uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 366 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 646-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 192-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 366 obunachiga ega bo‘ldi.

18 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -95 ga, so‘nggi 24 soatda esa 11 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.81% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.33% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 344 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 430 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 22 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 19 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 366
Obunachilar
+1124 soatlar
-67 kunlar
-9530 kunlar
Postlar arxiv
#ነሐሴ_፳፰ #እንኳን_ለአባታችን_ለአበ_ብዙኃን_አብርሃም_በዓለ_ዕረፍት_እንዲሁም_ለይስሐቅ_እና_ለያዕቆብ_መታሰቢያ_በስላም_አደረሳቹ     #አበዊነ_አብርሃም                     ❖ አባታችን አብርሃም የስሙ ትርጓሜ  አበ ብዙኃን ሲሆን ትርጉሙም የብዙኃን አባት ማለት ነው፡፡ የዕረፍቱ ነገር አንዲህ ነው                          ❖ አስከ ዕለተ ዕረፍቱ ድረስ በድንኳን የኖረ፣  ስለ ታዛዥነቱ ካራንን ጥሎ የወጣ ፣ አንድ ልጁን እስከ ማረድ የታዘዘ  አባት ነው ፡፡                      ❖ አግዚአበሄር  ለአብርሃም ከነበረው ፍቅር  ፤ የሞቱን ነገር ሲሰማ አብርሃም እንዲያዝን አልወደደምና ሚካኤልን  እንዲያጽናናው ልኮታል፡፡ በሰማይም ስላለው ነገር ወደሰማይ ነጥቆ ያሳየው ነበር ፡፡                      ❖ ቅዱስ ሚካኤልም በእንግድነት ባደረባት በዚያች ሌሊት ለልጁ ለይስሐቅ የሞቱ ነገር ተገልጦለታል ፡፡ ይስሐቅም በመንፈቀ ሌሊት እያለቀስ ሄዶ አባቱ ካለበት አንኳኳ፤ አባቴ አብርሃም ከእኔ ከመለየትክ በፊት  ገብቼ እጅ እነሳክ ዘንድ ፍቀድልኝ ፍቅርህንም እጠግብ ዘንድ ክፈትልኝ አለው ፡፡ አብርሃምም ደንግጦ ከፈተለት ይስሐቅም ወዲያውኑ አባቱን አቅፎ ሳመው ሁለቱም አንገት ለአንገት ተያዘው  እጅግ አለቀሱ እንደውም ቅዱስ ሚካኤል ፍቅራቸውን አይቶ አዘነ ፡፡ መጽሐፉ ሚካኤል አብሮዋቸው  አለቀሰ ይለዋል  ፡፡ርብቃም  ለቅሶዋቸውን ሰምታ መጣች  አብርሃምም << ከመጣክ ጀምሮ ልቤ ደንግጦብኛል ወንድሜ ሆይ ስለምን ነገር ወደዚ መጣክ አለው >> ሚካኤልም ልጅህ ይስሐቅ ያየውን ይንገር አለው ፡፡ ይሰሐቀም ነገራቸው ፡፡                      ❖ ቅዱስ ሚካኤልም እነደታዘዘው መልአከ ሞትን አስጠንቅቆ ሰደደው ፡፡ የሞቱ ሰዓት በደረስ ጊዜም  ይስሐቀም ያለቅስ ነበር ፤አብርሃምም ልጄ አታልቅስ ረዳትህ እግዚአብሔር ነውና  እስከምትሞትባት ቀን ድረስ እርሱ ይሁንህ አለው ፡፡ እግዚአብሔርም ዘርህን እንደ ምድር አሸዋ እንደ ሰማይ ከዋክብት  አበዛልሃልው ብሎ ቃል ገብቶለታል                     ❖ #ይቤሎ እግዚአብሔር ለአቡነ አብርሃም  ባርኮ አባርከከ ወአበዝህዎ ለዘርእ  ፣ ከመ ኮከበ ሰማይ ወከመ ወጻእ ዘደንገገ ባህር ፡፡                     ❖ የመላእክት ሰራዊት ብፅዕት ነፍስ  እያሉ ከገነት አኖሯት ፤ ይስሐቅም እያለቀስሰ   በፍጹም ክብር  ገንዞ ከኬጢ ልጆች በገዛዉ በሳራ መቃብር ቀበረው ስምንት ቀንም ሃዘን አደረጉለት፡፡                    ❖ የደጋግ አባቶቻችን የአብርሃም  ፣ የይሰሐቅ አና ያዕቆብን   ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን   ፡፡                     ❖     የአባታችን የአበ ብዙኃን አብርሃም በዓል  በአዲስ አበባ ወስጥ ብቸኛ በሆነው  በለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድ ና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም ይከብራል:: #አቅጣጫ ለቡ ፣ኃይሌ ጋርመንት #share                      ❖                      ✞

ልደቱ ለአቡነ ዘርዐ ብሩክ(ነሐሴ 27) በትንቢት ‹‹ከአንዲት ሴት ልጅ በጸሎቱ ዓለምን የሚያድን፣ በአማላጅነቱ ነፍሳትን የሚዋጅ ልጅ ይወለዳል›› ተብሎ ከተነገረ ከብዙ ዘመን በኋላ እግዚአብሔርን የምታመልክ ስሟ ማርያም ሞገሳ የምትባል ሴት ልጅ ተወለደች:: ያችንም ሴት ልጅ እናትና አባቷ ለአቅመ ሔዋን እስክትደርስ ድረስ እግዚአብሔርን በመፍራትና በዕውቀት አሳደጓት:: ዕድሜዋም ለትዳር ሲደርስ እናትና አባቷ እግዚአብሔርን ለሚፈራ ስሙ ደመ ክርስቶስ ለሚባል ሰው ዳሯት:: በዚያን ጊዜ ስልጣኑ ከሰማይ የሆነና ክብሩ እጅግም የሆነ ልጅ ጸነሰች:: እርሱን ከጸነሰች ጊዜ ጀምሮ እስክትወልደው ድረስም ልብሷን አትታጠቅም፤ ለወገቧም መቀነትን አትፈልግም ነበር:: በእናቱ ማህፀን ተአምራትን እንዳደረገ እንደ ዘካርያስ ልጅ እንደ ዮሐንስ በደስታ እየሰገደ በእናቱ ማህፀን ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርግ ነበርና:: እርሷም የመውለጃዋ ቀን እስኪደርስ በጾምና በጸሎት ተወስና ስታገለግል ኖረች:: በነሐሴ ፳፯ ቀን በሰው ዘንድ የተናቀ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ይህን ክቡር ጻድቅ ወለደችው:: በተወለደም ጊዜ በእናትና አባቱ እንዲሁም በሀገሩ ሰዎችም ዘንድ ፌሽታ ሆነ፤ እስከ ሰባት ቀንም ድረስ ግብዣ አደረጉ:: ይህም ጻድቅ ባሕታዊ በተወለደበት (ክርስትና) በተነሳበት ቀን በካህናት አፍ ጸጋ ክርስቶስ ተባለ:: የኃጢአት ማሰሪያን ሁሉ ያስርና ይፈታ ዘንድ ጵጵስና በሾመው ጊዜ እግዚአብሔር ያወጣለት ሁለተኛው ስሙ ዘርዓ ብሩክ ነው:: ሦስተኛ ስሙ ደግሞ ጸጋ ኢየሱስ (በጸሎት ተደጋግሞ ብዙ ይገኛል) ይባላል:: ከልደቱ በኋላ ያንንም ሕፃን አባቱና እናቱ እስከ ሰባት ዓመቱ ድረስ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በአምልኮት እና በዕውቀት አሳደጉት:: ሰባት ዓመት ሲሆነው የሚያልፈውንና የሚጠፋውን ዓለም ሁሉ እንዳያይ ዓይኖቹ ታወሩ:: የልጃቸው ዓይኖች በጠፉበት ቀን እናትና አባቱ አዘኑ፤ ታውሮም በቤታቸው አንዲት ዓመት ኖረ:: ከተወለደ ሰባት ዓመት ሲሆነው ረቡዕና ዓርብን መጾም ጀመረ:: እናትና አባቱም በተወለደ በሰባት ዓመቱ ሲጾም ባዩት ጊዜ ሀዘናቸው ወደ ደስታ ተለወጠ:: ከዚህም በኋላ በእኒህ እንዲተዳደር ብሎ እንደተናገረው መጽሐፍትን ቢማር ያለበትን ነውር እንደሚሰውር እና በእነዚህም እንዲተዳደር አውቀው የቤተ ክርስቲያንን መጽሐፍት ሁሉ እንዲያስተምረው ለመምህር ሊሰጡት ተማከሩ:: እርሱ ሲማር እግዚአብሔር ብርቱ መከራንና የሚያስጨንቅ በሽታ አመጣበት:: አባትና እናቱም በልጃቸው ላይ የሆነውን ነገር አይተው ዓይኖቹ የታወሩ ‹‹ይህ ልጃችን በምን ይተዳደራል? በዚህ ዓለምስ አኗኗሩ እንደምን ይሆናል?›› ብለው ታላቅ ሀዘንን አዘኑ:: እግዚአብሔርም ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) በቀር መጻሕፍትን ሁሉ ከማንም እንዲማር እንዳልፈቀደለት ፈጽመው አስተውለው አላወቁም ነበር:: ይህ ትንሽ ሕፃን ግን ለአባትና ለእናቱ ሲታዘዝ (ሲያገለግላቸው) ኖረ:: ሐዋርያትም በሲኖዶሳቸው እንዳዘዙት ከተወለደ ፲፪ ዓመት ሲሆነው ይጾም ነበር:: ዐሥራ ሁለት ዓመት ከሆነውም በኋላ የጌታችንን ጾም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ አምላክን የወለደች የእመቤታችን ማርያምን ጾም፣ ሐዋርያት የሠሩትን ጾም፣ ሁሉ መጾም ጀመረ:: አባትና እናቱም በዐሥራ ሁለት ዓመቱ ጾሙን ሁሉ ሲጾም አይተው ተደሰቱ:: ይህ ሕፃን ልጃቸው በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ እንደጸና አላወቁም:: እግዚአብሔር አምላክም ለዚህ ጻድቅ አባት መጻሕፍተ ብሉያትንና መጻሕፍተ ሐዲሳትን፤ መጻሕፍተ ሊቃውንትንና መጻሕፍተ መነኮሳትንም፤ አዋልድ መጻሕፍትንም፤ የመላእክትንና የሰውን ነገር (ፍትህን ሁሉ፤ የማኅሌታይ የቅዱስ ያሬድንም ዜማ) ገለጠለት፤ እግዚአብሔር ይህንን ድንቅ ተአምራት ለወዳጁ ለብፁዕ አባታችን ለአቡነ ዘርዐ ብሩክ የተሰጠው ገና በልጅነቱ ነበር:: ለእኛም ፈጣሪያችን እንዲሁ ተአምራትን ያድርግልን፤ በመከራችን ጊዜ ደስታን ያሰማን፤ ለእርሱ እንደገለጠለት መጻሕፍትን ሁሉ ይግለጥልን፤ መታሰብያውን ለምናደርግ፣ ስሙንም ለምንጠራ እና በጸሎቱ ለምንማጸን ለወንዶችና ለሴቶች ልጆቹ በጻድቁ ጸሎት ነፍሳችንን ይማርልን፤ አሜን !! ምንጭ፤ ገድለ ዘርዐ ብሩክ

እንኳን ለአባታችን #አቡነ_ሀብተማርያም በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሳቹ:: አቡነ ሀብተማርያም ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤ ፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤ ፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ ታለቅ አባታችን ናቸው፡፡፡፨ ፠ታላቁ ጻድቅ አባታችን #አቡነ_ሀብተማርያም የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡ የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እናታቸውም ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ #7_አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡ ፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡ ፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡ ለአብነትም፤ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤ በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤ በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤ ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤ በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋል፤ ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤ በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡ የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡ "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" የተባለላቸው ታላቅ አባታችን ናቸው ፡፡ ፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡ *የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡ ፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው:: "*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::" "በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው:: +ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: መላእክትም ዝማሬም ወሰዷት::  ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤ ፩ኛ. #መብረቅ፣ ፪ኛ. #ቸነፈር፣ ፫ኛ. #ረሃብ፣ ፬ኛ. #ወረርሽኝ፣ ፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡ ፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡ (ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡) ✞✞✞✞✞ #አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሀብተማርያም ✞ #ያን ጊዜ ክቡር የሆነ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ጠርቶኝ ልጄ #ሀብተ_ማርያም ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤ #ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣ #ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤ ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣ #……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ. ገድለ አቡነ ሃብተ ማርያም #አቡነ_ሀብተ_ማርያም በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን ! በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#እንዃን_ደስ_ያላችኹ የ2017 የትምህርት ዘመን በቀጨኔ ደብረሰላም ወ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት ምዝገባ እንኾ ተጀምሯል። #የምንሰጣቸው
#እንዃን_ደስ_ያላችኹ የ2017 የትምህርት ዘመን በቀጨኔ ደብረሰላም ወ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል  ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት  ተከታታይ መንፈሳዊ ትምህርት ምዝገባ እንኾ ተጀምሯል። #የምንሰጣቸው_ኮርሶች_:- - ትምህርተ ሃይማኖት - ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ወ ህይወት - የመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት - የቤተክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ - ሥርዓተ ወ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን - መዝሙርና ምሥጢራዊ ሥርዓቱ #መመዝገቢያ_ቦታ - በፍኖተ ህይወት ሰ/ት/ቤት አዳራሽ -ቤተመጻሕፍት -ፍኖተ ሱቅ (የሰንበት ት/ቤቱ ሱቅ ) #መመዝገቢያ_ስልኮች 09-33-09-54-12 09-34-11-30-23 09-60-41-25-71

#ደብረ_ሊባኖስ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ደብረ ሊባኖስ ወረዳ የሚገኝ ገዳም የጥንት ሰሙ #ደብረ_አስቦ ነበር። ገዳሙ የተቋቋመው በአራተኛው ክፍለ ዘመን #በአቡነ_ሊባኖስ አማካኝነት ነው። አቡነ ሊባኖስ በቦታው በጸሎት ተወስነው ሲኖሩ ከእርሳቸው በኋላ #ሌላ_ታላቅ_ሐዋርያ እንደሚመጣና ቦታውም በርሱ እንደሚከብር ነገር ግን ለመታሰቢያ ቦታው በስማቸው እንደሚጠራ ከእግዚአብሔር ተነገራቸው። በዚህ ምክንያት ለ700 ዓመታት ያህል ጠፍ ሆኖ ኖሯል። ሌሎች የታሪክ ምንጮች እንደሚሉት አባ ሊባኖስ ከሔዱ በኋላ አባ ዘመደ ሊቃኖስ የተባሉ አባት ወደ ቦታው እንደ መጡ፤ ከርሳቸውም በኋላ አባ ነገደ እስራኤል በኋላም አባ ዘድንግል በየዘመናቸው አያሌ የትሩፋት ሥራዎችን ሠርተውበታል። አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ ደብረ አስቦ ሲመጡ ሐረስ የተባለ ጠንቋይ ቦታውን ወስዶት እንደነበር ይነገራል። ወደ ዋሻው ሲገቡ "እንተ ሶበ ጸዋዕክዎ ለእግዚአብሔር እድኅን እምፀርየ፤ ወይባልሐኒ እምጸላዕትየ ምንስዋን" የሚለውን የዳዊት መዝሙር ይጸልዩ ነበር። ሐረስም ይህንን ሰምቶ አካባቢውን ጥሎ ጠፋ።  ጻድቁም ቦታውን ባርከው በአት አድርገውታል። አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚህ ገዳም በተጋድሎ መኖራቸው በየአካባቢው እየተሰማ ብዙ መነኮሳት ተሰባሰቡ። እርሳቸውም እመቤታችንን ይወዱ ስለነበር በዋሻዋ እኩሌታ በሰሌን ጋርደው ታቦተ ማርያምን አኑረው በእኩሌታዋ ደግሞ እርሳቸው ከዐሥራ አምስት ደቀ መዝሙሮቻቸው ጋር ይኖሩ ነበር። በዐፄ ሰይፈ አረእድ ዘመነ መንግሥት /1336-1364/ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተቀበሩበት ዋሻ በመናዱ ለዕጨጌ ሕዝቅያስ አቡነ ተክለሃይማኖት በራእይ በገለጡላቸው መሠረት ዐፅማቸው ግንቦት 12 ቀን ፈልሶ ቤተ መቅደሱ ወደ ተሠራበት አካባቢ መጥቷል። ደብረ ሊባኖስ እየተባለ ስሙ ገኖ መጠራት የጀመረው ከ15ኛው ምእት በተለይም ከዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ /1426 -1460 ዓ.ም/ ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል። የገዳሙ ዋና ሕንጻ ከኢትዮጵያ ነገሥታት ብዙዎቹ ያማረ በመሰላቸው ጊዜያቸው በፈቀደላቸው ጥበብ ሕንጻውን አሠርተዋል። ለምሳሌ የመጀመሪያውን ሕንጻ ያሳነፁት በ1280 የነገሡት አጼ ይኩኖ አምላክ ሲሆኑ፤ ሁለተኛው ደግሞ በ1405 ዓ.ም የነገሡት አጼ ይስሐቅ ነበሩ። እንዲሁም በ1804 ዓ.ም በወሰን ሰገድ ፤ በ1876 ዓ.ም አጼ ዮሐንስ፤ በ1900 ዓ.ም በዳግማዊ ምኒልክ እንደገና ታንጿል። የሥፍራው ገደላማ አቀማመጥ እና የአፈሩ የመሸሽ ባሕሪ ለሕንጻው የማይስማማ በመሆኑ ግንባታው ለብዙ ጊዜ ሊያገለግል አልቻለም። በመጨረሻም በቀዳማዊ  ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከጥልቅ የግንባታ ጥናት በኋላ ተሠርቶ ኅዳር 9, 1955 ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ተመረቀ። #በተስፋህ_ያመነውን፤ #በቃል_ኪዳንህ_የተማጸነውን፤ ሥጋህን የቆረስክበትን ደምህን ያፈሰስክበትንም #ቦታ_እጅ_የነሳውን ሁሉ #ከሞተ_ነፍስ_አድንልሀለሁ፤ ከዚህ ቦታ #በተስፋ_ጸንተው_በኪዳንህ_ተማጽነው የሚኖሩ ልጆችህን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛልሀለሁ ብሎ ጌታችን ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w, .Telegram... https://t.me/Finotehiwott http://tiktok.com/@finotehiwot #ቅዱሳን  #Saints  #ክብረ_በዓላት #Feasts   #አቡነ_ተክለሃይማኖት #ደብረ_ሊባኖስ

የመርዓስ ኤጵስ ቆጶስ የነበረው አባት አባ ቶማስ ክርስቶስን በማመን በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊት በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነበር። በዚህ ፅናቱ የክብር ባለቤት ጌታችን መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ መንጋውንም ይጠብቅ ዘንድ መረጠው አባታችን ቶማስም ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየፈፀመ፣ ሕዝቡን እየመራ ሳለ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሱ ላይ፣ በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ላይም ተነሳባቸው፣ ክርስቲያኖችንም ያሰቃያቸው ጀመር በአንድ ወቅት ከመኳንንቶች አንዱ የነበረው፣ ቅዱስ ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደ ውኃ ፈሰሰ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት «እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣኦታት አልሰግድም ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና» በዚህም ጊዜ መኮንንኑ በጣም ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን አሰቃየው የነዳጅ ድፍድፍን አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው እስከመጨመርም ደረሱ ልባቸው እንደ ድንጋያ የፀና ስለ ነበር ቅዱስ ቶማስን ገድለው ቶሎ ማሣረፍ አልፈለጉም ይልቁንም የስቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ እርሱም ስለ ስህተታቸው ይዘልፋቸው ነበር፣ እንደ ማይመልስም ሲገባቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት በየዓመቱም ወደ እርሱ እየሄዱ ከሕዋሳቱ አንድ፣ አንዱን ይቆርጡ ነበር፡፡ በዚህም ለሃያ ሁለት(፳፪) ዓመት ቆየ ሲቆይ ግን አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ ጆሮዎቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን ቆርጠው ነበር፤ በዚህም ምክንያት የአገሬው ሰው ሞቷል ብለው አስበው በየዓመቱ መታሰቢያ ያደርጉለት ነበር ይህ ለምን ሳይሞት ቢሉ ጊዜው ሲረዝም ቢሞት ነው እንጂ እስካሁንማ ይመጣ ነበር ብለው ስላሰቡ ነበር፤ ነገር ግን ከሕዋሳቶቹ አብዛኛው ክፍል ቆርጠው ቢጥሉትም አካሉ ግን ተቆራርጦ ሲጣል አንዲት ሴት አየችው፣ ይህችም ሴት በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበው ነበር፡፡ ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከገለጥ ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡ #ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ስለክርስቶስ በመታመን የታሠሩ እስረኞች ሁሉ እንዲፈቱ በማዘዙ ሁሉም ተፈቱ፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን የተጣለበት ቦታ፤ በሕይወት ያለም ስላልመሠላቸው አላወጡትም ነበር፤ ነገር ግን ይህን አዋጅ ትመግበው የነበረችው ሴት ሰምታ ነበርና ወደ ካህናቱ ዘንድ ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ሃያ ሁለት ዓመት በዚያ ስለመኖሩ ነገረቻቸው ቦታውንም አመለከተቻቸው እነርሱም ባገኙት ጊዜ አንስተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑም ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደስ ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱንም ይሳለሙ ነበር፡፡ ከቦታ ቦታ ይዘዋወር የነበረውም በቅርጫት ኹኖ በዘህያ ላይ ተጭኖ ነው፡፡ ✤ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ የከበሩ ፫፻፲፰ ኤጲስ ቆጶሳትን (ሠለስቱ ምዕት) የአንድነት ጕባኤን በኒቂያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት (ቅዱስ ቶማስ) ከሠለስቱ ምዕት አንዱ ነበር፤ ወደ ኒቅያ ጕባኤ በቅርጫት ሁኖ በአህያ ተጭኖ እየሄደ መሆኑን አርዮሳውያን ሲሰሙ፤ ቶማስማ በጕባኤው ከተገኘ ተከራክሮ ይረታናል አንችለውም በማለት መንገድ ላይ ባደረበት ይዘውት ይጓዙት የነበሩትን አህዮች በጨለማ በሰይፍ መተዋቸዋል፤ ነገር ግን ሌሊት ሊነጋጋ ሲል ለመንገድ ሲነሱ ቶማስ በተዓምራት አግልጋይ ረድኡን የተቆረጡትን የአህያዎቹን አንገታቸውን ከሰውነታቸው አጋጥመው ይነሳሉ ብሎ ሲያዘው የአንዱን አህያ ከሌላኛው አህያ ቢያጋጥመውም ቅሉ አህዮቹ ሕይወት አግኝተው ጕባኤ ኒቅያ አድርሰውታል፤ በዚያም አርዮስን መልስ እስኪያጣ ድረስ በጽናት ሲከራከረውና መልስ ሲያሳጠው የጕባኤው ሊቀ መንበር ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እስኪደነቅ ድረስ በማየቱ ሃይመኖትስ የእነ ቶማስ ዘመርዓስ ነች ብሎ አጽንቶ ወስኗል፡፡ በጕባኤውም አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ አውግዘው ለይተውታል፤ ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፤ ሕግና ሥርዐትን ሥጋዊና፤ መንፈሳዊ ፍርድንም ሰሩ። ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከተመለሰ በኋላ ካህናቱና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲያስተውሉት እንዲጠበቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ይህ አባት ለ፵ ዓመት ያህል በሢመቱ አገልግሎ በነሐሴ ፳፬ ቀን አርፋል፡ በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ፠፠፠ .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... Telegram https://t.me/Finotehiwott http://tiktok.com/@finotehiwot #Share #like

✤✤✤ #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ ✤✤✤ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ ሀገሯ #ሸዋ_ቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌየ ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ወላጆቿ ከአባተቷ ቅዱስ ደረሳኒ ከእናቷ ከቅድስት ዕሌኒ በግንቦት 12 ቀን ተወለደች፡፡ እነርሱም ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ከወለዱ በኋላ በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር ስላሳደጓት ከልጅነቷ ጀምራ በሥነ ምግባር፣ በሃይማኖት የታነጸች በመልኳም እጅግ ውብና ያማረች ሆነች፡፡ ባደገችም ጊዜ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ የንጉሥ ባለሟል ለሆነ ስሙ ሠምረ ጊዮርጊስ ለተባለ ደግ ሰው በሕግ አጋቧት፡፡ ከሕግ ባሏ ከሠምረ ጊዮርጊስም ዐሥራ ሁለት ልጆችን ወለደች፡፡ ከእነዚህም መካከል አስሩ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዐፄ #ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረች ኢትዮጵያዊት ጻድቅ ስለነበረች ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ገብረ መስቀል በትዳሯ፣ በሥነ ምግሯና በሃይማኖቷ በሁለመናዋ የተመሰገነች መሆኗን ዝናዋን ስለሰማ ‹‹#በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ከአገልጋዮቹ ውስጥ እርሷን እንዲያገለግሏት፣ 174 አገልጋዮቸን ላከላት፡፡ ብዙ ፈረስና በቅሎ እንዲሁም ለነገሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማም ላከላት፡፡ ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ‹‹ለዓላማዬ እንቅፋትና ውዳሴ ከንቱ ይሆንብኛል እንደዚሁም ወርቁ ጌጡ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ነገር ግን እነዚህን አገልጋዮች ምን አደርጋቸዋለው?›› እያለች ወደ እግዚአብሔር አመለከተች፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ #ሚካኤል ፊቱ እንደ ፀሐይ እያበራ ሦስት ኅብስት በእጁ ይዞ መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እነሆ ይህን #ኅብስት ተመገቢ እግዚአብሔር በቸርነቱ ብዛት ሰጥቶሻል›› አላት፡፡ እርሷም ፈጣሪዋን አመስግና ኅብስቱን ከመልአኩ እጅ ተቀብላ ተመገበች፣ መዓዛ ጣዕሙም ሰውነቷን አለመለመው፡፡ በዚህም የተነሳ እስከ ሦስት ቀን እህል ሳትበላ ውኃ ሳትጠጣ ቆየች ኃይለ መንፈስ ቅዱስ በሰውነቷ አድሮባታልና፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ ሆነ፡- ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ የከፋ ነበርና በጣም ስላበሳጨቻት በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት፡፡ ያም የእሳት ትንታግ እስከ ጉሮሮዋ ዘለቀና አገልጋይዋን ገደላት፡፡ በዚህ ጊዜ ብጽዕት ክርስቶስ ሠምራ ደንግጣ ወደ ሌላ ክፍል ገባችና ኃጢአቷን ለእግዚአብሔር እየተናዘዘች እጅግ በጣም አዝና ጥፋቷ እንደ ጸጸታትና እግዚአብሔር አምላክም በእጇ የሞተችውን አገልጋይዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ ቢያሥነሳላት ያላትን ገንዘብና ሀብት ትታ ባላት ዘመኗ ሁሉ አገልጋዩ እንደምትሆን ብጽዓት (ስዕለት) አደረገች፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቷን ሰምቶ አገልጋይዋን ከሞት አሥነሳለት፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ‹‹ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከእኔ ከባሪያው ያላራቀ አምላክ ይክበር ይመስገን›› ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔርን ካመሰገነች በኋላ አስቀድማ የገባችውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኩስናዋን አዘጋጀች፡፡ ሕፃን ልጅዋንም ይዛ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደች፡፡ ስትሄድም በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግሯ ከመንገዱ ብዛት ከእንቅፋቱም የተነሳ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሟ መሬት ለመሬት እየፈሰሰ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደረሰችና አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኩስናዋን ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችውን ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከደጅ ላይ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ሲያለቅስ ከመነኮሳቱ አንዲቷ ሕፃኑ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በአዓቷ ልታስገባው ስትል የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፡፡ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በ 3 ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ብፁዓን ገባ፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ተሸክሞ ከጣና ደሴት አደረሳት፡፡ ከዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ሳትወጣ ባሕሩ ውስጥ ዐሥራ ሁለት ዓመት ቆማ ስትጸልይ ኖረች፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም ጌታችን ተገልጦላት #ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ከዚህ በኋላ ሕይወቷን በሙሉ በታላቅ ተጋድሎ ስታሳልፍ ጌታችንም ከቅድስት እናቱ ጋር ሆኖ በየጊዜው ይጎበኛት ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልንም የሁልጊዜ ጠባቂዋ አድጎ ሰጥቷታል፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብሔረ ብፁዓን እየሄደች ከዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር እስከ ሰባት ቀን ድረስ ስትነጋገር ትቆይ ነበር፡፡ #ሄኖክና #ኤልያስ ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋንም እየሄደች ትመለስ ነበር፡፡ ✤✣✤ ከዕለታት አንድ ቀን በጣና ማዶ መዕቀበ እግዚእ የሚባል አንድ ሰው ነበረና መልአከ ጽልመት ወደ እርሱ ዘንድ መጥቶ ‹‹ፈጣሪውን ክደህ ይህን ዕፅ በሰውነትህ ብትቀብር ሞትና እርጅና አያገኝህም›› አለው፡፡ እርሱም ለዚህ ክፉ ሀሳቡ ፈቃደኝነቱን ስለገለጠለት መልአከ ጽልመት በሰውነቱ ውስጥ ዕፁን ቀብሮለት ሄደ፡፡ መዕቀበ እግዚእም ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ሰላም እልሻለው በጸሎትሽም ተማጽኛለሁ፣ የፈጠረኝን እግዚአብሔርን እስከ መካድ ደርሼ ብዙ ኃጢአት ሰርቻለውና›› አላት፡፡ ቅድስት እናታችንም በዚያን ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደችና ስለዚህ ሰው በፍጹም ኀዘን በመሆን ወደ ፈጣሪዋ አመለከተች፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ለዚህ ሰው ምሕረት አይገባውም፣ የምገድል የማድን የምቀስፍ ይቅር የምል አምላክ እኔ እያለሁ ፈጣሪውን ክዶ በሰይጣን ምክር ተማምኖአልና›› አላት፡፡ በዚህ ጊዜ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን እግሩ ሥር ተደፍታ ‹‹አንተ መዓትህ የራቀ ምህረትህ የበዛ ፈጣሪ ሆይ! ማርልኝ ሁሉ ይቻልሃልና…›› ስትል አጥብቃ ለመነችው፡፡ ሁሉን የፈጠረ ጌታችንም ‹‹ስለ አንቺ ፍቅር ምሬልሻለው›› አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ማዕቀበ እግዚእን ጠርታ ‹‹ኃጢአትህን ይቅር ብሎሃል›› አለችው፡፡ ከዚህ በኋላ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ የተቀበረውን ዕፅ ሰውነቱን ፍቃ ስታወጣለት ደሙ እንደ ቦይ ውኃ ወረደ፤ በዚያው ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ከማኅበረ ሰማዕታት ጋር አንድ ሆነች፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ #ስድስት ክንፎችን ሰጥቷታል፡፡ በበዓለ ጥምቀት ወቅት ሙሴ፣ ኤልያስና መጥመወቁ ዮሐንስ ጌታ የተጠመቀበትን የዮርዳኖስን ውኃ አምጥተው ሙሴ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ቀኝ እጇን፣ ኤልያስ ግራ እጇን ይዘዋት ዮሐንስ ውኃውን በራሷዋ ላይ አፍስሶ አጥምቀዋታል፡፡ ከጌታችን ጥምቀት በኋላ እንደዚህ ዓይነት መንገድ የተጠመቀ ማንም የለም፡፡ እነርሱም ጓንጉት በምትባል ገዳም ውስጥ የገዳም አስተዳዳሪ እንደምትሆንና እጅግ ብዙ ተከታዮች እንደሚኖሯት ትንቢት ነግረዋት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፡፡ የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ምልጃና ጸሎት አይለየን +++ ✤✤✤ #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ ✤✤✤

#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክለ_ሃይማኖት፣ የቅድስት እናታችን #ክርስቶስሠምራ እና የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ንግሥ ነው(ታሪኩን ከታች ይመልከቱ) ፡፡ በደብራችን ታቦታተ ሕጉን በማውጣት መከበር የተጀመረው #በ፲፱፻፹፪(1982) ዓ.ም እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡አሁንም የአባቶቻችንን ፈለግ የተከተልን እኛ ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ለማግኘት በየዓመቱ በድምቀት እናከብረዋለን፡፡ ✤✤✤ ነሐሴ ፳፬(24) ቀን የሦስቱም ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው ነው ታሪከ አቡነ #ተክለሃይማኖት ወቅድስት #ክርስቶስ ሠምራ እንዲሁም አርዮስን መልስ ለመስጠት በቅርጫርት ውስጥ ተጉዞ ለሄደው እና ከ 318 ሊቃውንት አንዱ የሆንው የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ ታሪክ:: ✤✤✤ ✤✤✤ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ✤✤✤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት #እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው«አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለውሥላሴ ን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያ ውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ኃሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም የኃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡ አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ /ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫/ ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አባታችን በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም 10፣ 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡ በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል ፡፡ በሐይቅ 10 ዓመት በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመፀለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው #ለ7 ዓመት በፀሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በፀሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ አባታችን ባረፉ 54 ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም ለአባታችን ለአቡነ #ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ# ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል ፡፡ በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ለእኚህ ዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው ለጻድቁ ተክለ ሃይማኖት በየዓመቱ በነሐሴ ፳፬ ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ✤✤✤

#ሊቀ_ማዕምራን_ብርሃኑ_ተክለያሬድ ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤ ዘተፈነወ ውስተ ምድርነ፤ ይክሥት ብርሃነ ይፈውስ ዱያነ፤ ሐዋርያ ዘኮነ ወተሰምዓ ዜናሁ፤ ውስተ ኲሉ ምድር። የታላቁ ደብራችን ፍሬ የሆኑት
#ሊቀ_ማዕምራን_ብርሃኑ_ተክለያሬድ ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤ ዘተፈነወ ውስተ ምድርነ፤ ይክሥት ብርሃነ ይፈውስ ዱያነ፤ ሐዋርያ ዘኮነ ወተሰምዓ ዜናሁ፤ ውስተ ኲሉ ምድር። የታላቁ ደብራችን ፍሬ የሆኑት #ሊቀ_ማዕምራን_ብርሃኑ_ተክለያሬድ የደቡብ እና ምዕራብ አፍሪካ አኅጉራተ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን በቅዱስ ፓትርያርኩ ተሹመው ወደ #ደቡብ_አፍሪካ አቅንተዋል። #ሊቀ_ማዕምራን_ብርሃኑ_ተክለያሬድ ከልጅነታቸው ጀምሮ በቅድስት ቤተክርስቲያን ዕውቀት ያደጉ፣ ከታላላቅ መምህራን የቤተክርስቲያንን ትምህርቶች የጠነቀቁ፣ በተለያዩ የቤተክርስቲያን ኃላፊነቶች ያገለገሉ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ቃለ ጉባኤ ያዥ በመሆን ለቅድስት ቤተክርስቲያን ታላቅ አስታዋጽዖ ያበረከቱ፣ ብዙ ፈተናዎችንም በጥብዓት የተሻገሩ ታላቅ መምህራችን ናቸው። #ሊቀ_ማዕምራን የሰንበት ት/ቤታችንን አገልግሎት ከመደገፍ፣ ከማስተማር፣ ከመምከር እንዲሁም በፈለግናቸው ጊዜ ሁሉ ጊዜያቸውን ዕውቀታቸውን ከማካፈል ያልቦዘኑ ታላቅ መምህራችን ናቸው። መምህራችን እንኳን ለዚህ ክብር አበቃዎት 🙏 ይደልዎ! ይደልዎ! ይደልዎ! በሁለገብ ዕውቀትዎ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ከዚህ በላይ እንደሚያገለግሏት ታላቅ ተስፋ አለን። ደቡብ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን... ሰናይ ለክሙ!

የ፳፻፲፮ ዓ.ም ተመራቂ የሰ.ት.ቤታችን አገልጋዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላቹሁ!
የ፳፻፲፮ ዓ.ም ተመራቂ የሰ.ት.ቤታችን አገልጋዮች በሙሉ እንኳን ደስ አላቹሁ!

• ይህን ችግር ለመቅረፍ የተነሡት የዘመኑ ፓትርያርክ ከሀቢብ ጊዮርጊስና ከሌሎች ሁለት ምእመናን ጋር በመሆን ሐዋሪያዊ ጉዞ አደረጉ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ሀቢብ በውጪ የሚገኙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ወጣቶችን የሚሰበስብበትን ዘዴዎች መመልከት የቻለው፡፡ ወዲያውኑ ከጉዞው መልስም ህጻናትና ወጣቶች ተሰብስበው የሚመሩባቸውን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማደራጀትና የሚመጥናቸውን ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ መንፈሳዊ መዝሙራትንም ለማዘጋጀት አቅዶ ሥራውን ጀመረ፡፡ በዚህ ሥራውም በሌላ እምነት ተማርከው የነበሩትን መመለስ ችሏል፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ #ጸሐፊነትን፣ #አስተዳዳሪነትን እና #ሰባኪነትን በእኩል ደረጃ አሳክቶ መያዝ የቻለ ሰው ነው፡፡ በአጠቃላይ #ሠላሳ_መጽሐፍትን አዘጋጅቷል፡፡ በመጨረሻ ዕድሜው ሲገፋ #ጤናውም_እየታወከ_መጣ፤ ቤቱም በደቀ መዛሙርቱ መሞላት ጀመረ፡፡ ለእርሱም የነበራቸውን ፍቅር ለመግለጽ መኝታን ከበው አብረውት ጸሎት በማድረግ ራሱ የደረሳቸውን #መዝሙራትም_ይዘምሩለት ነበር፡፡ በመጨረሻ ሀቢብ ጊዮርጊስ ነሐሴ 15 ቀን 1951 ዓ.ም (በ75 ዓመቱ) አረፈ፡፡ ዜና እረፍቱም በሀገረ ግብፅ ከዳር እስከ ዳር ተሰማ፡፡ ቀብሩም በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት መስከረም 17 ቀን 1951 ዓ.ም ተፈጸመ፡ ምንጭ፡-ሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስ እና ሥራዎቹ፣ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/Finotehiwott

#ሊቀ_ዲያቆናት_ሀቢብ_ጊዮርጊስ #ለግብጽ_ቤተ_ክርስቲያን_የንጋት_ጎህ (ነሐሴ 15 እረፍቱ) #ሀቢብ_ጊዮርጊስ_ማነው? ሀቢብ ጊዮርጊስ በ1976 ዓም #በካይሮ_ከተማ ተወለደ፡፡ አባቱ በሕጻንነቱ ስለሞተበት እናቱ ለብቻዋ በፍቅረ ቤተ ክርስቲያን አንጻ አሳደገችው፡፡ ትምህርቱን የተከታተለው አቡነ ቄርሎስ አምስተኛ በመሠረቱት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡ በዚያውም #ዲቁና ተቀብሎ ማገልገል ሲጀምር ዕድሜው #አሥራ_ሰባት ብቻ ነበር፡፡ በወቅቱ ፓትሪያርኩም በኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የተከሰቱትንና የቤተክስቲያኒቱን አገልግሎት እጅጉን የጎዱ እንቅፋቶች በማስወገድ ወደ ለውጥ መንቀሳቀስ የጀመሩበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ሆኖ የተገኘው #የሰለጠኑ_ካህናትን_የሚያፈራ_ተቋም_መክፈት ስለነበር ለዚህ ወሰኝ ተልዕኮ የሚመጥን ይሆናል የሚሉትን ሰው ሲፈልጉ ምርጫቸው ያረፈው በወጣቱን አገልጋይ ሀቢብ ጊዮርጊስ ላይ ሆነ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ ኃላፊነቱን እንደተቀበለ ትኩረቱን ያደረገው ለተቋሙ ግንባታ የሚያስፈልገውን ገቢ ማሰባሰብ ላይ ነበር፡፡ በውጤቱም ከሀገር ሀገር እየተዘዋወረ ባደረገው ቅስቀሳ የምእመኑን የታመቀ ፍቅር ማቀጣጠል የቻለ ሲሆን በጥቂት ቀናት ውስጥ የተገኘው ድጋፍም በቂ ሆኖ ስለተገኘ ኮሌጁ እንደታሰበው ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል፡፡ ኮሌጁ ተከፍቶ ማስተማር ሲጀምር ደግሞ ሀቢብ ጊዮርጊስም ከመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች አንዱ ለመሆን የቻለ ሲሆን በወቅቱ የተከሰተውን የመምህራን እጥረት መቅረፍ ግድ ሲሆን ደግሞ ተማሪ በሆነበት ዓመታት መምህርነትንም ደርቦ ያዘ፡፡ የሀቢብ አስደናቂ አገልግሎት በስፋት የተገለጠው ከተመረቀ በኋላ ሲሆን በሰባኪነት ተሰማርቶ የሰበካቸው ስብከቶች በወቅቱ ሰማዕያኑን የመሰጡ ብቻ ሆነው አልቀሩም፡፡ ይልቁንም ብዙዎች ከሞተ በኋላ እንኳ ሳይቀር የሚያስተውሷቸው እንዲሁም ታትመው የብዙዎችን ሕይወት ሲለውጡ የሚኖሩ ሆነዋል፡፡ ለመሠረተው ኮሌጅ ማደግ ከፍተኛ ራእይ የነበረው ሀቢብ ጊዮርጊስ በዚያ ወቅት ከሠራቸው ሥራዎች መሀከልም ጉልህ የነበረው በኮሌጁ ዙሪያ የነበሩ ቦታዎችን ባገኘበት አጋጣሚ ሁሉ በግል ገንዘቡ እየገዛ ለኮሌጁ ማስፋፊያ ይሆን ዘንድ ማበርከቱ ይጠቀሳል፡፡ በዚህና መሰል ወደር የለሽ ተግባራቱና ከፍ ያለ ትጋቱ የተደሰቱት ፓትሪያርኩ አቡነ ቄርሎስ #የሊቀ_ዲያቆንነት_ማዕረግን_ሰጡት፡፡ የሀቢብ ጊዮርጊስ ቀጣይ የአገልግሎት ምዕራፍ የኮሌጁ ርዕሰ መምህር በሞት በተለየ ጊዜ እርሱን በመተካት የርዕሰ መምህርነትን ኃላፊነት ሲጨምር የሚጀምረው ነው፡፡ በዚህ ወቅት ከሠራቸው ተግባራት መሀከልም ዋነኛው ኮሌጁን ከውጪ ተጽእኖ የተጠበቀ እንዲሆነ ማድረጉ የመጀመሪያው ሲሆን በመከላከል ብቻ ላይም ሳይወሰን ተቋሙ #የኦርቶዶክሳዊት_ቤተ_ክርስቲያንን_ትምህርት_በምልዓት_የሚያንጸባርቅ መብራት ማድረግ መቻሉ ደግሞ ሌላው ዘለዓለማዊ ስኬቱ ነው፡፡ በተለይ ኦርቶዶክሳዊያን ደቀመዛሙርት ወደ አንግሊካን የትምህርት ተቋማት ሄደው የከፍተኛ ትምህርት እንዲከታተሉ የሚል ግፊት ሲነሳና እንዲሁም የአንግሊካን ምሁራን በኮፕቲክ የሥነ መለኮት ኮሌጅ እንዲያስተምሩ ሐሳብ ሲመጣ ይህን በመቃወም ግፊቱ ከሐሳብ አልፎ በተግባር እንዳይውል ማድረግ መቻሉ ነበር፡፡ የሀቢብ ልዩ ችሎታ የነበረው በመቃወምና በመከላከል ላይ ብቻ አለመወሰኑ ይልቁንም ከተቃወመው ሐሳብ የተሻለ አማራጭ እንዲኖር መሥራቱ ነው፡፡ በዚህም የተነሣ በኦርቶዶክሳዊው የትምህርት ተቋም ውሰጥ የአንግሊካን ሊቃውንት እንዳያስተምሩ በማለት አጥብቆ ሲቃወም በምትኩ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውያን አስተምህሮ በጥልቀት የተረዱ ቀሳውስት እንዲኖሩ አጥብቆ ይሠራ ነበር፡፡ ሌላው የሀቢብ ጊዮርጊስ ጅምር የነበረውና ባለፉት ቅርብ ዓመታት ውሰጥ ለግብጽ ቤተ ክርስቲያን መነቃቃት መንስኤ የሆነው ተግባር ደግሞ ኮሌጁ የማታ የትምህርት መርሐ ግብር እንዲጀምር ማድረጉ ነው፡፡ የዚህ አዲስ መርሐ ግብር መከፈት በርካታ ምሁራንና ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጡና በትምህርተ ሃይማኖት እንዲታነጹ እድል ከመስጠቱም በላይ በዚህ ምክንያትነት #የግብጽ_የትምህርት_ሚኒስቴር_ለኮሌጁ_እውቅና_ሊሰጠው_ችሏል፡፡ በማታው መርሐ ግብር ተካፍለው ከነበሩ ወጣት ምሁራን መካከል #ፖፕ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ አንዱ ናቸው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ለኮሌጁ እድገት ዕድሜውን ሁሉ የተጋው ሀቢብ ጊዮርጊስ ኮሌጁን በማሳደግ ዓለም አቀፍ ደረጃውን እንዲጠብቅ ማድረግ የቻለ ሲሆን መደበኛው የሥነ መለኮት ትምህርት በፍልስፍናና በሥነ ልሳን ትምህርቶች የታጀበ እንዲሆንና እንዲሁም በብቁ መምህራን የተሞላ በማድረግ የምርጥ አገልጋዮች መፍለቂያ እንዲሆን ስላደረገው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በቤተ ክርስቲያን ክህነት የሚቀበሉ ሁሉ የኮሌጁ ዲፕሎማ እንዲኖራቸው የሚያስገድድ ሕግ ተሠራ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ በሕይወት ኖሮ የኮሌጁን አርባኛ ዓመት ለማክበር የበቃ ሲሆን በዚያው ዓመትም ‹‹#የነገረ_መለኮት_ኮሌጅ_ትናንትናና_ዛሬ›› የሚለውን መጽሐፉን ለሕትመት አብቅቷል፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤት_ጅማሮ ሀቢብ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ሰንበት ትምህርት ቤት በማቋቋም ሥራውን ሲጀምር የ24 ዓመት ወጣት ነበር፡፡ ጊዜውም 1900 ዓም ቦታው ካይሮ ከተማ ውስጥ በሚገኙ የኮፕቲክ አብያተ ክርስቲያናት፡፡ ጅማሮው ሕጻናትን ሰብስቦ በማስተማር ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ቸርነት አገልግሎቱ ተባርኮለት ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቋቋመ፡፡ ይህም ውጥን በሀገሪቱ በሞላ ተስፋፍቶ አገልጋዮች እጅግ የበዙ ሆኑ፡፡ በሀቢብ ጊዮርጊስ የተቋቋሙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በወጣቶች ልቡና ውስጥ መተከል እንዲችል ሕያው ምስክር ሆኑ፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ በግብጽ የመጻሕፍትና የበራሪ ጽሑፎች ስርጭት፣ ዐውደ ርእያት፣ ሴሚናሮች፣ ኮንፈረንሶች፣ ወደ አብያተ ክርስቲያናትና ወደ ገዳማት የሚደረጉ መንፈሳዊ ጉዞዎችንና የመሳሰሉ እንቅስቃሴዎች የመነጩት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_መስፋት_ምን_ጠቀመ? ሀቢብ ጊዮርጊስ የመሠረተው የሰንበት ትምርት ቤት እንቅስቃሴ ከተስፋፋ በኋላ በወቅቱ ቤተ ክርስቲያንን ይፈታተኑ የነበሩ ችግሮችን በእግዚአብሔር እርዳታ መፍታት የሚችል ሊሆን በቅቷል፡፡ ከነዚህም መሀከል የሚከተሉት ዐበይት ተግባራት አይዘነጉም፡፡ • መጽሔቶችን በማሳተም ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት ሥራ በብዛት የተሠራው በዚህ ዘመን ነው፡፡ • ወደ ቤተ ክርስቲያን ሳይመጡ የቀሩ ወጣቶች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀርቡ አድርጓል፡፡ • በዘመኑ የነበሩ እንግሊዛውያን ሚስዮናውያን የቅኝ ገዢዎችን አካሄድ በመከተል ኦርቶዶሳውያንን ከእምነት ለማስወጣት ይጥሩ ነበር፡፡ • ሚስዮናውያኑ በተለይ የትምህርት ዕድል በመስጠትና በመሳሰሉ ዘዴዎች በመጠቀም ወጣቶችን ለማማለል ይሞክራሉ፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩ ማራኪነት ባላው ጽሑፎችና ባሸበረቁ ሥዕላት ያዘጋጁዋቸውን ብሮሹሮች በመበተን የሚሠሩት የቅሰጣ ተግባር አልበቃ ብሏቸው የእናት ቤተ ክርስቲያንን ስም ጥላሸት እስከ መቀባት ደርሰው ነበር፡፡ በዚህም ተግባራቸው ብዙዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠፍተዋል፡፡