለው ካወጧቸው በኋላ ባሕሩን በእሳት አቃጥለውታል። ከአቡነ ማትያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ።
Hammasini ko'rsatish...
5
እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ በበትራቸው መሬትን ባርከው እንደ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ውኃ ላፈለቁት ዳግመኛም በባሕር የተጣሉ ልጆቻቸውን ባሕሩን በተአምራት አቃጥለው ልጆቻቸውን ላዳኑት #በኤርትራ_አገር_የሚገኘውን "#ደብረ_ብርሃን_ወደብረ_በረከት_ወደብረሰማዕት" ገዳም ለመሰረቱት #ለአቡነ_ማትያስ_ዘምራራ_ለዕረፍታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።  #አቡነ_ማትያስ (ማይታን) አባታቸው በዚህ ዓለም ሀብትና ንብረት ያፈራ ቢሆኑም በመጀመሪያ የክርስትና እምነትን ግን አልተቀበለም ነበር። ሀብቱንም የሚያወርሰው ልጅ ስላልነበረው በዚህ ይጨነቅ ነበር። የአቡነ ማትያስም እናት "…ክርስቲያን ሴቶች እኮ ወደ እግዚአብሔር ለምነው ልጅ ያገኛሉ፣ እኛም ወደ እግዚአብሔር እንለምንና ልጅ ካገኘን ለእግዚአብሔር ይሆናል" በማለት ለባሏ ነገረችው። እነርሱም ከተመካከሩ በኋላ "ልጅ ካገኘን እኛም ክርስቲያን እንሆናለን" ብለው ስዕለት ተሳሉ። ለቤተ ክርስቲያንም ዕጣን ሰጥተው ካህኑን "እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጠን ጸልይልን" አሉት። እመቤታችንንም በጸሎት ሲማጸኗት ቆይተው እግዚአብሔር ስዕለታቸውንና ጸሎታቸውን ተቀብሎ ልጅ ሰጣቸውና እጅግ ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርንና እመቤታችንን አመሰገኑ። ከዚህም በኋላ ወላጆቻቸው አምነው ተጠመቁና ስማቸው አብርሃም እና ኂሩተ ማርያም ሲባሉ የሕፃኑም ስም ድኁነ እግዚእ ተባለ። አብርሃምና ኂሩተ ማርያምም ፍጹም ክርስቲያኖች ከሆኑ በኋላ እግዚአብሔር በበረከት ጎበኛቸውና ሌሎች ፈቃደ እግዚእ፣ ባርያ እግዚእ፣ ንዋየ እግዚእ፣ ደጋፊነ እግዚእ እና ጥሪተ እግዚእ የሚባሉ አምስት ልጆችን ወለዱ። ስለዚህም አቡነ ማትያስ በ14 መ/ክ/ዘ ጽልማ ታኺታ በሚባል ቦታ ተወለዱ። እርሳቸውም በመጀመሪያ ስማቸው ጥሪተ እግዚእ ተብለው እንደ ቅዱስ ዳዊት የመጨረሻ ልጅ ሆነው በእረኝነት ወላጆቻቸውን ያገለግሉ ነበር። ጥሪተ እግዚእ ከዕለታት በአንደኛው ቀን ከእርሱ ጋር በግ የሚጠብቁ ጓደኞቹ ከሰው ማሳ እሽት ሰርቀው አምጥተው "ና ከእኛ ጋር ብላ" አሉት። እርሱ ግን የሌላን ሰው እህል አልበላም ብሎ እምቢ አለ፤ ለእናቱም ሲነገራት እናቱ ተደስታ አቅፋ ሳመችው። ጓደኞቹም በሌላ ጊዜ እንዲሁ የተሰረቀ እያመጡ ይበላ ዘንድ ቢፈታተኑትም እርሱ ግን እሺ አይላቸውም ነበር። በዚኸም ነገር ይህ ታናሽ ብላቴና ጥሪተ እግዚእ ኢትዮጵያዊውን ታላቅ ጻድቅ አቡነ ሀብተ ማርያምን መሰላቸው። ከዕለታትም በአንደኛው ዕለት አባታቸን ሀብተ ማርያም በጐችን ሲጠብቁ ሌሎች እረኞች በአመጻ ከሰው ሰርቀው ቆርጠው ያመጡትን እሸት "ና እንብላ" አሏቸው። አባታችን ግን "ከየት እንዳመጣቸሁት ምንም ስለማላውቅ አልበላም" አሏቸው። እረኞቹም ሀብተ ማርምን በቁጣ ዐይን እያዩአቸው ተቀምጠው ሲበሉ አባታችን "የማንችለው ዝናብ መጥቷልና ተነሡ በፍጥነት ወደቤታችን እንሂድ" አሏቸው። እረኞቹም "ሠማዩ ብራ ነው ምንም ደመና የለውም፤ ነፋስም አይነፍስም። እኛ የማናየው አንተ ብቻ የምታየው ምን ነገር አለ?" እያሉ በአባታችን ላይ ተዘባበቱባቸው። አባታችን ግን በጎቻቸውን እያስሮጡ በፍጥነት ወደ ቤታቸው ሔዱ፤ ወዲያውም በጣም ኃይለኛ ዝናብ ዘነበ፤ የጥፋት ውኃው በላያቸው እስኪፈጸምባቸው ድረስ እነዚያን እረኞች ከቦታቸው አልተነቃነቁም ነበርና በጥፋቱ ውኃ አለቁ። በዚያችም ሌሊት አቡነ ሀብተ ማርያን ከሰማይ ሦስት ጊዜ "ሀብተ ማርያም ሀብተ ማርያም" የሚል ድምፅ ጠራቸው። አባታችንም እንደ ሳሙኤል "ጌታዬ ባሪያህ ይሰማሃል ተናገር" ሲሉ ጌታችን አናገራቸው። ከዚህ በኋላ "ለሚሰሙ ለመረጥኳቸው ቃሌን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔም ጋር በምሥጢር በባለሟልነት ትነጋገር ዘንድ መርጨሃለሁ" አላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ አባታችን ዳግመኛ በጐችን እየጠበቁ ሳሉ አንድ አመጸኛ መጣና በትራቸውን በኃይል ነጥቆ ወሰደባቸው። አቡነ ሀብተ ማርያምም "በሕያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ እቋቋምህ ዘንድ ኃይል የለኝምና በትሬን መልስልኝ" ቢሉት የትዕቢትን ቃል ተናገራቸው። አባታችንም "እምቢ ካልክስ እሺ የእግዚአብሔርን ኃይል ታያለህ" አሉት። ወዲያም ያ አመጸኛ ላዩ ታች ታቹ ላይ፣ ግራው ቀኝ ቀኙ ግራ ሆኖ በአየር ላይ ተሰቅሎ ዋለና እየጮኸ አባታችንን ለመናቸው። አባታችንም "የቀጣህ እግዚአብሔር ይቅር ይበልህ ባሉት ጊዜ ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ። በዚያ የነበሩና ይህንን ተአምር ያዩ እረኞችም እጅግ ፈርተው ሔደው ለወላጆቻቸው ያዩትን ተናገሩ። የሀገሩ ሰዎችም "ቀድሞ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ እያለ ሲጸልይ ሲሰግድ አይተነዋል፣ አሁንም ጠላቱን በነፋስ የሚቀጣ ይህ ልጅ ወደፊት ምን ይሆን!" እያሉ አደነቁ። ወላጆቻቸውም ይህን በሰሙ ጊዜ በግ ጠባቂነቱን አስተዋቸውና ሃየማኖትን ይማሩ ዘንድ ወስደው ለመምህር ሰጧቸው። ወደ ጥሪተ እግዚእ ዜና ገድል እንመለስና እርሱም ከአመጸኞች ጋር ባለመተባበር ፈሪሃ እግዚአብሔርን ገንዘብ አደረገ። መንፈስ ቅዱስ በእናቱ ማሕፀን ሳለ እንደነቢዩ ኤርምያስ መርጦታልና በዋዛ ፈዛዛም ከእነርሱ ጋር አይተባበርም ነበር። ፊደልን እንኳን ሳይማር መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት መጻሕፍትን ዐወቀ፣ ትእዛዛትንም ሁሉ ጠበቀ። አባቱ አብርሃምም ዳግመኛ በጎችን መጠበቅ ትቶ ከብቶችን እንዲጠብቅ ስላዘዘው ሕፃኑም በኅብረት የማንንም ከብት ሳይለይ ይጠብቅ ነበር። በዚህም ወቅት ፈቃደ እግዚእ የተባለው ወንድማቸው ዓለምን ንቆ ገዳም ገብቶ ስለመነኰሰ ወንድሞቹ ሔደው ለአባታቸው ነገሩት፤ አባታቸውም "የእኛ ፈቃድ ሳይሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" አላቸው። እርሱም ከነልጆቹ እንደሚመነኵስ ራእይ አይቶ ልጆቹን ጠርቶ "ልጆቼ ሆይ! እኛም እንደ ፈቃደ እግዚእ እንመነኵስ ዘንድ አለን" ሲላቸው ልጆቹም "የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን፣ ስሙ በእኛ በባሪያዎቹ ይክበር ይመስገን" አሉ። ከዚህም በኋላ አራቱ የአብርሃም ልጆች ታኺታ የምትባለውን ቦታ ትተው ወንድማቸው ወደመነኰሰበት ገዳም ለማየት ሲሔዱ ታናሹ ጥሪተ እግዚእም አብሮ ለመሔድ ተነሣ። እነርሱም "መንገዱ ሩቅ ነው አንተ ትንሽ ልጅ ነህ ከዚሁ ቆይ" ብለው ትተውት ቢሔዱም እርሱ ግን ከኋላ ከኋላቸው እየተከተላቸው ሲሔድ እንዲመለስ ያባርሩት ነበር። ከዚያም ሕርሻ የሚባል ቦታ ላይ ሲደርሱ ጥሪተ እግዚእን "ንብረትና ስንቅ እየጠበቅህ ከዚህ ቆየን እኛ ማሳችንን አይተን እንመለሳለን",ብለው ትተውት ሔዱ። እርሱም በዚህ ጊዜ በደብረ ማርያም ያሉ መነኰሳትን ተመለከተና የሚጠብቀውን ንብረትና ስንቅ ትቶ መነኰሳቱን ተከትሎ ወደ ገዳም ሲገባ ወንድሙን ፈቃደ እግዚእን በዚሁ ገዳም ውስጥ አገኘው። ፈቃደ እግዚእ እና መነኰሳቱም ከየት እንደመጣ እየጠየቁት አቅፈው ሳሙት። ጥሪተ እግዚእም አመጣጡን ነገራቸው። ወንድሞቹም ከሔዱበት ሲመለሱ ጥሪተ እግዚእን ስላጡት እያዘኑ ሳለ የገዳሙ አንድ መነኵሴ ሕፃኑ ወደ ገዳም እንደገባና ከታላቅ ወንድሙ ጋር እንደተገናኘ ነገሯቸው። ወንድሞቹም ወደ ገዳሙ ገብተው አበ ምኔቱን አባ ተወልደ መድኅንን አግኝተው ተባረኩ። አበ ምኔቱም ከወንድሞቻቸው ጋር አገናኛቸውና እያለቀሱ ተሳሳሙ። ከዚያም ወንድሞቹ ወጥተው ወደ ማሳቸው ሲሔዱ ሕፃኑ ጥሪተ እግዚእ ግን በገዳም ቀረ። በዚያም መመንኰስ እንደሚፈልግ ሲናገር መነኰሳቱ "ልጄ ሆይ! ይህ ለአንተ ይከብድሃል ምንኵስና ለትልልቆች ነው የሚገባው፣ ትዕግሥት አድርግ…" ሲሉት እርሱም "…ለእኔ የሚሻለኝን ዐውቃለሁ" ብሎ መለሰ። እነርሱም በመልሱ ተገርመው አመነኰሱትና ማትያስ የሚል ስም ሰጡት።
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
"መዘንጋት ባለበት"| "Mezengat Balebet"| ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ መዘንጋት ባለበት መዘንጋት ባለበት በታናሽ ህሊና መዘመር ልጀምር ለድንግል ምስጋና እኔስ በውዳሴሽ ባህር እዋኛለው ገናንነትሽን ክብርሽን እያሰብኩ የትትናሽ ነገር ቢወሳ አያልቅም ታነቢያለሽ እና ለዚ ክፉ አለም ድንግል ሆይ ለሀጣን ታስቢያለሽ እና ልቦናዬ ባንቺ በምልጃሽ ተፅናና ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን አንቺን ተማጽነናል እንድታማልጂን ዘወትር እጆችሽ ተዘርግተዋል እና ስለበደለኞች ሊያቀርቡ ልመና እሳታውያኑ ሱራፌል ኪሩቤል ሊነኩት ያልቻሉት የሳቱን ነበልባል አንቺግን ታቀፍሽው ሳምሽው በከንፈርሽ ከፍጥረት ለይቶ ፍፁም ስላጸናሽ ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን አንቺን ተማጽነናል እንድታማልጂን ዘወትር እጆችሽ ተዘርግተዋል እና ስለበደለኞች ሊያቀርቡ ልመና ሊቀ-መዘምራን:- ይልማ ሀይሉ
Hammasini ko'rsatish...
_መዘንጋት_ባለበት_Mezengat_Balebet_ሊቀ_መዘምራን_ይልማ_ኃይሉ_BhkiZ_JWTdw_139.m4a1.80 MB
18👍 5👏 3🙏 3🕊 2❤‍🔥 1😢 1😍 1😘 1
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.