uz
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Kanalga Telegram’da o‘tish

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Ko'proq ko'rsatish
2 046
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kun
Ma'lumot yo'q30 kun
Postlar arxiv
*እናት አለሜ* ጉስቁል ያለ ቀየሽ መከራን ታቅፎ ያዘመመ ዳስሽ ሀዘንሽን ሸክፎ ካይንሽ የእምባ ዥረት ሰርክ እየወረደ ተስፋ ከጉያሽ ስር መክኖ እየነጎደ ምን ስቃይሽ በዝቶ ሀዘን ቢወርስሽም የሀዘን ረመጥ ሰርክ ቢፈጅሽም አምናለሁ አንድ ቀን ቀና እንደምትይ ሰንደቅሽ ከፍ ብሎ እንደምትታዪ። ✍Ab 01/07/2014

የመታመምሸ ልክ የታረዘ አንጀትሺን ቲብቲቦ ያሰረሺዉ መታረዝ መራብን እንደምን የቻልሺዉ ከደረቀዉ ጡትሺ ቁረንጮ እየጠባ ምራቁን በገላሺ አርሷ ለጠባ የመታረዙን ልክ የመራብን ጠኔ አይተሺ እንዳላዬ ምታልፊዉ ጨንቆሽ ነዉ ገብቶኛል እማዬ ለተራበዉ ሆደሸ ለሚፈሰዉ እንባሸ ለጨነቀዉ ልብሸ አንቺ ምኑን አዉቆሸ ምክኒያቱሱ መቺ ገብቶሸ ገሎሸ መኖር ሚመኝ የወሬ አለቃዉ ያ እሩቅ ያለዉ የማያዉቅሸ ልጂሸ ደልቶት የሚኖርዉ ብላቴና ልጂሸን እንዲያለቅስ ላረገዉ ማይተዉሸ አምላክሺ ቀድሞ ይግደልና እንባሺን ያብሰዉ በራማዉም ይሰማሸ መልሱንም ያፍጥነዉ።።።።ተፃፈ Fanta

ለሠላም ዘምሩ ✨✨✨✨✨ የሀገሬ ፈተና - አትስገዱ ዛቻ በምእመኑ ጥሪ - አትሮጡም ዛቻ የመንግስቱ አቋም - እኔ ያልኩት ብቻ ኑሮ ተወደደ - ዘይትም ጣራ ነካ ታድያ ምን ያደርጋል - ሙዝ በዳቦ እንካ ደሞ ሌላ ጊዜ... በአባቶች ችልታ ምናገባኝ ስሜት ፖሊሶች ሲሰርቁ አባቶች ቁጭ ብለው ልጆች ሲያስታርቁ ባዋቂው ዝምታ - ባላዋቂው ወሬ ሃገር የሚያክል ነገር እምነት የሚያክል ነገር ሆነ አንድ ፍሬ የሃገሬ ሠዎች - ለነብሳችሁ ኑሩ መልካም ፍሬን ዝሩ በብሄር ከፋፍሎ - ለፀብ ክመሯሯጥ ለሠላም ዘምሩ:: ✍️-ዳዊት(የለትዬ ልጅ) @DevZHab

ምሬት😩 ሀገሬ ከአራቱ አቅጣጫዎችሽ በአንዱ በኩል ሀዘን በዝቶ ልባችን ሲቆስል እንባን እያነባን 😭ደም እያፈሰስን በወገን እጦት በናፍቆት ተገረፍን እሱ አልበቃ ብሎ ሀብት ጎደለብን እጅጉን ተጠማን ፍቅር ሰላምን ተራብን ሳቃችን ተሰወረ በሩቁም ተቀበረ ኑሮም ተከመረ እራሱን አናረ😒 እየን ፈጣሪያችን🙏🙏 ውጣችን አረረ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ።።።።።።።።።።።።። ✍B.T

ወልደሻል ወልዳለች ኢትዮጵያ ወልዳለች እናቱ፣ አርቆ አሳቢ አንደበተ ርቱ። እዉነትም ወልዳለች መልካሙን ከመጥፎ አነጣጥሮ የሚያይ፣ ክፉውን ከደጉ ለይቶ የሚያሳይ። እውነትም ወልዳለች በዘር በሀይማኖት ከፋፍሎ የማያይ ሀሳቡ ወጥነው ውጥኑም አንድነት፣ ግቡም ያገር አድገት። እዉነትም ወልዳለች የነጭ ትርፍራፊ ከቶ የማያምረው፣ ያገሩን እንጀራ ጋግሮ የሚያሳይ ነው። እውነትም ወልደሻል እውነትም አርግዘሽ ጡትሽን አጥብተሽ በጀርባሽ አዝለሻል፣ እምዬ ኢትዮጵያ የወለድሽው ልጅሽ ዛሬ ደረሶልሻል። ምህረት ወርቁ 2/8/2014

1⃣

2⃣

3⃣

ሊጀምር ነው፨

ውድ የቻናላችን አባሎች የውድድር ግጥሞቻችሁን እስከ ምሽት 3:00 ድረስ እንጠብቃለን። በ ስንኝ ቋጠሮ ብቻ @gitmv

ሰላም ውድ የ ስንኝ ቋጠሮ አባሎች እንዴት ቆያችሁ? እሁድ ማታ ድንቅ የግጥም ውድድር ይኖረናል ስለሆነም ከታች ያሉ መስፈርቶችን በመከተል እንድትወዳደሩ አሳስባለው!! 👉"ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ችግር የሚገልፅ እና የመፍትሄ ሃሳብንም ጭምር የያዘ ግጥም" 👉 ከስምንት እስከ አስር ስንኝ 👉 60 like ቀድሞ የሞላ 25 birr Card ይሸለማል 👉ቀጥሎ ሁለተኛ የወጣ 15 birr Card 👉 ሶስተኛ ላይ 60 like የደረሰ 10 birr Card ይሸለማል ከ እሁድ ጠዋት ጀምሮ ግጥሞቻችሁን @abebekasu እና @mogea ላይ ላኩልን እስከ እሁድ ምሽት 3:00 ድረስ ግጥሞቻችሁን ላኩልን ልክ ሶስት ሰአት እንደሞላ ግጥም መቀበል እናቆማለን ስለዚህ ተሳተፉ ግጥም ለመላክ 👉 @mogea @abebekasu ይጠቀሙ!! የግጥም ችሎታችሁንም አሳድጉ በተጨማሪ ተወዳድራችሁ አሸንፉ ተሸለሙ !! በስንኝ ቋጠሮ ብቻ!

ሰላም ውድ የ ስንኝ ቋጠሮ አባሎች እንዴት ቆያችሁ? እሁድ ማታ ድንቅ የግጥም ውድድር ይኖረናል ስለሆነም ከታች ያሉ መስፈርቶችን በመከተል እንድትወዳደሩ አሳስባለው!! 👉 ርዕስ "ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ችግር የሚገልፅ እና የመፍትሄ ሃሳብንም ጭምር የያዘ" 👉 ከ ከስምን ከስምንት እስከ አስር ስንኝ 👉 60 like ቀድሞ የሞላ 25 birr Card ይሸለማል 👉ቀጥሎ ሁለተኛ የወጣ 15 birr Card 👉 ሶስተኛ ላይ 60 like የደረሰ 10 birr Card ይሸለማል ከ እሁድ ጠዋት ጀምሮ ግጥሞቻችሁን @abebekasu እና @mogea ላይ ላኩልን እስከ ምሽት 3:00 ድረስ ግጥሞቻችሁን ላኩልን ልክ ሶስት ሰአት እንደሞላ ግጥም መቀበል እናቆማለን ስለዚህ ተሳተፉ ግጥም ለመላክ 👉 @mogea @abebekasu ይጠቀሙ!!

እሁድ ምሽት 3:00 የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…👍 አይኑር የምትሉ 👎

ነገ ማታ 3:00 የግጥም ውድድር ይኑር የምትሉ…👍 አይኑር የምትሉ 👎

ትርታ የሶስት ሆሂት ጥይት የአንድ ቃል ቃታ የአንድ ልብ ድምፀት ስልተ-ምት ድምድምታ በናፍቆት ድንቅፍቅፍ በ'ፍቅር በትዝታ ቢገኝ ያጡት ወዳጅ ባልጠበቁት ቦታ ከደስታ በላይ ይጎላል ትርታ። @ *** 18

"ዘቅዝቀው ሰቅለውት ፣ የዓለሙን ካርታ እግር ነው ሚታየው ፣ በጭንቅላት ቦታ። (በረከት በላይነህ) ።።።።።። አለሙ በሙሉ የአለምን ካርታ ፣ ዘቅዝቆ ቢያዋቅር እግር አይታየኝም ጭንቅላት ለማየት ፣ ስለማቀረቅር ። (በላይ በቀለ ወያ) &&&&&&&$&&&&&& አለሙ በሙሉ የአለሙን ካርታ ቢያዋቅር ዘቅዝቆ እግር ሁሉ ቢታይ አናት ከስር ወድቆ እግር ያው እግር ነው ቢሰቀልም ልቆ። @*** 18 @gitmv 👈

#ኧረ_አምሳለ! (ምልዕቲ ኪሮስ ኃይሌሥላሴ) ሰዉ በዘመን ጅረት................... ዘመን በሠዉ ጀርባ እንደገሠገሠ ይኸዉልሽ እንግዲ ክፉ ቀን ደረሰ... ይኸዉ እንዲ ሆነ: አንች ስትሄጅ;- ፀሀይ ጠዋት ቀረች ጨረቃ አኮረፈች ሰማይ አለቀሰ መሬት ተቆረሰ ጨዋታ ፈረሰ.... አንች ሳትኖሪ:- አኩኩሉ አይነጋም... በሰኞ ማክሰኞ ዉብ ቤት አይገዛም ... በሌባና ፖሊስ ባባሮሽ ጨዋታም... እንደሮጠ ቀርቷል ማንም ሰዉ አልመጣም.... ህፃናቱ ከቦ አሁንም ቁጭ ብሏል... መሐረቤን ብሎ አንድ ልጅ ይዞራል... ህፃናቱ ከቦ ቁጭ ብሏል አሁንም... መሃረቡን ያየም አየሁኝ አይልም ... ብጫቂ መሐረብ መች ሆነና ቁቡ... ነገረ ጨዋታዉ አንች ነሽ አሳቡ.... ኧረ አምሣለ.... ኧረ ሆይ... ጨዋታ ለዛ አጣ አንዴ ብቅ በይ.... የህፃናት ተረት ከግማሹ አለቀ... ትመጣለች ብሎ አንቺን የጠበቀ.... ቤትና ሃገር ቤት የሚል ሃሳብ መክኖ... የሀገሪቱ ጉብል ቀረ ተበትኖ... እንካ ስላንትያ እንቆቅልሻቸዉ... ሳይፈታ ቀረ እርቀሽባቸዉ.... 'ቢበስል ባይበስል ትመጭ ይመስል' ብለን ያሟረት ነዉ.... ለካስ አንች ላይ ነዉ.... ኧረ አምሣለ ኧረ ምነዉ... ደጅሽ የተከልሽዉ ምን አይነት እንኮይ ነዉ.... ያዉም በአኩኩሉ በዉሸት ጨዋታ... እንደተደበቀች እሷ ብቻ ቀርታ.... ምድር በትካዜ ሰማይ በመከራ... አለ እስካሁን ድረስ እምባዉን ሲያዘራ..... የምሥኪኑ ደሀ አገዳዉ አሽቶ... ይሄዉ ባንች ምክንያት ዝናቡ በርትቶ.... የቀየዉ ገበሬ እህል ተበላሸ.... ኧረ አምሳለ እያለ በነጋ በመሸ.,. ያገር ሽማግሌ ያገሪቱን ዳኛ... ስልጣኑን ወሠደዉ ነጠቀዉ ቀማኛ.,. ፍርድ ተጏደለ... ድሃ ተበደለ... መነኩሴም ያለቅሳል ኧረ አምሣለ እያለ ..... ኧረ አምሣለ ኧረ ሆይ.... ያሳደገሽ መንደር አይናፍቅም ወይ....? የእናቶች እህታ የህፃናት እምባ.... ወዴት አደረሰሽ ወዴት ይዞሽ ገባ.... የእረኛ እሮሮ... ያዝማሪ ከበሮ... የገጣሚ ዋይታ... ያጋፋሪ እምቢልታ.... የዋሽንቱ ቅኝት ዜማና ምታቸዉ... ኧረ አምሣለ ሆነ አፍ መፍቻ ቋንቋቸዉ.... አለመምጣት አለ... አለመምጣት አለ አለመተያየት... ባንድ አምሣለ ናፍቆት ግጥም ብሎ መቅረት.... ስለእማምላክ ቢሉት አንጀቱ ሚራራ... በራብሽ ከች የሚል ከጭንቅሽ 'ሚጋራ.... ሀገር-እግር የለዉም ወጥቶ አይፈልግሽም... እርግማኑም ክፋ ላንችም አይቀናሽም... ወንዝና ተራራም ወገን አይሆንሽም.... ....... እናም... ሠዉና ቀየዉን እያሠናሠነ... የጉብሉን መዝሙር አጣፍጦ የከየነ.... ሰዉ ማለት... ሰዉ ማለት ... ሰዉ ማለት ሃገር ነዉ ባይልም በቃሉ.... ይግባሽ አንድ ሚሥጥር - ሰዉን ከሠዉ ብቻ የመቀላቀሉ::

ጨረቃ ሳያት ትስቃለች ደስታዋ ልዩ ነው፡ የብርሀኗም ፀዳል ለሰማይ ውበት ነው። በከዋክብት መሀል ታጅባ አሸብርቃ ሳያት የምታየኝ በፈገግታ ደምቃ። ንጋቱ እስከሚመሽ ጣር ይሆንብኛል የውስጤን ሳዋያት ሰላም ይሰማኛል ለሰው የፈራሁት ለሷ ይቀለኛል። አንዳንዴ ስጠፊ ልቤ ይሸበራል፣ የደመና ጭጋግ መቶ ሲሸፍንሽ ማረፊያ እንዳጣች ወፍ አይኔ ይንከራተታል። ምህረት ወርቁ 13/4/2014❤️

*ኖረሺኝ ለሌለሽ፤ኖሬልሽ ለሌለሁ* ጥያቄዬ ነች መልስ የማላገኝላት ለኔ ባላት መውደድ ልክ ስሜቷን ማልረዳላት አብሮ በማሳለፍ ውስጥ ፍፁም ማታውቀኝ፤እኔም ማላውቃት ህመሟን ማልታመመው፤ህመሜም ከቶ ማይገባት አብረን ሆነን ባለመሆን ውስጥ የማታገኘኝ የማላገኛት። ✍Ab

Abe