uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 335 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 641-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 191-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 335 obunachiga ega bo‘ldi.

14 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -76 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.40% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.40% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 435 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 595 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 25 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 15 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 335
Obunachilar
-124 soatlar
-67 kunlar
-7630 kunlar
Postlar arxiv
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክቶ ያስተላለፉት እንደሚከተለው ቀርቧል። ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት፤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ አሜን! + በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ + ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ + የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ + በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ + እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓስራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! “ወበዝንቱ ተዓውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር ላዕሌነ እስመ ለወልዱ ዋሕድ ፈነዎ ውስተ ዓለም ከመ ንሕየው በእንቲኣሁ፤ ወዝንቱ ውእቱ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር፡- የእግዚአብሔር ፍቅሩ በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፤ (፩ዮሓ. ፬፥፱) በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው እኛ ምሥራቃውያን ክርስቲያኖች በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል፣ የጌታችን የኣምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ነው፤ በዓለ ልደት የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት ዕለት ነው፤ በዚህ ዕለት የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅርና ሰላም ቃላዊ ወይም ተምኔታዊ ኣልነበረም፤ ወይም ደግሞ በርቀት በመልእክት የተላለፈ ኣልነበረም፤ ከዚህ ይልቅ ሰብእናችንን በመዋሐድ፣ በተግባር ሆኖ በመገኘት፣ እንዲሁም ለመሰጠት ዝግጁ በመሆን የተገለጠና የታየ ሰላምና ፍቅር ነው፤ እግዚአብሔር የኛን ሰላምና ፍቅር በእጅጉ የሚሻው መሆኑን ለመረዳት፣ የኛን ሰብአዊ ክዋኔ በምልአት ተዋሕዶ በመካከላችን ከመገኘት የተሻለ ሌላ ማረጋገጫ ሊኖር ኣይችልም፤ እኛ ሰዎች ለእግዚአብሔር ጠላቶቹ ተብለን በቅዱስ መጽሐፍ የተገለጽን ነን:: እግዚአብሔር ጠላቶቹን የራሱ አካል አደረጋቸው ሲባል ከመስማት የበለጠ አስደናቂ ነገር በዚህ ዓለም ምን ሊኖር ይችላል? የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እግዚአብሔር ሰብኣዊነታችንን በምልአት ተዋሕዶ በዓለማችን እንዲገለጥ የሆነበት ዋና ምክንያት እሱ እንዳስረዳን እኛ በሕይወት እንድንኖር ነው፤ ይህንንም ያደረገው ከሁሉ በላይ የሆነ ሌላ ገፊ ኃይል ገፋፍቶት ሳይሆን ድንበር የለሽና ፍጹም ፍቅሩ አነሣሥቶት እንደሆነ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን፤ የእግዚአብሔር ፍቅር እኛ ከምናውቀው ፍቅር ሁሉ በላይ መሆኑንም በዚህ እናስተውላለን፤ ለጠላቶቹ ሕይወት ፍቅርና ሰላም ሲል እነሱን ከመሆን አልፎ እስከ ቤዛዊ መሥዋዕት የሚዘልቅ ፍቅር እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ! እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፈቃድ እኛ በሕይወት በሰላምና በፍቅር እንድንኖርለት ከሆነ የእኛ ግብረ መልስም ከዚህ የተለየ ሊሆን ኣይገባም፤ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ለማዳን እንጂ ለማጥፋት አልመጣም፤ የእኛም ሕይወት የሚጠበቀው ኣንዱ ሌላውን በማዳን እንጂ በማጥፋት እንዳልሆነ ጌታችን በቃልም በተግባርም በኣጽንዖት ነግሮናል፤ በዚህ አስተሳሰብና እምነት እንድንኖርም አዞናል፡፡ ታድያ በቃሉ ለመኖርና ለእሱ ለመታዘዝ ቃል የገባን እኛ ክርስቲያኖች ይህን ሁሉ እርግፍ ኣድርገን በመተው እርስ በእርስ ለመጠፋፋት መሽቀዳደም ምን ይሉታል? ይህስ ለማን ይበጃል? የአንድ ሀገር ሕዝቦች ይመካከራሉ፣ ይቻቻላሉ፣ ይታገሣሉ፣ ጊዜ ሰጥተው ያስቡና መፍትሔ ያበጃሉ እንጂ ማን በማን ላይ ይነሣል? ይህ ለማንኛችንም አይበጀንምና ወደ ኣእምሮኣችን እንመለስ የሚል ጥሪ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን መልእክት ነው፤ በመጨረሻም፤ ይህንን የተቀደሰ በዓል ስለ ሃገራችን ዘላቂ ሰላም በመጸለይና በማሰብ እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት የምግብ፣ የልብስና የመጠለያ እጥረት ያጋጠማቸው ወገኖቻችንን በመደገፍና በመርዳት ለእግዚአብሔር ክብር ብለን ለሀገር ኣንድነትና ለሕዝብ ፍጹም ሰላም መስፈን ከልብ በመነሣሣት በዓሉን እንድናከብር አባታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!! መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን!! እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

እንኳን አደረሳችኁ ! #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ጌና_እና_ልደት ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡ #ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡ #ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ #‹‹ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/ ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡ መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡ ‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡›› ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡›› ‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ይህችም ዕለት፤  ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/ **ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡ **ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡ **ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ **ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ **ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ **ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott

፳፭. ሆሳዕና ደብረ ምሕረት ቅዱስ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ሆሳዕና ፳፮. ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሃገረ ስብከት፥ ቡኢ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ቡኢ ፳፯. ባሕር ዳር በዓለ ወልድ (በዐለ እግዚአብሔር) ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፳፰. ወለንጪቲ ጨመሪ በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ወለንጪቲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወለጪቲ፡፡ ፳፱. ወንዶ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሳዲማ ሃገረ ስብከት፥ ወንዶ ገነት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወንዶ ገነት፡፡ ፴. ደብረ ምሕረት ዱና በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ዱና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ዱና፡፡ ፴፩. ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሃገረ ስብከት፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ደብረ ገነት፡፡ ፴፪. ጫንቋ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደምቢያ ቆላ ድባ አጠገብ፡፡) ፴፫. ባርጫ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ከቆላድባ አጠገብ፡፡) ፴፬. ገምበራ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ በጯሂትና በጣና አጠገብ፡፡) ፴፭. ጉቢያ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደምቢያ፡፡) ፴፮. ማክሰኚት በዓለ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ጎንደር ዙሪያ ወረዳ፡፡) ፴፯. ዘንተራ ኢየሱስ፤ (ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ጎንደር ዙሪያ ወረዳ፤ ማክሰኚት፤ በግራኝ በርና በጎንድ ገዳም መሃል፡፡) ፴፰. ደባርቅ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፤ ደባርቅ ከተማ ወረዳ) #ከኢትዮጵያ_ውጪ_የሚከበርበት_፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድ ወሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሃገረ ስብክት፥ ሲያትል ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን)→ አሜሪካን (ሲያትል) / #ክብረ_በዓላት #Feasts / / #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches / /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ታኅሣሥ ፳፱፤ #ልደተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_ #የጌታችን_ልደት_የበዓለ_ወልድ_የገና_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፵፯ ገዳማትና አድባራት፡፡ (ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) #ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም፤ #ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም፤ #ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ ✧ ክብረ በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፤ የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፤ ልዩ ማስታወሻ፤ ከቅዱሳንም ሆነ ከእመቤታችን በላይ የጌታችን በዓል ከዋለ የጌታችን በዓል በዋነኛነት ስለሚከበር፤ ጾምም ከሆነ ጾሙ ቀርቶ በዓል ስለሚደረግ፤ በዓላቸው በዚህ ቀን የኾኑ ቅዱሳን በዓላቸው በሌላ ቀን ቅያሬ ሲከበር ነገር ግን በቦታቸው ላይ የጌታችን ልደት በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ ✧ ነገር ግን የጌታችን ልደት፤ ከ9ኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ በመኾኑ፤ በሁሉም ገዳማትና አድባራት ዋይዜማ ተዚሞ፥ ማኅሌት ተቁሞ፥ ሰዐታት ተቁሞ፥ ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ ይከበራል፡፡ #በመዲናችን_በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻ፤ አራዳ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ 4ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አራት ኪሎ ፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ለቡ ፫. ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ አድራሻው፤ ሐና፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሐና፡፡ ፬. አንቀፀ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የቅዱስ ላሊበላ ታቦት በድርብነት ይወጣል) አድራሻ፤ የካ_ክፍለ_ከተማ፥ ራስ ካሣ ታክሲ፤ ከ4 ኪሎ → ፈረንሳይ → አንቀጸ ምሕረት (ራሳ ካሣ ሚካአል) ፭. ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ አድራሻው፤ ፊሊዶሮ፡፡ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ(ፊሊዶሮ)፡፡ ፮. አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ፯. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻው፤ መካኒሳ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ ፰. ኮልፌ ቀራንዮ (ታቦት ማደርያ) ደብረ ተአምራት ዳግማዊ ጻድቃኔ ማርያም፡፡ (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ዘነበወርቅ ታቦት ማደሪያ ጀርባ፤ ከዘነበወርቅ ወደ ታቦት ማደሪያ በሚወስደው መንገድ ላይ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃይሎች → ዘነበ ወርቅ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_፳፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ቤተልሔም፥ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም (ጌተችን የተወለደባት) አድራሻ፤ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን) → እስራኤል ፪. ማኅበረ ሥላሴ ገዳም (የሺዎች ገዳም)፤ (ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ በኢትዮጵያ የተበሠረባት) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራና (መተማ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጎንደር → ሸዲ/መተማ/ ፫. ደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ (ዳግማዊት /አምሳለ/ ኢየሩሳሌም) አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ ፬. መንበረ ልዑል ደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወማኅበረ በኵር ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር ከተማ → ዳንሻ መስመር ላይ → በበው /አሸሬ/ የምትባል መንደር ላይ ተወርዶ → የእግር ጕዞ ፭. ዞዝ አንባ አቡነ አብሳዲ (ቅዱስ ላሊበላ ከፈለፈላቸው አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ በለሳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ማክሰኚት → በለሳ (ዞዝ አንባ) ፮. ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፯. ዲጎ ኢየሱስ፡፡ አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ወልድያን አልፎ፥ ዶሮ ግብር፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ → ወልድያ፡፡ ፰. ገሀ ኢየሱስ፤ (ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥) ፱. ኬላ ኢየሱስ፤ (ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥) ፲. ደንቀዝ ኢየሱስ፡፡ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፲፩. ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ /ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደ፥ እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው፥ ኋላ ላይ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ/ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፥ ጃንተከል ወርካ ጋር ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ፲፪. እስቴ መካነ ኢየሱስ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፫. ደብረ ታቦር ኢየሱስ አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደቡብ ጎንደር ከተማ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ታቦር፡፡ ፲፬. ብራ ኢየሱስ (ብራ ታዴዎስ)፡፡ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ወገራ፥ አምባ ጊዮርጊስ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → አምባ ጊዮርጊስ፡፡ ፲፭. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ የጎንደር ላይ ቤት አቋቋም ትምህርት ቤት ማስመስከርያ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ጥምቀተ ባሕሩ አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር ፲፮. መንደረ ኢየሱስ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ አዴት፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፯. ጃንገበር ኢየሱስ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ሃገረ ስብከት፥ አዴት አጠገብ፡፡ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፰. ሰንቀኛ በዓለ እግዚአብሔር፤ (ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፲፱. ሺገዢ ኢየሱስ፤ ባሕር ዳር በሞጣ መስመር(አዴት) ፳. አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ አለም ገና ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → አለም ገና፡፡ ፳፩. ገፈርሳ(ታጠቅ) በዓለ ወልድ ወአቡነ ሳሙኤል ወአቡነ ኪሮስ፤ አድራሻው፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ገፈርሳ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ታጠቅ ወይም መናገሻ የሚል ትራንስፖርት ይዘው ገፈርሳ ድልድዩ ጋር በዓለ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ፳፪. አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ ወልመራ ወረዳ፥ (አዲስ ዓለም አካባቢ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አምቦ (አዲስ ዓለም) ፳፫. ቂልጠፋት በዓለ ወልድ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እንደጋይ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፳፬. ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እነሞር ወረዳ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ

ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እና አካባቢው - 1951 ዓ.ም ኢቲሳ በሰሜን ሸዋ በቀድሞው ቡልጋ አውራጃ የሚገኝ እና ከ800 ዓመት በፊት እ.ኤ.አ በ1215 ዓ.ም አባታችን አቡነ ተ
+8
ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እና አካባቢው - 1951 ዓ.ም ኢቲሳ በሰሜን ሸዋ በቀድሞው ቡልጋ አውራጃ የሚገኝ እና ከ800 ዓመት በፊት እ.ኤ.አ በ1215 ዓ.ም አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱበት ታሪካዊ ቦታ ነው። University of Monash/Asian Collections/Forsyth, Elliott Christophe Photographs: https://repository.monash.edu

እንኳን አደረሳችኁ በዓለ_ልደቱ_ለሐዲስ_ሐዋርያ_ፀሐይ_ማር_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ታኅሣሥ 24 1196 ዓም በሰሜን ሸዋ ቡልጋ ጽላልሽ እቲሣ ተወልደው በአጠገቡ በምትገኛዋ ደብረ አጋዕዚት ክርስትና_ተነሡ፡፡ #አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘአብና እናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው በአካባቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻንና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡ #በ7ት ዓመታቸው ከግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡ ከዮዲት ጉዲት በኋላ ሃገራችን ሰሜኑና ደቡቡ ተቆራርጧል፤ የሐሳብን ልዕልና የሚያመጣው የመንፈስ ልዕልና ተዳክሟል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን የሚዋጅ ሐዲስ ሐዋርያ ያስፈልግ ነበርና አምላካችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጠራ፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀብለው በጽላልሽ አካባቢ በክህነት ከአባታቸው ጋር አገልግለዋል፡፡ አባታቸው ሲያርፉ በወንጌሉ ማንም ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር  ያለውን ሁሉ ትቶ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን በመከተል ሀብታቸውን ለድኾች መጽውተው በሸዋና በዳሞት በስብከተ ወንጌል አገለገሉ፡፡ ከዚያም፤ #በመጀመርያ ደቡብ ወሎ ቦረና ላይ ገዳማቸውን ደብረ ጎል ገድመው ወደሚገኙት ታላቁና ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወደኾኑት ጻድቅ አባት አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ዐሥር ሁለት ዓመታት በትምህርትና በሥራ (በአርድእትነት) አሳልፈዋል፡፡ በዚያም ዋሻ ፈልፍለው አስደናቂ ሕንፃ ሠርተው ነበር፡፡ #በ1216 ዓ.ም. አካባቢ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገሳም ገብተዋል፤ በዚሁ ገዳምም ከመመንኰሳቸው በፊት ሰባት ዓመት ከመነኰሱም በኋላ ሦስት ዓመት በድምሩ ለ10 ዓመታት በትምህርት፣ በእደ ጥበብ ሥራ፣ በአገልግሎትና ሥርዓተ ምንኩስናን እያጠኑ ቆይተዋል፡፡ #ከሐይቅ ወጥተው በዘመኑ በሥርዐተ ምንኩስናና በትምህርት ብሎም በጥበበ እድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ወደ ነበረው ወደ ደብረ ዳሞ በመሄድ በየገዳሙ አበምኔት ከሆኑት ከአቡነ ዮሐኒ ዘንድ መንፈሳዊ ትምህርት ፣ ሥርዐተ ምንኩስናና ጥበበ እድ ሲማሩ ለ12 ዓመታት ቆዩ ፡፡ ያነጹት ፍልፍል ድንጋይ ዋሻ፣ መጻሕፍት ሲጽፉ ቀለማቸውን ያስቀምጡባቸው የነበሩትን ሽንቁሮች ዛሬም በደብረ ዳሞ ማየት ይቻላል፡፡ #በደብረ ዳሞ የነበራቸውን ቆይታ ጨርሰው በገመድ ሲወርዱ ሰይጣን በቅንዐት መጥቶ ገመዱን በጠሰባቸው እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ወቅት የሚበሩበትን እንደ መላእክት ክንፍ ሰጣቸው፡፡ #ለአምስት ዓመታት #አኵስምን_ዋልድባን እንዲሁም ሎሎች የትግራይ ገዳማትን እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ቆዩ #ከሸዋ በወጡ በሃያ ሁለት ዓመት (እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ሲሆን) ለበለጠው ክብር እና ርእይ በግብጽ በኩል ወደ ኢየሩሳሌም ተሻገሩ፡፡ #ከኢየሩሳሌም ሲመለሱ በሐይቅ በኩል አድርገው ደብረ ጎልን ተሳልመው በሚዳ እና በመርሐ ቤቴ በኩል ወደ ሸዋ በመምጣት ከዮዲት ዘመን በኋላ በመንፈሳዊ ሕይወት የተጎዳውን ሸዋን እና ደቡብ ኢትዮጵያን በመዘዋወር ለዐሥር ዓመታት ያህል አስተምረዋል፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተግተው በማስተማራቸው የተኛው ሁሉ ነቃ፣ የደከመው በረታ፣ የጠፋውም ተገኘ፡፡ ሐዋርያትን ለማፍራት እንዲችሉ አንድ ገዳም ለመመሥረትና ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር አሰቡ፡፡ እናም ወደ ደብረ አስቦ ገዳም ገቡ ፡፡ ቦታውን አስተካክለው እና ከደብረ ዳሞ እና ከሐይቅ የተከተሏቸውን ጥቂት ደቀ መዛሙርት ይዘው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ልክ እንደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሁሉ ሦስቱን ነገሮች ያካተተ አገልግሎት ጀመሩ፡፡ ምንኩስና፣ ትምህርትና ሥራ፡፡ መነኮሳቱ መንፈሳዊ ትምህርት ይማራሉ፤ በሕገ ገዳም ይመራሉ፤ ለራሳቸው እና ለአካባቢው ሕዝብ ርዳታ የሚሆን እርሻ ያርሳሉ፡፡ #ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ገዳማቸውን አደራጅተው፣ ስብከተ ወንጌልንም አስፋፍተው ካደላደሉ በኋላ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ወደ ደብረ አስቦ ዋሻ ገብተው በአንድ እግራቸው በጾም እና በጸሎት ተወሰኑ፡፡ #አገልግሎታቸውን ፈጽመው ነሐሴ 24 ቀን 1297 ዓ.ም. በ99 ዓመታቸው ዐረፉ፡፡ ✤✤ #እቲሣ_ገዳም_ #በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤ #ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤ #ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣ #አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡ #ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤ #ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤ #ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤ #በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤ #ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤ #በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ ቦታው ከአ.አ በቅርብ ርቀት በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ይገኛል፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌቱን እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡ ጸሎትና በረከታቸው ፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w