uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 389 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 582-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 199-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 389 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 23 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.38% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.20% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 290 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 569 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 17 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 389
Obunachilar
-324 soatlar
+207 kunlar
+2330 kunlar
Postlar arxiv
ስተዋልን ቀስሞ፤ ወደ አጎቱ ተመልሶ ተምሮና ትምህርትን አምላክ ገልጾለት መምህረ መምህራን ሁኖ እንገኘዋለን፤ /እግዚአብሔር አምላክ ለቅዱስ ያሬድ ያንን ኹሉ ጥበብ ቶሎ ያልገለጸለት በቀላሉ ቢያገኘው ኋላ እንዳይታበይ ብሎ ነው፤ የሐዊራ ብስድር እስክንድራን ታሪክ ልብ ይሏል) ፠#መምህር ነው ስንል፤ መናኝ ባሕታዊ ኾኖ እናገኘዋለን፤ /በደብረ ሐዊ ለ22ዓመታት መመኑን ልብ ይሏል/ ፠#መናኝ ነው ስንል የተለያዩ የሃገራችንን ክፍሎች ገዳማትና አድባራት ሲጎበኝ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሲጓዝ እንገኘዋለን፤ /ጣና ቂርቆስ፤ ዙር አባ አቡነ አረጋዊ፣ …. ሌላውንም ልብ ይሏል) ፠#ወደ ገዳማትና አድባራት ይጓዛል ስንል፤ ወደ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ በደመና ተጭኖ ሂዶ ምሽቱን ወደ በዓቱ ሲመለስ እንገኘዋለን፡፡ ፠#በሃገራችን በዋና ከተማ አኵሱም ተወልዶ ያደገ ነው ስንል፤ ሰው ሊኖርበት በማይችለው፥ በረድ በሚፈላበት፥ የነፋስ እሩምታ በሚያይልበት፥ ቅዝቃዜው አጥንት በሚሰነጥቅበት፥ ውርጩ እጅጉን በሚቀዘቅዝበት፥ ደመና በሚፈስስበት በራስ ደጀን ተራራ አጠገብ በደብረ ሐዊ መንኖ እናገኘዋለን፡፡ ፠#ከሰዎች ጋር አብሮ ኑሯል ስንል፤ ከሰው የማይቀርቡና በዐለማችን ላይ ብርቅዬ ኾነው በሃገራችን የሚገኙ ከሃገራችን ኢትዮጵያም በሰሜን ተራሮች በአብዛኛው ከሚገኙት ዋልያ ጋር አብሮ ሲኖር፤ ዋልያዎችንም እንደ መጓጓዣና እንደ መጫኛ ሲያገለግሉት እንገኛለን፡፡ ፠#በሙራደ ቃል የመላእክት ዜማ ተገልጾለት ተማረ ስንል፤ የግእዝ ቋንቋ ምሁርና ጠበብት ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ለተሰዓቱ ቅዱሳን መምህር መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#የዜማ ጀማሪ አባት ነው ስንል ባለቅኔ ኾኖ እንገኘዋለን (ሕንፄሃ ወሡራሬሃ …. የሚለው ቅኔውን ልብ ይሏል)፤ ፠#ባለቅኔ ነው ስንል መተርጕም ኾኖ እንገኘዋለን፤ (ድጓው የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#መተርጕም ነው ስንል ባለታሪክ፥ የታሪክ ምሁር ኹኖ እናገኘዋለን፤ ፠#የታሪክ ምሁር ነው ስንል፤ የመርሐ አዝማን ሊቅ ኹኖ እናገኘዋለን፤ (ዓመቱን በሚገርም ሁኔታ ከወቅታቱ ጋራ አገናዝቦ መሠየሙን ልብ ይሏል) ፠#የመርሐ አዝማን ሊቅ ነው ስንል ቅዱስ ኾኖ እንገኘዋለን፤ የቅዱሳንም ጓደኛ ኹኖ እንገኘዋለን፡፡ /የአቡነ አረጋዊ፣ የአጼ ገብረ መስቀልን ታሪክ ልብ ይሏል፡፡/ ፠#ነቢይ ነው ሰንል ሐዋርያ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ስለ ዳግም ምጽአት፣ ስለ መንግሥተ ሰማያትና …. ሌሎችንም ልብ ይሏል) ፠#ሐዋርያ ነው ስንል ሰማዕት ኹኖ እናገኘዋለን፡፡ (እግሩን በጦር መወጋቱን ልብ ይሏል)፤ ሌላም ሌላም …. ፠#በአጠቃላይ ምድራዊ ነው ስንል ሰማያዊ፤ ሰማያዊ ነው ስንል ምድራዊ (ብእሲ ሰማያዊ ወመልአክ ምድራዊ) ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ #ዜማውን በግዕዝ ዕዝል አራራይ የዜማ ስልት የደረሰ፤ #በዓለም ደረጃ የዜማ ምልክቶች ባልታወቁበት ጊዜ ዜማዎቹን በምልክት የቀመረ፤ #የዜማ ሥርዓትን በመንደፍ የዓመቱን ቀለም ያዘጋጀ፤ #ዜማውን በ4ት ዘመናት ከፋፍሎ፤ ዘመናቱን በንዑሳን ዘመናት ከፋፍሎ ለወራቱና ለሰሙኑ ለእለቱ የሚገባውን ቀምሮ የደረሰ፤ #እንኳን በእርሱ ዘመን ዛሬ እንኳን ብዙ ነገሮች ተሰባስበዋል በተባለበት ዘመን ሊሠራ አይደለም ሊታሠብ በማይችሉ መልኩ መጽሕፍትን እንደ ንብ እየቀሰመ፤ እንደ ወይን እየጨመቀ፤ እንደ አረቂ እያጣራ፤ እየተረጐመ ላሰበው ድርሠት ያዋለ፤ … ስለ ቅዱሱ ምኑን ተናግረን እንጨርሰዋለን፡፡ … ##.. ይኼማ ኢትዮጵያዊ ሊኾን አይችልም ብለው ብዙ የውጭ ሃገራት ወደ ራሳቸው ለመውሰድ የሚዳዳቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት_፤ #የዜማው_ጠባያት_፤ #ከሌሎች_ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይና_ #የዜማው_ጥቅም #ሀ_የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት ፠ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ያዘጋጀው ከብሉያት፣ ከሐዲሳት፣ ከሊቃውንት መጻሕፍት እየመረጠ ለምስጋናና ለጸሎት እንዲኾኑ አድርጎ ነው፡፡ ፠ዜማው ምስጢሩ የማይጠገብ፥ቃሉ የሚያረካ፥ አነጋገሩ የተሳካ፥ ጣዕመ ቃሉና ኀይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ፥ ልብን የሚነካ ነው፡፡ ፠በይዘቱም የሥነ ፍጥረት ውበትን በማድነቅና የሥነ ፍጥረት አስገኝ የኾነውን እግዚአብሔርን በማመስገን ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ፠በአጠቃላይ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ጌታ ለሰው ልጆች ሲል በዚህ ዓለም የፈጸመውን የማዳን ሥራ ሁሉ ገልጦ የሚያስረዳ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የቅዱሳን መላእክትን፣ የነቢያትን፣ የሐዋርያትን፣ የጻድቃንና የሰማዕታትን ክብርና ቅድስና በማውሳት በስማቸው መማፀንና መጸለይ የሚያስገኘውን ጥቅም የሚያስረዳ ታላቅ ዜማዊ ሀብት ነው፡፡ ፠ከእርሱ በፊት የነበሩና በእርሱ ዘመን የተጻፉ የቅዱሳን ገድላትና ድርሳናትን እንዲሁም የበዓላትን ጥንታዊ አመሠራረት ውስጠ ምሥጢር በማስረዳት በዜማ ድርሰቱ አካቷል፡፡ ፠ምስጋናውንም ለአራቱ ክፍላተ ዘመን ለክረምት፣ ለመፀው (ለጥቢ)፣ ለሐጋይ (ለበጋ)፣ ለጸደይ (ለበልግ) እንዲኾን አዘጋጅቶታል፡፡ #ለ_የዜማው_ጠባያት ፨የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊ በመኾኑ ኅሊናን የመመሠጥ፣ ሥጋዊ ደስታንና ኀጢአትን ከማሰብ የመጠበቅ፣ ሰማያዊውን ድንቅ የምስጋና ምስጢር የማሳወቅ ኀይል አለው፡፡ ፨ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታም በመኾኑ ብልየት (እርጅና)፣ ውላጤ (መለወጥ) የማይታይበት ዘወትር ሕያው የኾነ ብቸኛ ዜማ ነው፡፡ ፨የመንፈስ ቅዱስ ስጦታም በመኾኑ ዘወትር አዲስና የማያልቅ ጥልቅ ምንጭ ያለው ሕይወትን የሚያለመልም ነው፡፡ ፨ዜማውም ሰማያዊና መንፈሳዊ፣ ከእግዚአብሔር የተገኘ ለመኾኑ ማስረጃ የሚኾነን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች ዜማውን ለተለያየ ዐላማ ይመኙታል፤ ነገር ግን ለመያዝም ኾነ ለመወሰን አይችሉም፡፡ ምክንያቱም በምድራዊ ጥበብና ፍልስፍና የሚያዝ የሚወሰን ሳይኾን ታላቅ መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ፣ ሌት ተቀን ልቡናን ለሥላሴ ሰጥተው ከእግዚአብሔር የሚያገኙት በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያጸኑት፣ የሚማሩትና የሚያዜሙት እንጂ በገንዘብ የማይገዛ ታላቅ ጸጋ መኾኑ ነው፡፡ #ሐ.#የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ከሌሎች _ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይ፤ ፠ዜማው አሳብን የሚገዛ፣ ከሥጋ ይልቅ በመንፈስ መመላለስን የሚያስተምር በመኾኑ፤ ፠ በአቀራረቡም የተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ያለው በመኾኑ፤ ፠ ዜማው በአዝማናት ተለይቶ በወቅት ተከፋፍሎ የሚዜም መኾኑ፤ ፠ ማንኛውም ሰው ከተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ውጪ በራሱ ፍላጎት የድምፅ ቅላጼውን ለማሳመር ስለፈለገ የሚያሻሽለው ወይም የሚለውጠው አለመኾኑ፤ ፠ ዜማው በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ምሥጢር የተሞላ መኾኑና ፠ የዜማው ምልክቶችና ዐይነቶች ጥልቅ ምሳሌና ምስጢር ያላቸው መኾናቸው ነው፡፡ #መ_የቅዱስ_ያሬድ_ዜማ_ጥቅም ሀ. የቤተ ክርስቲያንን አንድነት በመጠበቅ፤ በየትኛውም አካባቢ የምትኖር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ዓይነት መዝሙር፣ አንድ ዓይነት ቅዳሴ፣ አንድ ዓይነት ማኅሌት፣ አንድ ዐይነት ሥርዐት በአንድ ዓይነት ጊዜ በአንድ ቀን ማቅረብና መፈጸም እንድትችል አስችሏታል፡፡ ለ. በነገረ መለኮት ትምህርት፤ ሊቁ የትርጓሜ መምህር ስለሆነ ከብዙ መጻሕፍት ስለሚጠቅስና የሃይማኖት ትምህርቱትንም በዜማ አቀነባብሮ መድረሱ በጣም ተወዳጅ ትምህርት እንዲሆን አድርጎታል፡፡

#ማሕሌቱን_ለማሕሌት_አባት_እናቅርብለት:: #የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ #የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች #የቅዱስ_ያሬድ_የዜማው_ይዘት_፤ #የዜማው_ጠባያት_፤ #ከሌሎች_ዓለማዊ_ዜማዎች_የሚለይበት_ጠባይና_ #የዜማው_ጥቅም #የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች ፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ካህን (ካህነ ስብሐት) ፠ ማኅሌታይ፤ ፠ መዘምር ዘበድርሳን፤ ፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት) ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ ልዑለ ስብከት፤ ፠ ሰማዕት፤ ፠ ባሕታዊ፤ ፠ መናኝ ፠ የዜማ አባት፤ ፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ:: ፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ ፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ:: ፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ:: ፠ አእምሮው የመጠቀ፤ ፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …... #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ /ማኅሌቱን በአ.አ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ የምትቆሙ በደብረ ይባቤ የሚለውንና በሰማየዊ ቀለም የተቀባውን እየመረጣችሁ መጠቀም ስትችሉ፤ በሌሎች አድባራት ግን ሰማያዊ ቀለም የሌለበትን (በቢጫና እንዲሁ ያለቀለም የተቀመጠውን) እየመረጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ፡፡/ #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መምህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ * አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ *** አፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በአፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ፤ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ፤ በከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ፡፡ #፩ኛ) #ምዕራፍ (ውዳሴ ማርያም በዜማን፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠለስት፣ ክስተተ አርያምን) ያጠቃልላል፡፡ ፠ #የውዳሴ_ማርያም_ዜማ ቅዱስ ኤፍሬም ሦርያዊ የደረሰውን ለቅዱስ ያሬድ እየነገረው ልብን የሚመስጥ ዜማ ደርሶለታል፡፡ ፠ #መስተጋብዕ፤ ስብስብ ማለት ሲኾን፡፡ ከዳዊት መዝሙር (ከ180ው የመስተጋብእ ድርሰት 1ድ ድርሰት በስተቀር) ለጸሎትና ለዝማሬ ተስማሚ የኾነው እየተውጣጣ ለመዝሙር ተስማሚ የኾነው የተቀመረ ነው፡፡ መስተጋብዕ ሲጀምር ‹‹ወለቡ ጽራኅየ (ጩኸቴን ልብ አድርግ›› ብሎ ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ጠዋት ይዘመራል፤ የቀድሞ መምህራን በፍልሠታም ይዘምሩት ነበር፤ ዜማው በዋነኛነት በግዕዝና በዕዝል ሲኾን በአራራይ ከሐሙስ ‹‹አንተሰ እግዚኦ ለዓለም›› የሚለውና ከቅማዴ ‹‹መንግሠትከሰ መንግሥት›› የሚለው ይገኙበታል፡፡ በየእለቱ እንዲደርስ (ከእሑድ በስተቀር) አድርጎ የደረሰው ነው፤ ፠ #አርባዕት፤ አራት አራተኛ ማለት ሲን በዳዊት መዝሙር በአራተኛው መሥመር ውስጥ እየገባ የሚዘመር ነው፤ ‹‹ቃልየ አጽምእ እግዚኦ ወለቡ ጽራኅየ፤ ወአጽምአኒ ቃለ ስእለትየ፤ ንጉሥየኒ ወአምላኪየኒ፡፡ ከፈጸመ በኋላ አርባዕት ይገባል፡፡ አርባዕት ሲጀመር ‹‹ቃልየ፤ ከመ ያፈቅርለ ጐሥዓ፤ ዐቢይ፤ ተሣሃለኒ›› ብሎ ነው (በዳዊት መዝሙር ጀምሮ ቀጥሎ በቅዱስ ያሬድ ድርሠት በኾነው በአርባዕት ያጠናቅቃል፡፡አብዛኛው በግጥም መልክ የተቀመረ ሲኾን አልፎ አልፎም በስድ ንባብ መልክ ይገኛል፡፡ ግእዝ ዕዝልና አራራይ ዜማ አለው፡፡ ፠ #አርያም፤ አርያም ልዑል፥ ከፍተኛ ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ሰምቶ ‹‹ቀዳሚ ዜማ፤ አንድም ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ›› ስላመጣው ነው፡፡ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ የግጥም መልክ ባለው አርያም በተባለው ይጀምራል፡፡ በግጥም መልክና በስድ ንባብ ሲገኝ የግጥም አገጣጠሙ ከፍ ያለ የግጥም አገጣጠምን የተከተለነው፡፡ የሚባልበት ጊዜ በጾም ጊዜ በጾመ ድጓው እየገባ፣ በተለይ ደግሞ በክብረ በዓል ክሥተተ አርያም ሲደርስ ይዘመራል፡፡ #ሠለስት፤ ስምዐኒ ብሎ የሚጀምር ባለ ብዙ ሃሌታ ያለው፤ በዳዊት መዝሙር በሦስተኛው መሥመር እየገባ የሚዘመር፤ አንድም 3 መዝሙሮች ብቻ የሚዘመሩለት ብዙውን ጊዜ በግጥም የሚቀርብ ሲኾን፤ ይኽ ዜማ የሚደርሰው በክብረ በዓላት ዋይዜማ፤ በስብሐተ ነግህ፣ በአርያም፣ በጾመ ድጓ ውሎ፣ በአርያም፣ በሰንበት፣ በፍትሐት ጊዜ ነው፡፡ ክስተተ አርያም፤ የሰማይ መከፈት ማለት ሲኾን በታላላቅ በዓል ቀን እንዲሁም ታላላቅ? ሰዎች ሲሞቱ የሚዘመር ነው፤ ክስተትን ቅዱስ ያሬድ ያዘጋጀው ከዳዊት መዝሙራት፥ ከጸሎተ ነቢያትና ከራሱም ጭምር ኀይለ ቃል ያላቸውን ባለሁለት መስመሮች ሐረግ በመውሰድ ሲኾን ዜማው እጅጉን ነፍስና ሥጋን፥ ልብንና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡ ፪ኛ) #ጾመ_ድጓ፤ በዐቢይ ጾም የሚባል ነው፡፡ ፫ኛ) #ድጓ፤ በ4ት ክፍላተ ዘመናት የተቀመረና ጾመ ድጓን በውስጡ የሚያካትት ነው፡፡ ፬ኛ) #ዝማሬ፤ ቅዱስ ቊርባን ድርገት ሲወርድ ለቅዱስ ቊርባን ክብር የሚዘመር ነው፡፡ ፭ኛ) #መዋሥዕት፤ ሰው ሥጋው ከነፍ ስትለይ ፍትሐት የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡ ፮ኛ) #የ፲፬ቱ ቅዳሴያት ዜማ፤ 14ቱን ቅዳሴያት 14ት አባቶች የደረሷቸው ቢሆንም ዜማ የደረሰላቸው ግን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ፯ኛ) #አንቀጸ ብርሃንን፤ ድርሰቱ ነው፡፡ /ይቀጥላል……/ በተጨማሪም ደግሞ፤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ዐይነቶች ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በመባል ይታወቃል፡፡እነዚህ የዜማ ዐይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛው ድምፅ ያልተደባለቀ፣ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ትርጉም ያላቸው በሆኑ የዜማ ምልክቶች (ድፋት፤ ሂደት፤ ቅናት፤ ይዘት፤ ቁርጥ፤ ጭረት፤ ርክርክና ደረት) ደርሷል፡፡ የቅኔ ጀማሪም ነው፡፡ ‹‹ሕንፄሃ …›› የሚለውን ቤት መምቻ ያለውን ቅኔ ልብ ይሏል፤ አንድ ባለቅኔ ግን ይህን ሳይረዳ ‹‹ተትሕተ ያሬድ …›› የሚል ቅኔን ተቀኝቷል፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች ፠#ከጌዴዎን ዘንድ ትምህርቱን አቋርጦ ሄደ ስንል፤ በአንድ ሾላ ዛፍ ላይ በትል አማካይነት ትዕግስትንና ማ

#ለአጥቢያችን_ምዕመናን_ሙሉ ግንቦት 8/2013 ዓ.ም በቀ/ደ/መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ሊደረግ የነበረው #ሕገ_ወጥ የሆነ የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ሰላማዊ በሆነ መንገድ በነባሩ የሰበካ ጉባኤ አባላት፣በአካባቢው ምእመናን፣ በአካባቢው ወጣቶች ፣ በደብሩ የሰ/ት/ቤት አባላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ከሽፏል፡፡ ለ 3 ዓመታት ቤተክርስቲያኑን የሚመሩ ከካህናት 4፣ ከምዕመናን 3፣ ከሰ/ት/ቤት 1 አባላት የሚወከሉበት በቤተክርስቲያኑ አስተዳደር ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪ አካል ነው፡፡ አመራረጡም የሰበካ ጉባኤ ካርድ ያላቸው ምእመናን በሙሉ ፣ በደብሩ ላይ ቅጥር የሆኑ አገልጋዮች በሙሉ ፣ የደብሩ ሰ/ት/ቤት አባላት እድሜያቸው ከ 18-35 ዓመት የሆኑ በሙሉ በምርጫው ላይ ይሳተፋሉ፡፡ ምርጫም ከመደረጉ #ከ 1ወር በፊት ነባሩ ሰበካ ጉባኤ ለወከለው ምእመናን ፣ ካህናት እና ሰ/ት/ቤት አባላት የሰራውን ስራ ሪፖርት አቅርቦ የመዘበረው ካለ ተጠይቆ መልካም ከሰራ ደግሞ ተመስግኖ አዲስ ለሚመረጠው ሰበካ ጉባኤ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ያስረክባል፡ ስለሆነም ግንቦት 8/2013 ዓ.ም በደብሩ አስተዳደር ብቻ ተወስኖ ሊካሄድ የነበረው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ፡- 1. ቃለ አዋዲው በሚያዘው እና ብጽዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በሰጡት አባታዊ መመርያ መሰረት ሰበካ ጉባኤው 3 ዓመት የሰራውን ስራ ሪፖርት ለምዕመናን ሳያቀርብ ተጠያቂ ሳይሆኑ ተሸፋፍኖ ሊያልፍ የነበረ በመሆኑ 2. ምርጫው ፍትሐዊ የሚሆነው ሁሉንም አካላት በሚገባ ያሳተፈ መሆን ሲገባው ነገር ግን እውነተኛ ሰዎች በድምጽ ብልጫ እንዳይገቡ በምርጫው ላይ ከሰ/ት/ቤቱ 30 ሰዎች ብቻ እንዲገቡ ደብዳቤ ስለተሰጠው እና በአንጻሩ ደግሞ በእለቱ ያልተገኘ የደብሩ ሰራተኛ ከደሞዙ ላይ 1000.ብር እንዲቆረጥ መመርያ በመውረዱ ምክንያት ነው፡፡ በእነዚህ 2 ዋና ዋና ምክንያቶች ምርጫው ለሌላ ጊዜ እንዲዘዋወር ተደርጓል፡፡ በቀጣይም ህዝቡ ያመነበት ምርጫ እንዲካሄድ ያለፈው ሰበካ ጉባኤ አባላትን የደብሩ አስተዳደር ጠርቶ በግፍ ላባረረበት ይቅርታ ጠይቆ ሪፖርት በጋራ እንዲያዘጋጁና በሪፖርቱ ካልተማመኑ የየራሳቸውን ሪፖርት እንዲያቀርቡ በማድረግ ተሸፋፍኖ ሊያልፍ የፈለገውን አካል ማስጠየቅ መቻል፡፡ ከዚህም ባለፈ በቀጣይ የሚደረገው ምርጫ እንደመሆኑ መጠን ሌሎች አካላት በሙሉ እንዲገኙ ተደርጎ ለሰ/ት/ቤት 30 ሰው ብቻ እንዲገባ የሚለውን #ህገ_ወጥ አሰራር አስተካክሎ ሰ/ት/ቤቱ በጠየቀው ቁጥር ልክ ምርጫ ካርድ እንዲሰጠውና ሰላማዊ የሆነ ምርጫ እንዲካሄድ ሰ/ት/ቤቱ ያሳስባል፡፡ ምእመናንም በዚህ ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የምርጫ ካርዳችሁን እንድትወስዱና ለቤተክርስቲያን የሚጠቅመውን እንድትወክሉ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!!! ስለ ሁሉም ነገር ክብሩ ለመድኃኔዓለም ይሁን!!!

#ግንቦት_11 #እንኳን_ለቅዱስ_ያሬድ_በዓለ_ስዋሬ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #18ቱ_የቅዱስ_ያሬድ_ገዳማትና_አድባራት፡፡ እሑድ ግንቦት 11 ከዋይዜማው ጀምሮ ቀጠሯችሁን የት ለማድረግ አስባችኋል???፤ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን በዓሉን ታከብሩ ዘንድ 15ቱን የቅዱስ ያሬድ ገዳማትና አድባራት እናስተዋውቃችሁ፡፡ ꔰ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ ፩ኛ). #ደብረ_ሐዊ_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በበየዳ ወረዳ ቤተ ክህነት ከራስ ደጀን ተራራ አጠገብ የሚገኝ)፡፡ እመቤታችን በስደቷ ወቅት ያረፈችበት፤ ጃንደረባው ባኮስ የተሠወረበት፤ ቅዱስ ያሬድ ለ22 ዓመታት የመነነበት፥ ያስተማረበትና የተሠወረበት፤ በሀገራችን ትልቁ የሱባዔ መግቢያ ቅዱስ መካን፤ በዓለም ላይ በሃገራችን ብቻ፤ ከሀገራችንም በአብዛኛው በሰሜን ተራሮች ላይ ብርቅዬ ኾነው የሚገኙት ዋልያና ጭላዳ በአብዛኛው የሚገኙበት ቦታም ነው፡፡ በዚህ ቦታ ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበትና የተማሪዎቹ ወንበር ጕባኤ ቦታና የደንጊያ ወንበር፤ ጽዮንን ከሩቅ እያየ ያለቀሰበት ቦታ ላይ የፈለቀ ጠበልና በዘንጉ ያፈለቀው ፈዋሽ ጠበል፤ የተሠወረበት የዋሻ ቤተ ክርስቲያን፣ እንዲሁም አበውና እማት የሚኖሩበት ገዳም ይገኛል፡፡) ፪ኛ). #በየዳ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ከርስቲያን፤ በደብረ ሐዊ ተራራ በስተጀርባ የሚገኝ ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ በደብረ ሐዊ በምናኔ እንደመኖሩ መጠን በተራራው ጀርባ በገጠሩ መንደር የሚገኙ ምዕመናን እኛም ቅዱስ ያሬድን ልንዘክረው ይገባል፤ የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ደብረ ሐዊ ላይ ብቻ ሳይኾን በኹሉም ቦታ መኖር ይገበዋል በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥተው የሠሩት ነው፡፡) ፫ኛ). #ጣና_ቂርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (ከፎገራ ከመንገዱ የ3 ሰዓት መንገድ እንደተጓዙ፤ በመርከብ ደግሞ ከባሕር ዳር፣ ከጎርጎራ፣ ከደልጊ፣ ከቁንዝላ ተሣፍረው ከጣና ክርስቶስ ሠምራ አጠገብ የሚያገኙት ታላቅ ገዳም ነው፤ መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፤ ታቦተ ጽዮን ለበርካታ ዓመታት ያረፈችበት፤ ቅዱስ ያሬድ ምልክት ያለውን ድጓ የጻፈበት ቦታ ነው) ፬ኛ). #ወገራ_ደልደሊት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (በሰሜን ጎንደር ወገራ አውራጃ አምባ ጊዮርጊስ ወረዳ የሚገኝ ሲኾን፤ በቅዱስ ያሬድ ዜማ ከብቶች ኹሉ ተመስጠው ሳያርሱ በመቆማቸው ምክንያት ቅዱስ ያሬድ የተገረፈበት ቦታ ነው) ፭ኛ). #አኵሱም_ደብረ_ዝማሬ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ አጠገብ የሚገኝ ሲኾን፤ የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዴት ቅዱስ ያሬድ ተወልዶ ባደገባት፥ ተምሮ ባስተማረባት፤ ሰማያዊ ምሥጢራትና በተገለጡለት፤ የተሰዓቱ ቅዱሳንን የበርካታ ቅዱሳን መናኸሪያ በኾነችው፤ የገዳማትና የአድባራት ራስ፤ የምዕመናን ሁሉ አምባ መጠጊያ በኾነችው ከተማ እንዴት መታሰቢያ ቤተ ከርስቲያን ሳይሠራለት እስካሁን ቀረ ብለው በመንፈሳዊ መነሣሣት በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሠሩት ቤተ ክርስቲያን ነው) ፮ኛ). #አኵሱም_ማይኪራህ_ደብረ_መድኀኒት_ወፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ከአኵሱም ከተማ በ4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በቅዱስ ያሬድ የትውልድ ቦታ አጠገብ በዋናው መንገድ ዳር የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው፤ ቅዱስ ያሬድ ከትሏ መውደቅና መነሳት በመመልከት ማስተዋልን የተማረባት ቦታ ስትኾን ሾላዋ እስካሁንም ድረስ እየተካች ትገኛለች፤ ከሾላው ሠር የሚፈልቅ ፈዋሽ ጠበልም አለ፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን የተሠራው የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የደብረ ዝማሬን ቤተ ክርስቲያን ሲሰሩ የሃገሬው ሰው ተመልክቶ እንዴት የትውልድ ቦታው ላይ እኛ ቤተ ክርስቲያን ሳንሠራ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቀድመውን ሠሩ በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥጠው በተፋጠነ ሁኔታ ያነጹት ነው፡፡) ፯ኛ). 👉👉 #አዲስ_አበባ_ደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን (አዲስ አበባ ጎተራ ማሰለጫ መንገድ አጠገብ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ሲኾን፤ የቅዱስ ያሬድ ፍቅር በልባቸው ባደረባቸው እናት ወ/ሮ ደስታ ሞላ በ1948 የተሠራ ሲሆን ኋላ ላይ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት የፓትርያርክነት ዘመን በምዕመናን አሁን ያለው ሕንፃ ቤ/ክ ተሠርቷል፤ የቅዱስ ያሬድ ትምህርቶች እየተሰጡበት የሚገኝና ወደፊትም በኮሌጅ ደረጃ አስፋፍቶ በርካታ ደቀመዛሙርትን ለማስተማር እቅዱ አለ፤ በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ፈዋሽ ጠበልም ይገኛል፡፡) ፰ኛ). #ጎንደር_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሩፋኤል_ወአቡነ_ሐራ_ድንግል_ቤተ_ክርስቲያን፤ (ይህ ቤተ ክርስቲያን በጎንደር ከተማ የሚገኝ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ ሲኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፱ኛ). #ጎንደር_ጎሐ_ተራራ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን ፲ኛ). #ደብረ_ብርሃን_አንሳስ_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን (በደብረ ብርሃን ከተማ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን ፈዋሽ ጠበል ያለባትና፤ የአቋቋሙ ሊቅ፣ የቅዳሴና የሌሎች ዜማ ትምህርቶች መምህር የኾኑት የመምህር ለምኔ ማስተማሪያ ደብር ነች፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፩ኛ). #ጀርመን_ክሮምበርግ_ቅዱስ_ዑራኤልና_ቅዱስ_ያሬድ_ቤተ_ክርስቲያን (በጀርመን ሃገር በክሮምበርግ ከተማ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያናችን ነው፡፡) ፲፪ኛ). #ዋሽንግተን_ዲሲ_ኆኅተ_ምሥራቅ_ኪዳነ_ምሕረት_ቤተ_ክርስቲያን፤ (በአሜሪካ ሃገር ዋሽንግተን ዲሲ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፫ኛ). #ርዕሰ_አድባራት_ዱባይ_ሻርጃ_አጅማን_ሰአሊተ_ምሕረት_ቅድስት_ማርያም_ቤ/ክ (በዱባይ ሃገር ሻርጃ አጅማን የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ናት፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፬ኛ). #ባሕር_ዳር_ፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ማርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ ቤ/ክ፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ይባብ ካምፓስ አጠገብ የሚገኝ፡፡ ፲፭ኛ). #ደቡብ_አፍሪካ_የቅድስት_ሥላሴና_የቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ በደቡብ አፍሪካ የሚገኝ፡፡ ፲፮ኛ). #ድሬደዋ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔ_ዓለም፤ (በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) ፲፯ኛ). ደረስጌ ወረዳ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ፲፰ኛ). #ዳንግል_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሚካኤል_ቤ/ክ፤ በጎጃም ክፍለ ሃገር በአዊ ሃገረ ስብከት የሚገኝ ሲሆን በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ከ8/10/2008 ዓ.ም. ጀምሮ በድርብነት ይከበራል)፡፡ ፲ኛ)#ድሬዳዋ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም በድርብነት ይከበራል ከላይ በተጠቀሱት በአቅራቢያችን ባሉ ገዳማትና አድባራት እንድንገናኝ መድኀኔ ዓለም ይፍቀድልን፡፡ ꔰ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ꔰ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem www.Finotehiwotsundayschool.com ሌሎች ያላካተትናቸው ካሉ በፎቶ ከነን ጨምሩበት፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ

ታላቁ ደብራችን ቀጨኔ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አንጋፋነቱን ታሪካዊነቱን እንደያዘ ከ110 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ታላቅ ደብር ነው፡፡ ይህ ደብር የሚመራው በማኅሌቱም፣ በሰዓታቱም በቅዳሴውም በወንጌሉም በተመሰከረላቸው አለቆች ሲሆን አጥቢያውን የሚመሩትም የሰበካ ጉባኤ አባላት በአጥቢያው የተመሰከረላቸው፣ በሃይማታቸው የጸኑ በስነምግባራቸው የተመሰገኑ ምእመናን ናቸው፡፡ ደብራችን የዛሬ 3 ዓመት የአካባቢው ምእመናን ተጨንቆ ተጠቦ የመረጣቸውን አባላት የደብራችን አስተዳደር ከ 3 ወራት በፊት በውሀ ቀጠነ ምክንያት በትኖታል፡፡ ይህ እንዳለ አሁን ነባሩ ሰበካ ጉባኤ ቃለ አዋዲው በሚያዘው መሰረት የራሱን ሪፖርት ሳያቀርብ የደብሩ አስተዳደር ብቻ ያዘጋጀውን የ 3 ዓመት ሪፖርት ለምዕመናን አቅርቦ አዲስ ሰበካ ጉባኤ ለማቋቋም በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ሰ/ት/ቤቱም በምርጫው ላይ መሳተፍ ስላለበት ባሉን የአባላት ቁጥር ልክ የምርጫ መምረጫ ካርድ እንዲሰጠን በደብዳቤ ለ 3 ጊዜያት የጠየቅን ቢሆንም የደብሩ አስተዳደር ግንቦት 3/2013 ዓ.ም በደብዳቤ ቁጥር 669/432/13 ሰ/ት/ቤቱ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት 30 ሰው ብቻ በምርጫው እንዲያሳትፍ ታዟል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የደብሩ ማኅበረ ካህናት እና ሰራተኞች የምርጫው እለት የቀረ #1000.ብር ይቀጣል በማለት ፍትሐዊ እና ሰላማዊ ያልሆነ ምርጫ ለማድረግ ዝግጅት አድርጓል፡፡ የክፍለ ከተማችን ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤትም ይህንን ችግር በመመልከት ካላቸው ውድ ጊዜ ላይ አጣበው በቀን 05/09/2013 ዓ.ም በጽ/ቤታቸው የደብሩን ሰ/ት/ቤት ተወካዮች፣ የደብሩን አስተዳደር አካላት፣ የቀጨኔ ፖሊስ መምሪያ በተገኘንበት ረጅም ስብሰባ የተደረገ ሲሆን ሰ/ት/ቤቱም የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ሪፖርት ለምእመናን ሳይቀርብ ምርጫ መደረግ እንደሌለበት እንዲሁም ባስገባነው የአባላችን ልክ መምረጫ ካርድ ሊሰጠን እንደሚገባ በመነጋገር በመግባባት ምርጫው ላልተወሰኑ ቀናቶች እንዲራዘም ተስማምተን ስብሰባውን ጨርሰናል፡፡ የደብራችን አስተዳዳሪ የሆኑትም መልአከ ሰላም ስዩም ወ/ገብርኤልም በጉዳዩ ላይ አምነውበት ምርጫው እንደሚራዘም እና ከደብሩ ሰ/ት/ቤት ጋርም በቅርበት ተገናኝተን እንደምንወያይ የጋራ የመግባቢያ ሃሳብ ይዘን ምርጫው ወደፊት እንደሚደረግ በማሳሰብ በጸሎት ዘግተዋል፡፡ ስለሆነም መላው የሰ/ት/ቤቱ አባላት እና የአጥቢያው ምእመናን ምርጫው ሁሉንም አሳታፊ ያደረገ መሆን እንዳለበትና የምንመርጣቸው አባላት ተጨንቀን ተጠበን መሆን እንዳለበት ግልጽ ነው ፡፡ ከዚህም ባለፈ ያለፉት የሰበካ ጉባኤ አባላት ተገናኝተው ሪፖርታቸውን ሰምተን በስራቸው አመስግነን ወይም ያጠፉት ካለ ለቀጣዩ ሰበካ ጉባኤ እንዲስተካከል አድርገን በክብር መሸኘት ይኖርብናል፡፡ #ነገር ግን በቀን 05/09/2013 ዓ.ም ከተስማማነው ስምምነት ውጪ ሰ/ት/ቤቱ እና ምእመናን ያልተሳተፉበትን ምርጫ በቀን 08/09/2013 ዓ.ም ማድረግ ፍትሐዊ ስለማይሆን የሚመለከታችሁ አካላት ቆም ብላችሁ እንድታስቡ እየጠየቅን መላው የሰ/ት/ቤቱ አባላት እና የአካባቢው ምእመናን እሁድ ጠዋት #12 ሰዓት በደብራችን ውስጥ በመገኘት ከስምምነታችን ውጪ ምርጫውን ለማድረግ የሚያስቡትን ሰዎች ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን እንድናስቆም ሰንበት ት/ት ቤቱ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ #እሁድ ግንቦት 8/2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት መገናኛችን ቀጨኔ መድኃኔዓለም ይሁን:: ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን!!!

#ቅዱስ_ፓትርያርኩ_በተለያዩ_ቋንቋዎች_የተተረጎመውን_ቃለ_ዐዋዲ_በይፋ_መረቁ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስያን የምትመራበት ቃለ ዐዋዲ በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ አማካኝነት በእንግሊዘኛ
+3
#ቅዱስ_ፓትርያርኩ_በተለያዩ_ቋንቋዎች_የተተረጎመውን_ቃለ_ዐዋዲ_በይፋ_መረቁ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስያን የምትመራበት ቃለ ዐዋዲ በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ አማካኝነት በእንግሊዘኛ ኦሮምኛ እና ትግርኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ያሬድ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሰበካ ጉባዔ ማደራጃና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁአን አበው ሊነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ተመርቋል፡፡ (ኢኦተቤ ቴቪ ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም ) Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool

👉#ሥርዓተ_ማኀሌቱ ሰሙነ ፋሲካ ስለሆን እንደ #የደብሩ_ይትባህል እያጣቀሳቹህ እንድትጠቀሙ የበዓለ #ትንሣኤን እና #የልደታ_ለማርያም ሥርዓተ ማኀሌት እነሆ ብለናል፡፡ #እስከ_ዳግም_ትንሣዔ_ድረስ_መ
+6
👉#ሥርዓተ_ማኀሌቱ ሰሙነ ፋሲካ ስለሆን እንደ #የደብሩ_ይትባህል እያጣቀሳቹህ እንድትጠቀሙ የበዓለ #ትንሣኤን እና #የልደታ_ለማርያም ሥርዓተ ማኀሌት እነሆ ብለናል፡፡ #እስከ_ዳግም_ትንሣዔ_ድረስ_መልክእ_አይደረስም!