cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ዝክረ ብሒለ አበው

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
341
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

የሕገ ወጡ ሲኖዶስ ቡድን አማካሪ የተናገረው... "አንዴ በይቅርታ አንዴ በክህደት አድክሟቸው። ዕረፍት ንሧቸው። ሕዝቡን ተስፋ አስቆርጡት፤ ከዚያም ሕዝቡና አባቶች ይነጣጠላሉ። አንድነት ያጣሉ። ከዚያ በኋላ ሲኖዶሱም ፈውሱም ንጉሱም የእናንተ ይሆናል። በመጀመሪያ ሕዝቡንና አባቶችን ነጥሉ። ከዚያም በመጨቃጨቅ፣ በመካሰስ፣ በየአደባባዩ በመፈራረጅ በሰው ሕሊና ውስጥ የጵጵስናን ዋጋ አሳንሡት። በስተመጨረሻም መምታት የምንፈልገው ቅኔ ቤት ይመታል። መፍረስ የሚፈለገው ቅኔም ይፈርሳል። ሁሉም ቀላል የሚሆነው ከዚያ በኋላ ነው"
Hammasini ko'rsatish...
እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነወ። ከፊት ይልቅ አሁን ልንተጋ ይገባል አባቶች አባት ሆነውን ከፊታችን ቆመው እግዚአብሔር ለፀሎታችን መልስ ሰቶናል። እኛም በሁሉ ነገር ነቅተን እንኑር
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
#የካቲት_2_ዕረፍቱ_ለርዕሰ_ባህታውያን_አባ_ጳውሊ ይህም የበርሃው መልአክ፤ የባህታውያን ሁሉ አለቃቸው የሆነ አባ ጳውሊ ነው። ስርዓተ ብሕትውና በጳውሊ ስርዓተ ምንኩስና በእንጦኒ ተጀምሯል ይላል፤ ጳውሊ አባቱ ባለጸጋ ነበር ሲሞት ለታላቅ ወንድሙ በጴጥሮስ እጅ አድርጎ ኃላ አካለ መጠን ሲያደርስ ከፍለህ ስጠው ብሎት ተናዞ አረፈ፤ አባ ጳውሊ አካለ መጠን ሲደርስ “ ደረስሁ ልጅ ፈላሁ ጠጅ ” የአባቴን ገንዘብ ከፍለህ ስጠኝ አለው አይሆንም አልሰጥህም አለው ምነው ቢለው ልጅ ነህ ታጠፋዋለህ ብዬ ነው ይለዋል አላጠፋውም ስጠኝ ይለዋል ግድማ ካልኸኝ ብሎ ብዙውን አስቀርቶ ጥቂቱን፤ መልካሙን አስቀርቶ ተራ ተራውን ሰጠው አባ ጳውሊ በዚህ ተበሳጭቶ ዳኛ ጋር ሄደ በመንገድ ላይ አንድ ባለጸጋ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት አየ አባቴ ባለጸጋ ነበር ሞተ ይሄም ባለጸጋ ነበር ሞተ እኔስ ነገ እሞት የለምን ብሎ ወደ ወንድሙ ተመልሶ ወንድሜ ገንዘቡ ላንተ ይሁን ትቼልሃለው ብሎ ከቤት ወጠ፤ መጀመሪያ ለ 3 ቀን ከመቃብር ቤት ገብቶ ጸለየ በ3ኛው ቀን ከሰማይ ግማሽ ህብስት ወረደለት፤ ገረመው፤ ፈጽሞ ሳይለዩ እንዲህ ከሆነማ ፈጽሞ ቢለዩማ እንደምን ያለ ተአምር በተደረገ ብሎ አናብስት አናምርት አካይስት አቃርብት ካሉበት ነቃዐ ማይ ልምላሜ ዕፅ ከሌለበት ድሩክ ለተአቅቦ ይለዋል ዘር ተክል ከማይገኝበት ከጽኑ በርሃ ገባ፤ የሰው ፊት ሳያይ ለ 80 ዓመት በተጋድሎ ኖሯል። ምግቡን ግማሽ ህብስት በየቀኑ የሚያመጣለት ቁራ ነበር። የእረፍቱ ቀኑ ሲደርስ ከአባ እንጦንስ ጋር በእግዚያብሔር ፈቃድ ተገናኝተው ብዙ ነገር ተጨዋወቱ በተለይም በኃለኛው ዘመን ስለሚነሱት መነኮሳትና፤ ግብጽ በሙስሊሞች እንደምትወረር ብዙ ምስጢር አወሩ ብዙ ትንቢትም ተናገሩ። ከዚህ በኃላ አባ ጳውሊ አስኬማ መልአክ አምጣልኝ ብሎ ይልከዋል፤ አባ እንጦስ ወደ ገዳሙ ሄደ የ 2 ቀን ጎዳና ነው ሲመለስ በርሃው ላይ ሰማያውያን መልአክ ሰፍረውበት ሲዘምሩ ሲያመሰግኑ አየ፤ ልብን የሚመስጥ የእጣን መዓዛም አሸተተ፤ ምንድር ነው ? ብሎ አንዱን መልአክ ይጠይቀዋል አባ ጳውሊ ሞቶ ነፍሱን እያሳረግን ነው ይለዋል ይሄን አስኬማ አምጣልኝ ብሎኝ ነበር ምን ላድርገው ? ይለዋል፤ ጸሎት አድርሰህ አድርግለት፤ ደግሞም መቃብሩን የሚቆፍሩ አንበሶች ይመጣሉ ቦታውን ለክተህ ስጣቸው አለው፤ ወደ ገዳሙ ሲገባ እጁን መስቀልያ እንደዘረጋ ሞቶ አገኘው የሚጸልይ እንጂ የሞተ አይመስልም ነበር አስኬማውን አድርጎለት ሲያበቃ ከራስጌው ቆሞ ኤልያስ ልበልህ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ልበልህ እያለ አለቀሰለት፤ ሁለት አንበሶች መቃብሩን ቆፈሩለት ገንዞ ቀበረው። 80 ዘመን ሙሉ ለብሶት የኖረው የሰሌን ልብስ ነበረችው ወስዶ ለሊቀ ጳጳሱ ለአባ አትናቴዎስ ሰጠው፤ በዚህች ልብስ አባ አትናቴዎስ ብዙ ተአምራትን ሰረቶበታል ይልቁንም ሙት አስነስቶበታል። በነገራችን ላይ የዚህ አባት ገድሉ በስፋት ከመጻፉ ባሻገር ግብጻውያን ፊልም ሰርተውለታል ይህን ፊልም ማህበረ ቅዱሳን ጥሩ አድርገው ወደ አማርኛ ተርጉመውታል። የበረታ ገድሉን ያንብብ የደከመው ፊልሙን ይመልከት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባ ጳውሊ በረከት ያሳትፈን። አሜን!!!
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
#በሦስት_ቀን_ጾም_ጸሎት_የሕዝበ_እስራኤላውያን_የሞት_አዋጅ_ተቀለበሰ። ነገሩ እንዲህ ነው :- በፋርስ ንጉሥ አርጤክስስ ዘመን እስራኤላውያን በምርኮኝነት በፋርስ ይኖሩ ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን የፋርስ ንጉሥ አርጤክስስ በቤተመንግሥቱ ታላቅ ግብዣ አደረገ፡፡ በግብዣውም ላይ ባለሥልጣኖች፣ ባለሟሎች እና አገልጋዮች ተገኝተው እየበሉ እና እየጠጡ እጅግ በጣም ይደሰቱ ነበር፡፡ ነገር ግን በግብዣው ላይ የንጉሡ ሚስት ንግሥት እስጢን ስላልተገኘች ብዙ ሰዎች አለመኖሯን ይጠይቁ ስለነበር ንጉሡ ንግሥት እስጢን የንግሥት ዘውድ ደፍታ እንዲሁም በከበሩ ጌጣጌጦች አሸብርቃ በፍጥነት ወደ ግብዣው እንድትመጣ ታማኝ አገልጋዮቹን ላከ፡፡ ንግሥት እስጢን ግን በግብዣው ላይ እንደማትገኝ እንቢታዋን በመግለጿ ንጉሥ አርጤክስስ በጣም ተናደደ፡፡ ንጉሡ ከአማካሪዎቹ ጋር በመሆን ብዙ ከመከረ በኋላ እስጢን ንግሥት መሆኗ እንዲቀር እና በምትኳ ንግሥት የምትሆን ሴት እንድትፈለግ ተሰማማ፡፡ በንጉሡ ትእዛዝ መሠረት በፋርስ ይኖሩ የነበሩ መልከመልካም ሴቶች ከየሥፍራው ተሰብስበው ለምርጫ ቀረቡ፡፡ ከእነዚህ መልከመልካም እና ቆንጆ ሴቶች መካከል አስቴር አንዷ ነበረች፡፡ አስቴር በፋርስ በምርኮ ከሚኖሩ እስራኤላውያን መካከል አንዷ ስትሆን እናት እና አባት ስላልነበራት አጎቷ መርዶክዮስ ያሳድጋት ነበር፡፡ አጎቷ መርዶክዮስ የንጉሡን ዓዋጅ እንደሰማ አስቴር በጣም ቆንጆ ሴት ሰለነበረች በንጉሡ እንድትመረጥ አዘጋጃት፡፡ ከዐሥራ ሁለት ወራት ዝግጅት በኋላ ቆነጃጅቱ በንጉሥ አርጤክስስ ፊት ቀረቡ፡፡ ከቆነጃጅቱ መካከል አስቴር በንጉሡ እና በሚያዩአት ሰዎች ሁሉ ፊት ሞገስን በማግኘቷ አንደኛ ሆና ተመረጠች፡፡ ከዛን ዕለት ጀምሮ አስቴር የፋርስ ንግሥት ሆና የንግሥና ዘውድ ደፋች፡፡ ንጉሥ አርጤክስስ ቆንጆዋን እና ተወዳጅ የሆነችውን አስቴርን በማግኙቱ በጣም ተደስቶ ለአስቴር ክብር ታላቅ በዓል አድርጎ ሕዝቡን ጋበዘ፡፡ አስቴር በሰው ሀገር በምርኮ የምትኖር ሴት ስትሆን እግዚአብሔር ሞገስና ውበት ሆኗት የንጉሥ ሚስት ሆነች፡፡ በፋርስ መንግሥት ላይ እግዚአብሔር ንግሥት አድርጎ ሾማት፡፡ በንጉሥ አርጤክስስ ዘመን በፋርስ መንግሥት ላይ የተሾመ ሐማ የሚባል ባለሥልጣን ነበር፡፡ ሐማ ከፍተኛ ባለሥልጣንና የንጉሥ አርጤክስስ የቅርብ ሰው ሰለነበረ ወደ ቤተመንግሥት ሲገባ እና ሲወጣ ብዙ ሕዝብ ይሰግድለት ነበር፡፡ ነገር ግን የንግሥት አስቴር አጎት መርደክዮስ ለሐማ እንደማይሰግድ እና እይሁዳዊ እንደሆነ የሐማ የቅርብ ሰዎች ክፉ ነገር ስለተናገሩበት ሐማ በጣም ተቆጣ፡፡ ሐማ ንጉሥ አርጤክስስን በውሸት አሳስቶ በፋርስ መንግሥት ግዛት ውስጥ ያሉ አይሁዳውያን ሁሉ እንዲገደሉ በንጉሡ ማኅተም ዓዋጅ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ብዙ አይሁዳውያን በሐማ ተንኮልና በዓዋጁ በጣም አዘኑ፡፡ ነገር ግን መርዶክዮስ እግዚብሔር አስቴርን ንግሥት ያደረጋት ለዚህ ቀን እንደሆነ በማመን እና በአስቴር ምክንያት የሞት ዓዋጅ እንደሚቀየር ተስፋ በማድረግ ወደ አስቴር መልእክት ላከ፡፡ ንግሥት አስቴር እና ሕዝቡ ሦስት ቀን እና ሦስት ለሊት በጾም እና በጸሎት እግዚአብሔርን ከጠየቁ በኋላ አስቴር ወደ ንጉሥ አርጤክስስ ገብታ ሁኔታውን አስረዳችው፡፡ ንጉሡም አስቴር ሰለ ሕዝቧ ያቀረበችውን ልመና እና ምልጃ ተቀብሎ የሐማን ዓዋጅ ሻረ፡፡ ሐማ ንጉሥ አርጤክስስን በሐሰት በማሳሳቱ ሞት ተፈረደበት፡፡ አይሁድ በንግሥት አስቴር ምክንያት እግዚአብሔር የሞቱን ዓዋጅ በሕይወት እንደየቀረው፣ ሐማም እንደ ተፈረደበት ዜናውን ሲሰሙ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ በምርኮ ይኖሩ ለነበሩ አይሁዳውያን ንግሥት አስቴርን ከሞት እንዲያመልጡ እግዚአብሔር ምክንያት አድርጓታል በዚህ ትምህርት አውቃችኋል፡፡ ሕዝቡ በፍጹም ልባቸው በመታመን እግዚአብሔርን በጾም እና ጸሎት ተስፋ በማድረጋቸው በአስቴር ልመና እንዲሁም ምልጃ የሞት ዓዋጅ ሊየቀር ችሏል፡፡ ጾም ጸሎታችንን በቸርነቱ ተቀብሎ የእኛንም የሞት አዋጅ ያርቅልን!!!
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
#ጥር_30_ቅድስት_ሶፍያና_ሦስት_ልጆቿ_በሰማዕትነት_ዐረፉ ። ይኽችም ቅድስት ሶፍያ ከአንጾኪያ ከከበሩ ወገኖች የተገኘች ናት፡፡ የልጆቿ ስም ጲስጢስ፣ አላጲስና አጋጲስ ነው፡፡ የስማቸውም ትርጓሜ በቅደም ተከተላቸው መሠረት ‹‹ሃይማኖት፣ ተስፋ፣ ፍቅር›› የሚል ነው፡፡ ዕድሜአቸውም 12፣ 10 እና 9 ነው፡፡ የራሷ የሶፍያ የስሟ ትርጓሜ ደግሞ ጥበብ ማለት ነው፡፡ ልጆቿንም ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ እግዚአብሔርን መፍራትንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማረቻቸው፡፡ የልጆቹም ምግባር ሃይማኖታቸው በከሃዲው የሮም ንጉሥ በአርያኖስ ዘንድ ስለተሰማ ንጉሡ ጭፍሮቹን ልኮ አስመጣቸው፡፡ እናታቸውም ‹‹ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ፣ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሆናችሁ ወደ ሰማያዊው ሠርግ እንዲትገቡ ጠንክሩ…›› እያለች ትመክራቸውና ታጽናናቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ እናታቸው ይዛ ወደ ንጉሡ አቀረበቻቸው፡፡ ንጉሡም ታላቂቱን የ12 ዓመቷን ጲስጢስን ‹‹ስታድጊ ከመንግሥቴ ታላላቅ ባለሥልጣናት ውስጥ ከአንዱ ጋር አጋባሻለሁ፣ ብዙ ስጦታንም እሰጥሻለሁ፡፡ አሁን ግን ለጣዖቴ ለአጵሎን ስገጂ›› እያለ ሊደልላት ሞከረ፡፡ እርሷም ንጉሡንና የረከሱ አማልክቶቹን ረገመቻቸው፡፡ ንጉሡም አማልክቶቹንና እርሱን ስለረገመች ቅድስት ጲስጢስን እጅግ በጽኑ ሥቃዮች አሠቃያት፡፡ በብረት ዘንግ አስደበደባት፤ ጡቶቿን አስቆረጣቸው፤ በብረት ምጣድ አድርጎ ከሥር እሳት አስነደደባት ነገር ግን በእሳቱ ውስጥ ሆና ስትጸልይ እሳቱ እንደጠዋት ጤዛ ቀዝቃዛ ሆነ፡፡ በዙሪያዋ ያሉና ይህንን ተአምር ያዩ ሰዎች ሁሉ ‹‹በዚህች ብላቴና አምላክ እናምናለን›› ብለው ጮኹ፡፡ ወዲያውም ራሶቻቸውን ቆረጧቸውና በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ከዚህም በኋላ የቅድስት ጲስጢስ አንገት ይቆርጡት ዘንድ ንጉሡ አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም አንገቷን ሰየፏትና ሰማዕትነቷን በድል ፈጽማ የክብር አክሊልን ተቀዳጀች፡፡ እናቷም ሥጋዋን አንሥታ ወሰደች፡፡ አሁንም ንጉሡ በሁለተኛይቱ ልጅ በቅድስት አላጲስ ላይም እንዲሁ ተመሳሳይ ሥቃይ አደረሰባትና አንገቷን አስቆረጠው፡፡ አሁንም እናቷ ቅድስት ሶፍያ ሥጋዋን አንሥታ ከወሰደች በኋላ እንዳትፈራ በማሰብ ስለ 9 ዓመቷ ታናሽ ልጇ ስለ አጋጲስ ጸለየች፤ አጽናናቻትም፡፡ ወዲያውም አጋጲስን አንስተው በመንኰራኩር ውስጥ ጨመሯት፡፡ የታዘዘ መልአክም መንኰራኩሩን ሰበረውና በሰላም ወጣች፡፡ ዳግመኛም ነበልባሉ እስከ ሰማይ የሚደርስ እሳትንም አንድደው በዚያ ይጨምሯት ዘንድ ንጉሡ አዘዘ፡፡ ቅድስት አጋጲስም በመስቀል ምልክት አማትባ ወደ እሳቱ ተወርውራ ገባች፡፡ ጌታችንም መልአኩን ልኮ እሳቱ እንደ ውርጭ አቀዘቀዘላት፡፡ በዚያ ተሰብስበው የነበሩ ሰዎችም ሁለት ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሰዎች በልብሳቸው ሲጋርዷት አይተው እጅግ አደነቁ፡፡ በጌታችንም ስም አምነው ምስክንርነታቸውን ሲሰጡ ራሶቻውን በሰይፍ ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ በመጨረሻም የቅድስት አጋጲስንም አንገቷን በሰይፍ ቆርጠው ሰማዕትነቷን በድል ፈጽማ አክሊልን እንድትቀዳጅ አደረጓት፡፡ የከበረች ሶፍያም የሦስት ልጆቿን ሥጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸውና ከከተማው ውጭ ወስዳ ቀበረቻቸው፡፡ በ3ኛውም ቀን መቃብራቸው ላይ ሄዳ በማልቀስ ነፍሷን ይወስድ ዘንድ ጌታችንን ለመነችው፡፡ ጌታችንም ልመናዋን ሰምቶ ጥር 30 ቀን ነፍሷን ወሰዳት፡፡ ምእመናንም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበሯት፡፡ ከሃዲው ንጉሡ ግን በተአምራት ወዲያው ዐይኖቹ ጠፍተው ሥጋው ሁሉ ተሰነጣጠቀ፡፡ እጆቹም ተቆራርጠው፣ ሰውነቱ ተልቶና ሸቶ ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በሰማዕታቱም ጸሎት ይማረን!!!
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.