cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Debreselam Catholic School 9_1#

Online class

Ko'proq ko'rsatish
Advertising posts
1 744Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-2730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

ሰላም የተፈታኝ ተማሪ ወላጆች! ተማሪዎቻችን በሰላም እየተፈተኑ ስለሆነ ሃሳብ አይግባችሁ! የሁላችሁንም ስልክ ማስተናገድ ስለማይቻል የቴሌግራም ቻናሉን ብንጠቀም ጥሩ ነው!
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም የተፈታኝ ተማሪ ወላጆች ሁሉም ተማሪዎቻችን ሙሉ መረጋጋት በሰፈነበት ሁለቱንም ፈተናዎች(እንግሊዝኛና ሂሳብን)በድል አጠናቀዋል! ከአንዲት ተማሪያችን ጊዜያዊ የጨጓራ ህመም ስሜት ውጭ(እሷም ፈተናን በሚያስተጓጉል ደረጃ ያልደረሰ) ሌሎች በሙሉ ጤንነትና ስነልቦና ላይ ውለው ወደእራት መግባታቸውን አረጋግጠን ወጥተናል! ለተማሪዎቻችን መልካም ፈተናን አሁንም እንመኛለን
Hammasini ko'rsatish...
ሠላም! ዛሬ በ 25/11/2015 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ሁለቱንም ፈተናዎች በሠላም አጠናቀዋል። የሌሎች ወረዳ እና የእኛን ተማሪዎች በአካል አግኝተን አነጋግረናቸዋል። የሚገርም የመረጋጋት ስነ ልቦና ተማሪዎቻችን ላይ ይታይባቸው ነበር። ነገር ግን ጊዜ አጠረን፣ ማታ ማታ ዶርም ለማንበብ ስለማይመች አማራጭ የጥናት ቦታ ቢኖር፤ የሚል ጥያቄ አቅርበውልናል። እኛም ለግቢው አመራሮች ያደረስን ሲሆን ላይብራሪ መፈተኛ ሆኖ የሚያገለግል በመሆኑ የማይቻል ሲሆን፤ ስማርት ቦርድ ያለባቸው ክፍሎችም ኮምፒውተርና የመሳሰለት ማቴሪያሎች ያሉበት በመሆኑ ቁልፍ መሆኑን ተረድተናል። ይሁን እንጅ ከአቶ ዮሃንስ(+251 98 821 7215) ጋር በመነጋገር ለነገ የሚከፈቱ ከፍሎች ሊያመቻችልን ስለተነጋገርን መጠቀም የምንችል መሆኑን ገልጸውልናል። ዛሬ ትኩረት በመስጠት ተማሪዎቻቸውን ግቢ ውስጥ ገብተው ያበረታቱ ርዕሰ መምህራን:- 1=አቶ ሙሉ የአንገረብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር፤ 2=አቶ ሞላ አበበ የዋላጅ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር፤ 3=አቶ ተስፋሁን የደ/ሰ/ቅ/ማ/ካ/ 2ኛ ደ/ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር፤ 4=አቶ ሃብቱ የዕድገት ፈለግ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር፤  ሲሆኑ ከላይ የተገለጹትን ጥያቄዎች አደራጅተው ያቀረቡም እነርሱ ናቸው። 4ቱንም ርዕሰ መምህራን በተማሪዎች ስነምግባርና ውጤት ላይ ተደማሪ ነገር ለማስመዝገብ ለምታደርጉት ጥረት መምሪያው ማመስገን ይፈልጋል። ይህን ጉዳይ ቀላል አድርጎ ማየት ተገቢ አይደለም። ጠቀሜታው በብዙ መልኩ ከፍ ያለ ነውና ቀሪዎቻችሁ ካበረታታችሁ አይቀር ፈተናው ሲጠናቀቅ ሳይሆን ከወዲሁ በጊዜ ተገኝታችሁ እንድታበረታቷቸው መልዕክታችን ነው። እናመሰግናለን!!!
Hammasini ko'rsatish...
የእንግሊዝኛ ጥያቄዎችን በዚህ መልክ ሰብስበናቸዋል! ተማሪዎች በዚህ ላይ እየተጨቃጨቁ በቀጣይ ፈተናዎች ላይ ጫና እንዳያሳድር ስለፈለግን!!! ቀጥሎ ሂሳብንም እንሰበስባለን! አርብ እንዳለቀ እንመልስላቸዋለን!!
Hammasini ko'rsatish...
ተማሪዎቻችን በዚህ መልክ ወደፈተና አዳራሽ እየገቡ ይገኛሉ! የስነልቦና ዝግጅታቸው በጣም ጥሩ ላይ ናቸው:: ቀሪውን እግዚአብሔር ያግዛቸው! የእንግሊዝኛ ፈተና 3:00 ይጀምራል 5:00ያልቃል! እስካሁን የከፋ ችግር አልገጠመንም!!!! ለልጆቻችን መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው መልካሙን እንመኝላቸው
Hammasini ko'rsatish...
ለሁሉም የዩኒቨርስቲ መግቢያ አስፈታኝ ወላጆች ልጆቻችን ሁሉም ሰላም መሆናቸውን በአካል ተገኝተን አረጋግጠናል! የገጠመ ምንም ነገር የለም! በእየቤታችሁ በፆለት ብቻ አግዟቸው!
Hammasini ko'rsatish...
ሰላም ወላጆች እንዴት አደራችሁ? ዩኒቨርስቲ የገቡ ተፈታኝ ተማሪዎችን ማግኜት ከፈለጋችሁ ዛሬ ሰኞ 3 ስዓት ላይ ወደእኔ መደወል ትችላላችሁ!
Hammasini ko'rsatish...