1 671
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-177 kunlar
-8030 kunlar
Postlar arxiv
1 671
አረንጓዴ አሻራ የኢትዮጵያ ህዝብ ለችግሮች በቀላሉ እጅ የማይሰጥና ጠንካራ መሆኑን ማሳያ ነው !!
ኢትዮጵያ የበለፀገ ታሪክ፣ ባህልና ብዝሃነት ያላቸው ህዝቦች በጋራ የሚኖሩባት ሀገር ናት። እንደ ሀገር ድህነት፣ ድርቅ፣ ግጭትና የአየር ንብረት ለውጥ የመሳሰሉ ብዙ ፈተናዎች ገጥመዋታል። የሀገራችን ግብርና የኢኮኖሚው ዋና ምሶሶ ቢሆንም በዝናብ የዝናብ፣ የውሃ ሃብት እና የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር ላይ ከፍተኛ ጥገኛ በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ እጅግ ተጋላጭ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ የኢትዮጵያን የልማት ግቦች ፈተና ላይ የሚጥል እና የሚሊዮን ህዝብ መተዳደሪያ የሆነውን ግብርና አደጋ ላይ የሚጥል ነው።
ኢትዮጵያ ግን በቀላሉ ተስፋ የምትቆርጥ ሀገር አይደለችም። እድገቷንና ብልፅግናዋን ለመጪዎቹ ትውልዶች ማስቀጠል የሚችል ለአየር ንብረት ለውጥ ተመራጭ የሆነ አረንጓዴ ኢኮኖሚን የመገንባት ራዕይ ያላት ሀገር ናት።
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ እና ለማላመድ፣ የተራቆተ አካባቢውን ወደነበረበት ለመመለስ እና የተፈጥሮ ካፒታልን ለማሳደግ ደፋርና ትልቅ እርምጃ የወሰደች ሀገር ናት።
መልካም እለተ ሰኞ ተመኘን
#kolfe_prospertiy_party- ብልፅግና
#kolfepp
1 671
የብልጽግና ተምሳሌት የሆነች እንደ ስሟ አዲስ እና አበባ ከተማ በመገንባት ቃል በተግባር እንፈፅማለን !!
አዲስ አበባን እንደ እንደ ስሟ አዲስ እና አበባ የማድረግ ስራው በአመራሮቻችን ቁርጠኝነት እና ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ 7/24 መርህ አድርጎ በመስራት የኢትዮጵያን ብልፅግና አይቀሬነት የታየበት ከመሆኑም በላይ የስራ ባህልን ከአስተሳሰብ ጀምሮ የቀየርንበትም ነው ።
የአዲስ አበባ ስሟን የሚመጥን የቱሪዝም መዳረሻ እና በአለም ተወዳዳሪ ከተማ በማድረግ በአለም ላይ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ የማድረግ ስራ በፓርቲያችን ራዕይ በመነሳት ከተማ እና የከተማ ልማትን በማፋጠን እና ከተሜነትን ማስፋፋት መሰረት ያደረገ ነው ።
የኮሊደር ልማት ቃል በተግባር የመፈጸም በተግባር የታየበት ኘሮጀክትን በጥራት እና ፍጥነት ጊዜ መፈጸም የተቻለበት ነው። ይህን ተግባር በሁሉም መስክ አጠናክሮ በመቀጠል የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ ይገባል ።
መልካም ቀን ይሁንለዎ!
#Kolfe_Prosperity_Party- ብልፅግና
#kolfepp
1 671
+9
የረዳን ፈጣሪ ክብርና ምስጋና ይሁንለት!
"በጎነት"ብለን በሰየምነው የመኖሪያ መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ 9 ወለል ዘመናዊ ሕንጻዎችን እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላትን መርቀን ለ140 አቅመ ደካሞች እና አካል ጉዳተኛ ነዋሪዎች አስተላልፈናል።
በልደታ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ቆርቆሮ ሰፈር በሚባለው የተጎሳቆለ የመኖሪያ መንደር ይኖሩ ለነበሩ አቅመ ደካሞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ማየት ለተሳናቸው፣ ለተለያየ ማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ እና በልማት ለተነሱ ነዋሪዎች ያስተላለፍናቸው ምቹ የመኖሪያ ቤቶች ሳሎን፣ መኝታ ቤት፣ የማብሰያ እና የመጸዳጃ እንዲሁም የመኝታ ክፍሎች ያላቸው ዘመናዊ ቤቶች ናቸው።
በዚህ የበጎነት መንደር ካስተላለፍናቸው የመኖሪያ ቤቶች ጋር በማቀናጀት የእናቶችን ጫና የሚያቀል የህጻናት ማቆያ፣ ለአካባቢው እናቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር ዘመናዊ የእንጀራ መጋገሪያ፣ የሚሰሩ እጆችን ከስራ የሚያገናኙ የወንዶችና የሴቶች የውበት ሳሎኖችን እንዲሁም የልብስ ስፌት ማሽኖችን አዘጋጅተን ለነዋሪዎቹ የስራ እድል ፈጥረናል።
በመኖሪያ መንደሩ ቤት ለሰጠናቸው ማየት የተሳናቸው ነዋሪዎች እንቅስቃሴ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ኬኖች፣ ለአካል ጉዳተኛ ነዋሪዎች ደግሞ ክራንችና ዊልቸሮችን አዳርሰናል።
ሰርቶ ካገኘው ላይ ለወገን በጎ ለመስራት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመተባበር ቤቶቹን የገነባውን ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በራሴና በነዋሪዎቹ ስም እያመሰገንኩ፣ በጎነት አያጎድልምና ፈጣሪ ጨምሮ እንዲሰጠው እመኛለሁ።
የሚሰሩ ልማቶች ሁሉ ለሰው ልጆች ተስፋ የሚሰጡ እና የኑሮ ጫናን የሚያቃልሉ ይሆኑ ዘንድ ሰው ተኮርነታችን በተግባር የሚገለጽ ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1 671
+9
በክፍለ ከተማው የስልጤ ልማት ማህበር (ስልማ) አመታዊ ኮንፈረንስ በአሁኑ ሰዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በኮንፈረንሱ አቶ አሊ ከድር የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የስልማ ልማት ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ፣የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንገቱ ዳኛቸው ፤የኢትዮጵያ ኢንተር ፖራይዞች ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አብዱልፈታ የሱፍ፤የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሃላፊ እንዲሁም የክፍለ ከተማው ስልማ ኮሚቴ አስተባባሪ አቶ ኢብራሂም መሀመድ፣የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የልማት ማህበሩ አባላት እና የክብር እንግዶች ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በሸወ ከተመ በኮልፌ ጎ/ከተመ የስልጤ ላቶ ሴረ /ስልመ/ አይደኜ ኮንፈረንስ በትረሶት ደር ኢትረከባን።
የዲን አቦትቸ የፌድራል፣የከተመ አትንዳዳሪ ዋ የጎ/ከተማይ ጎትለኜ ዋሻሾ ፣የባድ ባሊቅቸ ፣የላቶ ሴራይ ቆራርቸ ዋ የማልነግዳዶ ዋ ሉላ ሉሌ የፌሩይ አመሠብ በትረከበቢ ኤት ባውጄ አያም ኢትሀበዳን።
1 671
+7
ባለፉት ጥቂት አመታት ዋናውን የዝናብ ወቅት ምርት ሳናስተጓጉል የበጋ ስንዴ ልማት ጥረታችንን ለማስፋፋት ችለናል። የዛሬው ምልከታ የስራዎችን ቀጣይነት የተመለከትንበት ነበር። ግብርና ጠንካራ ኢንቨስትመንት ይፈልጋል። በሰብል የምንሸፍነው የመሬታችን ይዞታም ቀስ በቀስ በመጨመር ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ( ዶ/ር)
#prosperity
#aa_prosperity
#aappaddis
1 671
+9
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ንግግሮችና መልዕክቶች የያዘና ከ''መስከረም እስከ መስከረም'' የተሰኘ መጽሃፍ ለንባብ በቃ። መጽሃፉ ላይም ሙያዊ ውይይት በወዳጅነት ፓርክ ተካሂዷል።
በመደረኩም ተማሪዎች ከመጽህፉ የተመረጡ ገጾችን ለውይይት መነሻ ሃሳብ እንዲሆኑ በንባብ ያቀረቡ ሲሆን፣ በተለያዩ የስራ መስኮች የተሰማሩ ተሳታፊዎችም በመጽሃፉ የተሰነዱ መልዕክቶች ላይ ሙያዊ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
መጽሃፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከመስከረም 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ አገር አቀፍ ሁነቶች፣ ዓለም አቀፉ ጉባኤዎችና በዓላት ላይ ያስተላለፏቸውን 91 መልክቶችና ንግግሮች ያያዘ ነው።
1 671
+6
የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ቅርንጫፍ ዛሬ አመታዊ ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ያካሄዳል።
Waldaan Misooma Oromiyaa Damee Kolfee Qaraaniyoo Konfiransii bara 2016 bifa ho'aa ta'een har'a ni geggeeffama.
1 671
የሀገር መገንቢያ መንገድ ትውልድን በማነፅ ውስጥ ያለው ሚስጥር ነው!
መደመር በለውጥ መንገድ ላይ የተወለደ የአተያይ ፓራዳይም ነው። ቁስሎች እንዲጠገኑ፣ ህመሞች እንዲድኑ፣ ችግሮች እንዲፈቱ፣ ፈተናዎች እንዲታለፉ፣ ያለፈውን ጉዟችንን መመልከቻና የቀጣይ ጉዟችን ጠቋሚ፣ አዲስ የእሳቤ ማዕቀፍ ነው።
...የመደመር ነገ_ ትውልድ ነው። እርግጠኛ የሀገር መገንቢያ መንገድም ትውልድን በማነፅ ውስጥ ያለው ሚስጥር ነው። የዛሬ መልካም ውጤቶችና እሴቶች ቀጣይነት የሚረጋገጠው በትውልድ ውስጥ ሲሰርጹ ነው። የመደመር ግብ ሀገር የሚያጠናክር እሴትና ባህል መገንባት ስለሆነ፤ ራሱን ትውልድ የሚግባባበትና የሚነጋገርበት ቋንቋ ለማድረግ ይተልማል። በፍቅር፣ በወንድማማችነትና በኅብር የሚግባባ ትውልድን ለማነጽ።
መደመር የዛሬን ትውልድ አቅም በማሰባሰብ፣ ካለፈው ትውልድ የወረሳቸውን ጥንካሬዎች በማሳደግ፣ እንዲሁም ክፍተቶችን በማረም፣ የቀጣዩን (የመደመር) ትውልድ የምንመለከትበት የሃሳብ መነጽርና የመግባቢያ ሰነዳችን ነው። ይህ የትውልድ ግንባታ እውን እንዲሆን፤ በተገዳዳሪ አፍራሽ እይታዎች (ፓራዳይሞች) ውስጥ የመደመር እይታንና እሴትን ያለማሰለስ በትጋት ማስረፅና ማጠናከርን ይጠይቃል።
(ከመደመር ትውልድ መፅሀፍ ከገፅ V_VI የተወሰደ)
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ /ፅ/ቤት
መልካም የስራ ሳምንት ይሁንላችሁ!
1 671
+7
"ከተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት ልምድ ለመቅሰም ወደ መዲናችን አዲስ አበባ ለመጡ መሪዎች የህጻናት መጫወቻ ስፍራዎችን እና እሁድ ጠዋት ለህጻናት መጫወቻነት በሚል ተለይተው የተዘጉ መንገዶችን ተዘዋውረን አስጎብኝተናቸዋል::
ህጻናት በአካልም ፣ በአእምሮም ሆነ በስነ ልቦና ዳብረው እንዲያድጉ 305 የመጫወቻ ስፍራዎችን እየገነባን የምንገኝ ሲሆን 114 መንገዶችን ዘወትር እሁድ ጠዋት ለትራፊክ ዝግ በማድረግ ህጻናት እንዲጫወቱባቸው በማድረግ ላይ እንገኛለን::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!"
:-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1 671
በህብር ወደ ብልፅግና!!
👉 154 ሚሊዮን ብር ተሰበሰበ!!
"የዛሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ለ #ጽዱኢትዮጵያ ስራችን ሃምሳ ሚሊዮን ብር ኢትዮጵያውያን ሁሉ ልናዋጣ አቅደን ነበር።
ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር ከ154 ሚሊዮን ብር በላይ ማዋጣት ችለናል። ኢትዮጵያን ሲያኮሩ የኖሩ አትሌቶች፣ ስፖርተኞች እና ደጋፊዎች፣ የዘወትር አገልጋይ የታክሲ አሽከርካሪዎች፣ ለኅሊናም ለአካባቢም ንፅህና የሚቀኙ ከያንያን፣ ምሁራን፣ ባለሃብቶች በቴሌቶኑ ስፍራ በመገኘት ላደረጉት አስተዋጽዎ እነሆ ምስጋና።
በመላው አለም ሆነው በዛሬዋ ጀምበር በዲጂታል ቴሌቶኑ የተሳተፉ ከአርባ ሺህ በላይ ዜጎች ለፅዱ ኢትዮጵያ ያላቸው ምኞት መግለጫ የሆነው አስተዋፅዖ በተግባር በየአካባቢው በሚገነቡ የሕዝብ መፀዳጃዎች ይታወሳል።
ይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እና ፅኑ መሰረት ደልድሎ ያወርሳል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው!"
:-ጠ/ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ጽዱኢትዮጵያ
#ፅዱኢትዮጵያ
#itoophiyaa_qulqulluu
#aa_prosperity
#Addisababa
#Ethiopia
1 671
+8
ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና!!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አዲሱን የባሕር ዳር ዓባይ ድልድይ መርቀዋል!
በባሕር ዳር ከተማ በዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባው አዲሱ የዓባይ ድልድይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት ተመርቋል።
ይህ ዘመናዊ ድልድይ የ380 ሜትር ርዝመት እና 43 ሜትር ስፋት ያለው በሁለቱም የመንገድ ክፍል ባለሶስት መስመር የተሽከርካሪ መንገድን ብሎም በጎን የብስክሌት መጋለቢያ መስመር የተሰናዳለት ግዙፍ ድልድይ ነው። የባህርዳር ከተማ ታላቅ መለያ ምልክት እንዲሆን የተገነባው የአባይ ወንዝ ድልድይ የአካባቢውን የኢኮኖሚ እድገት ብሎም የመገናኛ አውታር የሚያነቃቃ ይሆናል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት መሪዎች፣ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
1 671
+2
"ዛሬ በሁሉም ክፍለ ከተሞቻችን እና የከተማ አስተዳደራችን ተቋማት የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ 255 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ እና ለአቅመ ደካሞች በዓሉን በፍሰሀ እንዲያከብሩት ማዕድ አጋርተናል::
ሰርተው ካገኙት ለወገኖቻቸው ማካፈልን ባሕል ላደረጉ የከተማችን ልበ ቀና ባለሀብቶች እና በጎ ፈቃደኞች በከተማ አስተዳደራችን ስም ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ!
መልካም በዓል!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!"
:-ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1 671
ትላንትን ለዛሬ ፥ ዛሬንም ለነገ:- የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባራት!
በአልን ምክንያት በማድረግ የሚፈጠሩ ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪዎችን ለመከላከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ አካባቢዎች ምርቶች ከገበሬዎች በቀጥታ የሚቀርቡበትን እና በተመጣጣኝ ዋጋ የሚሸምቱባቸውን ማዕከላት በማዘጋጀት ለነዋሪዎች እና ሸማቾች ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ሲሆን ፤ ነዋሪዎች ለበአል የሚሆኑ ምርቶችን በአቅራብያቹ በሚገኙ የገበያ ማዕከላት እና የሰንበት ገበያዎች በቀጥታ ከአቅራቢ ማግኘት እንደምትችሉ ለማስታወስ እንወዳለን!
ሰናይ ቀን!
https://fb.watch/rOUFo4Iweq/?mibextid=Nif5oz
1 671
ጠ/ሚ ዐቢይ ከአማራ ክልል ተወካዮች ጋር በክልሉ የገጠሙ ቁልፍ ጉዳዮችን በተመለከተ ውይይት አደረጉ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች ከተውጣጡ ተወካዮች ጋር በክልሉ የገጠሙ ቁልፍ ጉዳዮችን አስመልክተው ውይይት አደረጉ።
በአማራ ክልል ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በመላው የክልሉ አካባቢዎች በብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የተደረገውን ውይይት ተከትሎ ነው ውይይቱ የተካሄደው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው በውይይቱ ወቅት በቀረቡ በርካታ ጉዳዮች ላይ ምላሽ በመስጠት ለጋራ አላማ የጋራ ጥረት የማድረግን አስፈላጊነት በአፅንዖት አንስተናል ብለዋል።
1 671
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ኅብረት የአፍሪካ አጠቃላይ የግብርና ልማት ፕሮግራም መሪነታቸው በፕሮግራሙ በየሁለት አመቱ ከሚቀርበው የግምገማ ሪፖርት አራተኛውን ለኅብረቱ ርዕሳነ ብሔር እና ርዕሳነ መንግሥት አቅርበዋል። የአፍሪካ አጠቃላይ የግብርና ልማት ፕሮግራም ለአፍሪካ የግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ ሀብት ፈጠራ፣ የምግብ ዋስትና እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት፣ የምጣኔ ሀብት እድገት እና ብልጽግና የፓሊሲ ማዕቀፍ ሆኖ የሚያገለግል ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ዕድገት የሪፖርታቸው አካል በማድረግም አቅርበዋል።
As the AU Leader of the Comprehensive Africa Agriculture Development Program, Prime Minister Abiy Ahmed presented the fourth biennial review report of CAADP to the African Union assembly of Heads of State and Government. The Comprehensive Africa Agriculture Development Programme is Africa's policy framework for agricultural transformation, wealth creation, food security and nutrition, economic growth and prosperity for all. The Prime Minister also shared Ethiopia’s progress in the agriculture sector as part of his report.
1 671
"ዛሬ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የብራዚል ኘሬዝዳንት ሉዊዝ ኢናቺዮ ሉላ ደ ሲልቫን ተቀብያለው። በውይይታችንም የግንኙነታችንን ጥልቀት የሚያንፀባርቁ የተለያዩ የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል። ኢትዮጵያ የተከበረው የብሪክስ ቡድን አባል ሆና በመቀላቀሏ ከብራዚል ጋር ያለን ግንኙነት የበለጠ እንደሚጠናከር እንጠብቃለን። የዛሬው ግንኙነታችንም የፀና ወዳጅነት የመገንባት አንድ ርምጃ ነው!"
Dr.Abiy Ahimed Ali
1 671
ዛሬ ጠዋት ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሃፊ ሞሊ ፊ፣ እና የአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል ሀመር ጋር በአህጉራዊ እና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት ለማድረግ ተገናኝተናል።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር )
